fa
Feedback
Ethiopian Catholic Charismatic

Ethiopian Catholic Charismatic

رفتن به کانال در Telegram
805
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
-130 روز
آرشیو پست ها
የመጀመሪያ ቀን ኖቬና ትምህርት በአቶ ሰለሞን ደጀኔ ርዕስ : የጌታ ኢየሱስ እና የመንፈስ ቅዱስ የጋራ ተልዕኮ የመንፈስ ቅዱስ ተልዕኮ በሕይወታችን በምንም ዓይነት ነገር እንዳንደገፍ ሊረዳን ሊያሳውቀን ነው። የትኛውም የፀጋ ስጦታ የእኛ የፀሎት ውጤት የእኛ መንፈሳዊነት ትጋት ውጤት ሳይሆን የእግዚአብሔር ታላቅ ምህረት : ፀጋ : ደግነቱ ሩሁሩነቱ እና መልካምነቱ መሆኑን መንፈስ ቅዱስ ያስረዳናል። የመንፈስ ቅዱስ ሙላት የአንድ ቀን ክስተት ሳይሆን በየዕለቱ የምንሞላው በየዕለቱ የምንጠጣው ነው። የመንፈስ ቅዱስ ተልዕኮ ክርስቶስ ኢየሱስን ማክበር ነው። ክርስቶስ ኢየሱስን መምሰላችን አካላዊ ሳይሆን መለኮታዊ ነው። መንፈስ ቅዱስ በፀጥታ ውስጥ ሆነን በግላችን የምናዳምጠው የሚያዳምጠን ነው። መንፈስ ቅዱስ ስለራሱ አይናገርም ነገር ግን በሕይወታችን ውስጥ ግራ በገባን እና አቅጣጫ በሚያስፈልገን የሕይወት ምልልስ ውስጥ መልካም የሆነውን የሕይወት አቅጣጫ ያሳየናል። መንፈስ ቅዱስ ወደ እውነት ሁሉ የሚመራን ሲሆን ይህ እውነት በሕይወታችን የሚገለጠው በወንድሞቻችን እና በእህቶቻችን ፊት ላይ ክርስቶስን ማየት ስንችል ነው ይሄን የሚያስችለን ደግሞ የመንፈስ ቅዱስ ምሪት ነው። መንፈስ ቅዱስ በሕይወት ውስጥ በቤተሰብ በስራ ቦታ ሕብረት በምናደርግበት ቦታ ሁሉ ትክክለኛ ውሳኔ በሚያስፈልግበት ሁኔታ ውስጥ በትክክል በታማኝነት እንድንወስን ይረዳናል።

የተወደዳችሁ የማህበራችን አባላት በሙሉ እንደምን አደራችሁ የፊታችን ቅዳሜ እና እሁድ በቤተክርስቲያናችን በተዘጋጀው ፕሮግራም (Catholympic for unity)ላይ ተሳታፊ ስለሆንን እያንዳንዱ አባል በቅዱስ ዮሴፍ ት/ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ ለሁለት ቀናት በሚኖረው ዝግጅት መገኘት መንፈሳዊ ግዴታ ያለብን መሆኑን አውቀን እንድንገኝ አደራ እንላለን:: በዚሁ ምክንያት ሚያዚያ30 መደበኛ ፕሮግራማችን እንደማይኖር በሚቀጥለው ሳምንት በወርሃዊ ፕሮግራማችን እንደምንቀጥል አስቀድመን እናሳውቃለን:: የተባረከ ቀን ይሁንላችሁ::

photo content

#በንስሐ_መመለስ “በስሜ የተጠሩት ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ፥ ፊቴንም ቢፈልጉ፥ ከክፉ መንገዳቸውም ቢመለሱ፥ በሰማይ ሆኜ እሰማለሁ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፥ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ።” — 2 ዜና 7፥14 የዳዊት ትልቁ ስኬት እግዚአብሔርን በመስማት በንስሐ የመመለስ ሕይወት ሲሆን የሳኦል ትልቅ ውድቀት እግዚአብሔርን ከመስማት ይልቅ ልቡን መስማቱ የሄደበት መንገድ ነው። 🧏ዛሬስ እኛ የትኛውን እየተከተልን ነው ማንን እየሰማን ነው። እግዚአብሔርን ወይስ ራሳችንን? ስለንስሐ ምን እናስባለን? 👉አንዳንዶቻችን ራሳችንን መመርመር ግዜ ያጣን 👉አንዳንዶቻችን ኃጢአትን ምንም እንዳይደለ የቆጠርን 👉አንዳንዶቻችን ሳንፀፀት ሳንመለስ እግዚአብሔር ፍቅር ስለሆነ ትቶኛል ብለን ለራሳችን በሚሆን መንገድ የምናመቻምች 👉አንዳንዶቻችን በካህን ፊት መናዘዝ እንደማያስፈልግ በመቁጠር በኃጢአታችን መዋረድ ያልፈለግን ራሳችንን የምንሸነግል። 👉አንዳንዶቻችን ኃጢአት በመለማመድ ኃጢአቱ ፅድቅ የመሰለን። ለማንኛውም ተፀፅቶ ራስን አዋርዶ በንስሐ በመመለስ የእግዚአብሔርን ፀጋ ለመቀበል ራስን ማዘጋጀት መልካም ነውና ራሳችንን እናዘጋጅ። ንስሐ እረፍት ይሰጣል ሰላም ይሰጣል ደስታ ይሰጣል ያሳርፋል አካሄድን ያቀናል። https://t.me/eccrm https://t.me/eccrm

ፊልጵስዩስ 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁵ በክርስቶስ ኢየሱስ የነበረ ይህ አሳብ በእናንተ ዘንድ ደግሞ ይሁን። ⁶ እርሱ በእግዚአብሔር መልክ ሲኖር ሳለ ከእግዚአብሔር ጋር መተካከልን መቀማት እንደሚገባ ነገር አልቈጠረውም፥ ⁷ ነገር ግን የባሪያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አደረገ፥ ⁸ በምስሉም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ፥ ለሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ። ⁹ በዚህ ምክንያት ደግሞ እግዚአብሔር ያለ ልክ ከፍ ከፍ አደረገው፥ ከስምም ሁሉ በላይ ያለውን ስም ሰጠው፤ ❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤ የመጨረሻው ደስ የሚለው የክርስትና ጉዞ መጨረሻው የሚያምረው በፍቅር በመመላለስ ሰዎችን ለመጥቀም የምንኖረው ሕይወት ነው እንጂ በብዙ እውቀትና በብዙ የፀጋ ስጦታ መታጀብ አይደለም። ዝቅ ብለን ክርስቶስን በመምሰል ሰዎችን መጥቀም ከቻልን እውነትም በጌታ ነን እውነትም የክርስቶስ ታማኝ ደቀ መዝሙር ነን። “በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ፥ ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም።” — ማቴዎስ 7፥21 ማቴዎስ 7 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²² በዚያ ቀን ብዙዎች፦ ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ በስምህ ትንቢት አልተናገርንምን፥ በስምህስ አጋንንትን አላወጣንምን፥ በስምህስ ብዙ ተአምራትን አላደረግንምን? ይሉኛል። ²³ የዚያን ጊዜም፦ ከቶ አላወቅኋችሁም፤ እናንተ ዓመፀኞች፥ ከእኔ ራቁ ብዬ እመሰክርባቸዋለሁ። የምንኖረው በተግባር የምንገልፀው ክርስትና ይኑረን። https://t.me/eccrm https://t.me/eccrm

#የማለዳ_የማሰላሰያ_ሀሳብ በትጋት የሚገኝበትን አስደሳች ሕይወት ማርቆስ 13 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ³⁶ ድንገት መጥቶ ተኝታችሁ እንዳያገኛችሁ ስለዚህ ትጉ። ³⁷ ለእናንተም የምነግራችሁ ለሁሉ እላለሁ፤ ትጉ።

ሕይወት በመንፈስ ቅዱስ ማነቃቂያ ሰሚናር #ምዝገባ_ተጀመረ ✅ ከየካቲት 29 እስከ መጋቢት 3 በሞጆ ሱባኤ ሴንተር ✅ መጋቢት 4 ሙሉ ቀን ልዪ የማነቃቂያ ፕሮግራም በአዲስ አበባ ✅ በእግዚአብሔር ቃል መንፈሳዊነቴን መቀየር እፈልጋለሁ ለምትሉ ልዩ እድል ነው። ለመመዝገብ ። 0910056879 0991172268 ለሳምንት ቆይታ ክፍያ 1000

“ሕግህ ለእግሬ መብራት፥ ለመንገዴ ብርሃን ነው።” — መዝሙር 119፥105 ብርሀናችንን ተረድተን የሕይወት ጉዞ እንጀምር የውጭውን ጨለማ ማሸነፍ የምንችልበት አስደናቂ የውስጥ ብርሀን እኛ ውስጥ አለ። እግዚአብሔር ይመስገን። https://t.me/eccrm https://t.me/eccrm

