cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

ግጥምን በገጣሚው ™®

#ግጥም የውስጥን ስሜት ፈንቅሎ በማራኪ ቃላት ለመግለፅ የሚጠቅም ሰዋዊ መሳሪያ ነው። 💚💚💚💛💛💛❤❤❤ በዚህ ቻናል ምርጥ ምርጥ ግጥሞችን ያገኛሉ 😘 .ቤተሰብ ይሁኑ @gtmnbegetamiw ለአስተያየትዎ @lijsalie21

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
201
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

"ዝም በል" (ኤልያስ ሽታኹን) ከሳሽህ ፊት ዘንበል ሰዳቢህ ፊት ዘንበል በነፍስህ ተናገር በቃልህ ዝም በል። ዝም እሺ በል አጎንብስ ፊደል አታገግበስብስ ዝም በል ጭጭ ጭጭ ስንፍናን በልምጭ ዝምታህን እቅጭ ነው ብለህ ተቀበል ዝም ብለህ አስጩህ እንደቅዱስ ፀበል:: አስብ ዝም ብለህ እንደሊቅ ተራቀቅ እንደንጉሥ ውደቅ:: ዝም ብለህ ሞክር ዝም ብለህ ጨክን ዝምበል ተንገዳገድ ማስራዳት ሲያስብ ነው ሰው የሚወላገድ:: ዝም:: እግዜርን ተመልከት ሊያስረዳህ ሲሞክር አታየውም ሲጥር መች ብዙ አወራ ዓለምን ሲፈጥር። (ዝም ብለህ ቀጥል….. @amharic_poems
نمایش همه...
ማህሌተ ገንቦ (በውቀቱ ስዩም) ባጭር ቀረን ስንል - እድሜ ላበደሩን ቀርፀው ላሳመሩን ለኩሰው ላበሩን ቺርስ!! ፊታችንን ዐይተው -እንደተቸገርነ- ካይናችን ላወቁ ስለማርያም ብለን እስክንለምናቸው-ቆመው ላልጠበቁ ቺርስ!!! ወድቀው ለማይጥሉ -ነግሰው ለሚያነግሱ ነውራችንን ዐይተው ልክ እንደ ድመት ኩስ ለሚያለባብሱ ብድር አበድረው ፈጥነው ለሚረሱ😉 ቺርስ!!!! ላባ ላረጉልን የመከራ ሸክሙን ቀልደው ላሳቁን-ተጫውተው ላከሙን በቸከ ዘመን ላይ- ስጋ ለበስ ትንግርት -ሆነው ላስደመሙን ቺርስ!!!!! SHARE🌼 =ኪ==ነ==ቃ==ል= @Write_Event @Write_Event @Write_Event
نمایش همه...
#ምን_ነበር? የፍቅራችን እሣት ነዶ ግሞ ንሮ በቅቶት ሲበርድ፤ አስመስሎን እንዳረፈ አንቺን ከሰል እኔን አመድ፤ አንቺ ዳግም ስትነድጂ ፍም ስትሆኚ ገጥመሽ ከሰው፤ እኔ ስዛቅ በመጫሪያ እንደትቢያ ስታፈሰው፤ ልረሳሽ ቃል ገብቼ ተግብሬአለሁ አንድ ነገር፤ ያደረኩት ግን ምን ነበር? ፡ ፡ አንቺን ማጣት፤ አንድ ግዜ የእግር እሣት፤ አንድ ግዜ የቋንጃ እከክ፤ እየሆነኝ ስብረከረክ፤ እኔው ለኔው ቃል ገብቼ፤ ካልረሳዋት ወንድ አይደለው ይቺን አባይ ብዬ ዝቼ፤ የተጫነኝ ዝግባ ቀንበር፤ ከልቤ ላይ እንዲሰበር፤ ትዝ ይለኛል ተግብሬአለሁ ምስ የሚሆን አንድ ነገር፤ ያደረኩት ግን ምን ነበር? እንዳይከፋሽ እንድትስቂ፤ አንዴ ህፃን አንዴ አዋቂ፤ መሆኔን ቢያይ ውስጥሽ ውስጤን አበክሮ ስላወቀው፤ አሳቻ ሰዓት ደባ ፈትለሽ ቀበቶዬን ሳላጠብቀው፤ መልህቁን የመርከቡን ሰውረሽው ድብቅ ቦታ፤ ማበል ወጀብ እየናጠኝ እያየሺኝ ስንገላታ፤ ብቅ ጥልቅ እያስባለኝ ከወደቡ እልፍ ርቄ፤ ለብቻዬ ተጠብቤ ለብቻዬ ተጨንቄ፤ መውጫ ባጣ ማርያም መንገድ፤ ቃል ገብቼ የዛን ግዜ ፍፁም አንቺን ላለመውደድ፤ ተግብሬአለው አንድ ነገር አንቺን ከቶ እንዲያስረሳኝ፤ ምን ነበር ግን ያደረኩት? አለኝ ዛሬ አልወሳኝ። ፡ ፡ አሁን ሳስብ በትውስታ፤ የሆነ ግዜ የሆነ ቦታ፤ ከልቤ ላይ እንዲነቅለው ያንቺን ሰንኮፍ የተጣባኝ፤ አንድ ነገር አድርጌአለሁ ግን ምን ነበር ግራ ገባኝ? ፡ ፡ ትዝ የሚለኝ ብቻ ዛሬ፤ ያንን ነገር መተግበሬ፤ አንቺን ማጣት አንቺን መርሳት፤ ግዙፍ ቋጦኝ ዳገት መግፋት፤ እንዳልሆነ ሰብቆልኛል ይባስ እንደው በተቃርኖ፤ አንቺን መርሳት ፊቴ ቆሟል ደቂቅ ገቢር ኢምንት ሆኖ። ፡ ፡ አይረሳኝም ስትዪ ሰማው ... እንኳን ያንቺን ፍቅር ቀርቶ ለኩነኔ ላሳር ሰቶኝ እኔን ያኔ ያሳነሰኝ፤ የዛን ግዜ የፈፀምኩት እንድረሳሽ ያደረገኝ ፅድቁም ተግባር መች ታወሰኝ። #ሄኖክ_ብርሃኑ SHARE🌼 =ኪ==ነ==ቃ==ል= @Write_Event @Write_Event @Write_Event
نمایش همه...
ያልጣዱት አይበስልም (በእውቀቱ ስዩም) ፍቅር እንደ ዝናብ ከሰማይ አይወርድም ያበባ መደብ ነው በሰው የሚታነፅ : በሰው የሚወድም ተዘርቶብን እንጂ :ተሰብከን አንወድም:: "ወዳጄ ወዳጄ " የሚያቀነቅኑ አገር ያቀኑ ለት መች ልብን አቀኑ ሳይወጡ ሳይወርዱ ውብ ስራን ከውብ ቃል :ሳያስተባብሩ ከድሜ እና ከምቾት ቆርሰው ሳይገብሩ ፍቅር መች ይፈልቃል? በስብከት በምልጃ በየዋህ ሰዎች ህልም ያልጣዱት አይበስልም ያልዘሩት አይበቅልም:: @minilikabera @minilikabera
نمایش همه...
"የአያቴ ገድል" (እዮብ ተፈሪ) አደዋ ሰማይ ላይ በደም እና በአጥንት የተከበረን ድል አርበኛው አያቴ የፃፈውን ድርሳን አነበብኩኝ ገድል የድርሳኑ መግቢያ በቀይ የደመቀ አደዋ የሚል ቃል አያቴ ክታብ ላይ ምኒልክ የሚል ስም በደም ያስታውቃል ታሪኩ ሲጀምር………… እምዬ ምኒልክ ንጉስ አባ ዳኛው ታቦቱ ጊዮርጊስ ማርያም መማፀኛው የዘወትር ፀሎት ዳዊት የሚደግም ባለማህተብ ነው መስቀል የሚሸከም የእምዬ ኢትዮጵያ እምዬ ምኒልክ የሀገር ካስማ ነው የእናትነት ምትክ ፒያሳ አደባባይ የቆመለት ሀውልት የጥቁሮች አርማ ነው