fa
Feedback
የቃ/መ/ብ/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ሐመረ ሕይወት ሰ/ት/ቤት

የቃ/መ/ብ/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ሐመረ ሕይወት ሰ/ት/ቤት

رفتن به کانال در Telegram
456
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

ابر برچسب‌ها
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
دسامبر '24
دسامبر '240
در 0 کانال‌ها
نوامبر '240
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '24
+51
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '240
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '240
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '240
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '240
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '24
+6
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '24
+3
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '24
+1
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '24
+4
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '24
+14
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '23
+1
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '230
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '230
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '23
+1
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '23
+11
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '23
+46
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '23
+3
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '23
+6
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '23
+7
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '23
+12
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '23
+46
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '23
+23
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '22
+7
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '22
+38
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '22
+10
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '22
+7
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '22
+11
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '22
+9
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '22
+35
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '22
+234
در 0 کانال‌ها
پست‌های کانال
አዲስ አበባ‼️ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ፣ የአዲስ አበባ አገረ ስብከት ቅጥር፣ ዕድገት፣ ዝውውር እና ከመደበኛው ውጭ የሆነ የገንዘብ እንቅስቃሴ እንዲቆም ትናንት ባካሄደው ስብሰባ ወስኗል። ቅዱስ ሲኖዶሱ፣ ይህን ውሳኔ የወሰነው፣ በአገረ ስብከቱ ውስጥ የተንሠራፋውን ሙስናና ብልሹ አሠራር እንዲያጣራ የተቋቋመው አጣሪ ቡድን ያቀረበውን ሪፖርት ከመረመረ በኋላ ኑው። ቅዱስ ሲኖዶሱ፣ ሦስት ሊቃነ ጳጳሳትና ሌሎች ሊቃውንት አጣሪ ቡድን ላይ እንዲጨመሩና ችግሩን በዝርዝር አጥንተው ለግንቦት የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ እንዲያቀርቡ ወስኗል:: በቴሌግራም https://t.me/hamerk በዩቲዩብ https://youtu.be/yKfRKR4g-v0 በፌስ ቡክ https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR ወቅታዊ መረጃዎችን ከሰንበት ትምህርት ቤታችን ያገኛሉ::

2
አጣሪ ኮሚቴው ሪፖርቱን ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ አቀረበ። ** ጥቅምት ፲፫ ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም ==================== አዲስ አበባ-ኢትዮጵያ """""""""""""""""""""""""""" በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ተከስተዋል የተባሉትን የመልካም አስተዳደር ችግሮች በተመለከተ ዝርዝር ጥናት ሲያካሒድ የሰነበተው አጣሪ ኮሚቴ የማጣራት ሥራውን በማጠናቀቅ  ዛሬ ጥቅምት ፲፫ ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ሪፖርቱን አቅርቧል። አጣሪ ኮሚቴው  በሰነድና በቪዲዮ የተደገፉ የማጣራት ሥራ ግኝቶችን  እንዲሁም ቤተክርስቲያንን ማዕከል በማድረግ የተከናወኑ ዘረፋና ሕገ ወጥ ተግባራትን፣ከተጠያቂነትና ወደፊት ሊወሰዱ ከሚገባቸው የመፍትሔ ሐሳቦች ጋር በማቀናጀት የቤተክርስቲያን ልዕልና የሚከበርበትን አቅጣጫ የሚጠቁም ሪፖርት አቅርቧል። የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤም በዛሬው ዕለት በሚያካሂደው ጉባኤ የቀረበለትን ሪፖርት ከመረመረ በኋላ ውሳኔ ያስተላልፋል ተብሎ ይጠበቃል። በቴሌግራም https://t.me/hamerk በዩቲዩብ https://youtu.be/yKfRKR4g-v0 በፌስ ቡክ https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR ወቅታዊ መረጃዎችን ከሰንበት ትምህርት ቤታችን ያገኛሉ::
384
3
የውንድማችን የዲያቆን መምህረ ምዕራፍ ላከማርያም ድንገተኛ እረፍት ከዚ አለም ደካም ሰላረፍ ነገ በ14/02/2017 ከቃሊቲ ቅዱስ ገብርኤል ወደ በደብረ ፀሐይ ሳሎ ቅዱስ ከ4ሰዓት እሰክ 5ሰዓት ሽኝት ይደረጋል በካእናትእና በሰንበት ተማሪሆች ታጅቦ ይሄዳል የቻላችሁ ተገኙ አምላክ ነፍስክን በአፀደ ገነት ያሳርፍልን
332
4
بدون متن...
322
5
بدون متن...
293
6
بدون متن...
