fa
Feedback
🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts

🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts

رفتن به کانال در Telegram

ይህ በአቡ ጁነይድ ሳላህ አህመድ የቀረቡ የድምፅና የፅሁፍ መልዕክቶች የሚሰበሰቡበት ቻነል ነው። አላህ ጠቃሚ እውቀትን ከመልካም ስራ ጋር ያግራልን! You can contact me here @salehom100

نمایش بیشتر
2 218
مشترکین
-124 ساعت
-67 روز
-3530 روز
آرشیو پست ها
የመውሊድ በዓል በሚዛን ላይ """""""""""""""""""""""" ነሲሓ መጽሔት ቅጽ Vol2 ቁጥር 1 ምስጋና ለአለማት ጌታ ለአላህ የተገባ ነው ፡፡ ሰላት እና ሰላም ለዐለማት እዝነት በተላኩት በነቢያችን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በሰሃባዎቻቸው እና እነርሱን በመልካም በተከተሉት ሁሉ ላይ እስከ እለተ ቂያማ (ትንሳኤ) ድረስ ይውረድ፡፡ ቁርዓን እና ሐዲስን እንዲሁም ዝርዝር የሸሪዓ ህግጋትን በትክክል መረዳት ለሁሉም ሙስሊም በእጅጉ አስፈላጊ ቢሆንም ቀላል ግን አይደለም። አላህ ለዚህ ኡማ ታላቅ ውለታ በመዋል ኡለማዎችን ሰጥቶን ያላቸውን ታላቅ ክብር ገልፆልናል፡፡ የሙስሊሞችን እምነት፣ የአምልኮ ‘ዒባዳ’ አተገባበር እና የስነምግባር እሴቶችን ማረም የዑለሞች ተቀዳሚ ተግባር ነው፡፡ ከሰሀቦችና እነሱን ከተከተሉ ታቢዒዮች መካከል ታላለቅ ዑለማዎች እና የፊቅህ ጠበብቶች ቁርዓንን በተገቢው መልኩ በመረዳት እና ዕድሜያቸውን ሙሉ በማስተማር ሀላፊነታቸውን ተወጥተዋል። ሰሃባዎች ከማንም በበለጠ በዕውቀት የበለፀጉ ከመሆናቸው ባሻገር የመልእክተኛውን ﷺ ንግግር እና ሱና በመተግበር ፋና ወጊዎች እንደነበሩ አያጠያይቅም። አብደላህ ኢብን መስዑድ አላህ ስራቸውን ይውደድላቸውና በአንድ ወቅት ስለሰሃባዎች እንዲህ ብለው ነበር፤ "ከዚህ ከነቢዩ ዑመት ከማንም በበለጠ፤ ቅን ልቦና፣ የጠለቀ እውቀት፣ የተቃና ፈለግ እና ያማረ ስብዕና ባለቤት ነበሩ። እነሱ ማለት አላህ ለነብዩ ጓደኝነት የመረጣቸው ህዝቦች ናቸው፡፡ ክብራቸውን እወቁላቸው። ፋናቸውንም ተከተሉ። እነሱ ቀጥተኛው መንገድ ላይ ነበሩ።" ኢብኑ ዐብደል በር / ጃሚዑል በያኒል ዒልም በሚባለው ኪታባቸው ቅጽ 2/946-947 ሰሃባዎች በሐቅ ላይ አንድነታቸውን ለመጠበቅ የተለያዩ ሸሪዓዊ አጀንዳዎች ላይ ይመካከሩና ይተራረሙ ነበር፡፡ ያልደረሳቸውን መረጃ ሲያገኙም ወደ ሐቅ ከመመለስ የሚያግዳቸው ነገር አልነበረም። ለሐቅ ተገዢ ስለነበሩ እርምት