“በውኃ አጠገብ እንደ ተተከለ፥ በወንዝም ዳር ሥሩን እንደሚዘረጋ ሙቀትም ሲመጣ እንደማይፈራ ቅጠሉም እንደሚለመልም፥ በድርቅ ዓመትም እንደማይሠጋ ፍሬውንም እንደማያቋርጥ ዛፍ ይሆናል።” — ኤርምያስ 17፥8 @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm

#የማለዳ_የማሰላሰያ_ሀሳብ “ምላሴ ጽድቅህን ሁልጊዜም ምስጋናህን ይናገራል።” — መዝሙር 35፥28 🙏ምስጋና ✅ምስጋና በሕይወት ውስጥ የተሰጠንን መልካም ነገር የሚያበዛ መሳሪያ ነው። ✅በጣም ትንሽ ለሚባሉ ነገሮች እንኳን ምስጋና ስታቀርብ ያመሰገንካቸው ነገሮች በዝተው ይመጡልሀል። ✅አብዝተህ አመሰግናለሁ ባልክ ቁጥር የማመስገኑ ስሜት ውስጥ አየሰረፀ ይሄዳል ሕይወትም ጤናና ደስታ ታላብስሀለች። ✅በሕይወት ውስጥ እንዲሆንልህ የምትመኘውን ነገር ቀድመህ እንዳገኘኸው ቆጥረህ አመስገን። ✅ለሆነልህ ሁሉ በቂ ምስጋና ማቅረብ የተደረገልህ ነገር ስለመቀጠሉ ማረጋገጫ ያስገኝልሀል። ✅ምስጋና ከማይጠቅሙ አስተሳሰቦች ወጥተህ የፍቅርን ኃይል ለመጠቀም የሚያሸጋግር ድልድይ ነው። 🙏ምስጋና የቆሰለውን የሚጠግን መድሀኒት ነው። 🙏ሕይወት ሙሉ ልትሆን የምትችለው በምስጋና ብቻ ነው። 🙏ዛሬ መለማመድ ጀምር መልካም ላደረጉልህ ሰዎች ደውለህ ወይም በtext አመሰግናሁ በላቸው። ዛሬ በጥቂቱም ላስተናገዱህ ሰዎች አመስግን ታክሲ ተሳፍረህ ላገለገለህ ረዳት አመሰግናለሁ በለው ስለሰውነትህ አመሰግናለሁ በል። ደስታህን ምትፈጥረው ጤንነትህን ምትጠብቀው አንተው ነህ። @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm

“ድንጋዩንም አነሡት፦ ኢየሱስም ዓይኖቹን ወደ ላይ አንሥቶ፦ አባት ሆይ፥ ስለ ሰማኸኝ አመሰግንሃለሁ።” — ዮሐንስ 11፥41 @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm

#የማለዳ_የማሰላሰያ_ሀሳብ ሮሜ 4 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁹ የመቶ ዓመትም ሽማግሌ ስለ ሆነ እንደ ምውት የሆነውን የራሱን ሥጋና የሳራ ማኅፀን ምውት መሆኑን በእምነቱ ሳይደክም ተመለከተ፤ ²⁰-²¹ ለእግዚአብሔርም ክብር እየሰጠ፥ የሰጠውንም ተስፋ ደግሞ ሊፈጽም እንዲችል አጥብቆ እየተረዳ፥ በእምነት በረታ እንጂ በአለማመን ምክንያት በእግዚአብሔር ተስፋ ቃል አልተጠራጠረም። አብርሀም እንደተደረገለት ቆጥሮ እግዚአብሔርን አስቀድሞ ያመሰግን ነበር። የምትፈልጉትን ነገር ከጠየቃችሁ በኋላ የምታደርጉት ነገር በሙሉ ከምኞታችሁ ጋር መመሳሰል አለበት። ምኞታችሁ ከድርጊታችሁ ጋር መቃረን የለበትም። የጠየቃችሁትን ለመቀበል ዝግጁ ስትሆኑ ያኔ ትቀበላላችሁ። የምትፈልጉት ነገር አለ? እንዳገኛችሁት አስቡና ማመስገን ጀምሩ ቀናችሁ ብሩህ ይሆናል። በማመስገን የምትፈልጉትን ነገር ሳቡ። https://t.me/eccrm https://t.me/eccrm

“ነገር ግን እውነትን በፍቅር እየያዝን በነገር ሁሉ ወደ እርሱ ራስ ወደሚሆን ወደ ክርስቶስ እንደግ፤” — ኤፌሶን 4፥15 @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm