cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

💠አምደ ሐይማኖት💠ዘ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ⛪️

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው ;ሰነፎች ግን ጥበብንና ተግሳጽን ይንቃሉ " ምሳሌ 1:7 👉 የቻናሉ አላማ ✔️💠የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስርዓት የጠበቁ ትምህርቶዎችን ✔️💠መንፈሳዊ ጥያቄና ዝማሬዎች ✔️💠ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን መረጃ ያገኙበታል አስታየት @Godoliyaswe28 ☞ ለመቀላቀል ይሕንን ይጫኑ

نمایش بیشتر
Advertising posts
1 686مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

“ወዳጄ ሆይ! የትዕቢት መርዝ ተጠራቅሞ አብጦብሃልን? እንኪያስ ወደ ቅዱስ ሥጋዉና ክቡር ደሙ ቅረብ፤ ስለ ወዳጆቹ ሲል አርአያ ገብርን የነሣ ትሑቱ ጌታም ትሕትናን ያስተምርሃል፡፡ የስግብግብነት ትኩሳት አስቸግሮሃልን? ወደ ቅዱስ ሥጋዉና ክቡር ደሙ ቅረብ፤ ደግነትንም ትማራለህ፡፡ የምቀኝነት ብርድ አስቸግሮሃልን? እንኪያስ ወደ ሰማያዊው መዓድ ቅረብ፤ ምህረት ማድረግንም ገንዘብ ታደርጋለህ፡፡ ትዕግሥትን የማጣት እከክ ይዞሃልን? እንኪያስ ወደ ቅዱስ ሥጋዉና ክቡር ደሙ ቅረብ፤ ራስን መግዛትንም ገንዘብ ታደርጋለህ፡፡ በመንፈሳዊ ሕይወትህ ልል ዘሊል ብትሆን ይህን መንፈሳዊ መዓድ ተመገብና ብርቱ ትሆናለህ፡፡ ቆሽሸሃልን? እንኪያስ ወደዚሁ መብልና መጠጥ ቅረብ ብዬ እመክርሃለሁ፤ ንጽሕናንም ገንዘብ ታደርጋለህ፡፡” ቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያ
نمایش همه...
5👍 2
❤ጎሳ-ልብየ❤ ጎሳ ልብየ ቃለ ሰናየ/2/ ወአነ አይድ ቅዳሴሃ ለማርያም/4/ አዝ ======= እኔስ የማርያምን ውዳሴዋን እናገራለው እንደ አባቴ ዳዊት በበገና እዘምራለው ቀን ከለሊት ሳልል ለምስጋና እተጋለሁ የኃጢአቴ ቁስል እንዲፈወስ አጮሀለው ምርኩዜ ነሽና እመቤቴ ባንቺ እመካለው አዝ ======= ኦ እመቤቴ በእውነት እንወድሻለን የእውነተኛ መብል ክርስቶስን ወለድሽልን ምክንያተ ድህነት ድንግልማርያም የአምላክ መገኛ ባማላጅነትሽ በመታመን እንጮሀለን እኛ ምረትን አሰጪን ኪዳነምህረት ያለም መዳኛ አዝ ======= ስለ ቸርነትሽ እመቤቴ ለእኔ እናቴ ነሽ ስለ ንግስትነትሽም እመቤቴ ነሽ ዝናባት ሳያጠጡት አየራትም ሳያሳድጉት ሰማያዊ እንጀራ የሰጠሽን ቤተልሔማዊት ቅድስተ ቅዱሳን የኖህ መርከብ ያምላክ እናት አዝ ======= ቃና ዘገሊላ በሰርጉ ቤት በዚያ ተገኝተሽ ሳለሽ ውሃውን ወደወይን ባንቺ ምልጃ እንዳስለወጥሽ ዛሬም የኔ ሂወት ወይኑ አልቆ ባዶ ሆኗልና አንቺ የአምላክእናት ንፅህት ቅድስት ርህርይተ ሕሊና ህይወቴን አንፅተሽ ቀድሰሺው ሙይው በምስጋና "ጎሳ ልብየ ቃለ ሰናየ" ቅዳሴ ማርያም አባ ሕርያቆስ ዘብህንሳ ጥቅምት 2 ይህቺ ቀን ለቅዱሱ የልደቱና ዕረፍቱ መታሰቢያ ናት:: የቅዱሱ በረከት የእመቤታችን አማላጅነት አይለየን
نمایش همه...
👍 2 1
ይቅርታ በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ … ከሠራተኞችህ አንዱ ከአንተ መቶ ቅንጣት ወርቆችን ተበደረ እንበል፡፡ ሌላ ሰው ደግሞ ከዚህ ሠራተኛህ የተበደረው ጥቂት ብር ነበረው፡፡ ከዚህ ሠራተኛህ የተበደረው ያ ሰውም ወደ አንተ መጥቶ ቸርነትን እንድታደርግለት ለመነህ፡፡ አንተም ሠራተኛህን ጠርተህ፡- “የዚህን ሰው ዕዳ ተውለት፤ ከእኔ ከተበደርከው ዕዳህም እቀንስልሃለሁ” ብትለውና ይህ ሠራተኛህ ከዚያ በኋላ በዚያ ሰው ላይ ቢጨክንና ቢከፋ ይህን ሠራተኛ ከእጅህ ሊያድነው የሚችል ሰው አለን? እጅግ እንደ ነቀፈህ አድርገህ ቈጥረህ ብዙ ግርፋትን አትገርፈውምን? [እንዲህ ብታደርግ] እጅግ ፍትሐዊ ነው፡፡ እግዚአብሔርም የሚያደርገው እንደዚህ ነው፤ በዚያች ዕለተ ምጽአት ላይ እንዲህ ይልሃልና፡- “አንተ ክፉና ተንኰለኛ ባሪያ ያንን ሰው ይቅር ብትለው ይቅርታው የአንተ ነበርን? ለእርሱ እንድታደርግለት የታዘዝከው ከእኔ የተበደርከውን ነበር፡፡ ያልኩህ ‘ዕዳዉን ብትተውለት እኔም እተውልሃለሁ’ ነው፡፡ በእውነት እንዲህ ይህን ኹኔታ ጨምሬ ባልነግርህም እንኳን ስለ እግዚአብሔር ብለህ ዕዳዉን ትተውለት ዘንድ በተገባህ ነበር፡፡ ነገር ግን እንደ ወዳጅ ኾኜ ውለታን ጠየቅሁህ እንጂ እንደ ጌታ አላዘዝኩህም፡፡ የጠየቅሁህ የእኔ ከኾነው ነው፤ ይህን ካደረግህም እጅግ በረከተ ሥጋን በረከተ ነፍስን እንደምሰጥህ ቃል ገብቼልህ ነበር፡፡ ነገር ግን ምንም ልትሻሻል አልቻልክም፡፡” ከዚህም በላይ ሰዎች እንደዚህ ሲያደርጉ የሚቀንሱት የዕዳ መጠን ሠራተኞቻቸው ላበደሩአቸው ሌሎች ሰዎች የቀነሱትን ያህል ነው፡፡ ለምሳሌ እንበልና አንድ ሠራተኛ ከአሠሪው መቶ ቅንጣት ወርቅን ይበደራል፡፡ ሌላው ሰው ደግሞ ከዚህ ሠራተኛ ዐሥር ቅንጣት ይበደራል፡፡ ሠራተኛው ዐሥር ቅንጣት ላበደረው ብድሩን ቢተዉለት አሠሪው ግን መቶ ቅንጣቱን አይተውለትም፤ የሚተውለት ዐሥር ቅንጣቱን ብቻ ነው፤ ሌላዉን እንዲመልስለት ይፈልጋል፡፡ በእግዚአብሔር ዘንድ ግን እንደዚህ አይደለም፡፡ አንተ ለባልንጀራህ ጥቂቱን ስትተውለት እግዚአብሔር ደግሞ ዕዳህን ኹሉ ይተውልሃል፡፡ ይህስ [መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ] የት ይገኛል? [ጌታችን] ስለ ጸሎት ባስተማረው ትምህርት ውስጥ አለ፡፡ “ለሰዎች ኃጢአታቸውን ይቅር ብትሉ የሰማዩ አባታችሁ እናንተን ደግሞ ይቅር ይላችኋልና” እንዲል (ማቴ.6፡14)፡፡ በ“መቶ ዲናር” እና በ“እልፍ መክሊት” መካከል ያለው ልዩነት ያህል ለሰው ይቅር የምንለው ዕዳና ከእግዚአብሔር ይቅር የሚባልልን ዕዳም አይነጻጸርም (ማቴ.18፡24፣28)! እንግዲህ መቶ ዲናርን ዕዳ ይቅር ብሎ እልፍ መክሊትን የሚቀበል ኾኖ ሳለ ይህቺን ጥቂት ዕዳስ እንኳን ይቅር ሳይል ጸሎቱን በራሱ ላይ የሚያደርስ ይህ ሰው የማይገባው ቅጣት እንደ ምን ያለ ቅጣት ነው? ምክንያቱም “እኛ የበደሉንን ይቅር እንደምንል በደላችንን ይቅር በለን” ብለህ እየጸለይክ ሳለ አንተ ግን ከዚያ በኋላ ይቅር የማትል ከኾነ እግዚአብሔር ምሕረቱን ወይም ቸርነቱን ኹሉ እንዲያርቅብህ ካልኾነ በቀር ሌላ ምንም እየለመንከው አይደለም፡፡ “እኔ ይቅር በለኝ ብቻ ነው እንጂ የበደሉኝን ይቅር እንደምል በደሌን ይቅር በለኝ ብዬ አልጸልይም” የሚል ሰው ደግሞ አለ፡፡ ታዲያ ይኼ ምንድን ነው? አንተ እንዲህ ብለህ ባትጸልይም እግዚአብሔር ግን እንዲህ አያደርግም፤ ይቅር የሚልህ አንተ ይቅር ስትል ነው፡፡ ይህም ከዚያ በኋላ እንዲህ ብሎ ግልጽ አድርጎታል፡- “ለሰዎች ኃጢአታቸውን ይቅር ባትሉ የሰማዩ አባታችሁም ኃጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም” (ማቴ.6፡15)፡፡ ስለዚህ ጸሎቱን ሙሉ ባትደግመው ወይም ዕለት ዕለት እንደዚያ ብለህ ስትጸልይ ፈርተህ ከባልንጀራህ ጋር እንድትታረቅ ብሎ እንድትጸልው ባዘዘህ መንገድ ሳይኾን ቈርጠህ ብትደግመው እንኳን ደገኛ መንገድ ነው ብለህ አታስብ፡፡ “ብዙ ጊዜ ለምኜዋለሁ፤ ተማጽኜዋለሁ፤ ማልጄዋለሁ፤ ሊታረቀኝ ግን አልቻለም” ብለህ አትንገረኝ፡፡ እስክትታረቀው ድረስ በፍጹም አታቁም፡፡ ጌታችን ሲናገር፡- “መባህን ትተህ ኺድ፤ ወንድምህንም ለምነው” አይደለምና፡፡ ያለው፡- “ኺድ፤ ታረቅ” ነው (ማቴ.5፡24)፡፡ ስለዚህ ምንም እንኳን ብዙ ጊዜ ለምነኸው ቢኾንም እስክታሳምነው ድረስ ግን ይህን ማድረግህን አታቋርጥ፡፡ እግዚአብሔር ዕለት ዕለት ይለምነናል፤ እኛ ግን አንሰማውም፡፡ ኾኖም [አልሰሙኝም ብሎ] መለመኑን አላቋረጠም፡፡ ታዲያ አንተ ባልንጀራህን ለመለመን ትታጀራለህን? እንዲህ የምታደርግ ከኾነስ ልትድን የምትችለው እንዴት ነው? የይቅርታ ልብ ይስጠን።
نمایش همه...
#ከፍቅር_ጉዞ_ወደ_ከንቱ_መመላለስ መንፈሳዊ ሕይወት እግዚአብሔርን በመውደድ ላይ የተመሰረተ ሲሆን ይህ ፍቅርም የሁሉም ነገር መነሻ ነጥብ ሊሆን ይገባል። የምንፀልየው እግዚአብሔርን ስለምንወደው ነው "ነፍሴ አንተን ተጠማች ሥጋዬ አንተን እንዴት ናፈቀች እንጨትና ውሃ በሌለበት ምድረ በዳ" መዝ. 62፥1 "አቤቱ ሕግህን እንደምን እጅግ ወደድሁ! ቀኑን ሁሉ እርሱ ትዝታዬ ነው" መዝ. 118፥97 የሚለውን የቅዱስ ዳዊትን ቃል እያሰብን። የመንፈስ ዝለት ካለ ግን ጸሎት ከፍቅር የመነጨ መሆኑ ቀርቶ ህሊናችን እንዳይወቅሰን ስንል ብቻ የምንፈጽመው ተግባር ይሆናል። የእውነተኛ ጸሎት መለኪያ የሆኑትን ከፍተኛ ስሜትና መመሰጥን ያጣል። ትሕትና አክብሮት ወይም ፍቅር የሌለው ይሆናል ሌሎችም መንፈሳዊ ተግባራት ሁሉ እንዲሁ ከመንፈሳዊነት ያፈነግጣሉ። ምናልባት መንፈሳዊ ሕይወትን ስጀምር ለእግዚአብሔር ፍቅር ኖሮን ሊሆን ይችላል። ነገር ግን አልገፋንበትም። ለምን?፦ ✞ ይህ ድካም የመታጣው ምን አልባት በጸሎት ጊዜ ከተመስሥጦ ይልቅ በብዛት ላይ ማተኮራችንና በቀመር በሚመራ ሕይወት ለመመራት በማሰባችን ይሆናል። ✞ ፀሎት ስናደርግ እኛን የሚያሳስበን ምን ያሕል ምዕራፍ እንደደገምን እንጂ እነዚህን በምን ዓይነት መልኩ እንደጨረስን አይደለም። ✞ በትዕዛዝ የተደነገገው የምዕራፎች ቁጥር ላይ ከደረስን በቂዬ ነው ብለን እግዚአብሔር በጸሎታችን በአምልኮታችን ተደስቷል ወይ? የሚለውን ዐብይ ጥያቄ ግን አናስተውለውም። እዚህ ነጥብ ላይ ስንደርስ ቅዱስ ማር ይሳሐቅ እንዲህ በማለት ያስጠነቅቃል። "በእግዚአብሔር ፊት የቆምሁት ቃላት ለመቁጠር አይደለም።" ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም እልፍ ቃላት በልሳን ከመናገር ይልቅ አምስት ቃላት በማስተዋል መናገርን መርጧል።(1ቆሮ 14፥19) ብዙዎቻችን ግን ቁጥሩና ብዛቱ ለይ ስለምናተኩር ጸሎታችን በችኮላ ስለሚደረግ ማስተዋል የለበትምና ምንም እርባና አይኖረውም። ስለዚህ ጸሎት መጸለይ ስላለበት ብቻ የሚፈጸም ግዲታ ወደ መሆን ሲለወጥ ከእግዚአብሔር ጋር በፍቅር በመነጋገርራችን ደስተኛ ሳንሆን ህጉን መተግበር ብቻ አላማችን ይሆናል ችኮላና ማነብነብ ማስተዋልን ይቀንሳል። ይህ አይነት የመንፈስ ዝለት ባጠቃን ጊዜ ለራሳችን " እንደ ቀራጩ ጥቂትነገርም ሆነ በቀኝ እንደተሰቀለው ወንበዴ አንድ ዓርፍተ ነገር ብናገር ጸሎቴ ከእግዚአብሔር ጋር ከልብ እገናኝ ዘንድ ነው። ልንል ይገባል። በብዛትና ያለፍቅር ሕግን ለመፈጸም ብቻ ከሚል ሕይወት ለመላቀቅ እንሞክር። በማስተዋልና በጥልቀት ስሜት ሆነን በመንፈስ ለመጸለይ እንትጋ። ይህንንም በሌሎችም መንፈሳዊ ተግባራት ላይ እንተርጎመው። '#የመንፈስ_ዝለት ከሚለው #የአቡነ_ሽኖዳ መጽሐፍ የተወሰደ'
نمایش همه...
👏 1
#የወደደኝ_ጌታ የወደደኝ ጌታ ምን አድርጌለት ነው ብዘምርለትም ያንስበታል ይኽው ከውድቀቴ አንስተህ ድካሜን ያገዝኸኝ ሰባራውን ድልድይ ገጥመህ ያሻገርከኝ በኢያሪኮ መንገድ ስለምን ቁጭ ብዬ ብርሃን እጅግ ናፍቆኝ ከሰው ተገልዬ የብርሃን ጌታ ወደ እኔ መጣና ዓይኔን አበራልኝ በእጁ ዳሰሰና #አዝ ለብዙ ዘመናት አልጋ ላይ ተኝቼ የሚረዳኝ አጣሁ ጠሉኝ ዘመዶቼ የእኔ ጌታ አምላኬ ወደእኔ መጣና አልጋህን ተሸከም አለኝ ፈወሰና #አዝ አሥራ ሁለት ዓመት ደም እየፈሰሰኝ ምራቅ እየተፉ ሁሉም ሲያንቋሽሹኝ የጌታዬ ልብሱን ጫፉን ብዳስሰው ኃይል ከእርሱ ወጣ ደሜን ቀጥ አረገው #አዝ ሰካራም ዘማዊ ወንበዴ ነበርኩኝ ያመፀኞች መሪ ደምን ያፈሰስኩኝ ዛሬ ግን ታሪኬን ጌታ ቀይሮታል ለኃያሉ ጌታ ምስጋና ይገባል 💚💛❤💚💛❤💚💛❤💚💛❤ @Amdehaymanotzeortodoxtewahdo @Amdehaymanotzeortodoxtewahdo 💚💛❤💚💛❤💚💛❤💚💛❤
نمایش همه...
2
"በጎ ነገር አግኝተህ እንደ ሆነ እግዚአብሔርን አመስግን፤ ያም በጎ ነገር ከአንተ ጋር ጸንቶ ይኖራል፡፡ በጎ ያልሆነ ነገር ደርሶብህ እንደሆነም እግዚአብሔርን አመስግን፤ ያም በጎ ያልሆነ ነገር ወደ በጎ ነገር ይቀየራል፡፡" ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
نمایش همه...
3
🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹 † እንኳን ለድንግልና ሰማዕት አርሴማ ቅድስት ወዮሐንስ ወንጌላዊ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። † † በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! † 🌹  †  ቅድስት አርሴማ ድንግል  †   🌹 †  እናታችን ቅድስት አርሴማን በምን እንመስላታለን? እርሷ በአድማስ ላይ ተቀምጦ እንደሚያበራ እንቁ ናትና ክብሯ ብዙ ነው:: መድኃኒታችን ክርስቶስ በወንጌል እንዳለው "በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሠወር አይቻላትምና" የሰማዕቷ ሕይወት በፊታችን እንደ ብርሃን ተገልጦ ይታያል:: ¤ ቅድስት አርሴማ እንደ ልጅ ወላጆቿን በመታዘዝ ደስ ያሰኘች ቡርክት ናት:: ¤ ቅድስት አርሴማ ይሕ ቀረሽ የማይሏት ውብ ናት:: ¤ ቅድስት አርሴማ ድንግል ናት:: ¤ ቅድስት አርሴማ ባሕታዊት ጻድቅ ናት:: ¤ ቅድስት አርሴማ ኃያል ሰማዕት ናት:: ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ :- አበው በትውፊት እንደ ነገሩን ከሆነ ቅዱሱ ጐርጐርዮስ የታላቋ ሰማዕት ቅድስት አርሴማ ትልቅ ወንድም ነው:: በዜና ሰማዕታት ተጽፎ እንደሚገኘው በዚያ የመከራ ዘመን ቅዱስ ጐርጐርዮስ ሦስት ኃላፊነቶች ነበሩበት :- ፩. ቅድስት አርሴማን ጨምሮ ደናግሉን ማጽናት:: ፪. ትምሕርተ ቤተ ክርስቲያንን በሚገባ ማጥናት:: ፫. የሚመጣውን መከራ ለመቀበል ራሱን ማዘጋጀት:: ቅዱሱ ሦስቱንም ኃላፊነቶች በሚገባ በመወጣቱ ከራሱ አልፎ ለሌሎቹ አርአያ መሆን ቻለ:: ያቺን ንጽሕት አርበኛ ቅድስት አርሴማንም አጽንቶ የደናግሉ መሪ አደረጋት:: መከራው በጣም ገፍቶ እስከ መጣበት ጊዜ ድረስ በአንድ የደናግል ገዳም ውስጥ ሆነው ይጸልዩ: ይጾሙ: ገዳማዊ ሥራንም ይሠሩ ነበር:: ለዚህም ነው ቅድስት አርሴማና ቅዱስ ጐርጐርዮስ ጻድቃን የምንላቸው:: በኋላ ግን ማሕደረ ሰይጣን ዲዮቅልጢያኖስ በመልኳ ተማርኮ ቅድስት አርሴማን ካላገባሁ በማለቱ ቅዱስ ጐርጐርዮስ ድንግሏን አርሴማን ጨምሮ ፲፳፯ ክርስቲያኖችን ይዞ ወደ አርማንያ ተሰደደ:: በአርማንያም በአንድ ገዳም ውስጥ ተደብቀው በጾምና በጸሎት ለጥቂት ጊዜ ቆዩ: ነገር ግን ረሃብ ፈጃቸው:: የሚላስ የሚቀመስ ነገር በአካባቢው ባለ መኖሩ ቅዱስ ጐርጐርዮስ ወደ ከተማ ለመውጣት ተገደደ:: በዚያም በድርጣድስ ቤተ መንግስት ውስጥ ባርነት ተቀጠረ:: በሚያገኛት ገንዘብም ወገኖቹን ይረዳ ነበር:: መከራው ግን አለቀቃቸውም:: ርጉም ዲዮቅልጢያኖስ ቅዱሳኑ ወደ አርማንያ መሔዳቸውን ስለ ሰማ ይዞ እንዲልክለት ድርጣድስን ላከው:: ድርጣድስ ግን ቅድስት አርሴማን ባያት ጊዜ ከውበቷ የተነሳ መታገስ ባለመቻሉ "ካላገባሁሽ" አላት:: ድንግሊቱ ግን "እኔ የክርስቶስ ሙሽራ ነኝ: አይሆንም" አለችው:: ሊያስፈራራት ሞከረ:: ዐይኗ እያየ ደናግሉን ጨፈጨፋቸው:: አልሳካልህ ቢለው በአደባባይ በግድ ሊያገባት ቢሞክር እጁን ጠምዝዛ በሰው ሁሉ ፊት መሬት ላይ ጣለችው:: እጅግ ስላፈረ አስገረፋት: አሰቃያት: ዐይኗንም አወጣ:: በመጨረሻም አንገቷን አስቆርጦ ከሰማዕታቱ ጋር ተራራ ላይ ጣላት:: ከነገር ሁሉ በኋላ ድርጣድስና ባለሟሎቹ ለአደን በሔዱበት ርኩስ መንፈስ ወደ አውሬነት [እሪያነት] ቀየራቸው:: የንጉሡ እንስሳ [አውሬ] መሆን በአርማንያ ታላቅ ድንጋጤን ፈጠረ:: የንጉሡ እህት ስታለቅስ በራዕይ "ለእመ ኢያዕረግምዎ ለጐርጐርዮስ አልብክሙ ድኂን - ጐርጐርዮስን ከተቀበረበት ካላወጣችሁት አትድኑም" አላቸው:: ወዲያውም ቆፍረው አወጡት:: ቅዱሱ እንደ ወጣ ዕረፍትን አልፈለገም:: ለ፲፭ ዓመታት ቀባሪ አጥቶ የተበተነውን የቅድስት አርሴማንና የሰማዕታቱን አጽም ሰብስቦ በክብር አኖረው:: ድርጣድስና ባለሟሎቹንም ወደ በርሃ ሒዶ ፈወሳቸው:: የሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ አጽም በ፲፬ኛው መቶ ክ/ዘመን ከሌሎች ሰማዕታት አጽም ጋር ወደ ሃገራችን እንደ መጣ አባቶቻችን በትውፊት ነግረውናል:: ለዚህም ይመስላል ቡርክቷ እናታችን ከሌሎች ሃገራት ለይታ ለኢትዮዽያውያን ልዩ ፍቅር ያላት:: በዋናው ገዳሟ [ወሎ / ኩላማሶ / ስባ / ውስጥ የሚገኝ ነው] ጨምሮ ስሟ በተጠራበት ሁሉ ኃይልን ታደርጋለችና:: ነገር ግን ወንድሞቼና እሕቶቼ በቅድስቷ እናታችን ስም የሚነግዱ ሥጋውያን ሰዎች በዝተዋልና እንጠንቀቅ:: የሰማዕቷ ክብር ብዙ ነውና በሕልም ላይ ብቻ አንታመን:: አባ እንጦንስ እንዳሉት "በሕልሙ የሚታመን ሰው ከንቱ ነውና::" በዚህ ዕለት ከሰማዕቷ ጋር የመንፈስ እናቷን ቅድስት አጋታን ልናስባት ይገባናል:: ይህች እናት እመ-ምኔት ስትሆን ቅድስት አርሴማን ታስተምራት: ታጸናት: ከጐኗም ትቆምላት ነበር:: ረሃቧን: ጥሟን: ስደቷን: መከራዋንም ሁሉ አብራት ተሳትፋለች:: በፍጻሜውም አብራት ተሰይፋለች:: 🌹  † ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ   †   🌹 - የቤተ ክርስቲያን ምሰሶ - ምድራዊው መልአክ - የጌታ ወዳጅ - የድንግል ማርያም የአደራ ልጅ - የንጽሕና አባት - ቁጹረ ገጽ - የፍቅር ሐዋርያ - የምሥጢር አዳራሽ - የሐዋርያት ሞገሳቸው - ነባቤ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ዛሬ ይከብራል:: ምክንያቱም "ቀዳሚሁ ቃል" [ዮሐ.፩፥፩] ብሎ እንደ ንስር መጥቆ ወንጌሉን በዚህች ቀን ጽፏልና:: ✞ አምላከ ቅዱሳን ለኛ ለባሮቹ የቅድስቷን ጽናት: የወንጌላዊውንም ፍቅር ያድለን:: በረከታቸውን ከማይጐድል እጁ አብዝቶ ይስጠን:: 🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹 ✞መስከረም ፳፱ [ 29 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 🌹🌹🌹🌹 ፩. ቅድስት አርሴማ ድንግል [ሰማዕት] ፪. ቅድስት አጋታ [እመ ምኔት] ፫. "፻፲፱" ሰማዕታት [የቅድስት አርሴማ ማሕበር] ፬. ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ [ነባቤ መለኮት] ፭. ቅድስት ክርስቶስ ክብራ ኢትዮዽያዊት [በዚህ ቀን ነፍሳትን ከሲዖል ታወጣለች] ✞ ወርኀዊ በዓላት 🌹🌹🌹🌹 ፩. የፈጣሪያችንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት ፪. ቅዱስ ዼጥሮስ ተፍጻሜተ ሰማዕት ፫. ቅዱስ ማርቆስ ዘቶርማቅ ፬. ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ኢትዮዽያዊት ፭. ቅዱስ ዘርዐ ክርስቶስ [ጻድቅና ሰማዕት] ✞ "በመጀመሪያ ቃል ነበረ:: ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ:: ቃልም እግዚአብሔር ነበረ :: ይህ በመጀመሪያው በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ:: ሁሉ በእርሱ ሆነ:: ከሆነውም አንዳች ስንኳ ያለ እርሱ አልሆነም:: በእርሱ ሕይወት ነበረች:: ሕይወትም የሰው ብርሃን ነበረች:: ብርሃንም በጨለማ ይበራል:: ጨለማም አላሸነፈውም::" ✞ [ዮሐ. ፩፥፩] ✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞ " ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን":: /የቅዱሳንን ዜና [ታሪክ] እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::  አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/🌹🌹🌹🌹🌹🌹
نمایش همه...
👍 1