ለሰጣቸው አካል ምስጋና እና ክብራቸው ከመጨመሩ ባሻገር በመካከላቸው የነበረው ወዳጅነት አልጎዳም። ኢብኑ ተይሚያ እንዲህ ብለዋል "ሰሃባዎች፣ ታቢዒዮች እና ከእነርሱ በኋላ የመጡት ዑለማዎች በመካከላቸው አለመግባባት በተፈጠረ ጊዜ የአላህን ትዕዛዝ ይከተሉ ነበር፡፡ አላህ እንዲህ ብሏል «በማንኛውም ነገር ብትከራከሩ በአላህና በመጨረሻው ቀን የምታምኑ ብትሆኑ የተከራከራችሁበትን ነገር ወደ አላህና ወደ መልክተኛው መልሱት፡፡ ይህ የተሻለ መጨረሻውም ያማረ ነው፡፡» ሱረቱ ኒሳዕ : 59 በተለያዩ የዲን አጀንዳዎች ላይ በምክክር መልክ ይወያያሉ፡፡ አልፎ አልፎ የዒልምና እና የተግባር ጉዳዮች ላይ የአቋም ልዩነት ሲኖር መዋደድን፣ መተሳሰርን እና ኢስላማዊ ወንድማማችነትን በጠበቀ ሁኔታ ይተራረማሉ።" መጅሙዑል ፈታዋ 24/172 በየዓመቱ የረቢዐል አወል ወር በገባ ቁጥር የነቢያችንን የልደት በዓል መውሊድን የማክበር ጉዳይ ሰዎችን ሲያወዛግብና መነጋገሪያ ሲሆን ይታያል። አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ ሙእሚኖችን በመሰረታዊም ይሁን በቅርንጫፋዊ የዲን ጉዳዮች ላይ አለመግባባት ቢፈጠሩ ጉዳያቸውን ወደ ቁርዓንና ሐዲስ በመመለስ መፍትሄ እንዲፈልጉ በሚከተለው የቁርዓን አንቀጽ አዟል፡፡ فَإِن تَنَازَعْتُمْ فِي شَيْءٍ فَرُدُّوهُ إِلَى اللَّهِ وَالرَّسُولِ إِن كُنتُمْ تُؤْمِنُونَ بِاللَّهِ وَالْيَوْمِ الْآخِرِ ذَٰلِكَ خَيْرٌ وَأَحْسَنُ تَأْوِيلًا ٤:٥٩ «በማንኛውም ነገር ብትከራከሩ በአላህና በመጨረሻው ቀን የምታምኑ ብትኾኑ የተከራከራችሁበትን ነገር ወደ አላህና ወደ መልክተኛው መልሱት፡፡ ይህ የተሻለ መጨረሻውም ያማረ ነው» ሱረቱ ኒሳዕ : 59 ከዚህ ቁርአናዊ መመሪያ በመነሳት ለአንባቢዎቻችን ነሲሓ ይሆን ዘንድ ትክክለኛውን አቋም እናመላክታለን። አላህ ሀቁን አይተው ከሚከተሉት ሰዎች ያድርገን። ይህ በዓል በሸሪዓ መሰረት የሌለውና ሰዎች በዲን ውስጥ የጨመሩት አዲስ ነገር ከመሆኑ ባሻገር አላህና መልእክተኛው ያልደነገጉትን ተግባር በቀን የተገደበ ወደ አላህ መቃረቢያ አምልኮ ማድረግ መሆኑ ዋነኞቹ የመውሊድ ችግሮች ሲሆኑ፤ በተጨማሪም ክርስቲያኖችን በመፎካከር የመጣ መሆኑ ከእነሱ ጋር መመሳሰል ነው። በተጨማሪ በዚህ በዓል ውስጥ በሸሪዓ የተወገዙ በርካታ ተግባራት ይፈፀማሉ። መውሊድ አንድን ስራ ቢድዓ የሚያሰኙ ምክንያቶች ሁሉ እንዳሉበት አያጠራጥርም። ይህም በሚከተሉት ሶስት ነጥቦች ይብራራል፤ 1) አዲስ ነገር መፍጠር (ኢሕዳስ) ካለ ሸሪዓዊ ማስረጃ፤ ማንኛውንም ቀን ወይም ወር ልዩ ሀይማኖታዊ ክንውን የሚፈፀምበት እንደሆነ በማሰብ በዋጂብነት ወይም ሱናነት ሰዎችን የምናበረታታበት ከሆነ በዲን ውስጥ አዲስ ነገር መፍጠር ነውና ሀራም ነው። አሏህ እንዲህ ብሏል:- أَمْ لَهُمْ شُرَكَاءُ شَرَعُوا لَهُمْ مِنَ الدِّينِ مَا لَمْ يَأْذَنْ بِهِ اللَّهُ «ከሀይማኖት አላህ በእርሱ ያልፈቀደውን ለእነሱ የደነገጉ ተጋሪዎች ለእነርሱ አሏቸውን?» ሱረቱ ሹራ ቁጥር 21 ቡኻሪ እና ሙስሊም በዘገቡት የተረጋገጠ ሰሂህ ሐዲስ ነቢያችን ﷺ ብለዋል፤ مَنْ أحْدَثَ في أمْرِنَا هَذَا مَا لَيْسَ مِنْهُ فَهُوَ رَدٌّ «በዲናችን ውስጥ ከእርሱ ያልሆነን ነገር የፈጠረ ስራው ተመላሽ ይደረግበታል» ብለዋል። ይህ ማለት በሸሪዓ ያልተደነገገን ነገር ፈጥሮ ቢፈፅም ተቀባይነት አያገኝም ማለት ነው። እንደሚታወቀው፤ መውሊድን ረሱል ﷺ የተከበሩት ኸሊፋዎች እና ሌሎችም ሰሀባዎች አላከበሩትም። እንደዚሁ በተከበረው ዘመን ውስጥ የኖሩት ሰሀባዎችን በመልካም ሲከተሉ የነበሩ ታቢዒዮች አልሰሩትም። እነሱ ደግሞ ከማንም በላይ የሱና አዋቂዎችና ለነቢያችን የነበራቸው ውዴታም ከማንም በላይ እንደነበር እሙን ነው። የነብዩን ፈለግ በሚገባ በመከተልም የማይታሙ እንደ ነበሩ ለማንም ግልፅ ነው። ለኛ አርአያ መሆናቸውም ተነግሮናል። ምንም ሳንጨምር መንገዳቸውን አጥብቀን እንድንይዝ የአላህ መልዕክተኛ አደራ ብለውናል፤ عَلَيْكُمْ بِسُنَّتِي وَسُنَّةِ الْخُلَفَاءِ الرَّاشِدِينَ الْمَهْدِيِّينَ، وَعَضُّوا عَلَيْهَا بِالنَّوَاجِذِ، وَإِيَّاكُمْ وَمُحْدَثَاتِ الْأُمُورِ، فَإِنَّ كُلَّ مُحْدَثَةٍ بِدْعَةٌ، وَكُلَّ بِدْعَةٍ ضَلَالَةٌ «የእኔን እና የቅን ምትኮቼን ሱና አደራ! በጥርሶችችሁ አጥብቃችሁ ያዙ! አዳዲስ ፈጠራዎችን ተጠንቀቁ (ተከልከሉ)፣ በዲን ውስጥ የተጨመረ ፈጠራ ሁሉ ጥመት ነው» ኢማሙ አህመድ ዘግበውታል መውሊድ በቀደምቶቹ ዘመን እንዳልነበረ እና ኃላ የተፈጠረ (ሙህደስ) ለመሆኑ መውሊድ አክባሪዎች ሁሉ የማይክዱት እውነታ ነው። መውሊድ ማክበርን ለመጀመሪያ ጊዜ የጀመሩት ከአራተኛው ክ/ዘመን በኋላ እራሳቸውን ፋጢሚዮች ብለው ይጠሩ የነበሩት ኡበይዲዩች ግብፅን በ362 ዓመተ ሂጅራ የወራሩ ጊዜ ነበር። ቀጣዩን ያንብቡ👇 https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=1336321059824881&id=1003047829818874

