WCU_Evange_Moblizers
رفتن به کانال در Telegram
2 187
مشترکین
-124 ساعت
+37 روز
-1330 روز
آرشیو پست ها
2 187
ሻሎም
ፀጋው በብዙ የተትረፈረፈላችሁ ወንጌላውያን እንዴት አላችሁ ለ Final Exam በትጋት እየተዘጋጃችሁ እንደሆነ እምነታችን ነዉ ፣በሚመጡት ቀናት (During Exam ) እግዚአብሔር የእጃቹን ስራ ይባርክላችሁ 🤗
➡️ ነገ ሰኞ የ Wel-go program እና GC Certification Day ነዉ
👉 እግዚአብሔር በዚህ ዓመት በእኛ አልፎ ስለ ሰራው ድንቅ ስራው እግዚአብሔር የምናመሰግንበት እና
👉GC ተማሪዎችን certify የምናደርግበት ቀን ነውና (ደግሞ የዓመቱ የመጨርሻው ሰኞ ) ሁላችሁም በሙላት በተባለው ሰዓት እና ቦታ እንድትገኙ ይሁን!
2 187
💫 የዓመቱ የመጨረሻው ዕረቡ
Official Out Reach Day The last Wednesday
*
ፀጋ የበዛላችሁ ወንጌላውያን ሁላችሁም ሰላም ለእናንተ ይሁን ነገ ዕረቡ 28/08/18 እንደተለምደው ይሄንን የምስራቹን ወንጌል የምንናገርበት ቀን ስለሆነ ሁላችሁ በሙላት በመገኘት ወንጌል በመስበክ ውስጥ ያለው በረከት እንድትካፈሉ ይሁን
👉 ልክ 11:00 ስል @Chaple እንገናኝ
NB :- በ Evange week ላይ የነበሩ ቀጠሮዎች ነገ ቀናቸው ነዉ ፣ደውላችሁ ለነገ ቅተሯቸው....
እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን! 1ቆር 1:24
2 187
ሃሌሉያ! ኢየሱስ ዛሬም ሕያው ነዉ ።
💥ትላንት ላልነበራችሁ ነዉ :- የምስራች
የ EVANGE -WEEK "Report "
ሃሌሉያ! እግዚአብሔር እንደተለመደው አስደንቆናል ሃሌሉያ 🙈👋🧎➡️
➡️ ተስፋ የሰጡ =5
➡️ በንስሐ የተመልሱ =12
➡️ የዳኑ =14 (ከ 14 ሰው ሁሉቱ የግቢ ተማሪዎች ናቸው and የግቢ ሰራተኛ ነዉ )
እንግዲህ በእኛ እንደሚሠራው ኃይል መጠን ከምንለምነው ወይም ከምናስበው ሁሉ ይልቅ እጅግ አብልጦ ሊያደርግ ለሚቻለው፥ ለእርሱ በቤተ ክርስቲያን በክርስቶስ ኢየሱስ እስከ ትውልዶች ሁሉ ከዘላለም እስከ ዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን። ኤፍ 3:20-21✨የታረደው በግ የምስዋትነቱን ዋጋ ይቀበል ይገባዋል! ሃሌሉያ ። 👉ይሄ የሆነው በእናንተ መታዘዘ ነውና እግዚአብሔር አብዝቶ ይበርካችሁ ፣ ስለምት ሰሙን፣ ስለምታከብሩን፣ ስምትታዘዙን እና ስምትወዱን በእኛ ዘንድ ያላችሁ ቦታ ከፍ ያለ ነዉ ከ ቃል በላይ ሆናቹብናል ተባረኩ ። ➡️አሁንም ግን አልተነካም ብዙ መከር አለና እንደተለመደው ከምን ጊዜውም በላይ በደንብ እንደንቀሳቀስ ይሁን #ወንጌል ለሁሉም ሁሉም ለወንጌል! #EVANGE_ MOBLIZER
2 187
#የምስጋና - ጊዜ
➡️ ሻሎም እንዴት ቆያችሁ ፀጋ የበዛላችሁ ወንጌላውያን ዛሬ ሰኞ (025/08/18) እግዚአብሔር ባሳለፍነው ሳምንት በ EVANGE -WEEK ስለረዳን ፣ስላገዘን ሰዎችን /ነፍሳትን አሳልፎ ስለ ሰጠን የምናመሰግበት ቀን ነዉ :-
💫 Payer time
💫 Worship and
💫 Report time
በሄዱ ጊዜ፥ ዘራቸውን ተሸክመው እያለቀሱ ተሰማሩ፤ በተመለሱ ጊዜ ግን ነዶአቸውን ተሸክመው ደስ እያላቸው ይመጣሉ። መዝ 126:6✨ስለዚህ ሁላችንም በጊዜ @11:00 @MKC እንገናኝ
2 187
ከአዳም ጀምሮ እስከ ክርስቶስ መወለድ ድረስ የነበሩት ቅዱሳን ተስፋ ያደረጉትና የተጠባበቁት የኢየሱስን መወለድ ነበር።እኛ ደግሞ ተስፋ የምናደርገዉና የምንጠባበቀዉ ዳግመኛ መምጣቱን ነዉ።ዳግመኛ መምጣቱንም ጌታ ራሱ ለደቀመዛሙርት፦
“ሄጄም ስፍራ ባዘጋጅላችሁ፥ እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ።”(ዮሐንስ 14፥3) በማለት ነግሮአቸው ነበር።ከሙታን ተነስቶ አርባቀን ለሐዋርያት ከታያቸው በኋላ ወደሰማይ ዓረገ።ሲያርግም ደቀመዛሙርት ትኩር ብለዉ እየተመለከቱ እያለ ሁለት መላእክት ተገልጠዉ፦
“ደግሞም፦ የገሊላ ሰዎች ሆይ፥ ወደ ሰማይ እየተመለከታችሁ ስለ ምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት፥ እንዲሁ ይመጣል አሉአቸው።”
(ሐዋርያት 1፥11)
ከዝህ የተነሣ ሐዋርያት የኃጢአትን ስርየት እንደሰበኩ ሁሉ የጌታን ተመልሶ መምጣት በትኩረት ሰበኩ።
በዉጤቱም የቀደሙት አማኞች ሕይወታቸው ከጌታ ዳግም ምጽዓት አንጻር የተቃኘ ሆነ።
ተመልሶ መምጣቱንም በራሳቸው ዘመን ስለተጠባበቁ በምድር የነበራቸውን ሕይወት በጥንቃቄ መሩ።ጌታም በቶሎ እመጣለሁ ስላለ ቤተክርስቲያንም መንፈሱም ና የሚል ናፍቆት ነበራቸው ።ፍጥሞ በምትባል ደሴት ላይ ታስሮ ለነበረው ለሐዋርያው ዮሐንስ ጌታ ኢየሱስ በቶሎ እመጣለሁ ሲለዉ የዮሐንስ ጸሎት፦“ አሜን፥ ጌታ ኢየሱስ ሆይ፥ ና።”(ራእይ 22፥20)
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የቅዱሳን ሁሉ ናፍቆት ስለሆነ የተባረከው ተስፋችን ተብሏል (ቲቶ 2፥12_13)
የተቀበልነዉ ጸጋ ከሚያስተምረን ትምህርቶች አንዱ የተባረከዉን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንን የመድኀኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እንድንጠባበቅ ነዉ(ቲቶ 2፥11_13)
#መምጣቱም በብዙ ክብርና አጀብ እንደሚሆን የእግዚአብሔር ቃል ይናገራል።
በአባቱና በራሱም ክብር ከመላእክት ጋር ይመጣል(ማቴ 16፥27፤ 25፥31)
#በእርሱ አምነዉ የሞቱትም ከእርሱ ጋር መጥተው የሥጋ ትንሳኤ በምድር ላይ ያገኛሉ (1ተሰ4፥13_16)
⨳በክርስቶስ ኢየሱስ አምነን የዳንን ሁላችንም የጌታችንን ታላቁን ትዕዛዝ በመታዘዝ እና ታላቁን ተልዕኮአችንን በመፈጸም ሁሉ ወደ ንሰሃ እንድበቁ /እንድደርሱ የመንግስቱን ወንገል ከወትሮዉም ይልቅ በኃይል በብዙ ትጋትና ተጋድሎ መመስከር ይጠበቅብናል።(2ጰጥ3፥9)
{ወንጌላዊ ወንጌሉን ይመሰክራል/ይናገራል }
⨳የእግዚአብሔር ቀን እየተጠባበቅን የምስራቹን በማብሰር፣በቅድስና/በቅዱስ ኑሮ በመኖር፣እግዚአብሔርን በመምሰል/ በእዉነተኛ መንፈሳዊነት በመመላለስ መምጫዉን እንድናፋጥንና እንድናስቸኩል መጽሐፍ ቅዱስ ያስተምረናል።(2ጰጥ3፥11_13)
{ወንጌላዊ ወንጌሉን ይኖረዋል }
⩩ ኢየሱስ ክርስቶስን የህይወትታችሁ ጌታና አዳኝ አድርጋችሁ ያልተቀበላችሁ በሙሉ ፦ሰዉ ኃጢአት ከሠራ በኋላ በእግዚአብሔር ፍርድ ሥር ስለወደቀ እግዚአብሔር ካላዳነዉ በቀር በምንም መንገድ ራሱን ማጽደቅ አይችልም።ስለዝህ ወደ እግዚአብሔር መንግስት መግባት የሚችለው በምህረት ብቻ ነዉ የሆነዉ።ምህረት የተገኘው ደግሞ ክርስቶስ ኢየሱስ በእኛ ምትክ በመሞት የኃጢአት ዕዳችንን በመክፈሉና ጽድቁን ሊሰጠን ከሞት በመነሳቱ ነዉ።ይህንን አለማመንና አለመቀበል ግን የዘላለም ፍርድ ያስከትላል።ፍርዱ ጌታ ኢየሱስ በመስቀል ላይ ሠርቶ የጨረሰዉን ይህንን የሚያህል ታላቅ የማዳንን ሥራ ባለማመን ምክንያት የሚመጣ ነዉ።የእግዚአብሔር ቃል ፦
ዮሐ 3
¹⁴-¹⁵ ሙሴም በምድረ በዳ እባብን እንደ ሰቀለ እንዲሁ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ የሰው ልጅ ይሰቀል ይገባዋል።
¹⁶ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።
¹⁷ ዓለም በልጁ እንዲድን ነው እንጂ፥ በዓለም እንዲፈርድ እግዚአብሔር ወደ ዓለም አልላከውምና።
¹⁸ በእርሱ በሚያምን አይፈረድበትም፤ በማያምን ግን በአንዱ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ስላላመነ አሁን ተፈርዶበታል።(በማያምን ግን በአንዱ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ስላላመነ አሁን ተፈርዶበታል)
⩩ ስለዝህ ፍርዱ የተመሠረተው ይህንን መዳን ባለመቀበል ላይ ነዉ በክርስቶስ ሞትና ትንሳኤ የተገኘውን የእግዚአብሔርን ማዳን ያላመኑና ያልተቀበሉ ስዎች ተፈርዶባቸዋል ።
⩩ በፍርድ ቀን የሚፈረድባቸው ያዉ ዓለምን ሊያድን ዋጋ የከፈለው የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ነዉ።(ራዕ1፥7 ራዕ 20፥11_15)
ስለዚህ ከዘላለም ፍርድ ፣ለሰይጣንና ለመላእክቱ ከተዘጋጀው ከዘላለም እሳት ባህር ትድኑና የዘላለም ዕረፍትና ህይወት የሆነዉን ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን የህይወታችሁ አዳኝና ጌታ አድርጋችሁ እንድትቀበሉ የፍቅርና የንሰሐ ጥር እናቀርብላችኋለን ።
“ይህን የሚመሰክር፦ አዎን፥ በቶሎ እመጣለሁ ይላል። አሜን፥ ጌታ ኢየሱስ ሆይ፥ ና።”
ራእይ 22፥20 (ማራናታ)
2 187
Repost from WCU Fellowship
#ቀን_አምስት
መሲሁ ማን ነው?
****
የዘላለም ህይወት ብቸኛው ሰጪ ነው።
➡️"መሲሁ ማን ነው"? የሚለው ጥያቄ በዘመናት መካከል ብዙ ሰዎችን ያከረከረ ደግሞም ዓለምን በብዙ እይታ የከፋፈለ አጨቃጫቂው ጉዳይ ሲሆን! ነገር ግን ለዚሁ ጥያቄ ጤናማ ምላሽ ለሰጡት እና ለተቀበሉት ህይወትን የሚያጎናጽፍ ነገር ነው።
- "መሲሁ ማን ነው"? _ የዘላለምን
ህይወት ሰጪ ነው። መሲሁ የዘላለምን ህይወት ሰጪ ነው ካልን ዘንደ ዘላለም የሚለውን ሀሳብ በደንብ መረዳት አለብን፡
💥 ዘላለም የሚለውን ሐሳብ በሁለት
አውድ ብንመለከት ይበልጥ ጥሩ መረዳት እና ጥሩ እይታ እንዲናገኝ ያደርገናል፦
1.የመጀመሪያው የ "ጥፋት ዘላለም " ሲሆን ይህ ዘላለም በኃጢአት ምክንያት ሰዎች የሚቀበሉትና ለኃጢአተኞች ሰዎች፣ በኃጢአትተኝነታቸው ምክንያት ሊቀበሉት የሚገባ ተገቢ ምላሽ ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ ሲናገር እንዲህ ይላል... የማቴዎስ ወንጌል 25:46
---
⁴⁶ እነዚያም ወደ ዘላለም ቅጣት፥ ጻድቃን ግን ወደ ዘላለም ሕይወት ይሄዳሉ።➡️ይህ የ"ጥፋት ዘላለም " በክርስቶስ ኢየሱስ ላላመኑ የተዘጋጀ የዘላለም ቅጣት ነው። ደግሞም ለኃጢአተኛ ሰው የተገባው የዘላለም ደሞዝ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ሲናገር እንዲህ ይላል... ወደ ሮሜ ሰዎች 6:23 ---
²³ የኃጢአት ደመወዝ ሞት ነውና፤..✨ ስለዚህ በክርስቶስ ኢየሱስ ላልሆኑት በደለኞች ተገቢው ክፍያው የዘላለም ሞት ነው። ጠቅለል ስናደርገው የ "ዘላለም ጥፋት " ከጌታ፣ሕይወት ሰጪ ከሆነው ከእርሱ ለዘላለም መለያት ነው። 2. ሁለተኛው ደግሞ የ "ዘላለም ህይወት"(Eternal life) ይህ የህይወት ዘላለም ከእግዚአብሔር ዘንድ በመሲሁ በኩል ለማይገባቸውና ለኃጢአተኞች የቀረበ የህይወት ዘላለም ሲሆን ማንኛውም ሰው ምንም ሳይሰራ ፣እንዲሁ በነፃ በጸጋው በኩል መሲሁን አምኖ ሲቀበል የሚበረከት የዘላለም ህይወት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ሲናገር እንዲህ ይላል... ወደ ሮሜ ሰዎች 6:23 ---
23 "...የእግዚአብሔር የጸጋ ስጦታ ግን በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን የ"ዘላለም ሕይወት" ነው።"♦የዘላለም ሕይወት (eternal life) ማለት የሰው ልጅ በኃጢአት ምክንያት አጥቶት የነበረውን ከእግዚአብሔር ጋር የመኖር አንድነት(ህብረት)፣ በክርስቶስ በኩል መልሶ ማግኘት ማለት ነው። ይህ ሕይወት ዛሬ በሰላምና በደስታ ይጀምራል፣ ከሞት በኋላ ደግሞ በክብር ይቀጥላል። የዘላለም ህይወት እግዚአብሔርን በማወቅና በእምነት በነፃ የሚሰጠውን ህይወት በመቀበል በምድር የሚጀመርና ከሞት በኋላ በሰማይ ለዘላለም የሚቀጥል ህይወት ነው። ✨ ዘላለምን ስንመለከት አንዱ የስራችን ውጤት " የኃጢአት" ደሞዝ ሲሆን ይህም የዘላለም ጥፋት ''ሞት" ነው። ሌላኛው ደግሞ ከዚህ በተቃራኒ ለማይገባው ሰው በጸጋ የተበረከተለት "የዘላለም ህይወት" ነው። ♦መጽፍ ቅዱስ እንደሚለው የዚህ የዘላለም ህይወት ብቸኛው "ምንጭ" ወይንም "ሰጪ " ደግሞ ራሱ የዘላለም ህይወት የሆነው መሲሁ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። የዮሐንስ ወንጌል 10:28 ---
²⁸ እኔም የዘላለም ሕይወትን እሰጣቸዋለሁ፥ ለዘላለምም አይጠፉም፥ ከእጄም ማንም አይነጥቃቸውም። ➡️ "እኔም የዘላለም ሕይወትን እሰጣቸዋለሁ፥" የዘላለምን ህይወት ሰጪው ራሱ እግዚአሔርና እግዚአብሔር ብቻ ነው ከእግዚአብሔር ውጪ የዘላለምን ህይወት ሊሰጥ የሚችል ማንም እንደሌለ ያሳያል። ኢየሱስ የሚሰጠው ሕይወት "የዘላለም" (Eternal) ነው። ይህ የሚያመለክተው፡- ከጊዜ በላይ መሆኑን፦ ይህ ሕይወት በሞት የማይቋረጥ፣ ከመቃብር በላይ የሚቀጥል መለኮታዊ ሕይወት ነው። የሕይወት ጥራት፦ የዘላለም ሕይወት ረጅም ዘመን መኖር ብቻ ሳይሆን፣ ከእግዚአብሔር ጋር የሚኖር ጥልቅ ግንኙነትና ሰላም ነው። #በዮሐንስ 17:3 ላይ እንደተጠቀሰው፣ የዘላለም ሕይወት እውነተኛ አምላክንና የላከውን ኢየሱስ ክርስቶስን ማወቅ ነው። ➡️ "ለዘላለምም አይጠፉም፥" ከእግዚአብሔር ዘንድ የሚሰጠው የዘላለም ህይወት የማይጠፋና የዘላለም ዋስትና እንዳለው ያሳያል። በጎቹ ደኅንነታቸው የተጠበቀው በራሳቸው ጥንካሬ ሳይሆን፣ በሰጪው በኢየሱስ ክርስቶስ ታማኝነትና ኃይል ነው። ➡️"ከእጄም ማንም አይነጥቃቸውም።" ከእግዚአብሔር ማንም ሊነጥቅ እንደማይችል ያሳያል። በክርስቶስ እጅ ውስጥ መሆን ማለት በሁሉን ቻይነቱ ጥላ ስር መሆን ማለት ነው። ከዚህ እጅ ነጥቆ ሊወስድ የሚችል ምንም ዓይነት ምድራዊም ሆነ መንፈሳዊ ኃይል የለም። 🎯ስለዚህ በክርስቶስ ለሚያምኑት ሁሉ የዘላለም ህይወት በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ቀርቧል። ➡️ስለሆነም በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን የሚገኘውን የዘላለምን ህይወት እንዲታገኙና ከዘላለም ጥፋት እንድታመልጡ የፍቅር ጥሪ እናቀርባለን። 👇👇👇👇👇 @wcuevang
2 187
መሲሑ፦ የዘላለም ሊቀ-ካህናት ነው!
✨ መሲሑ ኢየሱስ ክርስቶስ የዘላለም ሊቀ-ካህናት ነው!
➡️ሊቀ -ካህናት :- በእግዚአብሔር ተመርጦ ስለ ህዝቡ ኃጢአት ማተሰሪያ ይሆን ዘንድ ደምን ይዞ ወደ ቅድስተ ቅዱሳን ለምልጃ የሚገባ ፣በሰው እና በእግዚአብሔር መካከል የሚቆም መካከለኛ ማለት ነው ። እንዲ ተብሎ እንደተፃፈ :-
ሊቀ ካህናት ሁሉ ስለ ኃጢአት መባንና መሥዋዕትን ሊያቀርብ ከሰው ተመርጦ ለእግዚአብሔር በሆነው ነገር ሁሉ ስለ ሰው ይሾማልና፤ ዕብ 5፥1➡️ስለዚህ ሊቀ -ካህናት ፦ 1) ለእግዚአብሔር ስለ ህዝቡ መባን እና መስዋትን የሚያቀርብ ነው ➡️ ሊቀ -ካህናት መባን እና መስዋትን ስለህዝቡ ለእግዚአብሔር ማቅረብ ዋነኛ ስራው ነው ። እንዲሁ ኢየሱስ አንደሌሎች ንፁህ በግ ሳይሆን ከዚያ የሚበልጠውን ንፁህ እና ፍፁም የሆነው ራሱን መስዋት እና መባ አድርጎ ለእግዛብሔር ስለ ዓለም ሕዝብ ሁሉ ኃጢአት ራሱን አቀረበ ።
ክርስቶስም ደግሞ እንደ ወደዳችሁ ለእግዚአብሔርም የመዓዛ ሽታ የሚሆንን መባንና መሥዋዕትን አድርጎ ስለ እናንተ ራሱን አሳልፎ እንደ ሰጠ በፍቅር ተመላለሱ።2) ለእግዚአብሔር በሆነ ነገር የተሾመ ➡️ለእግዚአብሔር ቤት ፣ ለቤተመቅደሱ ስራ (ለመንፈሳዊ ) አገልግሎት የተለየ /የተሾመ ። ሊቀ ካህናት ሌላ ስራ አልነበራቸውም ከቤተመቅ ደስ አገልግሎት ውጪ ፥ ኢየሱስ ሊቀ ካህናት ሊያደርጉት ለተጠሩት ስራ የተሾመ ነበረ ። 3) ስለ ሰው (ስለ ሌላው ) የተሾመ ➡️ ስለ ራሱ ሳይሆን ስለ ሌላው የተጠራ /የተሾመ ነው ሊቀ ካህናት ። ኢየሱስ ራሱ አላገለገለም! ይልቁንስ የከበረው በአምላክ መልክ ይኖር የነበረ እርሱ ፣ስለ እኛ ስለ ሰው ልጆች ኃጢአት ሲል የራሱ ክብር ባለመፈልግ ዝቅ በማለቱ በእግዚአብሔር አብ "ባሪያዬ " ተብሏል ።
ከነፍሱ ድካም ብርሃን ያያል ደስም ይለዋል፤ ጻድቅ ባሪያዬም በእውቀቱ ብዙ ሰዎችን ያጸድቃል፥ ኃጢአታቸውን ይሸከማል። ት ኢሳይ 53 ፥114) መካከለኛ የሆነ ማለት ነው ። ➡️ ነቢያት እንደሚያደርጉት ከእግዚአብሔር ወደ ሰው ብቻ ሳይሆን ሊቀ -ካህናት ከሰው ወደ እግዚአብሔር፣ ከእግዚአብሔር ወደ ሰው በሁለቱም መንገድ የሚያገለግሉ ናቸው ። ➡️ ኢየሱስ እንደሌሎች ሊቀ -ካህናት በአገልግሎት ረገድ ብቻ መካከለኛ አይደለም ይልቁንስ ኢየሱስ በባህሪው ራሱ መካከለኛ ነው አንድም ከእግዚአብሔር ወገን የሆነ የእግዚአብሔርን ባህሪ የሚጋራ፣ የእግዚአብሔርን ፅድቅ ፣ቅድስና ፍትህ እንደ ራሱ እንደ እግዚአብሔር የሚያውቅ እና የሚረዳ ፣ ሁለትም ደግሞ የሰው ልጆችን ድካም ፣አለመቻል እግዚአብሔርን ለማስደሰት እየፈልጉ ግን ያለመቻል በኃጢአት ደጋግሞ የመውደቃችን ነገር የሚገባው ሰው (ፍፁም ) ሰው ስለሆነ ሰው የሚረዳ ነው ። ➡️በዚህም ምክንያት እውነተኛ "መካከለኛ" ነው በእውነትም በመካከል የገባ፣ በእግዚአብሔር እና በሰው ልጆች መካከል የነበረውን የጥል ግርግዳ በመስቀል ላይ ባፈሰሰው ደም ያፈረሰ በመስቀል ብቻ ያላበቃ ደሙን ይዞ ወደ እውነተኛው ወደ ሰማያዊው ድንኳን ስለ እኛ ኃጢአት አሁንም ይታይ ዘንድ የገባ እውነተኛ መካከለኛ ነው ።
አንድ እግዚአብሔር አለና፥ በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው ።1ጢሞ 2፥5 ➡️ማጠቃለያ :- ኢየሱስ ዘላለማዊ ስለሆነ የማይለወጥ ሊቀ -ክህነት አለው ፣ ሊቀ -ካህናት የሆነ እርሱ ደግሞ በገዛ ደሙ ወደ እውነትኛው ድንኳን ደሙን ይዞ ገብቷል ፣ ያደረገው መስዋትነት ዘላለማዊ ነውና ፣ ያደም አሁንም ስል ሰው ልጆች ኃጢአት በእግዚአብሔር ፊት ይታያል እንዲ ተብል እንደተፃፈ :-
ክርስቶስ በእጅ ወደ ተሰራች፥ የእውነተኛይቱ ምሳሌ ወደ ምትሆን ቅድስት አልገባምና፥ ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ስለ እኛ አሁን ይታይ ዘንድ ወደ እርስዋ ወደ ሰማይ ገባ። ዕብ 9፥24🎯ስለዚህ ኢየሱስ ይዞት በገባው ፣ ስለ እኛ በሚ ታው ዘላለማዊ ደሙ አማካኝነት ዛሬም አማላጅችን ነው ማለት ነው ። ሊቀ -ካህናት የሆነ እርሱ አማላጃችን ነው! ➡️ በዚህ መፅሐፍ ቅዱሳዊ እውነት ማመን ምርጫ ሳይሆን ግዴታ ነው! ዕረፍት ይሆንላችሁ ዘንድ በዚህ እውነት እመኑ ።
2 187
Repost from WCU Fellowship
#ቀን_ሶስት
መሲሁ :- የሁሉ ቤዛ ነው!
✨መሲሁ :-ኢየሱስ ክርስቶስ የሁሉ (የዓለም )ሁሉ ቤዛ ነው! መሲሁ ውልደቱም ሆነ የተወለደበት ምክንያት ከሰው ሁሉ ይለያል ። መሲሁ የተወለደው የዓለም ሁሉ ቤዛ ሊሆን ነው!
እንዲሁም የሰው ልጅ ሊያገለግል ነፍሱንም ለብዙዎች ቤዛ ሊሰጥ እንጂ እንዲያገለግሉት አልመጣም።ማቲ20:28👉 ቤዛ (ቤዝሆት ) ማለት :- "የመዋጀት ዋጋ ፣ማስፈቻ ፣ነፃ ማድረጊያ ፣አንድን ነገር ከጥፋት ወይም ከሞት በመመልስ ፣የራስ እንዲሆን የሚደርግ የምትክ ድርጊት ወይም የሚከፈል ዋጋ" ማለት ነው ። 💥ለዚህም ነው መፅሐፍ ቅዱስ ሲናገር በኢየሱስ በምትክ፣ ሞት ባፈሰሰው ደሙ በኩል ቤዛነታችንን አገኘን ይለናል ።
በውድ ልጁም፥ እንደ ጸጋው ባለ ጠግነት መጠን፥ በደሙ የተደረገ ቤዛነታችንን አገኘን እርሱም የበደላችን ስርየት።ኤፍ 1:7👉አዎን እውነት ነው! መፅሐፍ እንደሚናገር እኛ በኃጢያታችን እና በክፉ ስራችን ከእግዚአብሔር ሕይወት ፣ ከፅድቅ፣ ከቅድስና እና ከእውነተኛ መንፈሳዊ ሕይወት ተለይተን በመንፈሳችን ሞተን ነበር፣ እግዚአብሔር ግን በአንድ ልጁ ምትክ ሞት (ቤዛነት ) ወደ ነበረን ክብር መልሶ እንደገና የራሱ አደርገን አሁንም በኢየሱስ በኩል ከእግዚአብሔር ጋር ኃጢአተኛ የሆነ የሰው ልጅ ሁሉ እንዲታረቅ መንገድን አበጅቷል ። 👉 የኢየሱስ ሞት የምትክ የቤዝሆት ሞት ነው መፅሐፍ ቅዱስ እንደሚናገር የኃጢአት ደሞዝ ሞት ነው ፣ ሰው ሁሉ ደግሞ ኃጢያተኛ ነውና የዘላለም ሞት ይገባዋል! እግዚአብሔር ግን በምህረቱ ባለጠጋ ስለ ሆነና ፍቅር ስልሆነ አንድ ልጁን ለዓለም ሁሉ ሰጠንልጁም ኢየሱስ መሲሁ ለዓለም ሁሉ ኃጢያአት ቤዛ እንዲሆን በመስቀል ላይ ንፍሱን ሰጠን ። 💥እውነት ነው እኛን የሰው ልጆችን ከኃጢአት ፣እና ከውጤቱ ከዘላለም ሞት ለማዳን ኢየሱስ በመስቀል ላይ ሞቶልናል ፣ሞቶም አልቀረም በሶስተኛው ቀን ከሞት ተነስቷል ። 👉ስለዚህ ወዳጅቼ ሰው በራሱ ጥረት አይድንምና የሰውን ሁሉ ኃጢአት ዕዳ የከፈለውን ኢየሱስን በማመን ከእግዚአብሔር ጋር እንድትታረኩቁ በእርሱ በማመን እረፍት እንዲሆንላችሁ እንጋብዛቹሃለን ።
ሰው ዓለምን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱን ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል? ሰውስ ስለ ነፍሱ ቤዛ ምን ይሰጣል? 👇👇👇👇👇👇 @wcuevang
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