269
7
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በመጀመሪያ ቀን ጉባኤው አጀንዳ አርቃቂ ብፁዓን አባቶችን ሠይሟል። #የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ የጥቅምት 2017 ዓ/ም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት ጉባኤውን ማካሔድ ጀምሯል። በዚህ በዛሬው ከሰዓት ቀፊት በነበረው ጉባኤ ሰባት ብፁዓን አባቶች አባላት ያሉበትን አጀንዳ አርቃቂ ኮሜቴ ሠይሟል። በዚህም መሠረት 1.ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ 2.ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ 3.ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና ሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ 4.ብፁዕ አቡነ ማርቆስ በሰሜን አሜሪካ ሲያትል አይዳሆ ኦሪገን ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ 5.ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት 6.ብፁዕ አቡነ ኤጲፋንዮስ የምሥራቅ ጉራጌ ሀገረ ስብከት ጳጳስ 7.ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሶማሌ ጅግጅጋ ሀገረ ስብከት ጳጳስ መሆናቸውን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ገልጿል። የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ በጥቅምትና በግንቦት ርክበ ካህናት እንደሚካሄድ ይታወቃል። 🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚 #ስለአንዲት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን" #ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ #መረጃ ጥቆማ aadmedia05@gmail.com ይጠቀሙ። በፌስቡክ https://www.facebook.com/AddisAbabaDiocese?mibextid=2JQ9oc ከዚህ በተጨማሪ በሌሎች የበይነ መረብ አማራጮች ለመከታታል በቴሌግራም: https://t.me/AddisAbabaDiocese በዋትስ አፕ: https://whatsapp.com/channel/0029VaJznc90rGiNUScgwn3U በዩቱዩብ: http://www.youtube.com/@AddisAbabaDioceseMedia በቲውተር: https://twitter.com/AADioceseMedia/media በቲክቶክ:http://tiktok.com/@mediaofaadiocese መጠቀም ይችላሉ።
288
8
بدون متن...
259
9
የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት: የጥቅምት 2017 ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ  በጸሎት መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት ይጀመራል !!! የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የጥቅምት 2017 ዓ.ም  ምልዓተ ጉባኤ በነገው ዕለት በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ይጀመራል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በዓመት ሁለት ጊዜ ጥቅምት 12 እና በዓለ ትንሣኤ በዋለ በ25ተኛው ቀን ምልዓተ ጉባኤውን የሚያከናውን መሆኑ ይታወቃል። ምልዓተ ጉባኤው በዛሬው ዕለት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በሚደረገው የጸሎት መርሐግብር የሚከፈት ሲሆን ከነገ ጀምሮ ቅዱስ ሲኖዶስ በልዩ ልዩ ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያንና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ  እንደሚወያይ ይጠበቃል። በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ተከስተዋል የተባሉትን የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በተመለከተ የተሰየመው አጣሪ ኮሚቴ ሪፖርቱን ለቋሚ ሲኖዶስ አቀረበ። በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ተከስተዋል የተባሉትን የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በተመለከተ በዝርዝር በማጣራት የመፍትሔ ሐሳብ ጭምር እንደያቀርብ የተሰየመው አጣሪ ኮሚቴ ባለፉት ዐሥራ አምስት ቀናት ሲያከናውናቸው የሰነበተውን የማጣራት ሥራዎች በማስመልከት ያዘጋጀውን ሪፖርት ዛሬ ጥቅምት ፲፩ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም ለቋሚ ሲኖዶስ አቅርቧል። አጣሪ ኮሚቴው አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በአካል ተገኝቶ ማጣራት እንዳይችል የተከለከለ መሆኑን በመጥቀስ መረጃውን ለማሰባሰብ ይቻል ዘንድ ተበዳዮች በስልክ፣በቴሌግራምና በዋትስ አፕ እንዲሁም በአካል በመቅረብ በሰነድ ማስረጃ በማስደገፍ፣በድምጽና በቪዲዮ በተቀረጸ ማስረጃ ጭምር መረጃዎችን ማሰባሰቡን፣መተንተኑን፣ማደራጀቱንና ጥቅም ላይ ማዋሉን ገልጿል። በሪፖርቱም ከመልካም አስተዳደርና ከብልሹ አሠራር ጋር ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮች በማስረጃ ተደግፈው የቀረቡ ሲሆን በማጣራት ሥራው የተረጋገጡ ጉድለቶችንና ጥፋቶችን መሰረት በማድረግም በጊዜያዊነትና በቋሚነት ችግሮቹን ለመፍታትና የካህናትና የአገልጋዮችን ቅሬታ ዘላቂነት ሊፈቱ ይችላሉ ተብለው የቀረቡ  በሰባት ነጥቦች የተተነተኑ  የመፍትሔ ሐሳቦችና በዘጠኝ ነጥቦች የተተነተኑ ችግሮቹንና የመፍትሔ ሐሳቦችን አቅርቧል። የጥናት ሰነዱ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ቀርቦ ውሳኔ የሚሰጥበት ይሆናል። @የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
361
10
https://youtu.be/TYi7kuI6iL4
385
11
بدون متن...
392
12
ማስታወቂያ +++++++++++++++++++++++++++++++++ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተዳደር ጉባዔ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሚስተዋለውን የመልካም አስተዳደር ችግር ተከትሎ ችግሩን በማጥናት ከመፍትሔ ሐሳብ ጭምር የሚያቀርቡ  ሰባት አባላት ያሉት ኮሚቴ በማቋቋም ወደ ሥራ እንዲገቡ አድርጓል። በዚህም መሠረት የተቋቋመው ኮሚቴ መረጃዎችን መሰብሰብ፣ መተንተንና መጠቀም ይችል ዘንድ የስልክ፣የቴሌግራምና የዋትስአፕ ቻናሎችን በስልክ ቁጥር 0940467777  በኢሜይል አድራሻችን  eotcpr2024@gmail.com  በቢሮ ስልክ ቁጥራችን +251111262818 በቀጥታ ማቅረብ የምይችሉ ሲሆን በአካል ማስረጃዎችን መስጠት የምትፈልጉ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤት በመገኘት ሐሳብ፣መረጃና ማስረጃ መስጠት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን። አጣሪ ኮሚቴው ትኩረት ሰጥቶ የማጣራት ሥራውን የሚሠራው በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከትና በጠቅላይ ቤተክህነት አሠራርና አሠራሩን ተከትሎ በተፈጠሩት የመልካም አስተዳደር ችግሮች ላይ በማድረግ ተቋማዊ አሠራርና ሥርዓት እንዲከበርና ችግሮችን በዘላቂነት መፍታት ላይ የሚያተኩር መሆኑን እየገለጽን ነገር ግን በግለሰቦች፣ በተቋማት፣ በሕግ፣ በሚዲያና በልዩ ልዩ መንገድ የሚቀርቡ የአደባባይ ችግሮችን ሌላ መልክ በመስጠት የሚደረጉ የተለመዱ እንቅስቃሴዎችን ሁሉም አካል በአንክሮ እንዲከታተለውና ቤተ ክርስትያንን የመጠባቅ ሥራ ላይ ትኩረት እንዲደረግ በዚሁ አጋጣሚ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።      አጣሪ ኮሚቴው
497
13
"ምዕመናን ገንዘባቸውን የሚሰጡት ለሃይማኖት ማስፋፊያ እንጂ ለዘረፋ አይደለም።" ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ቅዱስ ፓትርያርኩ ለአጣሪ ኮሚቴው የሥራ መመሪያ ሰጡ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሚስተዋለውን የሙስናና ብልሹ አሰራር በዝርዝር በማጥናት የመፍትሔ ሐሳብ እንዲያቀርብ በጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤት የተቋቋመው አጥኚ ኮሚቴ ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖትና ከብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባህር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጋር ከተቋቋመ ጀምሮ እስካሁን የሠራቸውን ሥራዎች ሪፓርት በማቅረብ በቀጣይ በሚያከናውናቸው ተግባራት ዙሪያ በመወያየት የሥራ መመሪያ ተቀብሏል። ኮሚቴው በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሚስተዋለው የመልካም አስተዳደር ችግር ከውስጥ አልፎ በአደባባይ መነጋገርያ በመሆኑ በጥናት ላይ በተመሠረተ አግባብ ተቋማዊ ለውጥ ማምጣት የሚያስችልና የቤተ ክርስቲያናችንን ክብር በሚመጥን መልኩ እንዲደራጅ የሚያደርግ የመፍትሔ ሐሳብ ለማቅረብ የሚያስችለውን ዕቅድ በማውጣት ወደ ተግባር መግባቱን የኮሚቴው ሰብሳቢ መ/ሰ ቆሞስ አባ ቃለጽድቅ ሙሉጌታ (ዶር) እና ዲ/ን ስንታየሁ ምስጋናው ባቀረቡት ሪፖርት ገልጸዋል። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርኩ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሰጡት አባታዊ የሥራ መመሪያ "ምዕመናን ገንዘባቸውን የሚሰጡት ለሃይማኖት ማስፋፊያ እንጂ ለዘረፋ አይደለም” ያሉ ሲሆን ስለሆነም ሕግና ሥርዓትን አክብራችሁ፣ በእውነተኝነት ለቤተክርስቲያን፣ለእግዚአብሔርና ለራሳችሁ ብላችሁ ሳታፍሩና ሳትፈሩ ሥራችሁን ሥሩ። ሥራው ታማኝነት"ጥብዓት" ያስፈልጋል ብለዋል። ከብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ጋር ሆናችሁ በጋራ ሥሩ ያሉት ቅዱስ ፓትርያርኩ ጠንከር ያለ መድኅኒት ሊሆን የሚችል ጥናት ከመፍትሔ ሐሳብ ጭምር እንደምታቀርቡ እምነቴ የጸና ነው ያሉ ሲሆን አያይዘውም የተላካችሁበት ሥራ ያለ ውጤት የሚቀር መሆን የለበትም። ቤተክርስቲያን