cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

🥀ኑ ስለ ዲናችን እንማማር ☪️

ዲናችንን እንወቅ ስለ ነብያት ስለ ሰሀቦች ስለ ደጋግ ባሮች ቁርዓን ሀዲስ እና ስለ ሙጃሂዶች ታሪክ ታሪካችንን እንወቅ አኩሪ ታሪክ አለንና🥰

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استزبان مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
پست‌های تبلیغاتی
191
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

ወድቃቹ እንዳትቀሩ! ዱኒያ መሰናክሏ ብዙ ነዉ። የአንዱን ስናልፍ ሌላዉ ይተካል። አንዱን ስንሻገር ሌላ ይከተላል። አንዱን ስንዘል አንደኛው ይመጣል። ዱንያ ሁሉም መሰናክሎቿ አይጥሉም፤ ሁሉም መሰናክሎቿም አይታለፉም። ብዙዎቿን እናልፍ ይሆናል፤ አንድ ነገር ግን አንድ ቀን ግን ከአንዱ ላይ የምንወድቅበት ሁኔታ ይኖራል። ከዉድቀት ሁሉ የሚከፋዉ በሀጢያት መውደቅ ነዉ። ከአወዳደቅ ሁሉ አስፈሪዉ ደግሞ ወድቆ መቅራት ነዉ። እናም ወድቀህ እንዳትቀር ወዳጄ ወድቀሽ እንዳትቀሪ እህቴ! አትጨነቁ ከሚለው መፀሀፍ የተወሰደ!
نمایش همه...
​​#አንዲት_ገራሚ_ቂሷ #ነብዩ በሂወት በነበሩበት ወቅት አንድ ለማኝ ወደ ቤታቸው ይመጣል… #ከዛም አንድ ልብስ ስጡኝ በማለት ሲጠይቃቸው አዛኙ ነብይ አኢሻን አንሺና አንዱን ስጪው ይሏታል… #አኢሻም አንድ ልብስ ታነሳና እንካ ስትለው ይህን አልፈልግም ይላታል እሷም ቀይራ ሌላ ልብስ እንካ አለችው እሱም ይህንንም አልቀበልም ይላታል አሁንም ሶስተኛ ሌላ ልብስ እንካ ስትለው ይህንም አልፈልግም ይላታል… #በመጨረሻም አኢሻ እና የቱን ነው የምትፈልገው ስትለው እሱም ነብዩ ትናንትና ለብሰውት የነበረውን ቀሚስ (ጀላብያ) ነው የምፈልገው ሲላት… #አኢሻም እሱንማ ነብዩ በጣም ስለሚወዱት አልሰጥህም ስትለው ነብዩ ሰሟትና ስጪው ሲሏት አንስታ ስትሰጠው ተቀብሎ ሄደና… #ገቢያ ቦታ ይዞት ወጣና ከፍ ባለ ድምፅ ማን ነው የነብዩ ሙሀመድን ልብስ መግዛት የሚፈልግ በማለት መጣራት ጀመረ… #በግዜውም አንድ አይኑ የጠፍ ሰው ነበር ይህም ሰውዬ የነብዩ ሙሀመድ ልብስ ገቢያ መውጣቱን ሲሰማ ባሪያ ነበረውና ባሪያውን እንዲህ አለው…… #የነብዩ ሙሀመድ ልብስ ገቢያ ወጥቷልና እሱ በሚጠራበት ዋጋ ቢያስወድደውም እንኳን ገዝተህ ካመጣህልኝ ነፃ አወጣሀሉ ይለዋል… #ባሪያውም በፍጥነት ገቢያ ቦታ ሂዶ ልብሱን በጣም በውድ ዋጋ ገዝቶት ተመልሶ ለአሳዳሪው ይሰጠዋል የሸጠውም ሰውዬ ከበረ… #ልብሱን አምቶ ለአሳዳሪው ሲሰጠው ቃል ስለገባለት ባሪያውን ነፃ አወጣው… #ሰውዬውም የነብዩን ልብስ በእጁ ያዘና እንዲህ ሲል ዱኣ አደረገ "ያ አሏህ የነብዩሏህ የእቁብን አይን በነብዩሏህ ዩሱፍ ልብስ አማካኝነት እንዳበራህላች ሁሉ የኔንም በነብዩ ሙሀመድ ልብስ ይሁንብህ አብራልኝ ብሎ ፊቱን ሲያብስበት አይኑ በራለት ከዛ… #የነብዩ ሙሀመድን ልብስ ይዞ ሰውዬው ወደ ነብያችን ሄደና ሀድያ ብሎ ያንን ልብስ ሲሰጣቸው ነብዩን ከየት አገኘህው ሲሉ ጠየቁት… #እሱም ይቺ ልብሳቹህማ ድሃ የነበረን ሰው አክብራ ባሪያን ሁር አስብላ (ነፃ አስወጥታ) አይኑ የጠፍን አይኑን አብርታ ይሄው ተመልሳ መጣችላቹህ አላቸው… #ከዛም ነብዩ ወደ አኢሻ ዞሩና አየሽ አይደል በመስጠትሽ አማካኝነት ይህ ሁሉ ሰው ተጠቀመ አሏት። ❤️ሀቢቡና ሰለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም❤️
نمایش همه...
