fa
Feedback
🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts

🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts

رفتن به کانال در Telegram

ይህ በአቡ ጁነይድ ሳላህ አህመድ የቀረቡ የድምፅና የፅሁፍ መልዕክቶች የሚሰበሰቡበት ቻነል ነው። አላህ ጠቃሚ እውቀትን ከመልካም ስራ ጋር ያግራልን! You can contact me here @salehom100

نمایش بیشتر
2 174
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-27 روز
-1930 روز
آرشیو پست ها
🌟የወንዶች አለባበስ 🌟አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/542 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

የወንዶች አለባበስ .mp323.05 MB

🔠🔠🔠🔠🔠🔠 🔠🔠 ከረመዳን በፊት ከናይልሳት በተጨማሪ በኢትዮሳት ስርጭት ለመጀመር እንችል ዘንድ የሁላችሁንም ትብብር እንሻለን። በ ኢትዮሳት የ CBE ንግድ ባንክ አካውንታችን የቻሉትን ድጋፍ በማድረግ አጋርነትዎን በተግባር ያረጋግጡ። 🤍 444 የአካውንቱ ባለቤት ibnu Masoud islamic Center @Nesihatv

🔖 Apply for fully funded Saudi scholarships in different fields King Abdulaziz University Scholarship 2024-25 in Saudi Arabia (Fully Funded) Deadline: 28th dec,2023 Apply here:- https://graduatestudies.kau.edu.sa/Content-306-EN-278671 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🔖 Apply for fully funded Saudi scholarships in different fields King Abdulaziz University Scholarship 2024-25 in Saudi Arabia (Fully Funded) Deadline: 28th dec,2023 Apply here:- https://moe.gov.sa/en/knowledgecenter/eservices/pages/nonsaudiinternalscholarship.aspx ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🌟ከኢስባል እንጠንቀቅ! 🌟 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/537 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🔖 የእምነት ፈተና እና የኢማሙ አሕመድ ፅናት 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ ⌚️ 38:12 ደቂቃ 🍂 የአህሉሱና ኢማም አህመድ ኢብኑ ሀንበል በንጉሶች በታገዙ ጀህሚያዎች የደረሰባቸውን ከባድ ግፍና ፈተና ካለፉበት ፅናት የሚወሰዱ ትምህርቶች https://t.me/abujunaidposts/92 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

تلاوة_وسارعوا_إلى_مغفرة_الدوسري_231.mp32.16 MB

🔖 ዓቂዳ እና መንሐጅ... ዘጠኝ ወሳኝ ነጥቦች 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ 📌 ትኩረት የሚሹ 9 የአቂዳና የመንሐጅ ጉዳዮችን ይዳስሳል https://t.me/abujunaidposts/88

የሸህ አህመድ የህልም ደብዳቤ የመስጂደነበዊ ኻዲም ሸህ አህመድ ያስተላለፉት ደብዳቤ እየተባለ የሚሰራጨውን መልእክት ብዙዎቻችን ከልጅነት ጀምሮ እናውቀዋለን። ‘መልእክቱን ያሰራጨ ኸይር ያገኛል፤ ችላ ያለው መአት ያገኘዋል’ በሚሉ የሀሰት ምሳሌዎችና ማስፈራሪያዎች ስለታጨቀ መልእክቱ በየጊዜው በስፋት ተሰራጭቶ እናገኘዋለን። በተለይም ከማህበራዊ ሚዲያዎች መስፋፋት በኃላ የስርጭቱ ይዘት በእጅጉ ጨምሯል። አያሌ ስህተቶች ያሉበት ይህ ደብዳቤ ተጨባጭነት የሌለውና የሙስሊሞችን አቂዳ የሚሸረሽር በመሆኑ ከማሰራጨት ልንቆጠብ ይገባል። የኢስላም ሊቃውንትም በውስጡ ያሉትን ግድፈቶች እና ቅጥፈቶች በመግለፅ ውሸትነቱን አስረድተዋል። የኡለማዎቻችንን መልእክት ያዘሉ አያያዥ ሊንኮችን ከታች አስቀምጫለው። የአላህ ፈቃድ ከሆነ ሀሳባቸውን ጠቅለል አድርጌ በሌላ ፅሁፍ አካፍላችኃለው። ለግዜው ስለይዘቱ ከአንድ ወንድም ፅሁፍ ቀንጨብ አድርጌ ጥቂት ልበላችሁ። 1ኛ፦ ደብዳቤው እንደሚለው የነቢያችን ሸፋዐ ትርኪ ምርኪ ያዘለ ወረቀት በማባዛት አይገኝም፡፡ ሸፋዐህ ከሚገኝባቸው መንገዶች መካከል፡- ሀ. ከኡመታቸው ውስጥ በአላህ አምልኮ ላይ ምንንም ማንንም ሳያጋራ በተውሒዱ ላይ ጸንቶ የሞተ፡፡ ሙስሊም ከአቢ ሁረይራህ የዘገበው ሐዲሥ ቁ 338 ለ. ከልቡ በኢኽላስ "ላ ኢላሀ ኢለሏህ" ያለ ሰው፡፡ ቡኻሪይ ከአቢ ሁረይራህ የዘገበው ሐዲሥ ቁ 99 ሐ. ከአዛን በኋላ ያለውን ዱዓ ያደረገ ቡኻሪይ ከጃቢር ኢብኒ-ዐብዲላህ የዘገበው ሐዲሥ ቁ 614 اللَّهُمَّ رَبَّ هَذِهِ الدَّعْوَةِ التَّامَّةِ وَالصَّلَاةِ الْقَائِمَةِ آتِ مُحَمَّدًا الْوَسِيلَةَ وَالْفَضِيلَةَ وَابْعَثْهُ مَقَامًا مَحْمُودًا الَّذِي وَعَدْتَهُ መ. በሳቸው ሀገር በመዲና የኑሮም ይሁን ሌሎችን ችግሮችን በመቋቋም ጸንቶ የኖረና እዛው የሞተ ሙስሊም፡፡ ሙስሊም ከአቢ ሰዒድ አል-ኹድሪይ የዘገበው ሐዲሥ ቁ 477 ሠ. የሱንና ሶላቶችን ማብዛት፡፡ ሙስነድ ኢማሙ አሕመድ ሐዲሥ ቁ 16076 2ኛ፡- ወረቀቱን ያባዛ አንድ ሰው ብዙ ዕድሎች ገጠሙት ይላል፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ በኢስላም ዕድል የሚባል ነገር የለም፡፡ በዚህ ዓለም ላይ የሚከናውኑ ክስተቶች ሁሉ፤ አላህ ዘንድ ቀድሞ በታወቀው ለውሐል መሕፉዝ ላይ የተጻፉ አላህ በሻውና በፈቀደው መልኩ የሚከሰቱ የቀዷ ወል-ቀደር ውጤት ናቸው። እድል እና አጋጣሚ የሚባል ነገር የለም፡፡ ለመልካም እድል ምክንያት (ሰበብ) የሚሆኑ ነገሮዕን ለመጠቆም ካስፈለገ፤ አላህን መፍራት፡ ዝምድና መቀጠል፡ ሐላል ሪዝቅን ብቻ መከጀል እንጂ ወረቀት ኮፒ ማድረግ ዕድልን አያሰፋም፡፡ 3ኛ፡- ወረቀቱን ከማባዛት ችላ ያለው ሰውዬ በዚህ ሰበብ በዘጠነኛው ቀን ሞተ ይላል፡፡ ማንኛይቱም ነፍስ የምትሞተው አላህ የወሰነላትን ምድራዊ ቆይታ ስትጨርስ ብቻ ነው (አሊ-ዒምራን 145) ሰዓቱ ሲደርስ ወደፊት ወደኋላ የለም!! ለመሆኑ ወረቀት ኮፒ አለማድረግ እንዴት ለሰውየው ሞት ምክንያት ይሆናል? ለመሆኑ ይሄ ወረቀት ደርሷችሁ ችላ ያላችሁት ወይንም ቀዳችሁ የጣላችሁ ወንድምና እህቶች የላችሁም? 4ኛ፡- ወረቁቱን ያሰራጨ ሰው ከዚህ በፊት አይቶት የማያውቀውን ነገር ያያል፡፡ ኸይር ነገር የሚገኘው በአላህ ችሮታ ብቻ ነው። ወረቀትን በማሰራጨት የሚገኝ ዕድል ወይም የሚመጣ መአት የለም!! ሀሰትን ከማሰራጨት እንቆጠብ!! External links ☞ ሸይኽ ኢብኑ ባዝ (ረሒመሁላህ) ምንጭ፡- አል-ኢስላሙ ሱአሉን ወጀዋብ ጥያቄ ቁ 31833 https://www.binbaz.org.sa/article/26 ☞ ሸይኽ ሷሊሕ አል-ፈውዛን http://www.alfawzan.af.org.sa/node/3736 ☞ ሸይኽ አብዱልአዚዝ አሰድሀን الوصية المكذوبة للشيخ عبد العزيز السدحان https://saaid.net/Minute/mm63.htm 🍂 Lies about a dream falsely attributed to the Watchman of the Prophet’s tomb https://islamqa.info/en/31833 ✍ አቡጁነይድ Aug 4, 2018 t.me/abujunaidpost

🔖 የኑህ መርከብ 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ Share link https://t.me/abujunaidposts/520 @nesihastudio

🎙 ማውጫ (በየግዜው የሚታደስ) 1) ተውሒድ በሱረቱል ከሕፍ ታሪኮች https://t.me/abujunaidposts/136 2) ኢስላማዊ ማንነት https://t.me/abujunaidposts/391 3) ወደ አላህ ሽሹ https://t.me/abujunaidposts/184 4) ቁርአን የልብ ብርሃን! https://t.me/abujunaidposts/97 5) የእምነት ፈተና እና የኢማሙ አሕመድ ፅናት https://t.me/abujunaidposts/92 6) የሰለፎች ብሩህ ፋና! https://t.me/abujunaidposts/521 7) ደስተኛ ኢስላማዊ ቤተሰብ https://t.me/abujunaidposts/103 8) እህቴ ሆይ! ከሷሊሀት ነሽን? https://t.me/abujunaidposts/151 9) የትዳር አለመግባባትና ሸሪዓዊ መፍትሄዎቹ https://t.me/abujunaidposts/189 10)  የሙስሊም ወጣቶች ሚና እና ሃላፊነት https://t.me/abujunaidposts/143 11) ከተርቢያ ጥበቦች https://t.me/abujunaidposts/341 12) የተውሒድ እውነታ በቁርአን እይታ https://t.me/abujunaidposts/360 13) ተጋሾችን አበስራቸው https://t.me/abujunaidposts/416 14) መውሊድ.. ብዥታዎችና መልሶቻቸው https://t.me/abujunaidposts/105 15) ንፁሕ ልብ https://t.me/abujunaidposts/137 16) የሙስሊሞች አንድነት https://t.me/abujunaidposts/132 17) የቁርአን ወዳጆች https://t.me/abujunaidposts/147 18) የአላህ ስሞችና ሲፋት https://t.me/abujunaidposts/160 19) የረጀብ ወር እና ድንጋጌዎቹ https://t.me/abujunaidposts/152 20) የሰለፎች ልገሳና አርአያነቱ https://t.me/abujunaidposts/86 21)  ተውሒድ እና የሐጅ ፍሬዎች https://t.me/abujunaidposts/47 22) ዒባዳን ለመገንዘብ! https://t.me/abujunaidposts/209 23) የኑህ መርከብ https://t.me/nesihastudio/2152 24) ሸ/ ሙሀመድ ኢብኑ ዓብዲል ወሓብ (ብዥታዎችና መልሶቻቸው) https://t.me/abujunaidposts/215 25) የዳዕዋ መሰረቶች https://t.me/abujunaidposts/237 26) ዓቂዳ እና መንሐጅ... 9 ወሳኝ ነጥቦች  https://t.me/abujunaidposts/88 27) የመሰባሰብ (መጃሊስ) አዳቦች https://t.me/abujunaidposts/343 28)  አምስት ምክሮች ለቁርአን ሐፊዞች https://t.me/abujunaidposts/72 29) ተውሒድ በምሳሌ https://t.me/abujunaidposts/484 30) ሱናን መከተል https://t.me/abujunaidposts/394 31) የመስጂዶች ሚና https://t.me/abujunaidposts/399 32) ቅድሚያ ለተውሒድ (በትርጉም የቀረበ) ዶ/አብደላህ አልጀርቡዕ https://t.me/abujunaidposts/125 33) የህይወት ጥያቄዎች (በትርጉም የቀረበ) ዶ/ሚስዓድ አልሑሰይኒይ https://t.me/abujunaidposts/177 34) ከሱረቱል ፋቲሀ ቁምነገሮች (በትርጉም የቀረበ) ዶክተር ሙሀመድ አልሁጀይሊይ https://t.me/abujunaidposts/217 35) መውሊድ ኢስላማዊ በዓል ነውን? https://t.me/abujunaidposts/411 36) የትዕግስት ፍሬ በነብዩ አዩብ ታሪክ https://t.me/abujunaidposts/356 37) የሀሰን ታጁ መውሊድ መፅሀፍ ሲፈተሽ https://t.me/abujunaidposts/117 38) ሙስሊሟና የረመዳን ፆም ቀዷ https://t.me/abujunaidposts/328 39) እኛ እና መጅሊስ እውነታና አሉባልታ (ንባብ አቡሙስዓብ) https://t.me/abujunaidposts/299 40) በኢንተርኔት የሚሰራጩ ሰሂህ ያልሆኑ ዘገባዎች ክፍል 1 https://t.me/abujunaidposts/233 ክፍል 2 https://t.me/abujunaidposts/241 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🎙 የአቡ ጁነይድ ሙሐደራዎች ማውጫ 1) ተውሒድ በሱረቱል ከሕፍ ታሪኮች https://t.me/abujunaidposts/136 2) ኢስላማዊ ማንነት https://t.me/abujunaidposts/391 3) ወደ አላህ ሽሹ https://t.me/abujunaidposts/184 4) ቁርአን የልብ ብርሃን! https://t.me/abujunaidposts/97 5) የእምነት ፈተና እና የኢማሙ አሕመድ ፅናት https://t.me/abujunaidposts/92 6) የሰለፎች ብሩህ ፋና! https://t.me/abujunaidposts/521 7) ደስተኛ ኢስላማዊ ቤተሰብ https://t.me/abujunaidposts/103 8) እህቴ ሆይ! ከሷሊሀት ነሽን? https://t.me/abujunaidposts/151 9) የትዳር አለመግባባትና ሸሪዓዊ መፍትሄዎቹ https://t.me/abujunaidposts/189 10) የሙስሊም ወጣቶች ሚና እና ሃላፊነት https://t.me/abujunaidposts/143 11) ከተርቢያ ጥበቦች https://t.me/abujunaidposts/341 12) የተውሒድ እውነታ በቁርአን እይታ https://t.me/abujunaidposts/360 13) ተጋሾችን አበስራቸው https://t.me/abujunaidposts/416 14) መውሊድ.. ብዥታዎችና መልሶቻቸው https://t.me/abujunaidposts/105 15) ንፁሕ ልብ https://t.me/abujunaidposts/137 16) የሙስሊሞች አንድነት https://t.me/abujunaidposts/132 17) የቁርአን ወዳጆች https://t.me/abujunaidposts/147 18) የአላህ ስሞችና ሲፋት https://t.me/abujunaidposts/160 19) የረጀብ ወር እና ድንጋጌዎቹ https://t.me/abujunaidposts/152 20) የሰለፎች ልገሳና አርአያነቱ https://t.me/abujunaidposts/86 21) ተውሒድ እና የሐጅ ፍሬዎች https://t.me/abujunaidposts/47 22) ዒባዳን ለመገንዘብ! https://t.me/abujunaidposts/209 23) የኑህ መርከብ https://t.me/nesihastudio/2152 24) ሸ/ ሙሀመድ ኢብኑ ዓብዲል ወሓብ (ብዥታዎችና መልሶቻቸው) https://t.me/abujunaidposts/215 25) የዳዕዋ መሰረቶች https://t.me/abujunaidposts/237 26) ዓቂዳ እና መንሐጅ... 9 ወሳኝ ነጥቦች https://t.me/abujunaidposts/88 27) የመሰባሰብ (መጃሊስ) አዳቦች https://t.me/abujunaidposts/343 28) አምስት ምክሮች ለቁርአን ሐፊዞች https://t.me/abujunaidposts/72 29) ተውሒድ በምሳሌ https://t.me/abujunaidposts/484 30) ሱናን መከተል https://t.me/abujunaidposts/394 31) የመስጂዶች ሚና https://t.me/abujunaidposts/399 32) ቅድሚያ ለተውሒድ (በትርጉም የቀረበ) ዶ/አብደላህ አልጀርቡዕ https://t.me/abujunaidposts/125 33) የህይወት ጥያቄዎች (በትርጉም የቀረበ) ዶ/ሚስዓድ አልሑሰይኒይ https://t.me/abujunaidposts/177 34) ከሱረቱል ፋቲሀ ቁምነገሮች (በትርጉም የቀረበ) ዶክተር ሙሀመድ አልሁጀይሊይ https://t.me/abujunaidposts/217 35) መውሊድ ኢስላማዊ በዓል ነውን? https://t.me/abujunaidposts/411 36) የትዕግስት ፍሬ በነብዩ አዩብ ታሪክ https://t.me/abujunaidposts/356 37) የሀሰን ታጁ መውሊድ መፅሀፍ ሲፈተሽ https://t.me/abujunaidposts/117 38) ሙስሊሟና የረመዳን ፆም ቀዷ https://t.me/abujunaidposts/328 39) እኛ እና መጅሊስ እውነታና አሉባልታ (ንባብ አቡሙስዓብ) https://t.me/abujunaidposts/299 40) በኢንተርኔት የሚሰራጩ ሰሂህ ያልሆኑ ዘገባዎች ክፍል 1 https://t.me/abujunaidposts/233 ክፍል 2 https://t.me/abujunaidposts/241 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

👌 መውሊድን የተመለከቱ ብዥታዎችና መልሶቻቸው 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ ⌚️ የ 72 ደቂቃ ሙሀደራ (64 kbps = 34.65 mb) 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/267 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