የነፃነት አባት አያቴ ክታብ ላይ ……………… ዘመን እንደ ድውር ድንገት ተወርውሮ ጥበብ ሳይሸመን ሰማይ ተወጥሮ ቀን እየቆጠርን የእድሜ ጀንበር መሸ አዲስ ትውልድ መጣ የኛ ዘመን ሸሸ ትውልድ እንደ ዥረት በአሻው አየፈሰሰ የአያቶች እርግማን በልጅ ልጅ ደረሰ የንጉሱን መንበር ግዜው ቀን ሲገዛ ዓመታት ነጎደ እንዲሁ እንደዋዛ በመከነው ትውልድ በቁጭት ተክዤ አደዋ እላለሁ በትዝታ ፈረስ የኃሊት ተጉዤ የዛሬ መቶ ዓመት በንጉሱ ሰዓት ጃአኗሪ ሳይጠባ የፈረንጆች ዓመት ንጉስ ብሎ ነበር ጥቅምት እኩሌታ ወረኢሉ ክተት ፋሽት ጣልያን የባህር በር አልፎ ገብቷል ለጦርነት ====================== አደዋ ሰማይ ላይ በደም እና በአጥንት የተከበረን ድል አርበኛው አያቴ የፃፈውን ድርሳን አነበብኩኝ ገድል የድርሳኑ መግቢያ በቀይ የደመቀ አደዋ የሚል ቃል አያቴ ክታብ ላይ ምኒልክ የሚል ስም በደም ያስታውቃል አዋጅ አዋጅ አዋጅ የአገሬ ሰው ከአሁን ቀደም የበደልኩህ አይመስለኝም አንተም ብትሆን ለአገርህ ባንዳ ሆነህ አልካድከኝም ህዝቤ ስማኝ ከአንተ የተደበቀ ሚስጥር የለኝም እስከ አሁንም ጥላት ደፍሮ አልወጋኝም አሁን ግን……… ጥላቴ ጣልያን ዝም ስለው እያለፈ ጉድጓድ ይምሳል ተው ብለውም እንደፍልፈል መሬት እየቆፈረ ግዛት ያሰፋል እኔም አገሬው ሰብሉን ሳያጭድ የከብቱን ማለቅ አይቼ ለአዘኑ ቀን ብሰጠው ጣልያን መሰለው ፈርቼ እንጂ ማ እኔ ንጉስ ምኒልክ ፍርሃት በደሜ የለም ለሀገር ነፃነት መሞት ያ ለኔ ሞት አይባልም ======================== የጣልያኑ ባራቴሪ አለምን የሚስንቅ ጦር ቢደረድርም ጎራዴ የታጠቀ የኢትዮጵያ አርበኛ ለሞት ቢሰለፍሞ የምኒልክ ወኔን የታጠቀ ፋኖ ዘምቶ አይሸነፍም የዜግነት ክብር በጀግና ደም እንጅ በእንባ አይፃፍም ቃል ለምድ ለሰማይ ለሮማን ባርነት ደግ ህዝቤን አልሰጥም ማርያም ምስክሬ ናት ለፈረንጅ ሞግዚት ኢትዮጵያን አልተውም ብሎ እየፎከረ ያ የጥቁር ንጉስ የክተቱን ጥሪ አዋጁን ሲናገር ሃገሬው ልብ ውስጥ የወኔውን እሳት ያቀጣጥል ነበር የክተቱ አዋጅ በአራቱም ማዕዘን ነጋሪት ሲጎሰም የሀበሻ አርበኛ ወረኢሉ ከቷል ጥላቱን ሊገጥም ========================== አምባላጌ ላይ ጦሩ ሲቀድም የራስ መኮንን የራስ መንገሻ ጦርነት ቀዳሽ ገበየሁ ነበር ጥላት ማርከሻ በወኔ ፈረስ እየበረረ በጦር ጎራዴው አንገት የሚጥል ከጀግኖቹ መሀል ስሙ የሚቀድም ንጉስ ሚካኤል ከተራራው አናት የድል ባንዲራ ወጥቶ የሚሰቅል ራስ ወሌ ነው በአደዋ ሰማይ ይፅፋል ገድል የወኔው እሳት ከፊቱ ሲነድ ጥላት