ጥያቄ፡- ባሏ የሞተባት ሴት በ“ዒድ-ዳ” ጊዜዋ ላይ የምትከተለው የአለባበስ እና የጌጥ ስርዐት ምንድን ነው? በዒድ ቀንስ የተለየ ብይን ይሰጥ ይሆናል?  መልስ፡- ባሏ የሞተባት ሴት በዒድ-ዳ ጊዜዋ ላይ (አራት ወር ከአስር ቀን) እያለች ለጌጥ የሚሆኑ አልባሳትን ትከለከላለች። ያለምክንያት ከቤት መውጣትም ትከለከላለች። ነገርግን የተለየ ጌጥነት የሌለውን ጥሩ ልብስ ግን መልበስ ትችላለች። የአካሏን ንፅህናም ትጠብቃለች። ፀጉሯን ልታፀዳና ልታበጃጅ፣ ጥፍሮቿን ልትቆርጥ፣ ከሰዎች ጋር ልታወራ፣ አስፈላጊ ከሆነም ወንዶችን ልታነጋገር ትችላለች። እነዚህ ነገሮች ብዙዎች የሚከለከሉ ናቸው ብለው የሚያስቧቸው ናቸው። ነገርግን አስፈላጊ ላልሆነ ምክንያት ከቤት መውጣት የለባትም። ለምሳሌ ፍርድ ቤት ጉዳይ ካላት ወይም ሆስፒታል መሄድ ካስፈለጋት ትሄዳለች። ለንግድ፣ ለስራ እና ለሌሎችም ዱንያዊ ጥቅም ላላቸው ጉዳዮቿ መውጣት ትችላለች። ይህ ሁሉ አይከለከልም። ምክንያቱም ጃቢር ኢብኑ ዐብዲላህ እንዲህ ሲሉ ዘግበዋል፡- “አክስቴ በሦስት ተፈታች። ከዚያም የተምር ፍሬዎቿን ለማስለቀም ወጣች። አንድ ሰውዬ ግን መንገድ ላይ አገኛትና ከለከላት። ይህንንም ለነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ነገረች። እርሳቸውም፡- بلَى، فَجُذِّي نخلَكِ, فإنَّكِ عَسَى أَنْ تَتَصَدَّقي أو تَفْعَلِي معروفًا‎ “የለም! ተምርሽን አስለቅሚ። ምናልባት ሶደቃ ታደርጊ ወይም መልካም ትሰሪ ይሆናል።” በዚህ ረገድ የዒድ ቀን የተለየ አይደለም። ዒዳዋ እስካላለቀ ድረስ በዒድ ቀንም በሌላ ጊዜ ላይ የምትከተለውን ስርዐት ነው የምትተገብረው። አላህ የበለጠ ያውቃል
نمایش همه...
✅ተብሊግ የዚህ ፊርቃ በ …… አመተ ሂጅራ በሙሃመድ ኢልያስ ተመሰረተ፡፡ የሙሃመድ ኢልያስን እምነት መረዳት በቀላሉ የፊርቃው እምነቶች ምን ሊሆኑ እንደሚችሉ ለማወቅ ስለሚረዳ እነሆ  ሱፍያ ……  ወህደተል ዉጁድ እምነት ….. ተብሊግ ከሚታወቁባቸው መርሆዎች ውስጥ ሲፈቱ ሲታ ይገኝበታል፡፡ ሲፈቱ ሲታ ማለትም የሚከተሉት ናቸው ከሊመቱ ጠይባ (ላኢላሃ ኢለላህ ሙሃመዱ ረሱሉሉላህ) 2) ኢልም 3) ዚክር 4) ኢክራመል ሙስሊሚን 5) ንያን ማስተካከል ለአላህ ማጥራት 6) ሁሩጅ ፊሰቢሊላህ እያንዳንዱን መሰረቶች እንዴት እንደሚረዱት ማየቱ የወደቁበትን ችግር በቀላሉ ለመረዳት ይረዳል፡፡ 1) ከሊመቱ ጠይባ (ላኢላሃ ኢለላህ ሙሃመዱ ረሱሉሉላህ) ላኢላሃኢለላህን የሚተረጉሙት በተውሂደ ሩቡብያ ነው፡፡ ከአላህ ውጭ የሚያበላ የለም፤ ከአላህ ውጭ የሚያጠጣ የለም፤ ከአላህ ውጭ ጌታ የለም፤ ከአላህ ውጭ ፈጣሪ የለም፤ ከአላህ ውጭ ሰማይና ምድርን የፈጠረ የለም፤ ከአላህ ውጭ የሚገድል የለም እነዚህ ሁሉ የአላህን ጌትነት የሚጠቁሙ ናቸው እንጂ ተመላኪነቱን አይጠቁሙም፡፡ ይህንንም የመጀመሪያዎቹ የመካ ሙሽሪኮች እንኳን አያስተባብሉትም ነበር ለዚህም ማስረጃው የአላህ ቃል ነው ። ተብሊጎች ተውሂድን ካለማወቃቸው፤ ኡማውን ይከፋፍላል፤ ሰዎችንን ያሸሻል በማለት የተውሂድ ሰዎችን እንደጠላት ማየታቸው ሳይበቃቸው የአላህ ወዳጅ የሆኑትን የነብያት ሁሉ አባት የተውሂድ አባት ኢብራሂም (አለይሂ ሰላምን) እንዲህ በማለት መናገራቸው ታላቅ የሆነ በደል ውስጥ ከቷቸዋል ‹‹ከኢብራሂም ዳዕዋ የኛ ዳዕዋ ይሻላል፡፡ እሱ ጣኦታቱን ሲያፈርስ ሂክማ አልተጠቀመም›› ስለ ተብሊጎች ፦ وأما مجاعة التبليغ فإليك ما كتبه األخ الفاضل حممد بن عبد الوهاب الوصايب فقال - رمحه ه ደካማም ብቻ ሳይሆን ምንም አይነት ሸሪዐዊ መሰረት የሌላቸውን የቅጥፈት ሀዲሶችን በመቀበል አምልኮት ይፈጽማሉ፡፡ يعملون بالأحاديث الضعيفة بل والموضوعة وما لا أصل لها. በጣም በርካታ ቢድዓዎች ይገኙባቸዋል፡፡ ኧረ እንዳውም የደዕዋቸው የጀርባ አጥንት ራሱ በተወሰነ የጊዜ ገደብ ኹሩጅ መውጣት ነው፡፡ በየወሩ ሶስት ቀን ኹሩጅ በመውጣት፣ በአመት ዉስጥ አርባ ቀንን ዉጭ በማሳለፍ እንድሁም ከእድሜ ዉስጥ አራት ወራትን ኹሩጅ በመውጣት ላይ የተመሰረተ ነው፡፡ በየሳምንቱ ሁለት የጀመዓ እንቅስቃሴዎችንም ያደርጋሉ፡፡ አንደኛው በሚሰግዱበት መስጅድ የሚፈጸም ጀውላ ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ከመስጅድ ዉጭ ያለ ጀውላ (እንቅስቃሴ) ነው፡፡ توجد فيهم بدع كثيرة, بل إن دعوتهم مبنية على البدع إذ عمود دعوتهم الفقري هو الخروج بهذا التحديد: من كل شهر ثلاثة أيام , وفي السنة أربعون يوماً , وفي العمر أربعة أشهر , وفي كل أسبوع جولتان : جولة في المسجد الذي يصلي فيه, والثانية متنقلة ؛ ተውሂድን ማስተማር ሰዎችን እንደሚያርቅና እንደሚበታትን ያምናሉ ፡ ፡ ● ሱንና ማስተማርም ኡማውን እንደሚያለያይ ያምናሉ፡፡ በሁደይዳ ከተማ የሚገኘው መሪያቸውም ሰዎችን ከሚበታትን ሱንና ይልቅ ሰዎችን የሚያሰባስብ ቢድዓ የተሻለ ነው ይላል፡፡ يرون أن الدعوة إلى السنة تنفير للأمة. يقول أميرهم بالحديدة: بدعة تجمع الناس خير مِن سنة تفرق بينهم. ሰዎች ጠቃሚ እውቀትን በመቅሰም ላይ በጣም ቸልተኛ እንድሆኑ በይፋም በዘይቤያዊ አገላለጾችም ይገፋፋሉ ፡ ፡ ● እውቀትን ለመቅሰም ዝግጁ አይደሉም ፡፡ የመማር አላማውም የላቸውም ፡፡ ሸሪዓዊ እውቀትን ለማካበት የሚጠፋን ጊዜ ያላግባብ ከሚባክን ጊዜ ነው የሚቆጥሩት፡፡ የእነሱን መንገድ ከመከተል ዉጭ ለስኬት የሚያበቃ ሌላ መንገድ እንደሌለ ያምናሉ፡፡ እንቅስቃሴያቸውንም በኑህ መርከብ በመመሰል ከእነሱ ጋር ያልተሳፈረ ሁሉ ጠፊ መሆኑን ያውጃሉ፡፡ ለተውሂደል ኡሉሂያ (አላህን በብቸኝነት በማምለክ ዙሪያ ) እንድሁም ለተውሂደል አስማእ ወሲፈት (የአላህን ስምና ባህሪያቶችን በተመለከተ ) ምንም አይነት ትኩረት አይሰጡም፡፡ ሌሎች ሌሎች ጥፋቶችም አሉባቸው፡፡ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://telegram.me/eneweke https://telegram.me/eneweke
نمایش همه...
🥀ኑ ስለ ዲናችን እንማማር ☪️

ዲናችንን እንወቅ ስለ ነብያት ስለ ሰሀቦች ስለ ደጋግ ባሮች ቁርዓን ሀዲስ እና ስለ ሙጃሂዶች ታሪክ ታሪካችንን እንወቅ አኩሪ ታሪክ አለንና🥰

❥ልብ☞ በ6 ነገሮች ትበላሻለች📌 ① ኢልም (እውቀት) ኖሮት አለመተግበር ② ስራን ያለ ኢኽላስ መስራት ③ የአላህን ቀደር ( ዉሳኔ ) አለመውደድ ④ ተውበትን በመከጀል ሀጢያትን መዳፈር ⑤ የአላህን ሪዝቅ (ሲሳይ) እየበሉ አለማመስገን ⑥ የሞተን ሠው እየቀበሩ አለማስተንተን አላህ ይጠብቀን!!! አሚን #ሼር መድረጉን አይርሱ😊 💌::::::::::::::Telegram:::::::::::::💌 @eneweke @eneweke @eneweke
نمایش همه...
ጥያቄ፡- …ከዘመዶቼ ጋር ተሰብስበን እየተጨዋወትን እያለን አዲስ ለተወለደው ልጄ ሥም ስለማውጣት መወያየት ጀመርን። በዚህ መሀል በአንቢያዎች ወይም በሶሐቦች ስም በመጠራት ዙርያ ክርክር ጀመርን። አንዷ ሙሐመድ ወይም ዘከሪያ የሚባሉ ስሞችን እንደማትወድ ተናገረች! “ያረጁ ሥሞች ናቸው” ስትል ምክንያቷንም አስረዳች። የአላህን መልእክተኛ- ሙሐመድን (ሰ.ዐ.ወ)- እንደምትወድና እንደምታፈቅር ግን አስረግጣ ተናገረች። ሥሙ ግን ዘመናዊ አይደለም። ስለዚህ ዘመናዊ ሥም እመርጣለሁ አለች። ልክ እንዲሁ ዓኢሻ፣ ኑሰይባ፣ ዒሳ፣ ፋጢማ… የሚሰኙ ስሞችም ደስ እንደማይላት ተናገረች። ዘመናዊ ሥሞች ብላ የጠቀሰቻቸው ደግሞ ሸረፍ፣ ታሚር… የሚሰኙትን እንደሆነም አስረዳች። ጥያቄዬ ምን መሰላችሁ፡- ነብያትን በተመለከተ የተናገረችው ንግግር ይፈቀዳል? ስማቸው ያረጀ ነው ማለት ይቻላል? ሥማቸው አያምርም ማለትስ ይቻላል? እንዲህ ዓይነቱን ንግግር የተናገረ ሰው ኢማኑ አደጋ አይጋረጥበትም?  መልስ፡- በነብያት እና በሷሊሖች- ከማንም በላይ ደግሞ በሶሓቦች- ስም መጠራት ኃይማኖታዊ ጥቅም አለው። ምርጥ ሥም የነርሱ ስም ነው። አላህ ለምርጥ ባሮቹ የመረጠው ሥም ነው። በነርሱ ስም መጠራት እነርሱን ያስታውሳል። እነርሱን እንድንከተልም ይገፋፋል። ስለዚህ በሸሪዐው በነርሱ ስም መጠራት ተወዳጅ ነው። በሐዲስ እንዲህ የሚል ተዘግቧል፡- تسموا بأسماء الأنبياء  ‎ “በነብያት ስም ተጠሩ።” አቡዳዉድ እና አቡ የዕላ ዘግበውታል። በነብያት ስም መጥራት የጠላ ሰው ተሳስቷል። የነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) አስተምህሮንም ነቅፏል። ኢብኑል-ቀዪም “ቱሕፈቱል-መውሉድ ቢአሕካሚል-መውሉድ” የተሰኘው መፅሐፋቸው ላይ እንዲህ ይላሉ፡- “ሰዒድ ኢብኑል-ሙሰይ-ዪብ እንዲህ ብለዋል፡- አላህ ዘንድ ምርጡ ሥም የነብያት ስም ነው።” “ታሪኽ” በተሰኘው በኢብኑ አቢ ኸይሰማ ፅሑፍ ላይ እንደተዘገበው፡- “አቡጦልሓ አስር ልጆች ነበሩት። ሁሉም የሚጠሩት በነብያት ሥም ነው። ዙበይር አስር ልጆች ነበሩት። ሁሉም በሸሂዶች ስም ነው የሚጠሩት። ከዚያም አቡ ጦልሓ ‘እኔ ልጆቼን በነብያት ስም ስጠራቸው አንተ ግን በሸሂዶች ስም ትጠራቸዋለህ?’ አለው። ዙበይርም ‘ልጆቼ ሸሂዶች እንዲሆኑ ስለምመኝ ነው። አንተ ግን ልጆችህ ነብያት እንዲሆኑ አትከጅልም!’ አለው።” ሙስሊም ላይ የተዘገበ የአቡሙሳ ሐዲስ አለ። እንዲህ ይላሉ፡- “ወንድ ልጅ ተወለደልኝ። ከዚያም ወደ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) አመጣሁት። እርሳቸውም ሙሐመድ አሉት። በተምርም ተሕኒክ አደረጉለት።“ ተሕኒክ ማለት፡- ህፃን ልጅ ገና እንደተወለደ ተምርን በሷሊሕ ሰው ምራቅ በሚገባ አላምጠው ካላሙት በኋላ ምላሱን እና ድዱን በመለቅለቅ ወደ ሆዱ የሚገባው የመጀመሪያው ነገር እርሱ እንዲሆን ማድረግ ነው። ቡኻሪይ “በነብያት ስም ስለመጠራት” የሚናገረው ምዕራፍ ላይ የነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ልጅ ኢብራሂም ተብሎ መጠራቱን እንደ መረጃ ያቀርባሉ። ሸይኽ ሙሐመድ ሙኽታር አሽ-ሺንቂጢይ “ሸርሑ ዛዲል-ሙስተንቀዕ” ላይ እንዲህ ይላሉ፡- “ልጆችን በሷሊሖች ስም መጥራት ይወደዳል። ይህ በሙጊራ ኢብኑ ሹዕባ ሐዲስ ላይ ተመልክቷል። ሐዲሱ የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል ይላል፡- ‘ከናንተ በፊት የነበሩት ህዝቦች ልጆቻቸውን በነብያቶቻቸው እና በሷሊሖቻቸው ስም ይጠሩ ነበር።’ ጥበቡም ግልፅ ነው። ህፃኑ ወጣት ሲሆን፣ የተጠራበትን ነብይ ታሪክ ሲያውቅ ወይም የሷሊሑን ሰው ታሪክ ሲያጠና ወይም የዓሊሙን ህይወት ሲያውቅ ተፅዕኖ ይፈጥርበትና ፈለግ አድርጎ ሊይዘው ይችላል።… ስለዚህ ልጁ ላይ መልካም ስሜት እንዲፈጠር ያደርገዋል። ሥሙም የመልካም ነገር መነሻ ይሆነዋል። ተቃራኒ የሆኑት ስሞችም እንደዚሁ አሉታዊ ተፅዕኖ መፍጠራቸው የማይቀር ነው። ልጆችን በመጥፎና በመናጢ ሰዎች ስም መሰየምም ልጆችን ወደነርሱ ጠባይ ሊስብ ይችላል። ልጆችን በከኃዲያን ስም መጥራት ደግሞ ሐራም ነው። ምክንያቱም እነርሱን መመሳሰል ተከልክለናል።”… ነገርግን የሚያሳዝነው ሙስሊሞች ላይ ተፅዕኖ እየፈጠረ ያለው የምዕራቡ ዓለም የአስተሳሰብ ጫና አንዳንዶች ከምዕራቡ የሚመጡ ስሞችን ለልጆቻቸው መጠሪያነት እንዲመርጡ አድርጓቸዋል። ሸሪዐዊ ስሞች የሙስሊም ልጆች ጌጥ ነው። ከእምነታቸው ባዳ የሆኑ ስያሜዎች ማንነታቸውን አይወክሉም። ሸሪዐዊ ስሞችን የማይወድ ሰው ተሳስቷል። አላህን ምህረት መለመን እና ወደርሱ መመለስ ይገባዋል። ውዱን ነብይ ሙሐመድን (ሰ.ዐ.ወ) እወዳለሁ እያለ ስሙን አልወድም ማለት ከራስ ጋር መጋጨት ነው። አንድን ሰው የወደደ ስሙንም ይወዳል። የልጁ መጠሪያ እንዲሆንለትም ይመኛል። ተግባር ደግሞ የልብን ፍቅር ፍንትው አድርጎ ያሳያል። ንግግር ብቻውን ሙግት ነው እንጂ ፍቅርን አያረጋግጥም። ይሁንና ጠያቂያችን ንግግሯን የጠቀሰልንን ሴት በመልካም እንጠረጥራለን። የምትናገረውን በደንብ አላሰበችበትም ብለን እናስባለን። እንደዚያም ለማለት ፈልጋ ነው ብለን አናስብም። ነገርግን ንግግሯን ታርም። “ዘመናዊ” ሥም ከፈለገች የፈለገችው ስም ከዲን ጋር እስካልተጋጨ ድረስ ልጆቿን ትጥራበት። ነገርግን የነብያትን ስም አልወድም ማለት የለባትም። ሙስሊሞች ዘንድ ውድ የሆነውን ስም ግን አትንካ። ደግሞም እነዚህ ሥሞች “ዘመናዊ” አይደሉም ማለት ሀሰት ነው። የዐለም ሙስሊሞችን ተጨባጭ ያለማወቅም ምልክት ነው። ጥናቶች እንደሚጠቁሙት በአሁኑ ወቅት በብዛት ደረጃ ከማንም ስም በላይ የሆነው ስም ሙሐመድ ነው። አላህ የበለጠ ያውቃል!
نمایش همه...
ጥያቄ፡- ሴት ስፖርት መስራት ትችላለች? መከተል ያለባት ወሳኝ መርሆችስ ምንድን ናቸው? መልስ፡- ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን አካልን ለማጠንከርና ጤናን ለመጠበቅ ብሎ መከወን ወንድና ሴት የማይለያዩበት ጉዳይ ነው። የስፖርት ዓይነቱ ደግሞ ሸሪዓዊ ብይኑን ይወስናል። አካልን ለማጠንከር ወይም እንደ እግር ኳስ ያሉ አዝናኝ የሆኑ ስፖርቶችም ቢሆኑ ይፈቀዳሉ። እንደውም አንዳንዴ ግዴታ ሊሆኑ የሚችሉበት አጋጣሚ ሊፈጠርም ይችላል። ነገርግን በስፖርት እንቅስቃሴዎች ጊዜ ሃፍረተ ገላን መሸፈን ግዴታ ነው። ስፖርት እርም ከሆኑ የገንዘብ ልውውጦችም ውጪ መሆን አለበት። ለምሳሌ ቁማር ሊኖርበት አይገባም። ሴት በአለባበሷ ጥቅል የሆኑ የሸሪዓ ድንጋገዎችን በሙሉ መከተል አለባት። ጌጧን ለባዳ ማሳየት የለባትም። ውበቷን የሚያሳይ አለባበስ መከተል የለባትም። ከወንዶች ጋር የሚኖር ቅልቅልን (ኢኽቲላጥን) መጠንቀቅ አለባት። በሱዳን ዩኒቨርሲቲ የሸሪዓ መምህር የሆኑት ዶክተር ዐብዱል-ሐይ ዩሱፍ እንዲህ ይላሉ፡- አንድን ነገር ለመፍቀድ (ተህሊል)፣ ለመከልከል (ተህሪም)፣ ግዴታ ለማድረግ (ውጁብ)፣ በተወዳጅነት (መንዱብ) ለመፈረጅ የሚመጡ የሸሪዓ መልእክቶች በሙሉ ሁለቱን ፆታ እንደሚመለከት የታመነ ነው። ይኸውም በወንዶች ወይም በሴቶች ላይ የሚገድብ መረጃ እስካልመጣ ድረስ ነው። በሴቶች ወይም በወንዶች ላይ የሚገድብ መረጃ ሲመጣ ግን ልቅ የነበረው የሸሪዓ መልእክት በመጣው ገደብ ይታጠራል። ይህ ከታወቀ ተከታዩን ነጥብ ማብራራት እንችላለን፡፡ አንደኛ፡- ሸሪዓው አካልን ብቁ ማድረግ እና ጤናን መጠበቅ ተፈላጊ እንደሆነ አስገንዝቧል። ይህም ጥቅል በሆኑ የሸሪዓው መልእክቶች ውስጥ ሰፍሯል። የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ይላሉ፡- المؤمن القوي خير وأحبّ إلى الله من المؤمن الضعيف وفي كلّ خير‎ “ጠንካራ ሙእሚን ከደካማ ሙእሚን የተሻለ እና አላህ ዘንድ የተወደደ ነው። ሁለቱም ውስጥ ግን መልካም ነገር አለ።” ዑመር ኢብኑል-ኸጧብም እንዲህ ይላሉ፡- علموا أولادكم السباحة والرماية وركوب الخيل‎ “ልጆቻችሁን ውሃ ዋና፣ ቀስት ውርወራና ፈረስ ግልቢያ አስተምሯቸው።” አስለም ከሚሰኘው ጎሳ የሆኑ ሰዎች ቀስት ውርወራ ሲጫወቱ  የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) አገኟቸው። ከዚያም እንዲህ አሉ፡- ارموا بني إسماعيل فإن أباكم كان راميا‎ “ወርውሩ ኢስማዒል ልጆች፤ አባታችሁ ቀስት ወርዋሪ ነበር።” በሌላ ሐዲስም የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ፡- من تعلّم الرمي ثم تركه فليس منّا‎ “ቀስት ውርወራ የተማረ ከዚያም የረሳው ሰው ከእኛ አይደለም።” ሁለተኛ፡- በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ድርጊት እንደተረጋገጠው ነብያችን (ሰ.ዐ.ወ) አካልን ብቁና ጠንካራ የሚያደርጉ እና ለጂሃድ የሚያዘጋጁ ነገሮችን በሙሉ ያበረታቱ ነበር። ጉልበታቸውን በሚያጠናክር ሁኔታ አካላቸው የታነፁ ፈረሶችን እና ያልታነፁ ፈረሶችን አወዳድረዋል። ከዓኢሻ  ጋር ተወዳድረዋል። አንዴ ቀደመቻቸው፤ ሁለተኛው ውድድራቸው ላይ ደግሞ እርሳቸው ቀደሟት። ከዚያም እንደጨዋታ “هذه بتلك‎ – ይህኛው በዛኛው ይካካሳል።” አሉ። ሐሰን እና ሑሰይን በርሳቸው ፊት ትግል ተወዳድረዋል። “ይህ ነው ሐሰን!” ይሉም ነበር። ሦስተኛ፡- በዚህ ጉዳይ ላይ ያሉትን ሸሪዓዊ መርሆች መዘንጋት አይገባም። ጥቅሙን ማግኘት እንደምንፈልገው ሁላ ጉዳቱንም ማስወገድ እና ራሳችንን አላህን ከማመፅ መጠበቅ አለብን። ይህን በተከታዮቹ ነጥቦች መግለፅ ይቻላል፡- ስፖርት ወደ አንዳች ግብ የሚያደርስ መንገድ እንጂ ዋና ዓላማ አይደለም። ስለዚህ በስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች መሰረት ወዳጅና ጠላት መኳኳን የለም። እንደውም ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ለጠላትነት እና ለመቃቃር መንገድ የቀደደ እንደሆነ ወደ ሐራምነት ይለወጣል። ይህ ችግር በእግር ኳስ ጨዋታ አፍቃሪዎች ላይ ይስተዋላል። ከሚደግፉት ቡድን ጥቅም አኳያ ይዋደዳሉ፤ ይጣላሉ። አንዳንዴ ደም አፋሳሽ የሆኑ ጦርነቶች ይካሄዳሉ። ስፖርት በልኩ መሆን አለበት። እድሜን ለርሱ መለገስ ጊዜን በሙሉ- በሌሎች ኃላፊነቶች ሂሳብ- ለርሱ መስጠት አይቻልም። በዚህ ጎን ስፖርት እንደሌሎች የሚፈቀዱ ነገሮች (ሙባሃት) ይታያል። የሚፈቀዱ ነገሮች ላይ ወሰን ማለፍና ድንበር መጣስ እርምና የተጠላ ነው። ሁሉም ነገር በልኩ መሆን አለበት። ለመዝናናት የሚከወኑ- እግር ኳስ እና ቅርጫት ኳስን የመሳሰሉ- ስፖርቶች እና ለጂሃድ የሚያገለግሉ- የአካል ብቃት እና ቀስት ውርወራን የመሰሉ- ስፖርቶች የተለያየ ብይን ነው ያላቸው። የመጀመሪያዎቹ ይፈቀዳሉ። ሁለተኞቹ ደግሞ ዋጂብ ወይም ተወዳጅ ይሆናሉ። ሁሉንም አጅር የሚያስገኙ- የፊሰቢሊላህ ናቸው- ማለት አይቻልም። በእነዚህ ሁሉ ብይኖች ውስጥ- ስፖርቶቹ- ከሌሎች እርም ነገሮች ያገለሉ መሆን አለባቸው። መሰዳደብ፣ ፍስቀት፣ ሃፍረተ ገላን መግለጥ፣ ወንድና ሴት መቀላቀል፣ ሶላትን ማሳለፍ፣ ሰዎችን ማስከፋት… ስፖርት ውስጥ እርም ነው፤ በሌላ ጊዜም እርም እንደሆነው ሁሉ ማለት ነው። ወደሞት የሚያደርስ፣ ህይወትን አደጋ ላይ የሚጥሉና ክፉ ውጤት ያላቸውን ስፖርቶችም መራቅ ያስፈልጋል። ውሃ ዋና እና እግር ኳስ ላይ እንደተለመደው ደግሞ ሃፍረተ ገላን ማሳየት አይቻልም። “ታፋ ዓውረት (ሃፍረተ ገላ) ነው።” ይላሉ ታላቁ ነብይ። ወንድ የራሱ መለዮ አለው፤ ሴትም እንደዚሁ ተፈጥኣዊ መለያ አላት። ሴት ከሴትነት ተፈጥሮዋ የሚያወጣትን ስፖርት መስራት የለባትም። ለምሳሌ የአካል ግንባታ (የቅርፅ ውድድር) ሴትን ከተፈጥሮኣዊው ማንነቷ ያወጣታል። ምክንያቱም ታላቁ ነብይ አንዲት ሴት እንደወንድ ስትራመድ አይተዋት “እርጉም ናት!” ብለዋል። ወላሁ አዕለም!
نمایش همه...
إِنَّ الَّذِينَ يُحِبُّونَ أَن تَشِيعَ الْفَاحِشَةُ فِي الَّذِينَ آمَنُوا لَهُمْ عَذَابٌ أَلِيمٌ فِي الدُّنْيَا وَالْآخِرَةِ وَاللَّهُ يَعْلَمُ وَأَنتُمْ لَا تَعْلَمُونَ‎ “እነዚያ በእነዚያ ባመኑት ሰዎች ውስጥ መጥፎ ነገር እንዲስፋፋ የሚወዱ ለእነሱ በቅርቢቱም በመጨረሻይቱም ዓለም አሳማሚ ቅጣት አላቸው፡፡ አላህም ያውቃል እናንተ ግን አታውቁም፡፡” (24፤19) በጉዳዩ ላይ ሦስት ነጥቦችን እናንሳ፡- የቀድሞውና የአሁኑ ዘመን ጃሂሊያ፡- የዘመናችን ጃሂሊያና የቀድሞውን ጃሂሊያ የሚያመሳስል ነገር አለ፡፡ የነጃሳው ገበያ ያመሳስላቸዋል፡፡ የቀድሞውና የአሁኑ የነጃሳ ገበያ ቢለያይም ቅሉ በዋናው ነጥብ ላይ አንድ ናቸው፡፡ የድሮው ጃሂሊያ የሴት ባሮችን ስጋ ለገበያ ያቀርብ ነበር፡፡ የአሁኑ ጃሂሊያ ግን የሁሉንም ሴቶች ስጋ ለገበያ ያቀርባል፡፡ ነገርግን አዲሱ ጃሂሊያ ለነጃሳው ገበያ መልካም ሥም ያወጣል፡፡ የቁንጅና ውድድር፣ ጥበብ… እያለ ቆሻሻውን ይደብቃል፡፡ ነገርግን ጥበብ እብደት ሆነ፡፡ ትልቁ የአላህ ስጦታ የነበረው ፈን/ጥበብ በክፉ ሰዎች እጅ ታሸና አደፈ፡፡ የሰዎችን ስብዕና ሻረና በቦታው እንስሳነትን አሰረፀ፡፡ ኢስላም ለሴቶች ያለው እይታ፡- ሴት በኢስላም የሚሸጥ ሸቀጥ አይደለችም፡፡ የምትሸተት ፅጌሬዳም አይደለችም፡፡ እቃ ማሻሻጫ ቅርፅም አይደለችም፡፡ በክብካቤ የምትጠበቅ እንቁ ናት፡፡ የምታሳሳ ሉል ናት፡፡ ኢስላም ህፃን ሆና ይጠብቃታል፡፡ ይንከባከባታል፡፡ ትልቅም ሆና ይጠብቃታል፡፡ በዚህና በዚያ መሀልም በክብካቤ ትልቅ ደረጃ እንድትደርስ በመልካም አስተዳደግ ውስጥ የምታልፍ ልጅ፣ እገዛ የሚያሻት እህት፣ ባለ መብት ሚስት፣ የምትመሰገን እናት፣ ጀብዷ የሚወሳላት አያት ናት!… ከዋናው አጀንዳችን ማዘናጊያ፡- እነዚህ ውድድሮች ከባህላችን የራቁ፣ ማንነታችንን የማያንፀባርቁ፣ ከማንኛችንም ኃይማኖት -ከክርስትናም ሆነ ከኢስላም ያፈነገጡ ከመሆናቸው ጋር የህልውናችን መሰረት፣ የዘመናዊነት ማሳያ፣ የተራማጅነት ምልክት ተደርገው እንዲታዩ የተደረጉት ለምንድን ነው?! ለኢትዮጲያዊያን ትልቁ ጉዳይ ዳቦ ነው ወይስ የሴት ገላ? ለሴቶቻችንስ የሚያሻቸው ትምህርት ነው ወይስ ዝሙት? ርክሰት? እኛማ ጉዳዩ ማንነታችንን በማሳጣት ለራሳችን ክብር እንዳይኖረን፣ በዋና ዋና ችግሮቻችን ላይ እንዳናተኩር የሚያደርግ የቅኝ ገዢዎች ዘዴ ይመስለናል! አላህ የበለጠ ያውቃል
نمایش همه...
یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.