በካፊሮች በዓል እንኳን አደረሳችሁ ማለት ይፈቀዳልን? በበአላት ሰሞን በተደጋጋሚ እገሌና እገሌ ላይክ አድርገውታል ከሚለን ፖስቶች መካከል ከፊሎቹ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክቶች ናቸው። ለጌታ መወለድ፣ ለጌታ መሰቀል፣ ለጌታ ሞቶ መነሳት (ትንሳኤና) መሰል ክስተቶች እንኳን አደረሳችሁ ሲባል ሼር ወይም ላይክ የሚያደርጉ ብዙ እህትና ወንድሞችን አስተውያለው። አንዳንዴ በስህተት ሌላ ግዜም ነገሩን እንደቀላል በመውሰድ የሚፈፀም ሊሆን ይችላል። ሆኖም እጅግ ከባድና በአኼራ ዋጋ የሚያስከፍል መዘናጋት ነው!! በካፊሮች በአል፤ እንኳን አደረሳችሁ... እንኳን ደስ አላችሁ... እንኳን አብሮ አደረሰን ማለት እነሱን ለማስደሰትም ይሁን ለመመሳሰል ከአላህ ዲን መንሸራተት እና የካፊሮችን ኩፍር የመናገር ስነልቦና መካብ ስለሆነ ክልክል ነው። መከባበር እና አብሮነትን ለማሳየት ከእምነታችን መንሸራተት አይጠበቅብንም። ዲን ከምንም በላይ ነውና ሸሪዓን መተላለፍ ፍፁም ጥፋት ነው!! ፈጣሪ ወለደ ተወለደ የሚለው አስተምህሮ የጥፋትነቱ ክብደት ሰማያትንና ምድርን ሊሰነጥቅ እንደሚቀርብ ቁርአን ይነግረናል። አላህን የሚያስቆጣ ተግባር በመፈፀማቸው እንኳን ደስ ያላችሁ ማለት ከሙስሊም አይጠበቅም!! (وَقَالُوا۟ ٱتَّخَذَ ٱلرَّحۡمَـٰنُ وَلَدࣰا * لَّقَدۡ جِئۡتُمۡ شَیۡـًٔا إِدࣰّا *  تَكَادُ ٱلسَّمَـٰوَ ٰ⁠تُ یَتَفَطَّرۡنَ مِنۡهُ وَتَنشَقُّ ٱلۡأَرۡضُ وَتَخِرُّ ٱلۡجِبَالُ هَدًّا *  أَن دَعَوۡا۟ لِلرَّحۡمَـٰنِ وَلَدࣰا *  وَمَا یَنۢبَغِی لِلرَّحۡمَـٰنِ أَن یَتَّخِذَ وَلَدًا *  إِن كُلُّ مَن فِی ٱلسَّمَـٰوَ ٰ⁠تِ وَٱلۡأَرۡضِ إِلَّاۤ ءَاتِی ٱلرَّحۡمَـٰنِ عَبۡدࣰا *  لَّقَدۡ أَحۡصَىٰهُمۡ وَعَدَّهُمۡ عَدࣰّا *  وَكُلُّهُمۡ ءَاتِیهِ یَوۡمَ ٱلۡقِیَـٰمَةِ فَرۡدًا) [«አልረሕማንም ልጅን ያዘ (ወለደ)» አሉ፡፡ ከባድ መጥፎን ነገር በእርግጥ አመጣችሁ፡፡ በእርሱ (በንግግራቸው ምክንያት) ሰማያት ሊቀደዱ፣ ምድርም ልትሰነጠቅ፣ ጋራዎችም ተንደው ሊወድቁ ይቃረባሉ፡፡ ለአልረሕማን ልጅ አለው ስለአሉ፡፡ ለአልረሕማን ልጅን መያዝ አይገባውም!! በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉ (በትንሣኤ ቀን) ለአልራሕማን ባሪያ ኾነው የሚመጡ እንጂ ሌላ አይደሉም] Surah Maryam 88 - 95 ለመሆኑ አንድን ካፊር ለሀይማኖታዊ በአል እንኳን አደረሰህ ስትለው፤ ምን ማለት እንደሆነ ግልፅ አይደለምን? እንኳን አደረሰህ... ጌታ ተወልዶ ተሰቅሎ ሞቷል ብለህ ለማወጅ፣ ለመስቀል ለመስገድና  የፈጣሪን ክብር የሚነኩ ንግግሮችን ለመናገር እንኳን በቃህ! እንኳን አደረሰህ... ማርያም ፈጣሪዋን ወለደችው፤ በመጠቅለያም ጠቀለለችው እያልክ ለመዘመር እንኳን በቃህ! የኩፍር ተግባርን ለመከወን ከሆነ የደረሰው ለምንስ እንኳን አብሮ አደረሰን እንላለን? እውቁ አሊም ኢብኑል ቀይም ረሂመሁላህ ይህ ተግባር የተከለከለ ስለመሆኑ የኡለማዎች የጋራ አቋም መሆኑን በመጠቆም እንዲህ ብለዋል፤ «ኩፍርን ብቻ በሚያንፀባርቁ የሀይማኖታቸው መገለጫዎች እንኳን አደረሳችሁ...እንኳን ደስ ያለችሁ ማለት ሀራም መሆኑ የሁሉም ሊቃውንት ስምምነት ያለበት ነው። ለምሳሌ አንድ ሙስሊም በነሱ በዓላትና ፆም ጊዜ፤ «በአሉን የተባረከ ያድርግልህ» ወይም «መልካም የደስታ በአል ያድርግልህ» እና መሰል የደስታ መግለጫዎችን ቢያስተላልፍ፤ ተናጋሪው ከኩፍር ቢድን እንኳ ከባድ ወንጀል ነው የፈፀመው። ይህም፤ ልክ «እንኳን ለመስቀል ሰገድክ» ብሎ ደስታን እንደመግለፅ ነው! ይህ እንደውም፤ አንድ ሰው ነብስ በማጥፋቱ፣ አልኮል በመጠጣቱ፣ ዝሙት በመፈፀሙና በመሰል ተግባራት እንኳን ደስ ያለህ ከማለት በወንጀልነት የከበደ እና አስቀያሚ ነው። ለኢስላማዊ ድንጋጌዎች ተገቢዉን ክብር የማይሰጡ ብዙ ሰዎች ይህንን ይፈፅማሉ።  ምን ያክል የሚያስጠላ የግባር እንደፈፀሙም አያስተውሉም። ቢድአ፣ ኩፍር እና ወንጀሎች በመፈፀማቸው እንኳን አደረሰህ፣ እንኳን ደስ ያለህ እና መሰል የደስታ መግለጫዎችን ያስተላለፈ፤ እራሱን ለአላህ ቁጣና ጥላቻ የተገባ እንዲሆን የሚያደርግ ምክኒያት ፈፅሟል»  አህካም አህሉዚማህ የዘመናችን ፈቂህ ሸይኽ ኡሰይሚን ረሂመሁላህ እንዲህ አሉ «ካፊሮችን እንኳን አደረሳችሁ ማለት ኢብኑል ቀይም እንዳለው የዚህን ያክል ከባድ የሆነበት ምክኒያት እነርሱ የሚፈፅሟቸውን የኩፍር መገለጫዎች ማፅደቅ ስለሆነ ነው። ምንም እንኳን ለራሱ ይህንን ኩፍር መፈፀምን ባይወድም እነሱ መፈፀማቸውን ወዷልና። ሙስሊም ደግሞ የኩፍር መገለጫዎችን መውደድም ይሁን ሌሎችን እንኳን ደስ ያላችሁ ማለት አይፈቀድለትም።» መጅሙዑ ፈታዋ ወረሳኢል አሸይኽ ኢብኑ ኡሰይሚን 3/44  በተመሳሳይ መልኩ፤ ክሪስማስም ሆነ ሌሎች በአላት ላይ ስጦታ ወይም ፓስት ካርዶችን መለዋወጥ፤ እንዲሁም ማንኛውም ደስታን መግለጫ የሆኑ ነገሮችን መፈፀም በአሉን መካፈል ስለሆነ የተከለከለ ነው!! በዚህ ፅሁፍ መጠቆም የፈለኩት ምንም አይነት ማህበራዊ ግንኙነት ሀራም ነው የሚል መልእክት አይደለም። በተለይም ከክርስቲያን እና አይሁዶች ጋር ባለን ማህበራዊ ግንኙነቶች ላይ የተፈቀዱ ብዙ በመልካም የመኗኗር እሴቶች አሉን።  ሆኖም ሀይማኖታዊ ወሰኖች የሉም ማለት አይደለም። የተፈቀደውን ስንተገብር እንደ ያልተፈቀደ ጋብቻ፣ በአላት ላይ መሳተፍ፣ ለሞቱት የአላህን ማርታ መለመንና ባጠቃላይ በዲን መመሳሰልን ግን በፍፁም አንፈፅምም። ይህንን የእምነትና የሀይማኖት ወሰን መናድ አይቻልም። ማንነታችንን ማክበር፣ ግንኙነታችንን በዲናዊ ገደቦች ማጠር ብሎም አለመሟሟት ለሌሎች ሞራል ዲንና ማንነት ከመጨነቅ ይቀድማል። ዲን ከምንም በላይ ነውና ከመሸማቀቅ እንውጣ። ይህ  የዲናችን መገለጫ እንጂ እንደ ማክረርና ፅንፈኝነት የሚታይ አይደለም። በነገራችን ላይ የአንድ እምነት ተከታይ ከሌሎች ለመቀራረብ ብሎ ከራሱ እምነት ጋር የሚጣላበት ሁኔታ ድሮ ቀርቷል። ሌሎቹም ቢሆኑ ይህ በኛ ሀይማኖት አልፈቀድም እና ይቅርታ ይሉሀል። (فَلَا تُطِعِ ٱلۡمُكَذِّبِینَ * وَدُّوا۟ لَوۡ تُدۡهِنُ فَیُدۡهِنُونَ * وَلَا تُطِعۡ كُلَّ حَلَّافࣲ مَّهِینٍ) አስተባባዮችንም አትታዝዙ፡፡ ብትመሳሰላቸውና ቢመሳሰሉህ ተመኙ፡፡ [Surah Al-Qalam 8 - 10] ወላሁ አዕለም አላህ ከጥፋት ሁሉ ይጠብቀን! https://t.me/abujunaidposts/141 ____ አቡጁነይድ ረጀብ 24/1437 ዓ.ሒ / ሜይ 1/ 2016