👌 መውሊድን የተመለከቱ ብዥታዎችና መልሶቻቸው 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ ⌚️ የ 72 ደቂቃ ሙሀደራ (64 kbps = 34.65 mb) 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/105 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

📹 መውሊድ ኢስላማዊ በዓል ነውን? በነሲሓ ቲቪ  የቀረበ አጭር  ውይይት  🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/514 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

አሹራ... ታሪክና እርምት 1–4 በአሹራ፣ የቀብር አምልኮና የሁሰይን መገደል ዙርያ በሺዓዎች የሚነሱ ዋና ዋና ብዥታዎችን ለማጥራት ሞክረናል። አላህ በሱና ላይ እስከሞት ከሚፀኑት ያድርገን።  Part 1 https://youtu.be/WmK_NzcVYdg Part 2 https://youtu.be/xxSgqdIk5tQ Part 3 https://youtu.be/2hmD6EfzNzQ Part 4 https://youtu.be/YAmqFXfp8rU @nesihatv

🍂 منزلة اليقين من روائع كلام ابن القيم رحمه الله في كتاب مدارج السالكين ____ @abujunaidposts

የተመረጡ ነብያዊ ዱዓዎች.pdf5.67 MB

🗞 ስለ ዓረፋ ቀን ዱዓእ ሁለት ነጥቦች ✍ አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ [1] በኢድ ዋዜማው የዓረፋ እለት ዱዓእ ተቀባይነት እንዳለው የሚዘክሩ ሀዲሶች ሀጅ ላይ የሌሉ ሰዎችንም ይመለከታሉን?? የአላህ
🗞 ስለ ዓረፋ ቀን ዱዓእ ሁለት ነጥቦች ✍ አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ [1] በኢድ ዋዜማው የዓረፋ እለት ዱዓእ ተቀባይነት እንዳለው የሚዘክሩ ሀዲሶች ሀጅ ላይ የሌሉ ሰዎችንም ይመለከታሉን?? የአላህ መልእክተኛ «ከዱዓዎች ሁሉ በላጩ (የኢድ ዋዜማ) የአረፋ ቀን ዱዓ ነው...» ማለታቸውን ቲርሚዚይ ከአብዱላህ ኢብኑ ኡመር የዘገቡ ሲሆን፤ ሌሎች ተመሳይ ይዘት ያላቸው ሀዲሶችም ይገኛሉ። ታዲያ የዓረፋን እለት በዱአዕና በዚክር ያሳለፈ ሰው ታላቅ ክብርና ምንዳን የሚያገኘው ሀጅ ላይ ሲሆን ብቻ ነውን? በእርግጥ በዚህ እለት ክብር ባለው የዓረፋ ምድር የተገኘ ሰው የጊዜንም የቦታንም ክብር ተጎናፅፏልና በተሻለ ሁኔታ ላይ መገኘቱ እንዲሁም ዱአው ተቀባይነት ለማግኘት የቀረበ መሆኑ አያጠራጥርም። ይሁንና ሚዛን በሚደፋው የኡለማዎች አቋም መሰረት፤ እነዚህ ከአረፋ እለት ክብር ጋር ተያይዞ የዱአ ተቀባይነትን የተመለከቱ ሀዲሶች በማንኛውም ቦታ የሚገኙ ሙስሊሞችን ይመለከታሉ። በመሆኑም በሀጅ ስራ ላይ የሌሉ ሰዎችም በዱዓ ሊበረቱ ይገባል። ታላቁ አሊም ሸይኽ ሳሊህ አልፈውዛን በዚህ እለት የሚባሉ በሀዲስ የተላለፉ ዱአዎችን አስመልክቶ ሀጅ ላይ ላሉ ሰዎች መሆኑን ተጠይቀው ተከተዩን መልሰዋል¹ «በምላሻችን እንደገለፅነው፤ ይህ ለሁጃጆችንም ይሁን ሌሎችን የተመለከተ ጥቅል መልእክት ነው። ነገር ግን ሀጅ ላይ ላሉ ሰዎች ይበልጥ የተገባ ነው። ምክኒያቱም ሁጃጆች በዚህ እለት በዓረፋ ምድር በኢህራም ውስጥ ስለሚገኙ ከሌሎች በበለጠ ዱዓቸው ተቀባይነት ለማግኘት የቀረበ ነው። ስለዚህም የዓረፋን እለት በሀጅ ተግባር ላይ የሌሉ ሰዎች እንዲፆሙት ተደንግጓል። እለቱ ብልጫ ያለወወ ስለሆነም አላህን በማስታወስ፣ ማርታን በመለመን እና ዱዓ በማድረግ ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ፤ ሁጃጆችንም በኢባዳ ይካፈሏቸዋል ማለት ነው።» ከሸይኹ ድረገፅ የተወሰደ የድምፅ ፈትዋ [2] በዓረፋ እለት ሁጃጆች በአረፋ ምድር እንደሚሰባሰቡት ለዱዓና ለዚክር መሰባሰብ "ታዕሪፍ"ን በተመለከተ፤ ይህ ተግባር አንዳንድ ሰለፎች እንደፈፀሙት የተረጋገጠ ነው። ከነሱም መካከል ኢብኑ አባስ ይገኙበታል፤ ኢማሙ አህመድም ባይተገብሩትም እንደሚቻል ተናግረዋል። ነገር ግን ያወገዙትና ከቢድአ የመደቡትም አሉ። የኡለማዎቻችንን ማብራሪያዎች ስንፈትሽ ተከታዮቹ ድምዳሜዎች ላይ ያደርሱናል፤ 1) "ታእሪፍ"ን መተግበር በራሱ ችግር የለውም። ተግባሩን እንደሱና ወይም ሙስተሀብ ነገር መውሰድ ግን አይገባም። ጉዳዩ የኢጅቲሀድ መስአላ ነውና ተግባሩ የሚወገዝ ተግባር አይሆንም። የፈፀመውም ሰው ቢድአ ሰራ አይባልም። 2) ታእሪፍ ስንል ከምድረ አረፋ ውጭ ባሉ የየሀገሩና የየከማው መስጂዶች መሰባሰብን የተመለከተ እነጂ ለዚህ ብሎ ጉዞ ማድረግ አይፈቀድም። አላህ የአረፋን ምድር ለዚህ ቀን ኢባዳ መሰባሰቢያ እንደመረጠው በየሀገሩ አንዳንድ ቦታዎችን፣ መስጅዶችንና ቀብሮችን በመምረጥ ወደነሱ ጉዞ አድርጎ መሰባሰብ በፍፁም አይፈቀድም። ይህ የነብዩ መስጂድንም ይሁን በይተልመቅዲስን ያካትታል። 3) ይህ መሰባሰብ ጩኸትና ሱና ያልሆኑ የጋራ አምልኮዎች ከታከሉበት ቢድአ እንደሚሆን አያጠራጥርም። በተመሳሳይ መልኩ ኢባዳ ያልሆኑ ግጥሞችና መንዙማዎችን ለዚህ መለያ ማድረግ ጥፋት ነው። እነዚህን ነጥቦች በዝርዝር ለመረዳት የሚያስችሉ ማብራሪያዎችን ከኡለማዎች ድርሳናት እንደሚከተለው እናያለን። ቀሪዉን የፅሁፍ ክፍል ተከታዩን ሊንክ በመከተል ያንብቡት https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=10160553120869684&id=682494683 __ 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች t.me/abujunaidposts

