cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

ኢትዮ ደብተራ TUBE✍✍✍

ደብተራ TUBE የጦቢያ ስንቅ ☑ሥለጠቃሚ መረጃዎች ☑የተደበቀውን የጦቢያ እውቀት ማወቅ ☑........ስለ ዓለም እውቀት እናወራለን ☑ ለዓለም ደብተራ ስለሆነችው ጦቢያ ☑ ስለ ደብተራ አባቶች በአጠቃላይ ስለደብተራ ምንነት እና ሌሎችም...

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استزبان مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
پست‌های تبلیغاتی
132
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡በልበልሸሪ፡አስማት፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡በውጭ፡ሐገር፡በስፋትና፡በጥልቀት፡በሰዎች፡ዘንድ፡አምላክ፡እስከመባል፡ድረስ፡የተመለከ፡የአስማት፡ሐይል፡ነው፡ይሔው፡አስማት፡በሰዎች፡ዘንድ፡እንዲስፋፋ፡ለሰው፡ልጅ፡ያስተማረው፡በርቅኤል፡የተባለ፡አጋንንት፡ነው፡ይሕ፡አስማት፡ዛሬ፡በኛም፡ሀገር፡ለተንኮል፡ስራ፡በመሠራጨቱ፡ደጋሚና፡አስደጋሚ፡የያዙት፡ንግድ፡እጃቸውን፡በንፁሐን፡ደም፡ኢየታጠቡ፡ነው፡ወገኖቼ፡በዚሕ፡አስማት፡የሚፈፀመው፡ተግባር፡ሕፃናትን፡ለሰይጣን፡በመሰዋት፡ደም፡የሚያፈሱት፡ክፍሎች፡ይሕንን፡አስማት፡በማሰራት፡ሰይጣን፡ጋር፡ተገናኝተው፡ብር፡ገንዘብ፡በማይቆጠር፡መጠን፡ሲቀበሉ፡ሰይጣን፡ደግሞ፡በየአመቱ፡የሕጻናት፡ደም፡ስለሚላቸው፡ነው። ወገኖቼ፡በመጽሐፍ፡ቅዱስ፡እንዲሕ፡የሚል፡ቃል፡እናገኛለን፡መጽሐፈ፡መቃብያን፡ቀዳማዊ፡ምእራፍ፡25፡ቁጥር፡1፡ስራቸው፡ጠማማ፡ነውና፡ሑሉንም፡በሚያስት፡የሰይጣን፡ስራ፡ፀንተው፡ የሚኖሩ፡ናቸውና፡፡፡መፅሐፈ፡መቃብያን፡ቀዳማዊ፡4፡30፡ደግሞ፡ሴቶች፡ልጆቻቸውንና፡ወንዶች፡ ልጆቻቸውንም፡ለአጋንንት፡ይሰዉ፡ነበረ፡ይለናል፡ውድ፡ወገኖቼ፡ከእንደዚሕ፡አይነቱ፡የሰይጣን፡ምግባር፡ለገንዘብ፡ብለን፡እንዳንገባ፡ ከልቤ፡ አሳስባለሁ፡፡ የሰይጣን፡ማደሪያ፡ከመሆን፡ፈጣሪ፡ይሰውረን!!! @ethiodebteratube @ethiodebteratube
نمایش همه...
ግብፅን ጨምሮ 6 የአረብ አገራት የጋራ ወታደራዊ ልምድ ጀመሩ ! መሰረቱን በግብፅ ያደረገው የጋራ ወታዳራዊ ልምምድ ‹‹ስዎርድ ኦፍ አረብ›› ወይም የአረብ ሰይፍ የሚሰኝ መጠሪያ ተሰጥቶታል፡፡ እሁድ የጀመረው የጋራ ትርኢትና ልምምዱ ከግብፅ በተጨማሪ ሳዑዲ አረቢያን፣ የተባበሩት አረብ ኢሜሬትስ፣ ጆርዳን፣ ባህሬን እና ሱዳንን አካቷል፡፡ ግብፅና ሱዳን ከሳምንት በፊት እስከ ኅዳር መጨረሻ ሳምንት የሚዘልቅ ወታደራዊ የጋራ ልምምድን መጀመራቸው ይታወሳል፡፡ የ6ቱ አገራት ጥምር ልምምድ ደግሞ እስከ ሐሙስ ይዘልቃል፡፡ የግብፅ ጦር መግለጫ በሜዲትራኒያን ባህር ግዛት ውስጥ በሚገኘው የሞሃመድ ናጊብ ወታደራዊ ይዞታ ላይ የሚከወነው ጥምር ልምምዱ የየብስ፣ አየር እና ባህር ኃይሎችን ያካተተ ትርዒት የሚታይበት ነው ሲል መግለጫ አውጥቷል፡፡ የልምምዱ ዓላማ የግብፅን እና የአረብ አገራቱን ወታደራዊ ግንኙነት ለማጠንከር ብሎም የወታደራዊ ኃይላቸውን ቁመና ለማሳደግ ነው ተብሏል፡፡ በተለይም ቀደም ብሎ ስለተጀመረው የግብፅና ሱዳን ወታደራዊ ልምምድ ባለፈው አርብ ምን ትላለህ የተባለው የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተለመደ ነገር በመሆኑ ኢትዮጵያን የሚያሳስባት ጉዳይ አይደለም ማለቱ ይታወሳል፡፡
نمایش همه...
ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ድርጅት 858 የሰሜን ዕዝ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላትን እንዳልተቀበለ አስታወቀ። የትግራይ ቴሌቪዥን በትናንት ምሽት ዘገባው ባሰራጨው መረጃ በትግራይ መንግስት ስር ያሉ 858 የሰሜን ዕዝ የአገር መከላከያ ሰራዊት አባላትን ለዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል አስረክበናል ብሎ ነበር። በርክክቡ ወቅትም የቀይ መስቀል አባላት በአካል ተገኝተው ነበርም ሲል ነው ቴሌቪዥን ጣቢያው የገለፀው። ይሁንና ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ተቋም ግን 858 የአገር መከላከያ ሰራዊት አባላትን እንዳልተቀበለ በድረገፁ አሳውቋል። ቀይ መስቀል በሰሜን ኢትዮጵያ በተከሰተው ጦርነት የተጎዱ ዜጎችን ህክምና እንዲያገኙ በማድረግ ላይ መሆኑን አስታውቋል። ድርጅቱ ከሁለቱም ወገኖች የተጎዱ ዜጎችን በ11 አንቡላንሶችን በማሰማራት ድጋፍ በማድረግ ላይ መሆኑንም ገልጿል። በጦርነቱ የተጠፋፉ ቤተሰቦችንም የማገናኘት ስራ በመስራት ላይ ሲሆን አሁንም ቤተሰብ የጠፋባችሁ ዜጎች በስልክ ቁጥር 0943122207 ወይም በ0115527110 ደውላችሁ ብታስመዘገቡ ልንረዳችሁ እንችላለን ብሏል። Via ኢትዮ ኤፍ ኤም ሕዳር 15 ቀን 2013 ዓ.ም
نمایش همه...
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹 'ቶ' መስቀል (አንቅህ) 🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹 'አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል' [መስቀሌን በመስቀሌ ላይ አኑር/አስቀምጥ] የዚህን እጅግ የረቀቀ አባባል የምንረዳው በትርጓሜ እና በምርምር ነው። መስቀል ከእየሱስ በፊት የነበረ እና ያለ ነው። ምሳሌነቱም የሰው ልጅ የቁጥር መልክ ነው። ስለሆነም 'ተ' ን ሰብእ ድረስ ስንቆጥረው 'ቶ' ሳብኡን ወይንም ሰባተኛውን እናገኛለን። ይህንን ነው እንግዲ ምንም መነሻና መድረሻ ቃል ሳይጨምሩ ከነአጠራሩ በግዕዙ #'አንቅህ' [#ankh] ወይም የህይወት ምልክት በማለት የሚጠሩት ። 'ቶ' ራስ ያለው ሰው ወይም ሰብእ ማለት ነው። ሰብእ ማለት ሰው ማለት ነው ይህውም ከሰባት ባህርያት ከአራቱ የሥጋ በህርያት ውሃ፣ አፈር፣ እሳት፣ ነፍስ እንዲሁም ከሶስቱ የነፍስ ባህርያት ህያውነት፣ ልባዊነት፣ ንባባዊነት የተፈጠረ ነው። ከእየሱስ ክርስቶስ ልደት በፊት ኢትዮጵያውያን ነገስታት መስቀል በትረ መንግስታቸው ወይም መለያቸው ነበር።በቀደሙ ዘመናት ደግሞ ኢትዮጵያውያን ነገስታት በሄዱበት እና በተቀመጡበት ቦታ ሁሉ በእጃቸው ይይዙት ነበር።ይህም የበትረ መንግስት ቀዳሚ ምሳሌ መሆኑ ነው። “ቶ” ሠባተኛዋ ቁጥር በመሆኗ ፍፁምነትን የምታመለክት ነች፡፡ ትልቁ ከዚህ በላይ ያለው ሚስጥር አባቶቻችን ከመፅሐፍ ቅዱስ ትርጔሜ ሲተነትኑ በሰማይ መላዕክት ዘንድ ውጊያ ሆነ ቅዱስ ሚካኤል ቅዱስ ገብርኤል ከሣጥናኤል ጋር ሲዋጉ ሁለት ጊዜ ተሸንፈዋል፡፡ በሶስተኛው እንዲያሸንፉ ሲልካቸው ይህን ቀስተደመና ቀርፆ፣ ይህን ምልክት የኮከቡን ቅርፅ የ“ቶ” ቅርፅ ያለው መስቀል በየክንፋቸው ቀርፆላቸዋል። 'ኤል'የሚለውንም ሚስጢራዊ ስም አትሞባቸዋል።ይህን ካደረገላቸው በኋላ ተመልሰው ወደ ውጊያው ቢሄዱ ሳጥናኤል ሀይላቸውን ሊቋቋመው አልቻለም ውድቀቱ ፈጠነ ሽንፈቱ የከፋ ሆነበት ፅልመትን አልብሰው ወደ በርባኖስ ውስጥ ጥልቅ ጨለማ ላይ ወረወሩት። ሰወች 'ቶ'ን የህይወት ምልክት አድርገዉ የሚወስዱት ለኢትዮጵያዉያን ብቻ ነዉ::የሚገርመዉ ደግሞ ይህ ምልክት አገልግሎት ላይ የዋለዉ ከክርስቶስ ልደት በፊት 3000 አመታት ቀደም ብሎ ጥንት ግብፃዉያን ቶኔቶር ብለዉ በሚጠሯት ሀገር ነዉ:: ግብፃዉያን እንደሚሉት የፒራሚድ ግንባታ ጥበብን የተማሩት ከቶኔቶር (የአሁኗ ኢትዮጵያ) ሰወችና አማልክቶች ነዉ:: በ670 አ.አ በኢትዮጵያ ነግሶ የነበረዉ ንጉስ ቲርሀቅ እየሩሳሌም የኦሶር ንጉስ በሆነዉ በሰናክሬም ስትወረር ለእየሩሳሌም መከታ ሆኖ ሲዘምት ሀያላን ከሚባሉ ወታደሮች ጋሻ ላይ የቶ ምልክት እንደተቀረፀና ንጉሱም በ'ቶ' ቅርፅ የተሰራ መስቀል ማሰሩን የሚያስረዱ የድንጋይ ላይ ፅሁፎች ተገኝተዋል:: . የ'ቶ' ምልክት የተፈጠረዉ በቅርብ ግዜ ነዉ ለሚሉ ሰወች 'ቶ 'የተፈጠረዉ አለም ሲፈጠር ነዉ' ብል እዉነት እንጅ ዉሸት አይሆንም::ለዚህ ማስረጃየ ደግሞ የሰዉ ልጅ የተፈጠረዉ በ'ቶ' ቀመር መሆኑ ነዉ:: . ይህ ምልክት ግብፅ በሚገኙ የዋሻ ስእሎች ላይ የህይወትን ገፀ ባህሪ ይዞ እንደነበር የሚያስረዳ ሲሆን ይህ ምልክት አገልግሎት የጀመረዉ ኢትዮጵያ ላይ ከሆነ ግብፅ ላይ እንዴት ተገኘ? ብሎ ለሚጠይቅ ግብፅ ላይ የነገሱት 18 ኢትዮጵያዊ ንጉሶች ተጠቃሽ ናቸዉ:: ሜምኖን የተባለዉ ኢትዮጵያዊ የግብፅ ንጉስ ከ1320 አ.አ እስከ ሴፕዩምስኬኩረስ 170 አ.ም የቆመ ሀዉልት እንደነበረዉና ሀዉልቱም ጠዋት ጠዋት ፀሀይ ሲያርፍበት የክራር ድምፅ ያሰማ እንደነበር ሄሮዱተስ በፓፒረስ ወረቀት ላይ አስፍሮት ይገኛል::ክራር ደግሞ የኢትዮጵያ የባህል መሳሪያ መሆኑ አጀብ ያስብላል:: በሳባዉያን የዋሻ ላይ ስእሎችና ማህተሞች ላይ 'ቶ' ተመስሎ ጣቱን የቀሰረ ምስል እንዳለ (አስቻለዉ ከበደ የተባለ ፀሀፊ ከርከቤዴል ሳዶፍ) በሚል መፅሀፉ አስፍሮታል::ሳባዉያን ሰዉን ለመሳል 'ቶ'ን መጠቀማቸዉ ያጋጣሚ ይመስላችሁአል? አይደለም። #ዴርቶጋዳ፣ #ራማቶሀራ፣ #ዣንቶዣራ፣ #ዮራቶራድ፣ #ዮቶድ፣ #ዮቶር፣ወ.ዘ.ተ ቃላት በቶ ፊደል የተመሰረቱ ና የቶ ን የፊደል ትርጉም መነሻ አድርገው የተመሰረቱ ቃላት ናቸው።ስለሆነም የ 'ቶ' ምልክት አገልግሎት ላይ የዋለዉ ከክርስቶስ ልደት በፊት 3000 አመታት ቀደም ብሎ ጥንት ግብፃዉያን #ቶርኔተር ወይም #ቶኔቶር ብለው የሚጠሯት የስልጣኔ ምንጭ ከሆነችው ከኢትዬጵያ ምድር ነው።'ቶ' የህይወት ምልክት ነው። ቶኔቶር ማለት የአምላክ ሀገር ማለት ነው።ቶኔቶር ተብላ የምትጠራው ሀገር ደግሞ ኢትዬጵያ ናት።ይህ የ'ቶ' ፊደል ቅርፅ ሰማያዊ ነው(ከሰማይ የወረደ)ነው።የሚሉ የስነፅሁፍ ምሁራና ተመራማሪዋች የሀይማኖት አባቶች አሉ። 🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹 ኖኅ Book delivery @ethiodebteratube @ethiodebteratube @ethiodebteratube
نمایش همه...
ነገረ ህወሃት 👿ህወሃት ከመጀመሪያው ጀምሮ ለስልጣን ስግብግብ ነበር እነሆ ከንጉሡ ውድቀት በኋላ የውጭ ሀገራት በዚያን ወቅት ለነፃነት ታጋይ ነን ባዮቹ ኢትዮጵያውያን ሙሉ ድጋፍ ለማድረግ የቻሉት እንዲሁ አሳዝነዋቸው ወይም ስለለመኑቸው አይደለም። #ሚስጥራዊ ውል እና ስምምነት ስለነበራቸው እንጂ።ከከተማ ተባርረው ጫካ የገቡት ለነፃነት ትግል አልነበረም ።ነገሩ ከተጋጋለ በኋላ የነፃነት ትግል ሆኖ እንዲቀጥል ያደረጉት እነዚያ የውጭ ሀገራት ናቸው። #አንዴት? ካላችሁ እንዲህ ነው ነገሩ እይውልህ/ሽ መጀመሪያ በተማሪዎቹ ዘንድ የሩሲያንም፣የፈረንሳይንም፣የአሜሪካንም የፖለቲካ ርዕዮት ማስረፅ ነበረባቸው ከአገራቱ መምህራንን እየላኩ እንዲያስተምሩ በማድረግ አሰረፁ።ተማሪዎችንም ወደየ አገራቸው እየወሰዱ እስተማሩ። ራሳቸው በመሰረቱት ዩንቨርስቲ ራሳቸው በላኩልን መምህራን ና ከእኛው አገር ወስደው አስተምረው በላኩልን መምህራን አማካኝነት ተማሪው ፖለቲካ አወቀ ። አብዮት ገባው። አንደ አማራጭ አድርገው ባቀረቡልን የልዩ ልዩ አገራት የፖለቲካ ርዕዮቶች/ተሞክሮዎች አማካኝነት ተማሪው የየራሱን ምርጫ ና የፖለቲካ አቋም እንዲኖር ዕድሉን ፈጠሩልን ። ተማሪውም የተለያዩ አገራትን አብዮት በመምረጥ በሀሳብ ልዩነት መከፋፈል ጀመረ° ያቺ የተማሯት ትምህርት ገንፍላባቸው የን ርዕዮት ማቀንቀን ጀመሩ እና አመፁ። የብዙዎች ምርጫ ሆኖ የተገኘው በዚያን ወቅት ገንኖ የነበረው የሶሻሊዝም ርዕዮት ነበር። በንጉሳዊ አገዛዝ ስር ስለነበርንም ያንን አገዛዝ ለመገርሰስ ሶሻሊዝምን ማቀንቀን የተሻለ ነበር ። እናም #መሬት ላራሹ ፣#ፊውዳል፣ #ወዘተ እያሉ አመፁ ። ሙሉውንም ህዝብ በንጉሣዊ አገዛዝ ላይ እንዲነሳ አድርገው አሳመፁ ።የተማሪዎችን አመፅ ደግፎ ጦር ሰራዊቱ ጣልቃ ገባና ንጉሱን ከዙፉናቸው አወረደ። በዚህ ሰዓት ጭሰኛ መደብ ላይ ያሉ እና በተማሪው ዘንድ ደስታ ፌስታ ሆነ ። ለጊዜው ብሎ ወታደሩ ስልጣን ይዞ ቆየ ።ወታደራዊ ቡድኑ ስልጣኑን ይዞ መቆየት እንደሚፈልግ ሲረዱ ።ሙህራን ተብዬዎች "ስልጣኑን ለህዝብ አስረክበህ ወደ ካምፕህ ተመመለስ"አሉ ወታደራዊው ቡድን "አብዮቱን ለአደጋ አጋልጬ ወደ ካምፕ አልመለስም" አይነት አቋም ያዘ ።በዚህም ፀቡ ቀጠለ ።ወታደራዊው መንግስት ተማሪወች የሚፈልጉትን ርዕዮት ተግባራዊ እያደረገ ቀጠለ። ስለዚህ በፓለቲካ ርዕዮት ዓለም በኩል በሲቪሉ አና በወታደራዊው ኮሚቴ መካከል ፀብ አልነበረም ማለት ነው። ምክንያቱም ተማሪው የሚፈልገው ርዕዮት ተግባራዊ ስለተደረገ ስለዚህ የስልጣን ፀብ ሆነና ሲቪሉ ሙህር ተደራጅቶ ከወታደራዊው መንግስት አና ከእሱ ጋር አብረው ከማሰሩ ሲቪል አብዮተኞች ከሆኑ ሙህራን ጋር የከተማ ጦርነት ተገባ። እነዚህ የተደረጁ ሙህራን ተብዬዎች ወታደራዊ ቡድኑን በሃይል ና በጫና ወደ ካምፑ አስመልሰው ስልጣን ለመረከብ ሲሉ የተለያዩ ሽብሮችን መፍጠር ጀመሩ ።#ነጭ ሽብር የሚባለውን። በዚህ ግዜ ወታደራዊ ቡድኑ ራሱን መከላከል ጀመረ ።ነጭ ሽብርን በቀይ ሽብር ለመመከት ቆርጦ ተነሳ ሲቪል አብዮተኞች ወታደራዊ ቡድን ስልጣን እንደማይሰጣቸው በደንብ ሲረዱ ደርሰው ሽብርተኛ ሆኑና ብዙ ሽብር ፈጠሩ ብዙ ሰው ገደሉ። በየከተማው በየአደባባዩ ገድለው ሬሳውን ጎዳና ላይ በመዝረፍ ገዳዩ መንግስት አንደሆነ አድርገው ሰፌ ፕሮፖጋንዳ በማሰራጨት በህዝብ ሊያስጠሉ ሞከሩ/ተሳካላቸው ።ዛሬ ድረስ በብዙሃኑ ዘንድ ወታደራዊው መንግስት ጨፍጫፊ አንደነበር ነው የሚታወቀው። መንግስቱ ሀይለማርያም #ጥፋቱ ስልጣኑን እንዲህ በችኮላ አልሰጥም የሚለው ድርቅንናው ቢሆንም ፣ከእሱ በበለጠ ግን የእነሱ ችኩልነት ና #ስግብግብነት በልጦ ስለነበር ቶሎ ማስረከብ ሳይችል እንዲቀር አደረገው ይልቁንም ከመስገብገባቸው ብዛት ወታደራዊ ቡድን ስልጣን አስረክቦ ወደ ካምፕ እንዳይመለስ አደረገው ና መሪ ወደ መሆን ተሸጋገረ በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ አገሪቱን አንዴት መምራት አንዳለበት እያሰበ ና እያመቻቸ ጎን ለጎን ነጭ ሽብርን እየተከላከለ ቀጠለ ።እነዚያ የዛሬ ህወሃት የቀድሞ ስግብግብ ሙህራኖች የከተማ ሽብራቸውን ቀጥለው ነበር እና ወታደሩም አብዮቱን ከአደጋ ለመከላከል ሲል ሽብርተኞችን ከከተማ ጠራርጎ ማስወጣት ስራው ሆነ ። የታጠቀም ነበርና እነዚያን #ኢህአፓ ገሌመሌ እያሉ በአንድ ጀንበር ተቧድነው የየራሳቸውን ፖርቲ መስርተው ስልጣኑን ከወታደሩ ለመረከብ ሲሻኮቱ የነበሩ ቡድኖች ላይ ተደጋጋሚ ጥቃት በማድረግ ከከተማ አበረራቸው የተባረረው ቡድንም ሸሽቶ ጫካ ገባ ✍ ከንጉሱ መውረድ በኋላ የነበረው የነበረው የፖለቲካ ፀብ ይሄ ነው ። ላዛሬ እዚህ ላይ ይብቃን ከተመቻችሁ #share አስተያየት ካላችሁ በዚህ በ @creator_anelay ላኩልኝ ምንጭ ፍስሐ ያዜ የሳጥናኤል ጎል ኢትዮጵያ ቁጥር 3 ይህ ቅምሻ tube ነው @kemishatube
نمایش همه...
የአማራ እናት ማቅ ለብሳ ልጇን ስትቀብር፤ የኦሮሞ እናት ተውባ ልጇን አትሞሽርም። የአንዱ እናት አልቅሳ የሌላው እናት አትስቅም። መልዕክቴ ለኦሮሞ እናቶች ነው።#ማርያምን ጠብቁን የቀን ጉዳይ ነው እናንተም ደም እንባ ታለቅሳላችሁ። ማርያምን ቃሌ ነው።የኦሮሞ እናት አንቺም በተራሽ ደም እንባ ታለቅሻለሽ። [ናሆም በፍቃዱ።]
نمایش همه...
የአማራ ተማሪዎች በትግራይ፣በኦሮሚያ እና በቤንሻንጉል ዩኒቨርሲቲዎች ደህንነታቸው ሳይረጋገጥ እንዳይሄዱ አተማ ምክረ ሀሳብ አቀረበ። በርኖስ ሚዲያ /ጥቅምት /23/2013 ዓ.ም የአማራ ተማሪዎች ማህበር /አተማ በወቅታዊ የአማራ ተማሪዎች ጉዳዬ አስቸኳይ የውሳኔ መግለጫ በስራ አስፈጻሚው በኩል አስታውቋል። በመግለጫውም እንዳለው ባለፉት ሶስት ዓመታት ማህበራችን ህጋዊ ፈቃድ አግኝቶ መንቀሳቀስ ከጀመረበት ወቅት ጀምሮ በመላ ኢትዮጵያ በተለይም በኦሮሚያ፣በትግራይ በደቡብ ክልሎች እንደ ህዝብ በአማራ ላይ በተማሪ ደረጃም በልዩነት የአማራ ተማሪዎች ሲፈናቀሉ፣ሲገደሉ እንደነበር በተከታታይ ስናጠና የጥናት ውጤቱንም ይፋ ስናደርግ እና ከመንግስት ጋር ችግሮች በሰላም እንዲፈቱ ስንታገል ቆይተናል። ሀገሪቱ ያለችበትን ተቀያያሪ የፖለቲካ ሁኔታ ግምት ውስጥ በማስገባት የተከሰቱ ችግሮችን መንግስት በመዋቅሩ እንዲፈታ የመነሻ ሀሳብ እና የመፍትሔ አቅጣጫ ከመስጠት ጀምሮ እያንዳንዱን አካሄዳችን በህግ ገድበን ቆይተናል።በአንድ በኩል ብሔራዊ ትስስሩ ላይ ጫና ላለመፍጠር በሌላ በኩል ከለውጥ ማግስት ለተሰየመው መንግስት የመርጊያ ጊዜ ለመስጠት ከልክ በላይ በድርድርና በውይይት ችግሮች እንዲፈቱ አስቸጋሪ ወቅቶችን በትዕግስት ለማለፍ ሞክረናል። በሳለፍናቸው ሶስት ዓመታት አማራ እየተባሉ ተማሪዎቻችን ሲገደሉ ሬሳ ተቀብለን የቀረውን ትውልድ ለማሻገር በሚል አንገት ደፍተን ለማሳለፍ ሞክረናል። ነገር ግን እንደ ህዝብ ከአምናው የቀጠለ የዘር ፍጅት አሁንም በተከታታይ እየተካሄደ ስለሆነ መንግስትም አቅም ፈጥሮ ይህን ችግር በትክክል የመፍታት አቅም ይፈጥር እንደሆነ በሚል የተሰጠውን ጊዜ መጠቀም ባለመቻሉ፣ይልቁንም አጉል እምነት ዕለት ዕለት ለችግር እያጋለጠን እንዳለ በመገንዘብ የ2013 የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት አሁንም በህዝቡ ዘንድ እየደረሰ እንዳለው እልቂት ፣ተቋማቱ የተማሪ ደህንነትን በሚመለከት ምንም አስተማማኝ ሁኔታ እንዳልፈጠሩ እና አሁንም የተማሪዎቻችን መገደያ ሆነው እንደሚቀጥሉ ገምግመናል ስለሆነም በመጭው የትምህርት ዘመን ማንኛውም የአማራ ተማሪ በትግራይ፣በኦሮሚያ እና በቤንሻንጉል ዩኒቨርሲቲዎች እንዳይሄድ ስንል ምክረ ሀሳብ አቅርበናል ። በአንጻሩ በአማራ ክልል ውስጥ የሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተጠቀሱት ዩኒቨርሲቲዎች የሚገኙ የአማራ ተማሪዎች ትምህርት እስኪጀምሩ ድረስ ምንም ዓይነት የትምህርት እንቅስቃሴ እንዳይጀምሩ የሰላማዊ ተቃውሞ እንቅስቃሴዎችን ከወዲሁ እንደምንጀምር እንገልጻለን። የማህበሩ ቅርንጫፎች ተማሪውን በማስተባበር ረገድ ራሳቸውን ዝግጁ እንዲያደርጉ ትዕዛዝ አስተላልፈናል። የተማሪ ወላጆች ፣የክልሉ መንግስትና የፖለቲካ ፓርቲዎች እንዲሁም አጋር የሲቪክ ማህበራት ከጎኑ እንዲቆሙ ጥሪ አስተላልፏል። በዓለም ላይ ርኩስ ተብሎ እንደተወገዘው የሆሎከስት የአይሁድ የዘር ፍጅት፣አማሮችን በአንድ ቦታ ሰብስቦ መረሸናቸው ልባችን ያደማ ክስተት በመሆኑ ሀዘናችን እንገልጻለን። ይህን ለመመከት የሚያስችሉ አካሄዶችን ከመንደፍ ጀምሮ በተግባር እስከመሰለፍ በሚደርሱ የራስ መከላከል አርምጃወች ለመሰለፍ ዝግጁ ነን ብሏል አተማ በመግለጫው። @bernosmedia24@ethiodebteratube
نمایش همه...
🙏ሰላም የኢትዮጵያ ህዝብ🙏 #Share #Like #Join በቅርቡ ሰምታቹህ ከሆነ የአሜሪካኑ ጠቅላይ ሚኒስቴር የሆኑት ዶናልድ ትራንፕ በድህረ-ገፃቸው ምንም ትርጉም ሊሰጥ የማይችል ነገር ፖሰቱ። ይህ ፖስት አለምን አነጋገረ። በBBC CNN ብቻ ምን አለፋህ የሀገራችን ሚዲያዎች ሳይቀር ዘግበውታል። ትራንፕ የፖሰቱት ቃል የትኛዉም ዲክሽነሪ ላይ ትርጉም አልተገኘለትም። ታዲያ እኚህ ሰው ተሳስተውም ይሁን ሆን ብለዉ የፖሰቱት ትርጉም የሌለዉ ፖስት የአለም መነጋገሪያ ሆነ። አየህ እቺ አለም እንዲ ናት ብቻ እውቅና ይኑር በሰዎች ዘንድ እያንዳንዱ ተግባርህ ትኩረት ይደረግበታል። ስለዚህ ታዋቂና ዝነኛ የሆናቹ የሀገራችን ሰዎች እባካቹ ምትናገሩትም ሆነ በማሀበራዊ ገፃቹ ላይ የምትለቁት መልእክት ህዝቡን ሊያጋጭ የሚችል ፣ የሰው ሂወት የሚያረግፍ ፣ የአካል ጉዳት የሚያስከትል እንዳይሆን ተጠንቀቁ፡፡ እዉቅናችሁና ዝነኝነታቹን ተጠቅማችሁ አስተማሪ መልእክት በማስተላለፍ ህዝቡ ስራላይ እንጂ ዘር ላይ ትኩረት እንዳያደርግ በማድረግ ሀገራችንን አሁን ከገባችበት አሳዛኝ ሁኔታ እንታደጋት፡፡ ✍ እኔ ፣አንተ እና አንቺም ተራ ሶሻል ሚዲያ ተጠቃሚ ነኝ የምንለው ቢሆን ያገኘነውን ነገር ሁሉ ሼር አናድርግ፡፡ ሶሻል ሚዲያ ላይ የሰውን ብሔር ፣ እምነት ፣ ቀለም ዝቅ የሚያደርጉ ፁፎችን አንለጥፍ፤ አንሳደብ፡ 🇪🇹ሀገር ማለት ሰዉ ነዉ🇪🇹 🇪🇹ሰው ነው ሀገር ማለት🇪🇹 በቅንነት ሼር በማድረግ ለሁሉም እናዳርስ!!! #Join To My Official Telegram Channel @ethiodebteratube #Share For Your Friends. 🙏መልካም ሌሊት የነገ ሰው ይበለን 🙏
نمایش همه...
✍ቅኔ ናት ሀገሬ!✍ ።።።።።።።።።።።።።። (ሚካኤል አስጨናቂ) ጠፍጥፎ የሰራት ፥ ያበጃት ይመስል፣ ይሄ የቀለም ቀንድ ፥ የህሊና ስንኩል፣ ትፈርሳለች ይላል ፦ ሟርቱን ከሀገሬ ደጅ ፥ በራፏ ላይ ሊጥል። ደግሞም ... ወዲህ ለቅርሻቱ ፥ ሊጠቅስ ማስረጃ፣ ምሳሌ አስታኮ ፥ ሊያቆም የቃል ፍርጃ፤ መጥሀፉን ሊያብል ፥ ቃልኪዳኗን ሽሮ፣ ዓይኑ ሩቅ ማትሮ ... ሶሪያን ይጠራል ፥ ድንበሯን ተሻግሮ። #እኔ  የቃል ግንዝ አይጥ ፥ የጠቆረ ዶሮ፣ የሚከረፋ ደም ፥ የሟርት እንጉርጉሮ፣ ትፈርሳለች የሚል ፥ የምሁር ደንቆሮ፤ በሚዘራው ክፋት ፥ በሚያቆየው በደል፣  ልቤ ሳይሸነገል ! ፈገግ ብዬ አልፋለሁ ፥ ዥልነቱን ላቀል።  አትፈርስም ሀገሬ፣ የቃል ኪዳን ቅጥሬ። ምን ዳሷ ቢያጋድል ፥ መሰረቷ ዘሞ፣  ምንም ታላቅ ባትሆን ፥ እንዲያ እንደቀድሞ፤ መቶ ቅጠል በጣሽ ፥ ሚልዩን ደፍተራ፣ እልፍ ባለ ጋኔን ፥ የእርኩሰት ደመራ፤  ልበትናት ብሎ.. በየ አዳራሹ ... ቢፎክር ቢያቅራራ። ማንነቷን ሊያሽር ... ንጉስ ብረት ይዞ ፥  በሰይፍ ቢሸልል፣ ሀገሬ ቢላል ናት ... በስጋዋ ቁስል ፥ እምነቷን የማጥል። አትፈርስም ኢትዮጵያ! የአዳም መጀመሪያ። ጠኔ ክንዱ ቢያይል ፥ ውሀ ጥም ቢያደብናት፣ የማጣት ቀንበሩ ፥ ወገቧን ቢያጎብጣት። የወደቀች ብትመስል ፥  ከሁሉ ተናንሳ፣ በርባን ከስር ወጥቶ ፥ ደንፍቶ ቢያገሳ፣ ዓለሙ ሊሳለቅ ፥ እንጨቱን አጣምሮ ፥ መስቀሉን ቢያነሳ፣ ሀገሬ መሲህ ናት... የክርስቶስ ሀምሳል ፥ ቀብረናታል ሲሉ ፥ ሞታ ምትነሳ። አትፈርስም! አትፈርስም! ኢትዮጵያ አትፈርስም... ቢፈጡሩ ጥያቄ  ፥ የሰይጣን ካህናት ፥ ሳንቲም እያነሱ፣ የዘረጉት ወጥመድ ... የሚምሱት ጉድጓድ ፥ ሀገሬን ሳይጥላት ፥ ይተርፋል ለነሱ። አዎን ማህደር ናት! ማንም እሳት ቢጭር ፥ ማገዶ ቢከምር ፥ ሊያከስላት አሳሮ፣  ሀገሬ ሚስጥር ናት! የፈጣሪ ቅኔ ፥ የስንኞች ግማድ ፥ የፍቅር ቋጠሮ።  አፍራሿ ይፈርሳል.. በለኮሰው እሳት ፥ በቁሙ እያለቀ አካሉ፦ ቀንጭሮ። 🙌መልካም ምሽት ይሁንልን 🙌 #Share To Your Friends And #Join Me On Telegra @ethiodebteratube
نمایش همه...