በካፊሮች በዓል እንኳን አደረሳችሁ ማለት ይፈቀዳልን? በበአላት ሰሞን በተደጋጋሚ እገሌና እገሌ ላይክ አድርገውታል ከሚለን ፖስቶች መካከል ከፊሎቹ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክቶች ናቸው። ለጌታ መወለድ፣ ለጌታ መሰቀል፣ ለጌታ ሞቶ መነሳት (ትንሳኤና) መሰል ክስተቶች እንኳን አደረሳችሁ ሲባል ሼር ወይም ላይክ የሚያደርጉ ብዙ እህትና ወንድሞችን አስተውያለው። አንዳንዴ በስህተት ሌላ ግዜም ነገሩን እንደቀላል በመውሰድ የሚፈፀም ሊሆን ይችላል። ሆኖም እጅግ ከባድና በአኼራ ዋጋ የሚያስከፍል መዘናጋት ነው!! በካፊሮች በአል፤ እንኳን አደረሳችሁ... እንኳን ደስ አላችሁ... እንኳን አብሮ አደረሰን ማለት እነሱን ለማስደሰትም ይሁን ለመመሳሰል ከአላህ ዲን መንሸራተት እና የካፊሮችን ኩፍር የመናገር ስነልቦና መካብ ስለሆነ ክልክል ነው። መከባበር እና አብሮነትን ለማሳየት ከእምነታችን መንሸራተት አይጠበቅብንም። ዲን ከምንም በላይ ነውና ሸሪዓን መተላለፍ ፍፁም ጥፋት ነው!! ፈጣሪ ወለደ ተወለደ የሚለው አስተምህሮ የጥፋትነቱ ክብደት ሰማያትንና ምድርን ሊሰነጥቅ እንደሚቀርብ ቁርአን ይነግረናል። አላህን የሚያስቆጣ ተግባር በመፈፀማቸው እንኳን ደስ ያላችሁ ማለት ከሙስሊም አይጠበቅም!! (وَقَالُوا۟ ٱتَّخَذَ ٱلرَّحۡمَـٰنُ وَلَدࣰا * لَّقَدۡ جِئۡتُمۡ شَیۡـًٔا إِدࣰّا * تَكَادُ ٱلسَّمَـٰوَ ٰ⁠تُ یَتَفَطَّرۡنَ مِنۡهُ وَتَنشَقُّ ٱلۡأَرۡضُ وَتَخِرُّ ٱلۡجِبَالُ هَدًّا * أَن دَعَوۡا۟ لِلرَّحۡمَـٰنِ وَلَدࣰا * وَمَا یَنۢبَغِی لِلرَّحۡمَـٰنِ أَن یَتَّخِذَ وَلَدًا * إِن كُلُّ مَن فِی ٱلسَّمَـٰوَ ٰ⁠تِ وَٱلۡأَرۡضِ إِلَّاۤ ءَاتِی ٱلرَّحۡمَـٰنِ عَبۡدࣰا * لَّقَدۡ أَحۡصَىٰهُمۡ وَعَدَّهُمۡ عَدࣰّا * وَكُلُّهُمۡ ءَاتِیهِ یَوۡمَ ٱلۡقِیَـٰمَةِ فَرۡدًا) [«አልረሕማንም ልጅን ያዘ (ወለደ)» አሉ፡፡ ከባድ መጥፎን ነገር በእርግጥ አመጣችሁ፡፡ በእርሱ (በንግግራቸው ምክንያት) ሰማያት ሊቀደዱ፣ ምድርም ልትሰነጠቅ፣ ጋራዎችም ተንደው ሊወድቁ ይቃረባሉ፡፡ ለአልረሕማን ልጅ አለው ስለአሉ፡፡ ለአልረሕማን ልጅን መያዝ አይገባውም!! በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉ (በትንሣኤ ቀን) ለአልራሕማን ባሪያ ኾነው የሚመጡ እንጂ ሌላ አይደሉም] Surah Maryam 88 - 95 ለመሆኑ አንድን ካፊር ለሀይማኖታዊ በአል እንኳን አደረሰህ ስትለው፤ ምን ማለት እንደሆነ ግልፅ አይደለምን? እንኳን አደረሰህ... ጌታ ተወልዶ ተሰቅሎ ሞቷል ብለህ ለማወጅ፣ ለመስቀል ለመስገድና የፈጣሪን ክብር የሚነኩ ንግግሮችን ለመናገር እንኳን በቃህ! እንኳን አደረሰህ... ማርያም ፈጣሪዋን ወለደችው፤ በመጠቅለያም ጠቀለለችው እያልክ ለመዘመር እንኳን በቃህ! የኩፍር ተግባርን ለመከወን ከሆነ የደረሰው ለምንስ እንኳን አብሮ አደረሰን እንላለን? እውቁ አሊም ኢብኑል ቀይም ረሂመሁላህ ይህ ተግባር የተከለከለ ስለመሆኑ የኡለማዎች የጋራ አቋም መሆኑን በመጠቆም እንዲህ ብለዋል፤ «ኩፍርን ብቻ በሚያንፀባርቁ የሀይማኖታቸው መገለጫዎች እንኳን አደረሳችሁ...