የሚያስጨንቅ ገበየሁ ገቦ የአገሩን ጥላት በደም የሚያጠምቅ ፋሽት ጣልያን በሴራ መረብ ቀርበው ሲያጠምዱት ባለማተቡ በእናት ሀገሩ የማይደራደር ተክለ~ሐይማኖት በፍቅር እንጅ በጦር የማይወድቅ የአገር ከለላ የጦሩ አለቃ ድንበር ጠባቂው እራስ አሉላ የጦር ገበሬው የወንዶች ቁና ባልቻ አባ ነፍሶ ከጥላቱ ላይ መድፍ የሚማርክ ክላሽ ተኩሶ ያ የሳት ላንቃ ሀሞተ ቁጡ ትንፋሹ የሚፋጅ ትንታግ ነበልባል የሳት ረመጥ ጥላት የሚፈጅ ለእናት ሀገሩ ደረቱን ሰጥቶ ከመተረየስ ፊት የሀገር ደም መላሽ ባልቻ ተተካ ገበየሁ ሲሞት ================= ዘራፍ በል አንተ እምቢ ለአገርህ ዘራፍ ለእምዬ እምቢ ለእናትህ ጮማ ላበላህ ጠጅ ላጠጣህ ሀገር ለሰጠህ ጎጆህ ላስተኛህ ማሀይም ብትሆን ፊደል ባትቆጥር የጥላት አንገት በሰይፍህ ቁጠር ፈረጅ ልምዱ ነው መድፍ መተኮስ ጥንትም አያትህ በወንጭፍ ድንጋይ ጥላት የሚመልስ ዘራፍ በል አንተ እምቢ በል አንተ መድፍ መትረየስ ያልያዘ እሳት ፊት ጎራዴ እየመዘዘ በለው በለው እያለ ሲማረክ እየሸለለ ሲገድል እየፎከረ በድምፁ እያሸበረ በአደዋ ሰማይ ስር ሀገሩን የማያስደፍር =============== ያአቺም እቴጌይቱ ትንታግ ነበልባሊቱ ግፍን እንቢ የምትል ጀግኒት ጣይቱ ብጡል ለሀገር የቆመች ዳኛ እቴጌ የሴት ነፍጠኛ በጥበብ ጦር የምትመራ ጥላቷን ቅንጣት የማትፈራ ጣይቱ የሴቶች አውራ የእናቷን ታሪክ የምትሰራ ጥራልኝ እማ አንተዬ በሙዚቃ አንቺ ሆዬ ራስ ፊት አውራሪ ጀግኖቹን የአደዋ ጀነሎቹን የጦሩ አዛዥ ገበየሁ በጀግንነቱ ስንትአየሁ ታሪክ የሚፅፍ በደም እያለ ኢትዮጵያ ትቅደም:: ✍ እዮብ ተፈሪ
نمایش همه...
መዳፍ ማንበብ ትችያለሽ ? ድሮ ለታ የጨበጥሽኝ ቀኝ መዳፌን አሳከከኝ፣ ለእርግማን ነው ብየ ፈራሁ በልቶኝ መቼም አይባርከኝ፤ እስኪ እይልኝ እባክሽን የሚበላኝ የት ድረስ ነው ? እኔስ ቁስሌን ሳባብለው የምኖረው እስከ የት ነው ? መዳፍ ማንበብ ትችያለሽ? አበባ አለ ከ ዕጣዬ ጋር አይተሽዋል ቅጠል ግንዱን፣ መርገፍ ሊሆን የነገ ዕጣው እንዴት ይኑር ሰው የግዱን፤ ወይንስ ባጭር እሆናለሁ ያልኩት ተስፋ አጓጉቶ ያንቋጠጠኝ፣ በእፍኝ ተድላ ሊቀጨኝ ነው የእስከ ዛሬን ቀን የሰጠኝ፤ አንችስ... አንችስ... አንችስ ብሞት ትመጫለሽ ? በድኔን አፈር ታለብሻለሽ ? በ እንባሽ ሽቶ ታብሻለሽ  ? ብቻ ተይው መዳፍ ማንበብ ትችያለሽ ? ነገን ገልጠሽ ባታሳይው ከህመሙ ባትፈውሺው፣ ለእድሌ እንደሁ ግድ የለኝም እስኪ በዛው የናፍቆቴን አንዴ ብቻ እጄን ዳብሽው። ©️አስታወሰኝ ረጋሳ
نمایش همه...
አቤት ዘመን! ወጀቡ እጅግ አየለ ፣ ሊያናውጥ የዓለቷን ቅጥር አፍራሹ መች ገባውና ፣ እንዳለት የመልአክ አጥር። አይይ...! ምነው እናታለም... ጸዓዳ ለባሽ መላእክት ፣ በዙሪያሽ እንዳልቆሙልሽ ያ'ለም ብርሃን ክርስቶስ ፣ በደሙ እንዳላጸናሽ፣ ምን አይነት ክፍ ዘመን ነው ፣ የጽልመትን ማቅ ያለበሰሽ??! ኦ መሐረነ🙏 ኦ ተሰሃለነ🙏 ከዘመነ መንሱት አድኅነነ🙏 የእኛ የበደል ፅዋ ፣ ከልኩ ሞልቶ ፈሰሰ በታሪክ ከሆነው በላይ ፣ በዘመናችን ደረሰ። አዎ በድለናል... አዎን አምጸናል... ከትዕዛዝህ ውጪ ሆነን፣ ሕላዌህን ዘንግተናል፤ ዛሬ ግን እባክህ ማረን ፣ ባሮችህ ማቅን ለብሰናል። ይቅር ማለትን ታውቅ የለ? ፣ መሐሪ'ኮ ነህ ክርስቶስ አይተናል የነነዌን ሕዝብ ፣ በእንባቸው ቁጣህ ሲመልስ የኛንም ለቅሶ አድምጠህ ፣ የመጣውን እሳት ደምስስ። በርግጥ በነነዌ ሀገር... ሰውና እንስሳ ሳይቀር ፣ ንጉሥ አመድ ነስንሷል ስለሚገዛት ሀገሩ ፣ በፀፀት እንባን አፍስሷል። እነሆ በእኛ ሀገር ግን ፣ የተሾመብን ንጉሥ እንኳን ምሕረት ሊለምን ፣ እንኳንስ ቀርቶ ሊያለቅስ በቁስል እንጨት ይሰዳል ፣ ይውላል ችግር ሲያባብስ። አንተ ግን በቸርትህ... ወገኖችህ እስራኤልን ፣ ያውጣህ ከፈርኦን ክንድ እኛንም ባክህ አድነን ፣ ከመጣብን የእሳት ነዲድ ከከሀሊነትህ ሐኖስ ፣ ጠለ ምሕረትህን አውርድ። አዎ እናምናለን... ክርሰቶስ በደሙ የዋጃት ፣ አትጠፋም እርሷ ሃያል ነች አንድ ሆና እንደተሰጠች ፣ በ'አንዲት'ነት ትኖራለች። አንዲት ቤተ ክርስቲያን! አንድ ሲኖዶስ! አንድ ፓትርያርክ! "እግዚአብሔር የሰላማዊት ቤተክርስቲያናችንን ሰላሟን ይመልስልን"🙏✝🙏 ©ሳለአምላክ
نمایش همه...
መልክአ ሳጥናኤል (✍በሳለአምላክ) ለዝክረ ስምከ... ሲጠሩት ለሚመር፣ ከአፍ ውስጥ ሲወጣ ጥሩኝ ጥሩኝ ለማይል፣ ጭንቀት ለሚያመጣ ቀፋፊ ለሆነው፣ ለስም አጠራረህ ሰላምታ ሳይሆን ፣ ውርደት ነው 'ሚገባህ ለገጽከ... ከጨለማ በላይ ፣ በ'ጥፍ ለሚጠቁር ጽልመትን ተላብሶ ፣ ሲያዩት ለሚል ቅር እኩይ ለሌለው ፣ ለአስቀያሚው መልክህ ሰላምታ አይደለም ፣ ውርደት ነው 'ሚገባህ። . . . . . . . እያልኩኝ..... ልደረድር ሳለሁ ፣ እስካ'ጽፈረ እግርከ ብዕሬ ቀፈፈው ፣ መንፈሱ ታወከ። ዘገነነኝ... ቀፈፈኝ... ሰቀጠጠኝ... በትል ባሕር ውስጥ፣ ገብቶ እንደመዋኘት ከምግብ ጉርሻ ውስጥ ፣ ጸጉር እንደማግኘት በእባብ ገላ ላይ ፣ እንደመረማመድ በእጅ ለተቀረጸ ፣ ጣኦት እንደ መስገድ መርፌን እንደማኘክ ፣ ምላጭ እንደመዋጥ እንደዚያ ቀፈፈኝ.... ፤ ውርደትህን መግለጥ። ዳሩ ግን... የዓለሙ ጌታ፣ ክብሩ ተወድሶ፣ እንደማያልቅ ሁሉ ያ ን ተ ም እኩይነት ፣ እንደዚያ ነው ውሉ።
نمایش همه...
ማረን እግዚኦ መሀረነ ይቅር በለን ጌታ፣ ሞኝነት መሰለን የፍቅርህ ዝምታ። ምህረትህ በዝቶ ብትሆን እንዳላየ፣ ብለን ተመፃደቅን ፈጣሪ ዘገየ። በእንቅፋት የምጠፋ በስቅታ ምትነጠቅ፣ በኛ ሳይሆን ባንተው ብርታት ምትጠበቅ። ብትኖረን አንድያ ነብስ፣ አስከፋንህ ጥግ ድረስ። አለም ከንቱ ነገ ጠፊ፣ ካንተ ውጪ ሁሉ አላፊ። ስልጣን ገንዘብ ሀብት ዝና፣ ማያረጅ የሚመስል የፈካ ቁንጅና። እውቀት ጥበብ ልክ ቢያጣ፣ ካንተው እንጂ በኛ አቅም መቼ መጣ። ግና ያወቅን ሲመስለን ከክብርህ ተጋፋን፣ መስመርህን ስተን በራሳችን ጠፋን። ከመንበር መቀመጥ፣ ቢመስለን መመረጥ። ህግ ሻርን ተላለፍን ያንተን ወሰን፣ ምነው ጌታ በቃ ብለህ ወደቤትህ ብትመልሰን። የማታወርቅ ከበደ(ፋና ብዕር)
نمایش همه...
@ሃይማኖት_ንጉሴ(የዲማው) ለስሜቴ ገደብ አበጃለሁ ልጓም፤ ያየኹትን ሁሉ ለመቅመስ አልጓጓም፤ የማላውቀው ነገን፣ በምናብ እየሳልኹ፣ እንዲህ ብሆን ብዬ ፍፁም አልመኝም፤ ሰው የእድሉን እንጂ፣ የህልሙን እሳቤ በእውን አያገኝም። ብቻ ግን ዝም ብዬ ሁል ጊዜ እጓዛለሁ፤ የእዮብን ያህል ትዕግስት              በጫንቃዬ አዝያለሁ፤ ተፈጥሮ ልኳ ቢሆን ሙልጭልጭ፤ ሰርክ ቢገረፈኝ የህይወት ልምጭ፤ አላገደኝም ከመጓዝ ወድቄም እንኳተታለሁ፤ ደግሞ ዳግም ተነስቼ ለመሮጥ እኳትናለሁ፤ ህይወት ፈተናን እንጂ መቼም ተድላን አትወክል፤ ገና ነው ትልቁ እንቅፋት አትውደቅ በጠጠር እክል፤ እያልኩኝ ልቤን ሳፀና ከውድቀት አብዝቼ ስሸሽ፤ የመኖር ጣዕሙ ሳይገባኝ ታወቀኝ እድሜዬ ሲመሽ፤ ለካ ውሸት ነው አልጓጓም ያልኹት ሀሰት ነው ተራ ሽንገላ እውነትን ከልብ ማስወገድ፤ መጓጓት መፈለግ አይደል? በተስፋ ብቻ 'ሚያስጉዝ  መድረሻ በሌለው መንገድ፤ ባልፈልግ ባልጓጓ ኖሮ ስኬትን ልቤ ባይመኝ፤ ነገዬን አውቀው ይመስል ዛሬ ላይ ምን አደከመኝ፤ ተስፋ የለኝም ያልሁት ውሸት ነው ለካ ሳስበው፤ ጠማማው ተስፋዬ ነበር ኑረቴን ያወሳሰበው። ዛሬ ግን ልቤ ለመኖር ምክንያት ፈልጎ የእወነትን ተስፋ ወጠነ፤ ከሻማ ፀዳል ደብዛዛ ከድር ዘለላ የቀጠነ፤ መወፈር መስፋቱ አይደለም የተስፋ ቁምነገሩ፤ ሰበብ መሆን ብቻ ህይወትን ለማኖሩ፤ መጓዝም ይሁን መቀመጥ የህይወት ጣዕሙ ሲመርህ፤ ለራስህ ሰበብን ፍጠር ለመኖር ምክንያት ይኑርህ። እንደዚህ አልኹት ራሴን በልቤ ስዬ ምስልሽን፤ እንደ ማርያም አዛኝ ልብሽን፤ እንደ ጀምበር ፀዳል መልክሽን፤ አምሳልሽን በልቤ እያሰብኩ ለራሴ ቃል ገባሁለት፤ እሷ ናት በቃ ከእንግዲህ የመኖሬ ትልቁ ምክንያት። ........አልኹት። #ግጥም @haymanot6 _ የዲማው _ join @a1hay @a1hay @a1hay @a1hay @a1hay
نمایش همه...