የተዋረደችበት ጊዜ ማብቃት አለበት ያሉት ቅዱስነታቸው ቤተክርስቲያናችን ራሷን አንጽታ ለሌሎች መልካም አብነት መሆን አለባት ካሉ በኋላ ዓለማዊያን የሚሰሩት ሥህተት እንዳይኖር በተግባር የምታስተምር ተቋም እንጂ በሙስና የምትታማ መሆን የለበትም ብለዋል ሲል የቤተክርስቲያኗ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ አስታውቋል፡፡ ልጆቼ እውነቱን ለማውጣት ታጥቃችሁ ሥሩ በሙስና ህመም ለምትሰቃየው ቤተክርስቲያን መድኃኒት ፈልጉላት በማለት አባታዊ መልዕክታቸውን የቀጠሉት ቅዱስነታቸው አንመረመርም ማለት ራሱን ችሎ ወንጀል ነው ካሉ በኋላ ይህ ሥራ ለእናንተም ታሪክ ነው። እውነትን መሰረት አድርጋችሁ በመሥራት ታሪክ አስመዝግቡ ብለዋል። በመልዕክታቸው ማጠቃለያ ላይም ወደ እዚህ ተቋም የሚገቡ ሁሉ ይህን ያህል ጊዜ ቆይተን ይህን ያህል ይዘን እንውጣ የሚሉ እንጂ ለቤተክርስቲያን የሚቆረቆሩና የሚያስቡ እንዳልሆኑ ይታወቃል ካሉ በኋላ የተሰጣችሁን ኋላፊነት በትጋት ፈጽሙ ብለዋል።
457
14
#በ5 የመስቀል ደመራ በዓል ጥናት ማዕከላት #ከ260 ሰንበት ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ #8100 ሰንበት ተማሪዎች በዝማሪ እና በትርዒት አገልግሎት ላይ ተሳትፈዋል።+3
#በ5 የመስቀል ደመራ በዓል ጥናት ማዕከላት #ከ260 ሰንበት ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ #8100 ሰንበት ተማሪዎች በዝማሪ እና በትርዒት አገልግሎት ላይ ተሳትፈዋል።
655
15
መልዕክት ስለ ርቀት ትምህርት   የመክፈቻ መርሐ ግብር መቼ ነው? ጥቅምት 03 ቀን 2017 ዓ.ም በአባቶች  ፀሎትና ቡራኬ ይከፈታል። ትምህርቶቹ ምንድን ናቸው? ትምህርቶች ሀልዎተ እግዚአብሔር ፣ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ÷ስርዓተ ቤ/ክ÷የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናትና ክርስቲያናዊ ስነ ምግባር የርቀት ትምህርቱ የሚሰጠው እንዴት ነው ? እያንዳንዱ ተማሪ ለርቀት ትምህርቱ ተብለው የተዘጋጁ የመማርያ ሞጁሎችን ከሰ/ት/ቤቱ ያገኛል።በትምህርቱ መጨረሻ የተዘጋጀውን ወርክሽት ወስዶ በመስራት በሚቀጥለው ጉባኤ ያስገባል በተጨማሪም በየወቅቱ መመዘኛ ፈተናዎች ይኖረዋል። ትምህርቱ ምን ያህል ጊዜ ይፈጃል? አንድ ዓመት ከመስከረም 2017-ነሐሴ 2017.ዓ.ም ግሩፕ ውስጥ ገባው ማለት ተመዘገብኩ ማለት ነው? አይደለም  ግሩፑን ጆይን ማድረግ ብቻ መመዝገብ አይደለም ስለሆነ ስም የመኖርያ አድራሻ ና ስልክ ቁጥር አስቀምጡን። ትምህርቱ መች መች ነው የሚሰጠው በወር አንድ ቀን እሁድ ከሰዓት በኋላ 7:00-10:00 በቃሊቲ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ✨✨✨ጥቅምት 03 ይጀምራል ✨✨✨ https://t.me/+54ijITEXeIdjNTNk
519
16
🕊 💖 🕊 [ 🌼 ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ 🌼 ] 🕊 🕊 እንኳን ለቅዱስ እና ታማኝ ሐዋርያ ዮሐንስ ወንጌላዊ የልደቱ መታሰቢያ አደረሳችሁ። ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬ [ መስከረም ፬ [ 4 ] ቅዱ
🕊                    💖                   🕊 [   🌼  ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ  🌼  ]                         🕊                        🕊                    እንኳን ለቅዱስ እና ታማኝ ሐዋርያ ዮሐንስ ወንጌላዊ የልደቱ መታሰቢያ አደረሳችሁ። ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬ [ መስከረም ፬ [ 4 ] ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ልደቱ ] ካህናቱ በሰዓታት ምስጋናቸው የአምደ ሃይማኖት አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫን ቃል አንደበታቸው በማድረግ እንዲህ ያመሰግኑታል። 🕯 [ ዮሐንስ እንደ መላእክት ንጹሕ ነው ፤ ድንግል ዮሐንስ የቅዱሳን መመኪያ ነው ፤ ዮሐንስ በብርሃን መጎናጸፊያ ሐር የተጌጠ ነው ፤ ዮሐንስ የቤተክርስቲያን አርጋኖን ነው በኤፌሶን የአዋጅ ነጋሪ ዮሐንስ ኃጥአን ለምንሆን ለእኛ ይቅርታን ይለምንልን።] [ መከራ ተቀብሎ በመስቀል ላይ ደሙ በፈሰሰ ጊዜ ዮሐንስ ፍቅሩን አላጎደለም። ] [ በወዳጁህ በዮሐንስ ድንግልና በንጽሐ ሥጋውም አቤቱ ይቅር በለን።] 🕊 † በዚህች ዕለት ቅዱሱ ሐዋርያ ከእናቱ ማርያም ባውፍልያ: ከአባቱ ዘብዴዎስ መወለዱን ቤተ ክርስቲያን ታስተምራለች:: የግፍና የመከራ ጽዋዕ በመላባት ዓለማችን… ትዕግሥቱ ፤ ጥላቻና መገፋፋት በነገሠባት ምድራችን… ፍቅሩ ፤ ኃጢአትና መተላለፍ በሠለጠነባት ሕይወታችን… በረከቱ ፤ እርሱ በተወለደባት በዚህች ዕለት በእኛም ልቡና ይወለድ ዘንድ ምልጃው አይለየን። †                       †                        † 🌼                    🍒                     🌼
506
17
https://t.me/+54ijITEXeIdjNTNk
https://t.me/+54ijITEXeIdjNTNk
414
18
🕊 💖 🕊 [ ግፉዕ ወቅቱል ንጹሕ ወቅዱስ ! ] 🕊 ❝ ሰላም ለዮሐንስ ግፉዕ ወቅቱል ንጹሕ ወቅዱስ ወስቡሕ ላእከ ወነቢይ ወሰማዕት ድንግል ካህን ጸያሒ ወሰባኪ መጥምቀ እግዚኡ ❞ [ ጌታውን ያጠ
🕊                    💖                   🕊 [  ግፉዕ ወቅቱል ንጹሕ ወቅዱስ  !  ]                         🕊                        ❝ ሰላም ለዮሐንስ ግፉዕ ወቅቱል ንጹሕ ወቅዱስ  ወስቡሕ ላእከ ወነቢይ ወሰማዕት ድንግል ካህን ጸያሒ ወሰባኪ መጥምቀ እግዚኡ ❞ [ ጌታውን ያጠመቀና ሰባኪ ፤ መንገድ ጠራጊ ፤ ካህን ድንግል ሰማዕት ፣ ነቢይና አገልጋይ ፤ ምስጉን ቅዱስና ንጹሕ ፤ ተገፍቶ የተገደለ ለኾነ ዮሐንስ ሰላምታ ይገባል። ] [ በጣፋጭ አንደበቱ ወንጌልን የሚሰብክ ፣ ቀኙ የሚያቃጥል መለኮትን የዳሰሰች ፣ ጀርባው በግመል ጸጉር የተሸፈነ ፣ የዮሐንስን ደግነት ፈጽመን እንናገራለን ] [ አቤቱ ስላጠመቀኽ ስለ ዮሐንስ ብለኽ በምሕረትኽ ዐስበኝ ፤ ከታናሽነቴ ዠምሮ እስከ ዛሬ አንተን የበደልኹኽን ኅጢአቴን ስለ ርሱ ብለኽ እኔን አገልጋይኽን አንጻኝ አሜን። ] [   ተአምኆ ቅዱሳን   ] 🕊 የቅዱስ ዮሐንስ የጸሎቱ ኃይል የምልጃዉ በረከት ዘወትር በምንማጸነዉ ልጆቹ ላይ አድሮና ጸንቶ ይኑር ለዘለዓለሙ አሜን። 🕊 [ ምትረተ ርዕሱ ለዮሐንስ መጥምቅ ]  🕊 [      🕊   እንኳን አደረሳችሁ   🕊      ] 🕊                        💖                       🕊
415
19
ረስርሳ ድርቀቷ ተወግዶ በአርንጓዴ እጸዋት ተውባ ሜዳው፣ ሸለቆውና ተራራው በአደይ አበባ ተንቆጥቁጠው የሚታዩበት ወቅት በመሆኑ ዕለቱ “እንቁጣጣሽ” የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ በዚህ ወቅት ሕፃናትና ልጃገረዶች ነጭ ባሕላዊ ልብስ በመልበስ፣ ለምለም ቄጤማና አደይ አበባ በመያዝ በአካባቢያቸው በመዞር አዲስ ዘመን መበሠሩን “እንኳን አደረሳችሁ” በማለት በቸርነቱ ዓመታትን የሚያፈራርቀውን እግዚአብሔርን በዝማሬ ያመሰግናሉ፡፡ የዘመን አቆጣጠራችን ከምዕራባውያን ለምን ተለየ? ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ ባሕረ ሐሳብ በሚል መጽሐፋቸው የኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር ከምዕራባውያን የተለየበትን ምክንያት ሲገልጹ “ሮማውያን የሮም ከተማ የተቆረቆረችበትን ዘመን መነሻ ያደርገው ይተቀማሉ፤ ታላቁ እስክንድርም የገነነበት ዘመን መቁጠሪያቸው ሆኖ ነበር” የእኛ ካህናትም ዘመነ እስክንድር በሚል ይጠቀሙበት እንደነበር መጻሕፍት ይመሰክራሉ፡፡ ሶርያውያን የዘመን አቆጣጠራቸውን የሚለኩት በፀሐይ ቆጥረው ለዓመቱ ፫፻፷፭ ቀን ከስድስት አካፍለው ዕለትን መስጠትን ከሮማውያን በተዋሱት ጊዜ የዓመቱን መጀመሪያ አዲስ ዓመት ይሉታል፡፡ በኋላ የሰማዕታት መታሰቢያ እንዲሆን በ፬፻፷ ዓመተ እግዚእ ወደ መስከረም አንድ ቀን ለወጡት፡፡ የሀገራችን ሊቃውንትም አዲስ ዓመታችን መስከረም አንድ ቀን እንዲሆን የወሰኑት ይኸንን በመከተል ነው፡፡ የዓመቱን መጀመሪያ በመስከረም ማድረግን ከሶርያውያንም ሆነ ከግብጾች ብናገኘውም ጀማሪው በ፵፮ ቅድመ ልደተ ክርስቶስ ይገዛ የነበረው ዩልዮስ ቄሣር ስለነበር በዩልዮስ ባሕረ ሐሳብ ይባላል፡፡ ዩልዮስ ቄሣ በ፵፮ ቅድመ ልደተ ክርስቶስ ባወጣው የዘመን አቆጣጠር ሥርዐት መሠረት ዓመቱን ፫፻፷፭ ዕለት ከስድስት ሰዓት አድርጎ ለአራቱ ወራት ፴፣፴ ዕለት ለእንዱ ፳፰ ቀን በአራት ዓመት አንዴ ፳፱ ቀናት ለቀሩት ሰባት ወራት ፴፩፣፴፩ ቀናት መድቦላቸው በ፲፪ ቦታ ከፍሎታል፡፡ አውሮፓውያኑ የሚጠቀሙበትን ይህን አቆጣጠር መነሻ አድርገው ነው፡፡ የእኛ ዘመን አቆጣጠር ከአውሮፓውያን እንዴት እንደተለየ አሥራት ገብረ ማርያም የዘመን አቆጣጠር በሚለው መጽሐፋቸው ሲገልጹ “ዲዮናስዮስ የተባለው የሮም መነኩሴ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ተወለደበት ዘመን በስሌት ለመድረስ የተከተለው መንገድ የታሪክ ክስተትን ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት ዘመን ለመሰወን የታሪክ ክስተትን አልተከተለችም፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን የተከተለችው ከክርስቶስ ልደት በፊት ያለውን 5500 ዘመንን ነው” በማለት የልዩነቱን ምክንያት ይገልጻሉ፡፡                                                                                                                                                                                                                                                         የዘመን አቆጣጠር ልዩነት መነሻው የዚህ ክስተት መሆኑን አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ሲያረጋግጡ “ኢትዮጵያ ዘመነ ብሉይን እንዲህ አስከትላ አምስት ሺሕ አምስት መቶ ዓመት ብላ ስትቆጥር ዘመነ ሐዲስ ልዩ ሆኖ ከማንም ቁጥር አይገጥምም፡፡ ከሌሎች አብያተ ክርስቲያናት ከምስራቆቹም ከምዕራቦቹም ሁል ጊዜ በሰባት ዓመት ታጎድላለች፡፡ ምክንያቱም ባለ ታሪኮችን ትታ ወንጌል ተርጓሚዎችን መነሻዋ ስላደረገች ነው” ብለዋል፡፡ በዚህም መሠረት የኢትዮጵያና የአውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር ልዩነት ሊኖረው ቻለ፡፡                                                                                                                                                                                                                                                 እንደመውጫ                                                                                                                                                                                                                                                  እግዚአብሔር አምላካችን ዕድሜ ለንስሐ ዘመን ለፍስሐ የሚሰጠን መልካም ነገር እንድንሠራበት ነው፡፡ በየዓመቱ አዲስ ዓመት የሚሰጠን የትናንት ስሕተታችንን እንድናርምበት፣ የተጣላን እንድንታረቅ፣ የበደልን እንድንክስ፣ የታረዘን እንድናለብስ፣ የተጠማን እንድናጠጣ፣ የራበውን እንድናበላ እንጂ፤ በኃጢአት ሕይወት እንድንመላለስ አይደለም፡፡ የዘመኑ መቀየር ከቁጥር በዘለለ የእኛው አስተሳሰብ እንዲቀየር ነው፡፡ ለሥጋዊ ኑሮአችን መሳካት በእቅድ እንደምንመራው ሁሉ ለመንፈሳዊ ሕይወታችን እናስብ፤ ቃለ እግዚአብሔር ለመማር፣ ንስሐ ለመግባት፣ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለመቀበል መንፈሳዊ እቅድ እናውጣ! ተግባራዊ ለማድረግም ጥረት እናድርግ፡፡ ከዘመን ወደ ዘመን የምንሸጋገረው ቅዱሳን መላእክት በሚለምኑልን የብደር ዕድሜ እንደሆነ እንረዳ፡፡ አምላካችን ከእኛ ሕይወት ፍሬ ለማግኘት በልጅነታችን፣ በወጣትነትና በሽምግልና ዕድሜያችን ሦስት ጊዜ መጣ፤ ፍሬ ሃይማኖትና ምግባር አጣብን አትክልተኞቹን ቅዱሳን መላእክትን “ስለምን ደግሞ መሬቱን ታጎሳቁላለች?” ቢላቸው “ጌታ ሆይ ዙርያዋን እስክኮተኩትላትና ፋንድያ እስካፈስላት ድረስ በዚች ዓመት ደግሞ ተዋት” እያሉ በለመኑት የብድር ዕድሜ ነው አዲስ ዓመቱን ለማየት የቻልነው /ሉቃ. ፲፫፥፮-፱/፡፡ በተሰጠን የንስሐ ዕድሜ መልካም ነገር ለመሥራት እንነሣ፤ በስንፍና ያሳለፍነው ጊዜ ይብቃን! ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በመልእክቱ “የአሕዛብን ፈቃድ ያደረጋችሁበት በመዳራትና በሥጋ ምኞትም በስካርም በዘፈንም ያለ ልክም በመጠጣት ነውርም ባለበት ጣዖት ማምለክ የተመላለሳችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃልና”  እንዲል /፩ኛ ጴጥ. ፬፥፫/፡፡ አዲሱን ዓመት ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሔድ፣ አቅመ ደካሞች የኾኑ ወገኖቻችን ጋር አብረናቸው በዓል እናክብር፤ ያን ጊዜ እኛ በሕይወት ተቀይረን አዲሱ ዓመት መቀበላችን እውነት ይኾናልና፡፡                                                                   መልካም አዲስ ዓመት ይሁንልን!                                     ወስብሐት ለእግዚአብሔር ዋቤ መጻሕፍት                ✍️  መጽሕፍ ቅዱስ                ✍️  ድርሳን ዘቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ                 ✍️  የቤተክርስቲያን ታሪክ በኢትዮጵያ                 ✍️  ባሕረ ሐሳብ (አቡሻኸር)                 ✍️  መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ                 ✍️  መርሐ ዕውር                 ✍️  ሐመር መጽሔት መስከረም 2000 ዓ.ም
268
20
ቅዱስ ዮሐንስ፡ ርእሰ ዐውደ ዓመት                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                          ዘመን አልፎ ዘመን ሲተካ የመሸጋገሪያው ዕለት በየዓመቱ “ቅዱስ ዮሐንስ” እየተባለ ይጠራል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የዘመን መለወጫ፣ ዕንቁጣጣሽ፣ ርእሰ ዐውደ ዓመት ይባላል፡፡ ርእሰ ዐውደ ዓመት የበዓላት ሁሉ የበላይ፣ ራስ ማለት ነው፡፡ ይህ በዓል የዓመት መጀመሪያ እንደመኾኑ መጠን በየዓመቱ ወሮች በመጀመሪያ ቀን ይከበራል፡፡                                                                                                                                                                                                                                                      ቅዱስ ዮሐንስ ለምን ተባለ?                                                                                                                                                                                                                                                   ቅዱስ ዮሐንስ ተብሎ የተሰየመው በነቢዩ ዘካርያስ ልጅ በመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እንጂ በሐዋርያው (ወንጌላዊው) ቅዱስ ዮሐንስ አለመሆኑን ልብ ማለት ይገባል፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው፡- ቅዱስ ማርቆስ ወንጌሉን ሲጽፍ “የእግዚአብሔር ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል መጀመሪያ እነሆ መንገድህን የሚጠርግ መልእክተኛዬን በፊትህ እልካለሁ፡፡ የጌታን መንገድ አዘጋጁ፡፡ ጥርጊያውን አቅኑ” እያለ “በምድረ በዳ የሚጮኸ ሰው ድምፅ” ተብሎ በኢሳይያስ እንደተነገረ የነቢዩ ዘካርያስ ልጅ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በዘመነ ብሉይ መጨረሻና በዘመነ ሐዲስ መጀመሪያ ላይ ተነስቶ “መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ!” እያለ ስለ ክርስቶስ አዳኝነት እየመሰከረ በምድረ በዳ የንስሐን ጥምቀት እያጠመቀ መጣ ብሎ ለዘመነ ወንጌል የመጀመሪያ ምዕራፍ ትምህርትና ተግሳጽ እንዳደረገው ቅዱስ ማርቆስ በወንጌሉ ይነግረናል፡፡ /ማር. ፩1፥፲፬፤ ኢሳ. ፵፥፫-፬/፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ በመጨረሻም  በሄሮድስ ትዕዛዝ ራሱን የተቆረጠ ታላቅ ሰማዕት ነው፡፡  የመጥምቁ ዮሐንስ ተግባር ለዘመነ ወንጌል በር ወይም መነሻ ሆኖ መገኘቱን በመረዳት የቤተ ክርስቲያን አበው የበዓላትን ድንጋጌ በወሰኑበት አንቀጽ የመጥምቁ ዮሐንስ መታሰቢያ በዓል የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት በሚከበርበት መስከረም አንድ ቀን እንዲከበር በየዓመቱ የዘመኑ መጀመሪያ በእርሱ ስም እንዲጠራ እንደወሰኑ የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ መጽሐፍ ይነግረናል፡፡ /ድርሳን ዘቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ገጽ ፩-፫/፡፡ ዘመን መለወጫ  በኢትዮጵያ ዘመን መለወጫ በመስከረም ወር የሆነበትን ምክንያት ሊቃውንቱ ሲያትቱ ብርሃናት ፀሐይ፣ ጨረቃ፣ ክዋክብት የዓመት ዑደታቸውን በጳጉሜ ጨርሰው በመስከረም ወር ስለሚጀምሩ ነው፡፡ ያን ጊዜ ሌሊቱ ከቀኑ ጋር እኩል ፲፪ ሰዓት ይሆናል፡፡ ዓመቱን ጠንቅቀው ሲቆጥሩ ፫፻፷፬ ቀናት ይሆናል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ “ለዘመን መታወቂያው ይሆን ዘንድ ፀሐይና ጨረቃ ከዋክብትንም ፈጠረ” ይላልና /ሔኖክ. ፳፩፥፵፱/፡፡ በሌላ በኩልም በዘመነ ኖኅ በፍል ውኃ አጥለቅልቆ በኃጢአት ሕይወት ይኖሩ የነበሩት የኖኅ ዘመን ሰዎች ቀጥቶ ካጠፋ በኋላ ከንፍር ውኃ ምድር የተገለጠችበት ወር በመኾኑ ነው /ኩፋሌ. ፯፥፩/፡፡ “በመጀመሪያው ወር ምድር ታየች የንፍር ውኃም ከምድር ደረቀ” የሚለውን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ቃል መሠረት አድርገው የአቡሻኸር ሊቃውንት የዘመን መለወጫን ታሪካዊ አመጣጥ ያስቀምጣሉ፡፡ የቤተ ክርስቲያኒቱን ቀኖናዊ ሥርዐት ያጠኑ ሊቃውንት ደግሞ አዲስ ዓመት መስከረም አንድ ቀን መሆኑን አስመልክተው በክታባቸው እንዳስቀመጡት በአራቱ ወንጌላውያን ዘመኑን ይከፍሉታል፡፡ ምክንያቱም በዘመነ ዮሐንስ ተፀንሶ በዘመነ ማቴዎስ ተወልዶአል፡፡ በዘመነ ማርቆስ ተጠምቋል፡፡ በዘመነ ሉቃስ ተሰቅሎ ዓለምን ከፍዳና ከመርገም ነጻ አውጥቷል፤ እያሉ ታሪካዊ ሐረጋቸውን ጠብቆ አራቱ ወንጌላውያን ተከትለው ያለ እንቅፋት እንደሚጓዙ ያስረዳሉ፡፡                                                                                                                                                                                                                                                        እንቁጣጣሽ                                                                                                                                                                                                                                                     እንቁጣጣሽ የተባለበት ምክንያት አንደኛ “እንቁ – ዕፅ አመጣሽ” ብሎ የአበባውን መፈንዳት ያመለክታል፡፡ ሁለተኛ ኖኅ ለሦስቱ ልጆቹ አህጉራትን በዕጣ ሲያካፍላቸው አፍሪካ ለካም ደረሰችው፡፡ በአፍሪካ ምድርም ሲገባ በመጀመሪያ ያረፈው በኢትዮጵያ ነበር፡፡ ሀገሪቱም በአደይ አበባ አሸብርቃ ነበር፡፡ ወሩ ወርኀ መስከረም በመኾኑ ደስ ብሎት “እንቁ ዕጣ ወጣሽልኝ” በማለት ይህችን ወቅት እንቁጣጣሽ ብሏታል፡፡ ሦስተኛው /፩ ነገ.፲፥፩-፲/ ኢትዮጵያዊቷ ንግሥት ሣባ (አዜብ) ጋር የተያያዘ ትውፊት ነው፡፡ የንጉሡን ጥበብ ከመስማት ማየትን መርጣ ወደ ንጉሥ ሰሎሞን ከብዙ ሠራዊቶቿ ጋር የእጅ መንሻ በመያዝ ሄደች፡፡ ንጉሡም በደስታ ተቀብሎ እርሱም “እንቁ ለጣትሽ ጌጥ ይሁንሽ” በማለት ኢትዮጵያዊቷ ንግሥት ሳባ የጠቢቡ ሰሎሞንን ዝና ሰምታ ኢየሩሳሌም ተጉዛ ስትመለስ ንጉሥ ሰሎሞን  “እንቁ ለጣትሽ (ለጣትሽ እንቁ) ጌጥ ይሁንሽ” በማለት አራት ዓይነት ቀለም የሚታይበት በቀንና በሌሊት የምታበራ ቀለበት ሰጥቷታል፡፡ ወሩም ወርኀ መስከረም ነበር፡፡ ከዚህ በመነሣት እንቁጣጣሽ የሚለው ስያሜ ወጥቷል፡፡ ይህን ታሪክ መነሻ አድርገው “እንቁጣጣሽ” የሚለው ስያሜ ከዚያ እንደመጣ የታሪክ ድርሳናት ያስረዱናል፡፡ በኢትዮጵያ የዘመን መለወጫ ዕለት ምድሪቱ በክረምቱ ዝናብ
244