cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

WORLD PHILOSOPHICAL LIFE 🌎

🌎W PHILOSOPHICAL life ፍልስፍና_~እራስን ከማወቅ ይጀምራል.... ᜰ꙰ꦿ➢የፍለስፍና ወጎች ᜰ꙰ꦿ➢ጥንታዊ ፍልስፍናዎች ᜰ꙰ꦿ➢ግሪካዊያን ፍልስፍናዎች ᜰ꙰ꦿ➢ግጥሞች.ታሪኮች..ልብ-ወለድ and school of law course with , world politics book ᜰ꙰ꦿ➢የተለያዩ ሀሳቦችን ወደ እናንተ እናደርሳለን ~ለማንኛውም አስተያየት @wpl# ☞Join በማለት ቤተሰብ ይሁኑ.!!

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استزبان مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
پست‌های تبلیغاتی
198
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ሙስሊም ወገኖቼ ሁሉ በሙሉ ! እንኳን ለኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ !!! እንኳን ለዒድ አል አደሐ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የደስታ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ። ኢድ ሙባረክ 💚💛 🕊 ነገ መልካም ይሆናል ! 🕊 💫 Wpl 💫
نمایش همه...
00:12
Video unavailableShow in Telegram
Video
نمایش همه...
Video
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
በታንዛኒያ አንድ የፓርላማ አባል በአካባቢያችን መንገድ ሊሰራልን አልቻለም የሚለዉን ቅሬታ ለማሰማት በእጃቸዉ መቆማቸዉ መነጋገሪያ ሆኗል አንድ የታንዛኒያ የፓርላማ አባል በምርጫ ክልላቸው ባለው የመንገድ ችግር በመበሳጨት በፓርላማው ቅሬታቸውን ያቀረቡበት መንገድ ትኩረት ስቧል፡፡የምቡሉ ሰሜናዊ ምርጫ ክልል የፓርላማ አባል የሆኑት ፍላቲ ማሳይ ሰኞ ዕለት በበጀት ግምት ላይ አስተያየት ሲሰጡ መንግስት በምርጫ ክልላቸው 100 ኪ.ሜ ያለው የአስፋልት መንገድ ለመገንባት የገባውን ቃል እንዲፈጽም ጠይቀዋል። የተገባው ቃል ባለፉት ሶስት በጀት ዓመት ችላ መባሉን ተናግረው እጃቸዉን በጠረጴዛ ላይ አድርገዉ በእጃቸዉ ቆመዋል፡፡ አንዳንዶች የሰርከስ ትርኢት የምንመለከት ነበር የመሰለን ሲሉ ሌሎች ደግሞ ጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጠው ያደርጋል ሲሉ ተስፋ እንዳላቸዉ ገልጸዋል፡፡ "ይህን ሁሉ የማደርገው ህዝቤ በመንግስት ቅር እንደተሰኘ ለመግለጽ ነው። መንግስት የገባዉን ቃል መተግበር አለበት ብለዋል፤ ሌሎች አካባቢዎች ቃል የተገባላቸዉን እያገኙ እኛ የምቡሉ ሰዎች ለምን ምንም አናገኝም?" ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ Wpl
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
አነጋጋሪው መረጃ‼️‼️ በደቡብ ሱዳን በአንዲት ሴት ግድያ ጥፋተኛ የተባለዉ በግ በሶስት ዓመት እስር እንዲቀጣ ተወስኗል!! በደቡብ ሱዳን በአንዲት አዛዉንት ደረት ላይ ተደጋጋሚ ጥቃት በመፈጸም ለሞት ዳርጓል የተባለዉ በግ በሶስት አመት እስር እንዲቀጣ መወሰኑን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።የበጉ ባለቤትም ለተጎጂው ቤተሰብ አምስት ላሞችን እንዲከፍል በደቡብ ሱዳን ሩምቤክ ከተማ የሚገኘው የአካባቢው ፍርድ ቤት ብይን ሰጥቷል። ሱዳን ቱዴይ ጋዜጣ እንደዘገበው በደቡብ ሱዳን ሌክ ግዛት የሚገኘው የሩምቤክ ፖሊስ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ሴትየዋን የገደለዉን በግ በቁጥጥር ስር አውሏል። በጉ በሴቲቱ ላይ ጥቃት ሰንዝሮ ከመሞቷ በፊት ደረቷ ላይ ብዙ ጊዜ እንደመታት ተነግሯል። በልማዳዊ ህግ ማንኛውም የቤት እንስሳ ሰውን የገደለ እንደሆነ ለሟች ቤተሰብ ካሳ ይከፈለዋል የሚል መመሪያ ቢኖርም የቤት እንስሳ በእስር መቀጣቱን አነጋጋሪ ሆኗል። Wpl
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
up‼️ ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ በ2022 የታይምስ መጽሔት 100 ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ዝርዝር ውስጥ ተካተቱ። መጽሔቱ ይፋ ባደረገው የ100 ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ዝርዝር በአመራር ዘርፍ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መካተታቸውን አስታውቋል። መፅሔቱ በፖለቲካ እና ዲፕሎማሲ፣ በኪነጥበብ፣ በስፖርት፣ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ፣ በአመራር እንዲሁም በሌሎችም ዘርፎች በተያዘው የፈረንጆቹ 2022 በዓለማችን ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ያሳረፉ ግለሰቦችን አንባቢዎቹ እንዲመርጡለት በዕጩነት አቅርቦ ነበር፡፡ከቀረቡት በርካታ ዕጩ ተመራጮች ውስጥ በመሪነት 23 ግለሰቦችን አካቷል፡፡ በዚህ ተፅዕኖ ፈጣሪ መሪዎች ዝርዝር ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ በተጨማሪ የአሜሪካው ጆ ባይደን፣ ጦርነት ላይ የሚገኙት የሩስያው ቭላድሚር ፑቲን እና የዩክሬኑ ዘሌንስኪ እንዲሁም የምስራቅ አፍሪካዋ ታንዛንያ መሪ ሳሚያ ሱሉሁ ሐሰን ተካተውበታል፡፡ ታይም በድረገጹ ይፋ ባሠፈረው መረጃ በ2019 ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ከጎረቤት ኤርትራ ጋር ሰላም ማስፈናቸውን ተከትሎ የኖቤል የሰላም ሽልማትን ማሸነፋቸውን እንዲሁም 19 ወራት ባስቆጠረው የትግራይ ጦርነት ተከትሎ የደረሰውን ጥፋትና ከአለም አቀፉ ማህበረሰብ ጋር አመራራቸው ያለውን ግንኙነትና ሌሎች ሁነቶችን አንስቷል። Wpl
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
#ሃይማኖት ኢትዮጵያ የሁሉም አማኞች ብቻ ሳትሆን "እምነት የለኝም" የሚሉ ዜጎች ጭምር መሆኗን መዘንጋት የለብንም። የበላይ እና የበታች ሳይኖር ሁሉም እምነቶች በእኩልነት ሊስተናገዱ ይገባል። #ባህል በሀገሪቱ ያሉ ሁሉም ባህሎች እኩል የመልማት እድል ሲያገኙ ጠቃሚ የሆኑትን ማኅበረሰቡ ራሱ ተንከባክቦ የሚያሳድጋቸው ሲሆን ጎጂዎቹን እና ኋለቀሮቹ በሂደት መክሰማቸውን ማስቆም አይቻልም። #ቋንቋ በሀገራችን ከ80 በላይ ነገዶች የሚናገሯቸው ልዩ ልዩ ቋንቋዎች እንዳሉ ይታመናል። ሁሉም የአፍ መፍቺያ ቋንቋዎች ልዩነት ሳይደረግባቸው ለተናጋሪዎቻቸው እኩል አገልግሎት የመስጠት እድል ሊሰጣቸው ይገባል። ይህ ማለት ግን ቴክኖሎጂን እና ሥልጣኔን ተከትሎ የሚጠፉ ቋንቋዎች አይኖሩም ማለት አይደለም ለምሳሌም በቅርቡ The Australian National University (ANU) ጥናት እንዳመለከተው በአሁኑ ወቅት በዓለማችን 7,000 ያህል ቋንቋዎች የሚነገሩ ሲሆን በአንድ ትውልድ እድሜ (በ25 ዓመታት) ግማሹ ሙሉ በሙሉ ይጠፋሉ። የብሔር/ የሃይማኖት ፖለቲካ! ብሔርም ሆነ ሃይማኖትን የፖለቲካ ማጠንጠኛ ካደረግናቸው በሀሳብ ልዕልና ላይ ከሚመሠረት ምክንያታዊነት ይልቅ በደመነፍስ በሚመራ መንጋ ወደመነዳት ስለምንወርድ ፍጻሜያችን ውድመት ብቻ ነው።
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
ሰበር ዜና❗️ በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ የኢድ ሰላት ከመሰገዱ በፊት በሰማዕታት ሀውልት አካባቢ ጥቂት ግለሰቦች ባስነሱት ረብሻ በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን የከተማዋ ፖሊስ አስታውቋል!! ምዕመኑ አሁን ተረጋግቶ ወደ መጣበት እየተመለሰ ስለሆነ ህብረተሰቡ በመረጋጋት ራሱንና አካባቢውን እንዲጠብቅ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡ በቀጣይ የረብሻውን መነሻና ከዚህ ጋር ተያያዥነት ያላቸውን ሌሎች ጉዳዮችን ለህዝብ እንደሚያሳውቅ መግለጹን ከአዲስ አበባ ፖሊስ every መረጃ ያመለክታል፡፡ በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን የከተማዋ ፖሊስ አስታውቋል። ምዕመኑ አሁን ተረጋግቶ ወደ መጣበት እየተመለሰ ስለሆነ ህብረተሰቡ በመረጋጋት ራሱንና አካባቢውን እንዲጠብቅ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡ በቀጣይ የረብሻውን መነሻና ከዚህ ጋር ተያያዥነት ያላቸውን ሌሎች ጉዳዮችን ለህዝብ እንደሚያሳውቅ መግለጹን ከአዲስ አበባ ፖሊስ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ Wpls
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
እንኳን ለ1443ኛዉ ኢድ አል-ፈጥር በዓል አደረሳችሁ!! ውድ የእስልምና እምነት ተከታይ ለሆናችሁ የኢትዮ መረጃ NEWS ቤተሰቦች እንኳን ለ1443ኛዉ ኢድ አል-ፈጥር በዓል አደረሳችሁ ። ውድ የኢትዮ መረጃ NEWS ቤተሰቦቻችን በዓሉን ስናከብር ፤ የተቸገሩ ወገኖቻንን አለንላችሁ በማለት ፣ የወደቁትን በማንሳት ፣ በሀዘን ላይ ያሉ ወገኖችን በማፅናናት ፣ ከክፉ ድርጊት እና ሀሳብ ርቀን ሊሆን ይገባል ። ኢድ አል-ፈጥር በዓል ስናከብር ፤ በሰላም እጦት ፣ በግጭት ፣ በድርቅ ክፉኛ የተጎዱ ወገኖቻችንን እያሰብን ፤ በገዛ ቄያቸው ከሞቀው ቤታቸው ተፈናቅለው ሜዳ ላይ የወደቁትን፤ በፀሃይና ዝናብ የሚንከራተቱትን ፤ የተቸገሩትን ፣ የሚወዱትን ተነጥቀው በጥልቅ ሀዘን ላይ የሚገኙትን ፣ ታመው በየሆስፒታሉ የተኙትን ፣ በየሰው ሀገር በስደት ስቃያቸውን እያዩ ያሉ ወገኖቻችንን እያሰብን ፤ በግልም ፤ በሀገርም ላለብን ችግር ሁሉ አምላክ መፍትሄ እንዲያበጅልን እየተማፀንን እንድናሳልፍ አደራ እንላለን። የሰላም፣ የመተሳሰብና የበረከት ኢድ አል-ፈጥር በዓል ያድርግልን ! ፈጣሪ ሀገራችን ሰላም ያድርግልን ፤ በምድር ላይ ያሉ የሰው ልጆችን ሁሉ ይጠብቅልን። ኢድ - ሙባረክ!! Wpl
نمایش همه...
ጉባኤው ወንጀልን በሌላ ወንጀል ለማረም መሞከር ሕገ ወጥነት ነው ሲል አስታወቀ! የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ወንጀልን በሌላ ወንጀል ለማረም መሞከር ሕገ ወጥነት ነው ሲል አስታውቋል፡፡ ጉባኤው በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ ÷በስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አብያተ ክርስቲያናት እና በፕሮቴስታንት አማኞች ቤተ አምልኮዎች ላይ የተፈፀመውን ሕገ ወጥና የወንጅል ተግባር አውግዛለሁ ብሏል። በደቡብ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል፣ በስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አብያተ ክርስቲያናት እና በፕሮቴስታንት አማኞች ቤተ አምልኮዎች ላይ የተፈፀመውን ሕገ ወጥና የወንጅል ተግባርን የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በእጅጉ ያወግዛል፡፡ ተግባሩ በየትኛውም ሃይማኖት ተቀባይነትየሌለው ከመሆኑም በላይ ደረቅ ወንጅልና በህግ ሊያስጠይቅ የሚገባው ተግባር መሆኑንምጉባኤያችን በጽኑ ያምናል፡፡ ሚያዚያ 18 ቀን 2014 ዓ.ም በአማራ ክልል ጎንደር ከተማ የተፈፀመወን አስነዋሪ ተግባርን አስመልክቶ ጉባኤያችን በትናንትናው ዕለት ዕለት ባወጣው መግለጫ ተግባሩን አምርሮ በማውገዝ ጥፋትን በጥፋት፣ ወንጀልን በወንጀል ለማረም የሚደረግ ሙከራ እንዳይኖር ማስገንዘባችን ይታወሳል፡፡ ይሁን እንጅ ትናንት በሆነው ሁሉ አዝነንሳንጨርስ ይህ መከሠቱ በእጅጉ አሳዝኖናል፡፡ ሁሉም ሃይማኖቶች ሰላምን የሚሰብኩ፣ ትህትናን የሚስተምሩና ለሌሎች ስለመኖርና መስዋዕት ስለመክፈል የሚገዳቸው እንደሆኑ የሚታወቅ ቢሆንም በሃይማኖት ስምና ሃይማኖትን ሽፋን በማድረግ የሚፈፀመው ሁሉ ሕገ ወጥና ደረቅ ወንጀል እንደሆነ ታውቆ መንግስት ሕግና ስርኣትን እንዲያስጠበቅ ጉባኤያችን አበክሮ ይጠይቃል፡፡ መንግስት ሕግና ስርኣትን ለማስፈፀም እንዲችል ቀደም ብሎ ያወጣቸውን ህጎችን ሁሉ ተፈፃሚ ሊያደርግ ይገባል፡፡ ሕዝበ ሙስሊሙም ይሁን ሕዝበ ክርስቲያኑ በየትኛውም አካባቢ የተከሠተው ችግርና የደረሰው ውድመት ሃይማኖታዊ መሠረት የሌለው መሆኑ በመገንዘብ አካባቢያቸውን በጋራ በመጠበቅ፣ ችግሮች እንዳይባባሱም አንዱ ሌላውን በመጠበቅ የበኩላችሁን እንዲወጡ እየጠየቅን ችግር ፈጣሪዎችንም በማጋለጥና አሳልፎ ለሕግ አካላት መስጠት እንደሚገባ ለማሳሰብ እንወዳለን፡፡ በማኅበራዊ ሚዲደያው መልዕክት የምትላላኩ አካላትም በምትጽፉት ጽሁፍና በምታስተላልፉት መልዕክት ሀገራችሁንና ወገናችሁን ለከፋ ጉዳት እንዳይጋለጥ ሁሉንምተግባር በማስተዋል እንድትከውኑ እየጠየቅን በሃይማኖት ስም የሚደረግ የጥላቻ ቅስቃሳን ባለማጋራት ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ አደራ እንላለን፡፡ ፈጣሪ ኢትዮጵያን ይባርክ! Wpl
نمایش همه...