እንኳን ደስ ያለችሁ ማለት ሀራም መሆኑ የሁሉም ሊቃውንት ስምምነት ያለበት ነው። ለምሳሌ አንድ ሙስሊም በነሱ በዓላትና ፆም ጊዜ፤ «በአሉን የተባረከ ያድርግልህ» ወይም «መልካም የደስታ በአል ያድርግልህ» እና መሰል የደስታ መግለጫዎችን ቢያስተላልፍ፤ ተናጋሪው ከኩፍር ቢድን እንኳ ከባድ ወንጀል ነው የፈፀመው። ይህም፤ ልክ «እንኳን ለመስቀል ሰገድክ» ብሎ ደስታን እንደመግለፅ ነው! ይህ እንደውም፤ አንድ ሰው ነብስ በማጥፋቱ፣ አልኮል በመጠጣቱ፣ ዝሙት በመፈፀሙና በመሰል ተግባራት እንኳን ደስ ያለህ ከማለት በወንጀልነት የከበደ እና አስቀያሚ ነው። ለኢስላማዊ ድንጋጌዎች ተገቢዉን ክብር የማይሰጡ ብዙ ሰዎች ይህንን ይፈፅማሉ። ምን ያክል የሚያስጠላ የግባር እንደፈፀሙም አያስተውሉም። ቢድአ፣ ኩፍር እና ወንጀሎች በመፈፀማቸው እንኳን አደረሰህ፣ እንኳን ደስ ያለህ እና መሰል የደስታ መግለጫዎችን ያስተላለፈ፤ እራሱን ለአላህ ቁጣና ጥላቻ የተገባ እንዲሆን የሚያደርግ ምክኒያት ፈፅሟል» አህካም አህሉዚማህ የዘመናችን ፈቂህ ሸይኽ ኡሰይሚን ረሂመሁላህ እንዲህ አሉ «ካፊሮችን እንኳን አደረሳችሁ ማለት ኢብኑል ቀይም እንዳለው የዚህን ያክል ከባድ የሆነበት ምክኒያት እነርሱ የሚፈፅሟቸውን የኩፍር መገለጫዎች ማፅደቅ ስለሆነ ነው። ምንም እንኳን ለራሱ ይህንን ኩፍር መፈፀምን ባይወድም እነሱ መፈፀማቸውን ወዷልና። ሙስሊም ደግሞ የኩፍር መገለጫዎችን መውደድም ይሁን ሌሎችን እንኳን ደስ ያላችሁ ማለት አይፈቀድለትም።» መጅሙዑ ፈታዋ ወረሳኢል አሸይኽ ኢብኑ ኡሰይሚን 3/44 በተመሳሳይ መልኩ፤ ክሪስማስም ሆነ ሌሎች በአላት ላይ ስጦታ ወይም ፓስት ካርዶችን መለዋወጥ፤ እንዲሁም ማንኛውም ደስታን መግለጫ የሆኑ ነገሮችን መፈፀም በአሉን መካፈል ስለሆነ የተከለከለ ነው!! በዚህ ፅሁፍ መጠቆም የፈለኩት ምንም አይነት ማህበራዊ ግንኙነት ሀራም ነው የሚል መልእክት አይደለም። በተለይም ከክርስቲያን እና አይሁዶች ጋር ባለን ማህበራዊ ግንኙነቶች ላይ የተፈቀዱ ብዙ በመልካም የመኗኗር እሴቶች አሉን። ሆኖም ሀይማኖታዊ ወሰኖች የሉም ማለት አይደለም። የተፈቀደውን ስንተገብር እንደ ያልተፈቀደ ጋብቻ፣ በአላት ላይ መሳተፍ፣ ለሞቱት የአላህን ማርታ መለመንና ባጠቃላይ በዲን መመሳሰልን ግን በፍፁም አንፈፅምም። ይህንን የእምነትና የሀይማኖት ወሰን መናድ አይቻልም። ማንነታችንን ማክበር፣ ግንኙነታችንን በዲናዊ ገደቦች ማጠር ብሎም አለመሟሟት ለሌሎች ሞራል ዲንና ማንነት ከመጨነቅ ይቀድማል። ዲን ከምንም በላይ ነውና ከመሸማቀቅ እንውጣ። ይህ የዲናችን መገለጫ እንጂ እንደ ማክረርና ፅንፈኝነት የሚታይ አይደለም። በነገራችን ላይ የአንድ እምነት ተከታይ ከሌሎች ለመቀራረብ ብሎ ከራሱ እምነት ጋር የሚጣላበት ሁኔታ ድሮ ቀርቷል። ሌሎቹም ቢሆኑ ይህ በኛ ሀይማኖት አልፈቀድም እና ይቅርታ ይሉሀል። (فَلَا تُطِعِ ٱلۡمُكَذِّبِینَ * وَدُّوا۟ لَوۡ تُدۡهِنُ فَیُدۡهِنُونَ * وَلَا تُطِعۡ كُلَّ حَلَّافࣲ مَّهِینٍ) አስተባባዮችንም አትታዝዙ፡፡ ብትመሳሰላቸውና ቢመሳሰሉህ ተመኙ፡፡ [Surah Al-Qalam 8 - 10] ወላሁ አዕለም አላህ ከጥፋት ሁሉ ይጠብቀን! ____ አቡጁነይድ ረጀብ 24/1437 ዓ.ሒ / ሜይ 1/ 2016 ከጥቂት ማሻሻያዎች ጋር https://t.me/abujunaidposts/141

📹 ይህ እንዴት የሙስሊሞች ኢባዳ ሊሆን ይችላልን? የኢባዳ መስፈርቱ ለአላህ በኢኽላስ መፈፀሙና በነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ፈለግና አርአያነት መሰረት መተግበሩ ነው። ኢባዳ ለአላህ በፍፁም ውዴታ መተናነስን የምናሳይበት ነው። ለመሆኑ ከሳቸውና ከሰሀቦች ይህ አይነቱ ድለቃ ይታወቃልን? ዱዓ ከሆነ ደግሞ ለአላህ እራስን ዝቅ በማድረግ የሚፈፀም ብቻ ነው። አላህ እንዲህ ይላል፤ { ٱدۡعُوا۟ رَبَّكُمۡ تَضَرُّعࣰا وَخُفۡیَةًۚ إِنَّهُۥ لَا یُحِبُّ ٱلۡمُعۡتَدِینَ } ጌታችሁን ተዋርዳችሁ በድብቅም ለምኑት፡፡ እርሱ ወሰን አላፊዎችን አይወድምና፡፡ [Surah Al-Aʿrāf: 55] ሱብሀነላህ! ወዴት ወዴት ነው? አላህ በዚህ መልኩ ቅጥ ያጣ አምልኮ የሚፈፅሙ ብሎ የጠቀሰው ኢአማንያንን ነበር። { وَمَا كَانَ صَلَاتُهُمۡ عِندَ ٱلۡبَیۡتِ إِلَّا مُكَاۤءࣰ وَتَصۡدِیَةࣰۚ فَذُوقُوا۟ ٱلۡعَذَابَ بِمَا كُنتُمۡ تَكۡفُرُونَ } በቤቱ ዘንድም (በካዕባ) ስግደታቸው ማፏጨትና ማጨብጨብ እንጂ ሌላ አልነበረም፡፡ ትክዱት በነበራችሁትም ነገር ቅጣትን ቅመሱ (ይባላሉ)፡፡ [Surah Al-Anfāl: 35] በቀድሞ ዘመን ኩፋሩ ቁረይሽ ባሁንም ዘመን የሌላ እምነት ተከታዮች ዘንድ በሚታወቅ ሁኔታ የሚፈፀም ኢባዳ የአላህን ውዴታ ያስገኛል ተብሎ ነውን? አላህ ከጭፍን ተከታይነትና መታወር ይጠብቀን። ሀቅን ይግለጥልን በሱና ላይ ያፅናን። አሚን! 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/523 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

የመውሊድ በዓል በሚዛን ላይ """""""""""""""""""""""" ነሲሓ መጽሔት ቅጽ Vol2 ቁጥር 1 ምስጋና ለአለማት ጌታ ለአላህ የተገባ ነው ፡፡ ሰላት እና ሰላም ለዐለማት እዝነት በተላኩት በነቢያችን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በሰሃባዎቻቸው እና እነርሱን በመልካም በተከተሉት ሁሉ ላይ እስከ እለተ ቂያማ (ትንሳኤ) ድረስ ይውረድ፡፡ ቁርዓን እና ሐዲስን እንዲሁም ዝርዝር የሸሪዓ ህግጋትን በትክክል መረዳት ለሁሉም ሙስሊም በእጅጉ አስፈላጊ ቢሆንም ቀላል ግን አይደለም። አላህ ለዚህ ኡማ ታላቅ ውለታ በመዋል ኡለማዎችን ሰጥቶን ያላቸውን ታላቅ ክብር ገልፆልናል፡፡ የሙስሊሞችን እምነት፣ የአምልኮ ‘ዒባዳ’ አተገባበር እና የስነምግባር እሴቶችን ማረም የዑለሞች ተቀዳሚ ተግባር ነው፡፡ ከሰሀቦችና እነሱን ከተከተሉ ታቢዒዮች መካከል ታላለቅ ዑለማዎች እና የፊቅህ ጠበብቶች ቁርዓንን በተገቢው መልኩ በመረዳት እና ዕድሜያቸውን ሙሉ በማስተማር ሀላፊነታቸውን ተወጥተዋል። ሰሃባዎች ከማንም በበለጠ በዕውቀት የበለፀጉ ከመሆናቸው ባሻገር የመልእክተኛውን ﷺ ንግግር እና ሱና በመተግበር ፋና ወጊዎች እንደነበሩ አያጠያይቅም። አብደላህ ኢብን መስዑድ አላህ ስራቸውን ይውደድላቸውና በአንድ ወቅት ስለሰሃባዎች እንዲህ ብለው ነበር፤ "ከዚህ ከነቢዩ ዑመት ከማንም በበለጠ፤ ቅን ልቦና፣ የጠለቀ እውቀት፣ የተቃና ፈለግ እና ያማረ ስብዕና ባለቤት ነበሩ። እነሱ ማለት አላህ ለነብዩ ጓደኝነት የመረጣቸው ህዝቦች ናቸው፡፡ ክብራቸውን እወቁላቸው። ፋናቸውንም ተከተሉ። እነሱ ቀጥተኛው መንገድ ላይ ነበሩ።" ኢብኑ ዐብደል በር / ጃሚዑል በያኒል ዒልም በሚባለው ኪታባቸው ቅጽ 2/946-947 ሰሃባዎች በሐቅ ላይ አንድነታቸውን ለመጠበቅ የተለያዩ ሸሪዓዊ አጀንዳዎች ላይ ይመካከሩና ይተራረሙ ነበር፡፡ ያልደረሳቸውን መረጃ ሲያገኙም ወደ ሐቅ ከመመለስ የሚያግዳቸው ነገር አልነበረም። ለሐቅ ተገዢ ስለነበሩ እርምት ለሰጣቸው አካል ምስጋና እና ክብራቸው ከመጨመሩ ባሻገር በመካከላቸው የነበረው ወዳጅነት አልጎዳም። ኢብኑ ተይሚያ እንዲህ ብለዋል "ሰሃባዎች፣ ታቢዒዮች እና ከእነርሱ በኋላ የመጡት ዑለማዎች በመካከላቸው አለመግባባት በተፈጠረ ጊዜ የአላህን ትዕዛዝ ይከተሉ ነበር፡፡ አላህ እንዲህ ብሏል «በማንኛውም ነገር ብትከራከሩ በአላህና በመጨረሻው ቀን የምታምኑ ብትሆኑ የተከራከራችሁበትን ነገር ወደ አላህና ወደ መልክተኛው መልሱት፡፡ ይህ የተሻለ መጨረሻውም ያማረ ነው፡፡» ሱረቱ ኒሳዕ : 59 በተለያዩ የዲን አጀንዳዎች ላይ በምክክር መልክ ይወያያሉ፡፡ አልፎ አልፎ የዒልምና እና የተግባር ጉዳዮች ላይ የአቋም ልዩነት ሲኖር መዋደድን፣ መተሳሰርን እና ኢስላማዊ ወንድማማችነትን በጠበቀ ሁኔታ ይተራረማሉ።" መጅሙዑል ፈታዋ 24/172 በየዓመቱ የረቢዐል አወል ወር በገባ ቁጥር የነቢያችንን የልደት በዓል መውሊድን የማክበር ጉዳይ ሰዎችን ሲያወዛግብና መነጋገሪያ ሲሆን ይታያል። አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ ሙእሚኖችን በመሰረታዊም ይሁን በቅርንጫፋዊ የዲን ጉዳዮች ላይ አለመግባባት ቢፈጠሩ ጉዳያቸውን ወደ ቁርዓንና ሐዲስ በመመለስ መፍትሄ እንዲፈልጉ በሚከተለው የቁርዓን አንቀጽ አዟል፡፡ فَإِن تَنَازَعْتُمْ فِي شَيْءٍ فَرُدُّوهُ إِلَى اللَّهِ وَالرَّسُولِ إِن كُنتُمْ تُؤْمِنُونَ بِاللَّهِ وَالْيَوْمِ الْآخِرِ ذَٰلِكَ خَيْرٌ وَأَحْسَنُ تَأْوِيلًا ٤:٥٩ «በማንኛውም ነገር ብትከራከሩ በአላህና በመጨረሻው ቀን የምታምኑ ብትኾኑ የተከራከራችሁበትን ነገር ወደ አላህና ወደ መልክተኛው መልሱት፡፡ ይህ የተሻለ መጨረሻውም ያማረ ነው» ሱረቱ ኒሳዕ : 59 ከዚህ ቁርአናዊ መመሪያ በመነሳት ለአንባቢዎቻችን ነሲሓ ይሆን ዘንድ ትክክለኛውን አቋም እናመላክታለን። አላህ ሀቁን አይተው ከሚከተሉት ሰዎች ያድርገን። ይህ በዓል በሸሪዓ መሰረት የሌለውና ሰዎች በዲን ውስጥ የጨመሩት አዲስ ነገር ከመሆኑ ባሻገር አላህና መልእክተኛው ያልደነገጉትን ተግባር በቀን የተገደበ ወደ አላህ መቃረቢያ አምልኮ ማድረግ መሆኑ ዋነኞቹ የመውሊድ ችግሮች ሲሆኑ፤ በተጨማሪም ክርስቲያኖችን በመፎካከር የመጣ መሆኑ ከእነሱ ጋር መመሳሰል ነው። በተጨማሪ በዚህ በዓል ውስጥ በሸሪዓ የተወገዙ በርካታ ተግባራት ይፈፀማሉ። መውሊድ አንድን ስራ ቢድዓ የሚያሰኙ ምክንያቶች ሁሉ እንዳሉበት አያጠራጥርም። ይህም በሚከተሉት ሶስት ነጥቦች ይብራራል፤ 1) አዲስ ነገር መፍጠር (ኢሕዳስ) ካለ ሸሪዓዊ ማስረጃ፤ ማንኛውንም ቀን ወይም ወር ልዩ ሀይማኖታዊ ክንውን የሚፈፀምበት እንደሆነ በማሰብ በዋጂብነት ወይም ሱናነት ሰዎችን የምናበረታታበት ከሆነ በዲን ውስጥ አዲስ ነገር መፍጠር ነውና ሀራም ነው። አሏህ እንዲህ ብሏል:- أَمْ لَهُمْ شُرَكَاءُ شَرَعُوا لَهُمْ مِنَ الدِّينِ مَا لَمْ يَأْذَنْ بِهِ اللَّهُ «ከሀይማኖት አላህ በእርሱ ያልፈቀደውን ለእነሱ የደነገጉ ተጋሪዎች ለእነርሱ አሏቸውን?» ሱረቱ ሹራ ቁጥር 21 ቡኻሪ እና ሙስሊም በዘገቡት የተረጋገጠ ሰሂህ ሐዲስ ነቢያችን ﷺ ብለዋል፤ مَنْ أحْدَثَ في أمْرِنَا هَذَا مَا لَيْسَ مِنْهُ فَهُوَ رَدٌّ «በዲናችን ውስጥ ከእርሱ ያልሆነን ነገር የፈጠረ ስራው ተመላሽ ይደረግበታል» ብለዋል። ይህ ማለት በሸሪዓ ያልተደነገገን ነገር ፈጥሮ ቢፈፅም ተቀባይነት አያገኝም ማለት ነው። እንደሚታወቀው፤ መውሊድን ረሱል ﷺ የተከበሩት ኸሊፋዎች እና ሌሎችም ሰሀባዎች አላከበሩትም። እንደዚሁ በተከበረው ዘመን ውስጥ የኖሩት ሰሀባዎችን በመልካም ሲከተሉ የነበሩ ታቢዒዮች አልሰሩትም። እነሱ ደግሞ ከማንም በላይ የሱና አዋቂዎችና ለነቢያችን የነበራቸው ውዴታም ከማንም በላይ እንደነበር እሙን ነው። የነብዩን ፈለግ በሚገባ በመከተልም የማይታሙ እንደ ነበሩ ለማንም ግልፅ ነው። ለኛ አርአያ መሆናቸውም ተነግሮናል። ምንም ሳንጨምር መንገዳቸውን አጥብቀን እንድንይዝ የአላህ መልዕክተኛ አደራ ብለውናል፤ عَلَيْكُمْ بِسُنَّتِي وَسُنَّةِ الْخُلَفَاءِ الرَّاشِدِينَ الْمَهْدِيِّينَ، وَعَضُّوا عَلَيْهَا بِالنَّوَاجِذِ، وَإِيَّاكُمْ وَمُحْدَثَاتِ الْأُمُورِ، فَإِنَّ كُلَّ مُحْدَثَةٍ بِدْعَةٌ، وَكُلَّ بِدْعَةٍ ضَلَالَةٌ «የእኔን እና የቅን ምትኮቼን ሱና አደራ! በጥርሶችችሁ አጥብቃችሁ ያዙ! አዳዲስ ፈጠራዎችን ተጠንቀቁ (ተከልከሉ)፣ በዲን ውስጥ የተጨመረ ፈጠራ ሁሉ ጥመት ነው» ኢማሙ አህመድ ዘግበውታል መውሊድ በቀደምቶቹ ዘመን እንዳልነበረ እና ኃላ የተፈጠረ (ሙህደስ) ለመሆኑ መውሊድ አክባሪዎች ሁሉ የማይክዱት እውነታ ነው። መውሊድ ማክበርን ለመጀመሪያ ጊዜ የጀመሩት ከአራተኛው ክ/ዘመን በኋላ እራሳቸውን ፋጢሚዮች ብለው ይጠሩ የነበሩት ኡበይዲዩች ግብፅን በ362 ዓመተ ሂጅራ የወራሩ ጊዜ ነበር። ቀጣዩን ያንብቡ👇 https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=1336321059824881&id=1003047829818874

🍂 የሰለፎች ብሩህ ፋና! 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/521 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts