WU Freshman program
رفتن به کانال در Telegram
Wollo University Social Science and Natural Science Freshman Program
نمایش بیشتر3 820
مشترکین
-424 ساعت
-477 روز
-11030 روز
آرشیو پست ها
3 820
ለመጀመሪያ ድግሪ ተማሪዎች፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ለምርጫ የቀረበ የባችለር ሳይንስ ዲግሪ በሙያ ጤንነትና ደህንነት (Bachelor of Science Degree in Occupational Health and Safety) የፕሮግራም ገለጻ
መግቢያ
የሰው ልጅ ህልውና የተቆራኘው ከሚሰራው ስራ ጋር ነው። በስራ ላይ እያለ ደግሞ የተለያዩ አደጋዎችና የጤና እክሎች ሊያጋጥሙት ይችላሉ። እነዚህ አደጋዎችና የጤና እክሎች የሚከሰቱበትን፣ የሚባባሱበትን እና ወደ ሞት የሚያደርሱበትን ሁኔታ በሳይንሳዊ ዘዴ የሚተነትን፣ የሚከላከል እና የሚቆጣጠር የሙያ ዘርፍ Occupational Health and Safety (የሙያ ጤንነትና ደህንነት) ይባላል።
በሰራተኞች ላይ የሚስተዋሉ ጉዳቶች እና የጤና ችግሮች
በከተሞች፣ በኢንዱስትሪዎች እና በአገልግሎት መስጫ ተቋማት መስፋፋት እና በህዝብ ቁጥር መጨመር ምክንያት ከስራ ጋር የተያያዙ የጤና ችግሮች በመላዉ አለም (ኢትዮጵያን ጨምሮ) እየተባባሱ መጥተዋል፡፡ የዘላቂ ልማት ግብ (SDG8) ሁሉም ሰራተኞች ደህንነቱ በተጠበቀ የስራ አካባቢ መስራት እንዳለባቸው ያስቀምጣል። ሆኖም ግን የአለም አቀፉ የሰራተኛ ድርጅት (ILO) በቅርቡ ይፋ ባደረገው መረጃ በአለም አቀፍ ደረጃ በየቀኑ 1,000 ሰዎች በስራ ላይ አደጋዎች እና 6,500 ሰዎች ከስራ ጋር በተያያዙ በሽታዎች እንደሚሞቱ ገልጿል። በተጨማሪም 374 ሚሊዮን ሰራተኞች ደግሞ ገዳይ ባልሆኑ የስራ ላይ ጉዳቶች ይሰቃያሉ ብሏል። እንዲሁም ከስራ ጋር በተያያዙ አደጋዎች እና በሽታዎች የሚጠፉ የስራ ቀናት በአለም አቀፍ ደረጃ ምርታማነትን በአማካይ በ4% እንደሚቀንሱ አመልክቷል። ኢትዮጵያን ጨምሮ በማደግ ላይ ባሉ ሀገራት ከስራ ጋር በተያያዘ የሚከሰቱ ጉዳቶች ከበለፀጉ አገራት ጋር ሲነጻጸር ከ10 እስከ 20 እጥፍ ከፍ እንደሚል ይታመናል። ምክንያቱም በማደግ ላይ ባሉ ሀገራት አብዛኛው የሰው ሃይል በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንዱስትሪዎች የተሰማራ በመሆኑ የWHOን እና የILOን ዝቅተኛ የሙያ ነክ ጤንነትና ደህንነት መስፈርቶች አሟልቶ ባለመገኘቱና ለዚህም ጉዳይ ሙያዊ ድጋፍ ሊያደርግ የሚችል በቂ የተማረና የሰለጠነ የሰዉ ሃይል ባለመኖሩ ነው። ኢትዮጵያን እንደምሳሌ ብንወስድ በአዲሰ አበባና በድሬዳዋ ከተሞች በ16 የተለያዩ ፋብሪካዎችና በ1000 ሰራተኞች ላይ በሁለት የተለያዩ ጊዚያት በተደረገ ጥናት በድምሩ 374 አደጋዎች ተመዝግበዋል፡፡ አብዛኛው የዓለም የሰው ኃይል የሙያ ጤንነትና እና የደህንነት አገልግሎቶችን አያገኝም፡፡ በእያንዳንዱ የሥራ ቦታ የሠራተኞችን ጤና እና ደህንነት የመከላከልና የመቆጣጠር ሙያ ትኩረት ተነፍጎት የቆየ መስክ ነው፤ ወይም ለሁሉም ሰራተኞች ተደራሽ ሳይሆን የቆየ ነው። እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ታዳጊ አገሮች በተለያዩ የሥራ ሁኔታዎችና የአካባቢ ባህሪያት ምክንያት ሙያ ነክ አደጋዎችና የጤና እክሎች እየጨመሩ ነው።
የሙያ ጤንነትና ደህንነት ባለሞያዎች አስፈላጊነት
በወሎ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ፣ በአካባቢ ጤና አጠባበቅ ትምህርት ክፍል ይህንን ሙያ በመጀመሪያ ዲግሪ ደረጃ በ2015 ዓ/ም ለማስጀመር የስርአተ ትምህርት ቀረጻው (Curriculum) ተጠናቆ በዩኒቨርሲቲዉ ሴኔት ጸድቆ ለእናንተ ክፍት ሆኗል፡፡ ስርዓተ ትምህርቱ ከመቀረጹ በፊት በሁሉም የሀገሪቱ ክልሎች (አዲስ አበባን ጨምሮ) የስራውን ተፈላጊነት በተመለከተ የቅድመ ዳሰሳ ጥናት የተደረገ ሲሆን 231 አሰሪዎች ተጠይቀዉ 223(96.5%) የሚሆኑት ፕሮግራሙ መከፈት እንዳለበት (አስፈላጊ እንደሆነ) አምነዋል፡፡ ከተጠየቁ ቀጣሪ ተቋማት ውስጥ 62.8% በዚህ ሙያ የሰለጠነ ሰራተኛ አልቀጠሩም፡፡ 75.6% የሚሆኑ ተቋማት ደግሞ ተጨማሪ ሙያተኛ መቅጠር ይፈልጋሉ፡፡ በአንጻሩ 64.9% የሚሆኑ የስራ ቦታዎች በሙያው ያልሰለጠኑ ሰዎች ተቀጥረውባቸው ተገኝተዋል።
የአካባቢ ጤና አጠባበቅ ትምህርት ክፍል ሰው ሃይል እና መሰረተ ልማቶች
በትምህርት ክፍሉ ውስጥ 6 ፒኤችዲ (ከነዚሀ መካከል 2ቱ አሶሼት ፕሮፌሰር የሆኑ)፤ 6 አሲሰታንት ፕሮፌሰር፤ 3 ፒኤችዲ ተማሪ ፤ 10 ሌክቸረር፤ 2 ረዳት መምህር፤ 2 ረዳት ምሩቅ፤ 2 ፒኤችዲ ተማሪ፤ 9 የማስተርስ ተማሪዎች፤ 7 የላብራቶሪ ቴክኒካል እረዳቶች፤1 ጸሃፊ እና 1 የላቦራቶሪ የጽዳት ባለሙያ በድምሩ 47 መምህራንና ሰራተኞች ይገኛሉ፡፡ ከሰው ሐይል በተጨማሪ የኢንተርኔት ክፍል፣ የላቦራቶሪ አገልግሎት፣ የተቀናጀ የኢንዱስትሪ እና የመስክ ልምምድ የምታደርጉበት የትምህርት ስርዓት ተዘርግቶላችኋል፡፡
ከምረቃ በኋላ ያለውን የስራ እድል በተመለከተ
በወሎ ዩኒቨርሲቲ፣ በህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ፣ በአካባቢ ጤና አጠባበቅ ትምህርት ክፍል የተመረቀ አንድ የሙያ ጤንነትና ደህንነት ባለሙያ በኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኙ ኢንዱስትሪዎች፣ በግንባታ ድርጅቶች፣ በኤሮስፔስ ሳይንስ ምርምር ጣቢያዎች፣ በኅትመት ድርጅቶች ፣ በኤሌክትሮኒክስ ኢንዱስትሪዎች፣ በኢንሹራንስ ኩባንያዎች፣ በመገልገያ ድርጅቶች፣ በፌደራል ኤጀንሲዎች፣ በክልል ኤጀንሲዎች እና በአለም አቀፍ የተለያዩ ድርጅቶች ውስጥ ሊቀጠሩ ይችላሉ። እንዲሁም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ደግሞ አስተማሪ፣ ተመራማሪ፣ አማካሪ፣ አሰልጣኝ፣ የከፍተኛ ደረጃ ፖሊሲ ቀራጺ እና የፕሮግራም ዳይሬክተር ሆኖ ሊቀጠር ይችላል።
የትምህርት እድልን በተመለከተ
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፤የጎንደር ዩኒቨርሲቲ እና ሃረማያ ዩኒቨርሲቲ በማስተርስ ደረጃ በሙያ ጤንነትና ደህንነት እያስተማሩ ያሉ ሲሆን ወሎ ዩኒቨርሲቲን ጨምሮ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች እነዚህን ፕሮግራሞች በቅርብ ጊዜ የሚከፍቱ ስለሆነ መማር የሚፈልግ አንድ የሙያ ጤንነትና ደህንነት ባለሙያ የሚፈልገውን የመማር እድል ይኖረዋል። ለምሳሌ አንድ የሙያ ጤንነትና ደህንነት ባለሙያ በአካባቢ ጤና አጠባበቅ ዉስጥ ከሚገኙ የማስተርስ እና ፒኤችዲ ዲግሪ መካከል የማስተርስ ዲግሪ በሙያ ጤንነትና ደህንነት:የማስተርስ ዲግሪ በአካባቢ ጤና አጠባበቅ፤ የማስተርስ ዲግሪ በዉሃ እና ጤና፤ የማስተርስ ዲግሪ በዉሃ፤ሳኒቴሽንና ሃይጅን፤ የማስተርስ ዲግሪ በአካባቢ ሣይንስና ቴክኖሎጅ፤የማስተርስ ዲግሪ በኢንቫይሮንሜንታል ኢንጅነሪንግ እና ሌሎችንም መማር የሚቻል ሲሆን በፒኤችዲ ዲግሪ ደረጃ ደግሞ ፒኤችዲ ዲግሪ በአካባቢ ጤና አጠባበቅ፤ ፒኤችዲ ዲግሪ በዉሃ እና ጤና፤ፒኤችዲ ዲግሪ በሂዉማን ኢኮሎጅ እና ሌሎች በርካታ የት/ት እድል ማግኘት የሚያስችል ነዉ፡፡ ከላይ ከተዘረዘሩት ፕሮግራሞች መካካል በወሎ ዩኒቨርሲቲ በአካባቢ ጤና አጠባበቅ ት/ት ክፍል ስር ከታች የተዘረዘሩት የት/ት እድሎች ተማሪዎችን ተቀብለን በማስተማር ላይ እንገኛለን፡፡
የማስተርስ ኦፍ ሳይንስ ዲግሪ በአካባቢ ጤና አጠባበቅ (MSC in Environmental Health)
የማስተርስ ኦፍ ሳይንስ ዲግሪ በዉሃ እና ጤና (MSc in Water and Health, specialization in Water and Public Health, Specialization in Water and Wastewater Treatment)
የማስተርስ ኦፍ ሳይንስ ዲግሪ በዉሃ፤ሳኒቴሽንና ሃይጅን(MSc in Water, Sanitation and Hygiene)
የማስተር ኦፍ ፐብሊክ ሄልዝ በአካባቢ ጤና አጠባበቅ (MPH in Environmental Health)
የማስተርስ ኦፍ ፐብሊክ ሄልዝ በዉሃ፤ሳኒቴሽንና ሃይጅን (MPH in Water, sanitatioS and Hygiene)
3 820
ወሎ ዩኒቨርሲቲ
ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ
አካባቢ ጤና አጠባበቅ ት/ት ክፍል
ለመጀመሪያ ድግሪ ተማሪዎች፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ለምርጫ የቀረበ የባችለር ሳይንስ ዲግሪ በሙያ ጤንነትና ደህንነት (Bachelor of Science Degree in Occupational Health and Safety) የፕሮግራም ገለጻ
መግቢያ
የሰው ልጅ ህልውና የተቆራኘው ከሚሰራው ስራ ጋር ነው። በስራ ላይ እያለ ደግሞ የተለያዩ አደጋዎችና የጤና እክሎች ሊያጋጥሙት ይችላሉ። እነዚህ አደጋዎችና የጤና እክሎች የሚከሰቱበትን፣ የሚባባሱበትን እና ወደ ሞት የሚያደርሱበትን ሁኔታ በሳይንሳዊ ዘዴ የሚተነትን፣ የሚከላከል እና የሚቆጣጠር የሙያ ዘርፍ Occupational Health and Safety (የሙያ ጤንነትና ደህንነት) ይባላል።
በሰራተኞች ላይ የሚስተዋሉ ጉዳቶች እና የጤና ችግሮች
በከተሞች፣ በኢንዱስትሪዎች እና በአገልግሎት መስጫ ተቋማት መስፋፋት እና በህዝብ ቁጥር መጨመር ምክንያት ከስራ ጋር የተያያዙ የጤና ችግሮች በመላዉ አለም (ኢትዮጵያን ጨምሮ) እየተባባሱ መጥተዋል፡፡ የዘላቂ ልማት ግብ (SDG8) ሁሉም ሰራተኞች ደህንነቱ በተጠበቀ የስራ አካባቢ መስራት እንዳለባቸው ያስቀምጣል። ሆኖም ግን የአለም አቀፉ የሰራተኛ ድርጅት (ILO) በቅርቡ ይፋ ባደረገው መረጃ በአለም አቀፍ ደረጃ በየቀኑ 1,000 ሰዎች በስራ ላይ አደጋዎች እና 6,500 ሰዎች ከስራ ጋር በተያያዙ በሽታዎች እንደሚሞቱ ገልጿል። በተጨማሪም 374 ሚሊዮን ሰራተኞች ደግሞ ገዳይ ባልሆኑ የስራ ላይ ጉዳቶች ይሰቃያሉ ብሏል። እንዲሁም ከስራ ጋር በተያያዙ አደጋዎች እና በሽታዎች የሚጠፉ የስራ ቀናት በአለም አቀፍ ደረጃ ምርታማነትን በአማካይ በ4% እንደሚቀንሱ አመልክቷል። ኢትዮጵያን ጨምሮ በማደግ ላይ ባሉ ሀገራት ከስራ ጋር በተያያዘ የሚከሰቱ ጉዳቶች ከበለፀጉ አገራት ጋር ሲነጻጸር ከ10 እስከ 20 እጥፍ ከፍ እንደሚል ይታመናል። ምክንያቱም በማደግ ላይ ባሉ ሀገራት አብዛኛው የሰው ሃይል በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንዱስትሪዎች የተሰማራ በመሆኑ የWHOን እና የILOን ዝቅተኛ የሙያ ነክ ጤንነትና ደህንነት መስፈርቶች አሟልቶ ባለመገኘቱና ለዚህም ጉዳይ ሙያዊ ድጋፍ ሊያደርግ የሚችል በቂ የተማረና የሰለጠነ የሰዉ ሃይል ባለመኖሩ ነው። ኢትዮጵያን እንደምሳሌ ብንወስድ በአዲሰ አበባና በድሬዳዋ ከተሞች በ16 የተለያዩ ፋብሪካዎችና በ1000 ሰራተኞች ላይ በሁለት የተለያዩ ጊዚያት በተደረገ ጥናት በድምሩ 374 አደጋዎች ተመዝግበዋል፡፡ አብዛኛው የዓለም የሰው ኃይል የሙያ ጤንነትና እና የደህንነት አገልግሎቶችን አያገኝም፡፡ በእያንዳንዱ የሥራ ቦታ የሠራተኞችን ጤና እና ደህንነት የመከላከልና የመቆጣጠር ሙያ ትኩረት ተነፍጎት የቆየ መስክ ነው፤ ወይም ለሁሉም ሰራተኞች ተደራሽ ሳይሆን የቆየ ነው። እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ታዳጊ አገሮች በተለያዩ የሥራ ሁኔታዎችና የአካባቢ ባህሪያት ምክንያት ሙያ ነክ አደጋዎችና የጤና እክሎች እየጨመሩ ነው።
የሙያ ጤንነትና ደህንነት ባለሞያዎች አስፈላጊነት
በወሎ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ፣ በአካባቢ ጤና አጠባበቅ ትምህርት ክፍል ይህንን ሙያ በመጀመሪያ ዲግሪ ደረጃ በ2015 ዓ/ም ለማስጀመር የስርአተ ትምህርት ቀረጻው (Curriculum) ተጠናቆ በዩኒቨርሲቲዉ ሴኔት ጸድቆ ለእናንተ ክፍት ሆኗል፡፡ ስርዓተ ትምህርቱ ከመቀረጹ በፊት በሁሉም የሀገሪቱ ክልሎች (አዲስ አበባን ጨምሮ) የስራውን ተፈላጊነት በተመለከተ የቅድመ ዳሰሳ ጥናት የተደረገ ሲሆን 231 አሰሪዎች ተጠይቀዉ 223(96.5%) የሚሆኑት ፕሮግራሙ መከፈት እንዳለበት (አስፈላጊ እንደሆነ) አምነዋል፡፡ ከተጠየቁ ቀጣሪ ተቋማት ውስጥ 62.8% በዚህ ሙያ የሰለጠነ ሰራተኛ አልቀጠሩም፡፡ 75.6% የሚሆኑ ተቋማት ደግሞ ተጨማሪ ሙያተኛ መቅጠር ይፈልጋሉ፡፡ በአንጻሩ 64.9% የሚሆኑ የስራ ቦታዎች በሙያው ያልሰለጠኑ ሰዎች ተቀጥረውባቸው ተገኝተዋል።
የአካባቢ ጤና አጠባበቅ ትምህርት ክፍል ሰው ሃይል እና መሰረተ ልማቶች
በትምህርት ክፍሉ ውስጥ 6 ፒኤችዲ (ከነዚሀ መካከል 2ቱ አሶሼት ፕሮፌሰር የሆኑ)፤ 6 አሲሰታንት ፕሮፌሰር፤ 3 ፒኤችዲ ተማሪ ፤ 10 ሌክቸረር፤ 2 ረዳት መምህር፤ 2 ረዳት ምሩቅ፤ 2 ፒኤችዲ ተማሪ፤ 9 የማስተርስ ተማሪዎች፤ 7 የላብራቶሪ ቴክኒካል እረዳቶች፤1 ጸሃፊ እና 1 የላቦራቶሪ የጽዳት ባለሙያ በድምሩ 47 መምህራንና ሰራተኞች ይገኛሉ፡፡ ከሰው ሐይል በተጨማሪ የኢንተርኔት ክፍል፣ የላቦራቶሪ አገልግሎት፣ የተቀናጀ የኢንዱስትሪ እና የመስክ ልምምድ የምታደርጉበት የትምህርት ስርዓት ተዘርግቶላችኋል፡፡
ከምረቃ በኋላ ያለውን የስራ እድል በተመለከተ
በወሎ ዩኒቨርሲቲ፣ በህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ፣ በአካባቢ ጤና አጠባበቅ ትምህርት ክፍል የተመረቀ አንድ የሙያ ጤንነትና ደህንነት ባለሙያ በኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኙ ኢንዱስትሪዎች፣ በግንባታ ድርጅቶች፣ በኤሮስፔስ ሳይንስ ምርምር ጣቢያዎች፣ በኅትመት ድርጅቶች ፣ በኤሌክትሮኒክስ ኢንዱስትሪዎች፣ በኢንሹራንስ ኩባንያዎች፣ በመገልገያ ድርጅቶች፣ በፌደራል ኤጀንሲዎች፣ በክልል ኤጀንሲዎች እና በአለም አቀፍ የተለያዩ ድርጅቶች ውስጥ ሊቀጠሩ ይችላሉ። እንዲሁም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ደግሞ አስተማሪ፣ ተመራማሪ፣ አማካሪ፣ አሰልጣኝ፣ የከፍተኛ ደረጃ ፖሊሲ ቀራጺ እና የፕሮግራም ዳይሬክተር ሆኖ ሊቀጠር ይችላል።
የትምህርት እድልን በተመለከተ
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፤የጎንደር ዩኒቨርሲቲ እና ሃረማያ ዩኒቨርሲቲ በማስተርስ ደረጃ በሙያ ጤንነትና ደህንነት እያስተማሩ ያሉ ሲሆን ወሎ ዩኒቨርሲቲን ጨምሮ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች እነዚህን ፕሮግራሞች በቅርብ ጊዜ የሚከፍቱ ስለሆነ መማር የሚፈልግ አንድ የሙያ ጤንነትና ደህንነት ባለሙያ የሚፈልገውን የመማር እድል ይኖረዋል። ለምሳሌ አንድ የሙያ ጤንነትና ደህንነት ባለሙያ በአካባቢ ጤና አጠባበቅ ዉስጥ ከሚገኙ የማስተርስ እና ፒኤችዲ ዲግሪ መካከል የማስተርስ ዲግሪ በሙያ ጤንነትና ደህንነት:የማስተርስ ዲግሪ በአካባቢ ጤና አጠባበቅ፤ የማስተርስ ዲግሪ በዉሃ እና ጤና፤ የማስተርስ ዲግሪ በዉሃ፤ሳኒቴሽንና ሃይጅን፤ የማስተርስ ዲግሪ በአካባቢ ሣይንስና ቴክኖሎጅ፤የማስተርስ ዲግሪ በኢንቫይሮንሜንታል ኢንጅነሪንግ እና ሌሎችንም መማር የሚቻል ሲሆን በፒኤችዲ ዲግሪ ደረጃ ደግሞ ፒኤችዲ ዲግሪ በአካባቢ ጤና አጠባበቅ፤ ፒኤችዲ ዲግሪ በዉሃ እና ጤና፤ፒኤችዲ ዲግሪ በሂዉማን ኢኮሎጅ እና ሌሎች በርካታ የት/ት እድል ማግኘት የሚያስችል ነዉ፡፡ ከላይ ከተዘረዘሩት ፕሮግራሞች መካካል በወሎ ዩኒቨርሲቲ በአካባቢ ጤና አጠባበቅ ት/ት ክፍል ስር ከታች የተዘረዘሩት የት/ት እድሎች ተማሪዎችን ተቀብለን በማስተማር ላይ እንገኛለን፡፡
የማስተርስ ኦፍ ሳይንስ ዲግሪ በአካባቢ ጤና አጠባበቅ (MSC in Environmental Health)
የማስተርስ ኦፍ ሳይንስ ዲግሪ በዉሃ እና ጤና (MSc in Water and Health, specialization in Water and Public Health, Specialization in Water and Wastewater Treatment)
የማስተርስ ኦፍ ሳይንስ ዲግሪ በዉሃ፤ሳኒቴሽንና ሃይጅን(MSc in Water, Sanitation and Hygiene)
የማስተር ኦፍ ፐብሊክ ሄልዝ በአካባቢ ጤና አጠባበቅ (MPH in Environmental Health)
Metadele Adane:
ወሎ ዩኒቨርሲቲ
ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ
አካባቢ ጤና አጠባበቅ ት/ት ክፍል
3 820
ማስታወቂያ
በተፈጥሮ እና በማህበራዊ ሳይንስ ለሙያ መስክ ፈተና ለተፈተናችሁ የ 2014ዓ.ም የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች በሙሉ
የ 2014ዓ.ም የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች ስለ ሙያ መስክ ፈተና ውጤት በተደጋጋሚ ጠይቃችኋል፤ ሁኖም ግን ከጤና ሳይንስ ኮሌጅ የህክምና ትምህርት ቤት በ ቁጥር 207/14 በቀን 29/12/2014ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ ለህክምና ትምህርት የሚቀርቡ ተማሪዎች የቃለ መጠይቅ፣ የአካልና የስነ ልቦና እይታዎች እንዲሚያስፈልጋቸው የጠቀሰ ሲሆን፤ የህግ ትምህርት ቤት ደግሞ ጠቅላላ ከተመዘገቡት ተማሪዎች ውስጥ ለፈተና የቀረቡት ተማሪዎች ቁጥር አናሳ በመሆናቸው ተማሪዎቹ ከተመለሱ በኋላ ለፈተና እንዲቀርቡልኝ የሚል ጥያቄ አቅርቧል፡፡ በዚህ መሰረት ተማሪዎቹ ወደ ግቢያቸው ከተመለሱ በኋላ የተማሪዎች አጠቃላይ ውጤት የሚገለጽ መሆኑን አሳውቃለሁ፡፡
3 820
ማስታወቂያ
በተፈጥሮ እና በማህበራዊ ሳይንስ ለሙያ መስክ ፈተና ለተፈተናችሁ የ 2014ዓ.ም የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች በሙሉ
የ 2014ዓ.ም የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች ስለ ሙያ መስክ ፈተና ውጤት በተደጋጋሚ ጠይቃችኋል ሁኖም ግን ከጤና ሳይንስ ኮሌጅ የህክምና ትምህርት ቤት በ ቁጥር 207/14 በቀን 29/12/2014ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ ለህክምና ትምህርት የሚቀርቡ ተማሪዎች የቃለ መጠይቅ፣ የአካልና የስነ ልቦና እይታዎች እንዲሚያስፈልጋቸው የጠቀሰ ሲሆን፤ የህግ ትምህርት ቤት ደግሞ ጠቅላላ ከተመዘገቡት ተማሪዎች ውስጥ ለፈተና የቀረቡት ተማሪዎች ቄጥር አናሳ በመሆናቸው ተማሪዎቹ ከተመለሱ በኋላ ለፈተና እንዲቀርቡልኝ የሚል ጥያቂ አቅርቧል፡፡ በዚህ መሰረት ተማሪዎቹ ወደ ግቢያቸው ከተመለሱ በኋላ የተማሪዎች አጠቃላይ ውጤት የሚገለጽ መሆኑን አሳውቃለሁ፡፡
3 820
ለወሎ ዩኒቨርሲቲ የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች፣ መምህራን፣ ወላጆች፣ ቤተሰቦች፣ ወዳጆች፣ የዩኒቨርስቲው ሠራተኞች፤እና የዩኒቨርስቲው አመራር አካላት
እንደሚታወቀው በኢትዮጵያ መንግስት እና በትግራይ አማጽያን መካከል በተደረገው ጦርነት ምክንያት፡ በዩኒቨርስቲያችን የመማር ማስተማር ሂደት ላይ ከፍተኛ መስተጓጎልን በፈጠረበት ወቅት ያሳለፍነው ጊዜ ከባድ ዓመት ሆኖብናል፤
ጦርነቱም በየኒቨርስቲያችን ላይ ከባድ ኪሳራ አድርሷል። ሆኖም ግን የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች የመማር ማስተማሩ ስራ በጀመረበት ወቅት ሁላችንም የድርሻችንን በመወጣት ያደረግነው ተሳትፎ የዩኒቨርስቲውን የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች የትምህርት መርሃ ግብር ለማስቀጠል የሚያስችለንን ሁኔታ በማድረጋችን እና ይህንንም ሸክም በእኩል ለመካፈል ሁላችንም ተባብረን በመስራታችን የትምህርት መርሃ ግብሩን በተሳካ ሁኔታ ለማጠቃለል ችለናል።
በመሆኑም ይህ የበዓል ሰሞን ደግሞ የበለጠ አእምሯዊና አካላዊ ጥንካሬያችንን ለመመለስ የምንሞክርበት ትልቅ አጋጣሚ ነው። መልካም የዝግጅት ወቅት!!! መልካም በዓል እንዲሆንላችሁ እንመኛለን!!! አዲሱ ዓመት ለሁላችንም ጤና እና ደህንነት ያድርግልን!!! በሠላም ለመገናኘት ያብቃን!!! We wish you happy holidays and may the New Year find us all healthier and safer.
ዳኛቸው ማሩ በጊዜው (ዶ/ር)
የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች መርሃ ግብር ዲን
ሞባይል; 0949896584
ኢሚል; dagnachew.maru06@gmail.com
3 820
የፈተና ዝግጂት ስራ እንዳለቀ ፈተናውን የምንስጥ ስለሆነ የዲፓርትመንት መግቢያ ፈተና የምትፈተኑ ተናሪዎች ቀድሞ በተገለፀው ቦታ ተረጋግታችሁ የትም ሳትሄዱ እየተዘጋጃችሁ ጠብቁ።
3 820
የትራንስፖርት እጥረት ስለነበር:
ይህንን የተማሪዎች ችግር ለመፍታት: ለህሊናችን እና ለፈጣሪ ሰንል: ሶስት አውቶብስ ከ ላኮመንዛ ንግድ ሰራ ጋር በ መተባበር 165 ተማሪዎች ነገ ረብዐ በ 25/12/2014ዓ. ም በራሳቸው ወጭ ወደ አዲስ አበባ መሰመር እንዲሄዱ አመቻችተናል:: የላኮመንዛ አመራሮች ጥያቄዬን ተቀብላችሁ አፋጣኝ መልስ ስለሰጣችሁኝ በአንደኛ ዓመት ተማሪዎች ስም አግዚአብሔር ይስጥልኝ:: ለቀጣይም ተመሳሳይ ስራዎችን ለ መስራት ትጉ ::
3 820
የዲፓርትመንት መግቢያ ፈተና የምትፈተኑ የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች የዲፓርትመንት ምርጫችሁን እስከ ዛሬ 24/12/14 6:00 መርጣችሁ እንድትጨርሱ ለማሳሰብ እንወዳለን።
3 820
Student Banteamlak Gizaw Mulatu
You have exchanged your ID card with Student Yordanos Melaku. Please call her with 0906846440 and give her ID card and take yours!
3 820
Notice
We want to inform you that the field selection (Entrance) exam for 2014 entry students will be held on Wednesday morning (25/12/2014) at 2:30 L.T. Block 62