ኡድሂያ ለማረድ ካቀዱ ከወዲሁ ጥፍርና ጸጉርዎን ከመቁረጥ ይቆጠቡ! ------------------- ☞ እንድ ሙስሊም ሀጅ የማያደርግ ከሆነና በዒድ አል አድሀ እለት ኡድሂያን ለማረድ ካሰበ የዙልሂጃ ወር ከገባበት የምጀመሪያዉ ቀን ጀምሮ ጥፍሩንና ጸጉሩን አይቆርጥም፤ ቆዳውንም አይቀርፍም። ይህም ተከታዩን የኡሙሰለማ ሀዲስ መሰረት ያደረገ ነው። عن أم سلمة رضي الله عنها أن النبي صلى الله عليه وسلّم قال : " إذا رأيتم هلال ذي الحجة ، وفي لفظ : "إذا دخلت العشر وأراد أحدكم أن يضحي فليمسك عن شعره وأظفاره ". رواه أحمد ومسلم ، وفي لفظ : " فلا يأخذ من شعره وأظفاره شيئاً حتى يضحي ". وفي لفظ : "فلا يمس من شعره ولا بشره شيئاً ". ከኡሙ ሰለማ በተላለፈ ሀዲስ የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል፤ «የዙልሂጃ ወርን ጨረቃ ካያችሁና ከናንተ መካከል አንዱ ኡድሂያ ለማረድን ካቀደ፤ ፀጉሩንና ጥፍሩን ከመቁረጥ ይቆጠብ» አል ኢማም አህመድ ዘግበውታል። በሌላም ዘገባም «ኡድሂያውን እስኪያርድ ድረስ ከፀጉሩና ከጥፍሩ ምንንም አይቁረጥ» ብለዋል። እንደዚሁ፤ «ከሰውነቱ ቆዳ ወይም ከፀጉሩ ምንንም አይቁረጥ» ብለዋል። ይህ ማንኛውም ሙስሊም እራሱን በሀጅ ላይ ካሉ ሰዎች ጋር የሚያመሳስልበት እና የተወሰኑ የኢህራም ክልከላዎችን ከነሱ ጋር የሚጋራበት ዲናዊ ስርአትና ነብያዊ ትዕዛዝ ነው። ☞ ጸጉርንና ጥፍርን ከመቁረጥ የሚከለከለው ለራሱ ወይም ለሰው በራሱ ገንዘብ የሚያርድ ሰው ብቻ ነው። ህጉ የሚመለከተው የሚያርደዉን ሰው ብቻ ነው ሲባል፤ በወኪልነት ለሌላ ስው የሚያርድን ሰው አይጨምርም። ☞ እያወቀ ጥፍሩን ወይም ጸጉሩን የቆረጠ ወንጀል ፈጽሟልና ወደ አላህ በተውበት ሊመለስ ይገባዋል፤ ኡድሂያው ግን አይበላሽም ማካካሻ ከፋራም የለበትም። አንዳንዶች እንደሚያስቡት ሳይሆን ወንጀሉን ቢፈፅምም ኡድሂያ ማረዱን መተው የለበትም። ☞ በስህተት ወይም በመርሳት ፀጉሩን ወይም ጥፍሩን የቆረጠ ሰው ምንም ወንጀል የለበትም። በተመሳሳይ መልኩ በጣም አስፈላጊ ሲሆን ቢቆርጥ ችግር የለውም። ለምሳሌ የተጎዳን የሰውነት ቆዳ ለማከም ወይም የተሰበረ ጥፍሩን ለማስተካከል መቁረጥ ይፈቀድለታል። ፠ ስለ ኡድሂያ ጥቂት ተጨማሪ ነጥቦች 1 - በዙልሂጃ አስር ቀናት ከተወደዱ ተግባሮች መካከል ኡድሂያን በማረድ ወደ አላህ መቃረብ አንዱ ነው። 2- ኡድሂያ በጣም ከጠነከሩ የነብዩ صلى الله عليه وسلم ሱናዎች መካከል ነው። ኡድሂያ የነብዩ ኢብራሂምን ሱና ህያው ከማድረግ በተጨማሪ ለድሆች እና ችግረኞች መድረስ ነው። 3- ኡድሂያን በተመለከተ አላህ ከኛ የሚፈልገው ለእርሱ ያለንን ፍራቻ ተቅዋና ታዛዥነት ግልጽ ማድረጋችንን ብቻ ነው። አላህ እንዲህ ብሏል፤ {ﻟَﻦ ﻳَﻨَﺎﻝَ اﻟﻠَّﻪَ ﻟُﺤُﻮﻣُﻬَﺎ ﻭَﻻَ ﺩِﻣَﺎﺅُﻫَﺎ ﻭَﻟَٰﻜِﻦ ﻳَﻨَﺎﻟُﻪُ اﻟﺘَّﻘْﻮَﻯٰ ﻣِﻨﻜُﻢْ ۚ ﻛَﺬَٰﻟِﻚَ ﺳَﺨَّﺮَﻫَﺎ ﻟَﻜُﻢْ ﻟِﺘُﻜَﺒِّﺮُﻭا اﻟﻠَّﻪَ ﻋَﻠَﻰٰ ﻣَﺎ ﻫَﺪَاﻛُﻢْ ۗ ﻭَﺑَﺸِّﺮِ اﻟْﻤُﺤْﺴِﻨِﻴﻦَ} الحج 37 አላህን ሥጋዎቿም ደሞቿም ፈጽሞ አይደርሰውም፡፡ ግን ከእናንተ የሆነው ፍራቻ ይደርሰዋል፡፡ እንደዚሁ አላህን በመራችሁ ላይ ልታከብሩት ለእናንተ ገራት፡፡ በጎ ሠሪዎችንም አብስር፡፡» አል ሐጅ 37 4- ኡድሂያ የሚታረደው ከዒድ ሰላት በኋላ ነው። የአላህ መልዕክተኛ صلى الله عليه وسلم ከኢድ ሰላት በፊት ያረደ ሰው እንዲደግም አዘዋል። 5- ሚዛን በሚደፋው የኡለማዎች አቋም መሰረት የዒድ ሰላት ከተጠናቀቀበት ጊዜ ጀምሮ የሶስተኛው ቀን ጸሀይ እስክትጠልቅ ድረስ ኡድሂያን ማረድ ይቻላል። 6- ወንድም ይሁን ሴት ግመል፣ የቀንድ ከብቶች፣ በግና ፍየል ለኡድሂያ ይታረዱሉ። 7- የአላህ መልዕክተኛ صلى الله عليه وسلم እንከን ያለባቸውን እንስሳት እንዳናርድ ከልክለዋል። አንድ አይኑ የታወረ፣ ስብራት ያለበት፣ የከሳና የደከመ ወይም የታመመ እንስሳ ለኡድሂያ አይሆንም። 8- ኡድሂያን ለብቻ ማረድ እንደሚቻለው ሁሉ ለሰባት ሆኖ አንድን ወይፈን ወይም በሬ መጋራትም ይቻላል። 9- አንድ ሰው ኡድሂያ ሲያርድ ለራሱ እና በህይወት ላሉም ይሁን በህይወት ለሌሉ ቤተሰቦቹ አስቦ ሊያርድ ይችላል። 10- የኡድሂያውን ስጋ፣ ለቤት፣ ለስጦታ እና ለሰደቃ አድርጎ ሶስት ቦታ መከፋፈሉ ሱና ነው። ይህ ማለት ግን እንደ አስፈላጊነቱ ለሶስቱም ያውለዋል ማለት እንጂ ሶስት እኩል ቦታዎች ይከፋፍለዋል ማለት አይደለም። አቡጁነይድ Http://www.t.me/abujunaidposts

🗞 ከዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ያላቸው አስርቱ የዙልሂጃ ቀናት ✍ ዝግጅት፦ አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ ህዳር 2004 🔗 የፅሁፉ ሊንክ https://d1.islamhouse.com/data/am/ih_articles/single/am_Virtues_of_the_Ten_Days_of_Dhul_Hijjah.pdf 🔗 telegram Share Link https://t.me/abujunaidposts/374 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

ውድ የኢስላም ወንድሞቼ፤ እንኳን ለዒድ አልፊጥር አደረሳችሁ። አላህ ስራችንን እንዲቀበለንና ለቀጣዩ ረመዳን ዕውቀትና ተግባርን ወፍቆ እንዲያደርሰን እለምነዋለሁ። ወንድማችሁ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ
ውድ የኢስላም ወንድሞቼ፤ እንኳን ለዒድ አልፊጥር አደረሳችሁ። አላህ ስራችንን እንዲቀበለንና ለቀጣዩ ረመዳን ዕውቀትና ተግባርን ወፍቆ እንዲያደርሰን እለምነዋለሁ። ወንድማችሁ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال وأعاده الله علينا ونحن في عز وكرامة وسعادة أخوكم في الله أبو جنيد صالح أحمد T.me/abujunaidposts

🌟ይህ ነው ዳዕዋችን 🌟አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/551 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🌟ይህ ነው ዳዕዋችን 🌟አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/550 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

*ረመዳን ሙባረክ!* እንኳን ለታላቁ የረመዳን ወር አደረሳችሁ። አላህ ተቀባይነት ያለው ፆም እና ኢባዳን ይወፍቀን። ለረመዳን ያልደረሱ ወዳጆቻችንን ሁሉ አላህ ይማራቸው። አሚን t.me/abujunaidposts

💥 ታላቅ የምስራች! ◻️ አልሐምዱሊላህ... የነሲሓ ቲቪን የቀጥታ ስርጭት ከዛሬ እሁድ መጋቢት 1/2016 ጀምሮ ከየትኛውም የዓለም ክፍል ሆናችሁ ከዌብሳይታቸን https://live.nesiha.tv
💥 ታላቅ የምስራች! ◻️ አልሐምዱሊላህ... የነሲሓ ቲቪን የቀጥታ ስርጭት ከዛሬ እሁድ መጋቢት 1/2016 ጀምሮ ከየትኛውም የዓለም ክፍል ሆናችሁ ከዌብሳይታቸን https://live.nesiha.tv መከታተል ትችላላችሁ። ለአጠቃቀም ይበልጥ ምቹ እንዲሆን የሞባይል አፕሊኬሽኑን ከስርጭት ፔጁ ላይ ወይም ከቴሌግራም ቻናላችን ማውረድ ትችላላችሁ።  በአላህ ፈቃድ የተጠቃሚዎችን አስተያየት መሰረት በማድረግ ማሻሻያዎች ከተደረጉለት በኃላ በአፕሊኬሽን ስቶሮች ላይ የምታገኙት ይሆናል። ብዙ ወዳጆቻችን ሲጠይቁት የነበረና የጣቢያውን ተደራሽነት በእጅጉ የሚጨምር ስኬት ስለሆነ የተሰማንን ደስታ እየገለፅን ። ለነሲሓ የ አይ ቲ ባለሞያዎች ከፍ ያለ ምስጋናቸነንን እናቀርባለን። ነሲሓ ቲቪ... ኢስላማዊ ዕውቀት ለሁሉም! @nesihatv

ነሲሓ ኮንፈረንስ የሚታደሙበትን የመግቢያ ትኬት online በመመዝገብ በነፃ ይውሰዱ ታላላቅ ኡለማዎች የሚሳተፉበት ልዩ የነሲሓ ኮንፈረንስ በአላህ ፈቃድ በሚሊኒየም አዳራሽ መጋቢት 1/2016 ይካሄዳል
ነሲሓ ኮንፈረንስ የሚታደሙበትን የመግቢያ ትኬት online በመመዝገብ በነፃ ይውሰዱ ታላላቅ ኡለማዎች የሚሳተፉበት ልዩ የነሲሓ ኮንፈረንስ በአላህ ፈቃድ በሚሊኒየም አዳራሽ መጋቢት 1/2016 ይካሄዳል። በተከታዩ ሊንክ ከዌብሳይታቸን በስምዎ ነፃ የመግቢያ ቲኬት ማግኘት ይችላሉ። https://conference.nesiha.tv ለፕሮግራሙ ድጎማ በማድረግ አጋራችን ለመሆን Cbe 444 የሂሳብ ቁጥራችንን ይጠቀሙ። እናመሰግናለን ____ 🕌 ibnu Masoud islamic Center @merkezuna

ነሲሓ ኮንፈረንስ የሚታደሙበትን የመግቢያ ትኬት online በመመዝገብ በነፃ ይውሰዱ ታላላቅ ኡለማዎች የሚሳተፉበት ልዩ የነሲሓ ኮንፈረንስ በአላህ ፈቃድ በሚሊኒየም አዳራሽ መጋቢት 1/2016 ይካሄዳል
ነሲሓ ኮንፈረንስ የሚታደሙበትን የመግቢያ ትኬት online በመመዝገብ በነፃ ይውሰዱ ታላላቅ ኡለማዎች የሚሳተፉበት ልዩ የነሲሓ ኮንፈረንስ በአላህ ፈቃድ በሚሊኒየም አዳራሽ መጋቢት 1/2016 ይካሄዳል። በተከታዩ ሊንክ ከዌብሳይታቸን በስምዎ ነፃ የመግቢያ ቲኬት ማግኘት ይችላሉ። https://conference.nesiha.tv ለፕሮግራሙ ድጎማ በማድረግ አጋራችን ለመሆን Cbe 444 የሂሳብ ቁጥራችንን ይጠቀሙ። አናመሰግናለን ____ 🕌 ibnu Masoud islamic Center @merkezuna

🌟የወንዶች አለባበስ 🌟አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/545 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🌟የወንዶች አለባበስ 🌟አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/543 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts