cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

Řăyyän

We work in oromo community

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استزبان مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
پست‌های تبلیغاتی
166
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

نمایش همه...
TAFAKKUR /تفكر

Ƭ♬⨏♬ƙƙ⩏Ʀ Da'awaa,odeeffannoo,Barnoota islaamaa,leenjiwwaan adda addaa,akkasumaa wantoota akkaan nama dinqisiisan barachuu yoo feetan chaanaalii Ƭ♬⨏♬ƙƙ⩏Ʀ jedhu hordofaa

https://t.me/Ibrahim_92taf

Ibraahim Eda'oo (Abul-mansuur): #Bareedinna Walakkaan bareeduma ilma namaa #arraba keessa jira jedhan,walakkaan hafe immoo #sammuu keessaa jira,fuulli ammoo gogaa zamana wajjiin dhumaa deemu . Irra caalaan bareedumaa bareeduma smmuuti,Rabbiin bareeduma sammuu isiniif haa kennu . Share👇 @tafak_or @tafak_or
نمایش همه...
እዉነተኛ ታሪክ  😢 #አስለቃሽ #የቴሌግራም               #ፕሮፋይል       🌀 #Part 1⃣7⃣ ✍ ፀሀፊ #አሚር #ሰይድ እኔ ከተቀመኩበት ስነሳ ፊርዶስ አብራኝ ተነስታ ....... እንባየን ከጉንጬ እየጠረገች ሂኩየ አንቺኮ አሁንም ንፁህ ሰዉ ነሽ ወንጀል ሸይጧን አሳስቶሽ ልሰሪ ትችያለሽ ግን ወደአላህ ተመልሰሽ ማረኝ እያልሽ እያለቀሽ ነዉ፡፡ አላህ መሀሪ ነዉ የወንጀል ጉዳቱ ወንጀል መሆኑን እያወቁ እዛዉ ያለተዉበት በዛዉ ወንጀል ላይ ሁኖ ሳይቶብት መቼ እንደምንሞት ሳናቅ ዛሬ ወይ ነገ እቶብታለሁ እያልን ወይም ሀዲስ ስንሰማ መስጊድ ስንገባ ደአዋ ስናዳምጥ አልቅሰን ወንጀሎኞች ነን ከአሁን ቡሀላ ወደ ወንጀል አልሄድም ብለን እንቶብታለን ግን ወይ ከመስጊድ ስንወጣ ወይ ደአዋዉ ሲያልቅ የቶበትነዉን እንረሳዉና ወደ እዛ ወንጀል እንሄዳለን ይሄ አይነት ደግሞ መቶበት ሳይሆን በራስ ጭንቅላት ላይ ጌም እንደመጨዋት ነዉ...አሁን ብዙ ሰዉ ጋር የሚታየዉ ጥርት ያለ ተዉበት ሳያረጉ  አላህ ጋር መገናኘታቸዉ ነዉ፡፡ ........ሂኩየ አንቺ ከእነዚህ ሰዎች ትለያለሽ ወንጀል ሰርተሽ  ወደ አላህ ነዉ እያለቀሽ ያለሽዉ እንጂ ወንጀል አብራችሁ ወደ ሰራሽዉ ሰዉ አይደለም ስንት እህቶቻችን ይህን ወንጀል ሰርተዉ ወንጀል ከሰሩት ሰዉ ጋር ተጣብቀዉ አንተዉ ቅብረኝ እሞታለሁ መርዝ እጠጣለሁ የሚሉ የፈጠራቸዉን ጌታ የረሱ አሉ አይደል፡፡ አንቺ እኮ የምታለቅሽዉ ወደ ፈጠረሽ ጌታ ወደ አላህ እንጂ ወደ ሀይደር አይደለም ስለሆነም አንቺ ከሌሎቹ ሴቶች ልዩ ነሽ፡፡ ጥራት የሚገባዉ አላህ ጌታችን እንዲህ ይላል፦ የባሮችን ጉዳይ ተውልኝ እስኪ ከነሱ ወደኔ የተመለሰ (የተፀፀተ) እኔ ወዳጁ ነኝ። እኔኮ እናት ለልጇ ከምታዝነው በላይ ለባሮቼ አዛኝ ነኝ። ከነሱ ወደኔ ተፀፅቶ የተመለሰ «አንተ ተውበት አድራጊ ሆይ እንኳን ደህና መጣህ ብየ ከርቀት እቀበለዋለሁኝ ።ወንጀል ሰርቶ ከኔ ለሚሸሸው ደግሞ፦ ወደርሱ ቀርቤ ፦ ባርያዬ ወዴት ነው የምትሄደው??? ከእኔ ውጭ ሌላ ጌታ አገኘህን??? ከኔ ውጭስ ሌላ አዛኝ የሆነ ጌታ አገኘህን የምትሸሸኝ??? »በማለት እጠራዋለሁኝ። እናንተ ስንዝር ስቀርቡኝ በእርምጃ እቀርባችሇለሁ ....በእርምጃ ስቀርቡኝ እኔ በሩጫ በፍጥነት እቀርባችሆለሁ  ብሏል ሂኩየ ፡፡ ስለሆነም ከአሁን ቡሀላ የአንቺን ለቅሶ ሳይሆን የምፈልገዉ ደስታሽን ነዉ ሂኩየ አንቺ ከአሁን ቡሀላ የረከሽ ወንጀለኛ አይደለሽም ልታለቅሺ ሳይሆን.... የባሰ አለ ብለሽ ልታመሰግኚ ነዉ የሚገባዉ  አንቺ ልታለቅሺ አይገባም አላህ መሀሪ አዛኝ የሆነ ጌታ ነዉ ብላ አንገቴ ስር ጥምጥም አለችብኝ፡፡ ከዛም ወደ ቤቴ ልሂድ ብላኝ ሸኝቻት ተመለስኩኝ፡፡    ዉይ ለፊርዶስ ከነገርኳት ቡሀላ ይህ ሚስጥር ተሸክሜዉ እንዳታሳርፊ የተባልኩ ይመስል አፍኘዉ ኑሮ ቅልል አለኝ ፡፡ ዲፕሬሽን ዉስጥ ነበርኩ አንድ ሰዉ ዲፕሬሽን ዉስጥ ከሆነ መፍትሄ ይሰጠኛል ብሎ የሚያማክረዉ ሰዉ ከነገረዉ 50% ከዲፕሬሽን ይላቀቃል፡፡ የሆነ የደስታ ስሜት ተሰማኝ ማታ ላይ ልተኛ ስል ፊርዶስ ደዉላልኝ በቃ በደስታ አወረሇት .. .....እሷም ሂኩ ምን ተገኘ ደስተኛ ሁነሻል ??? ስትለኝ ......ምንም አልተገኘ ግን ቅልል ብሎኛል የደስታ ስሜት ተሰማኝ አልኳት ፡፡ ብዙ ነገሮችን አወራን ስንጨርስ በስልክ ተሰነባብተን ወደ መኝታየ አመራሁ ለመጀመሪያ ጊዜ ሳልጨናነቅ ደስተኛ ሁኜ አደርኩ፡፡ የመጀመሪያ የደስታ ሂወት የጀመርኩ ይመስለኛል አልሀምዱሊላህ ተገላገልኩ..... ዙበይር ከአሁን ቡሀላ ተስፋ ይቆርጣል ፊርዶስ እዉነቱን ትነግረዋለች ወደ እኔ በጭራሽ አይደርስም ብየ እራሴን አሳመንኩት፡፡     ሳስበዉ የቸገረን የልባችንን የምነነግረዉ ለአላህ ብለን የምንወደዉ በአላህ መንገድ በዲነል ኢስላም ያገኘነዉ ጓደኛ ነዉ፡፡ ማንኛዉም ሰዉ አንድ የልብ ጓደኛ ያስፈልገዋል በደስታዉም በሀዘኑም ከጎኑ የሚሆን ሀሳብ ሲያስብ የማያማክረዉ በሀሳቡ ገንቢ አስተያየት መስጠት የሚችለዉ  ሰዉ ለሌላ ሰዉ መድሀኒት ነዉ ፡፡ ተማክረዉ የፈሱት ፈስ አይሸትም አይደል የሚባለዉ የልብ ጓደኛ ወሳኝ ነዉ፡፡ ጓደኛ ማለት በክፉም በደስታም በሀዘንም አብሮ መግባባት ሲቻል ነዉ፡፡ መጠንቀቅ ያለብን ሴቶች ማንኛዉም ነገር እስከ ዚና መስራት ወንጀል ድረስ የሴት ጓደኛ ተፅእኖ ግፊት ነዉ ጥሩ ሴቶች እየተበላሹ ያሉት በመጥፎ ሴቶች ጓደኛ ይዘዉ ነዉ፡፡         የአሁን ጓደኝነት ስታማክረዉ ወይ ሚስጥርህን ለሌላ ያሳልፈዋል ወይም በቀኝ ጆሮዉ አዳምጦ በግራ ጆሮዉ ያፈሰዋል፡፡ ጫት ማን አስጀመረህ?? ጓደኛየ..የቱርክ ልብስ ማን ልበሺ አለሽ?? ጓደኛየ....የያሽዉ የወንድ ጓደኛ ማን አስተዋወቀሽ?? ጓደኛየ...ሶላት አልሰገድሽም የት ነበርሽ?? ጓደኛየ ቤት....ሜካፕ ሊፒስቲክ ኮስሞቲክስ ማን እንድትቀቢ አስለመደሽ ???ጓደኛየ.......ዚና እንድሰሪ ማን አስተዋወቀሽ ???ጓደኛየ...ነዉ መልሳችን፡፡ አሁን የያሽዉ የሴት ጓደኞችሽ ከስንት አንድ ካልሆነ ከነዚህ ዉጭ ያሉት ብዙዎቹ ሴቶች የሚሸወዱት የሚበላሹት በሚይዙት የሴት ጓደኛ ስበብ እንደሆነ መገንዘብ አለብን፡፡      ሴትን ለሴት እሾህን ለሾህ አይደል የሚባለዉ በጓደኛ አመራረጥ ቢያንስ እንደፊርዶስ አይነት ጓደኛ መያዝ መቻል አለብን፡፡ አሁን ላይ ትዉልዱ ከቤተሰብ ቁጥጥር ዉጭ ሁነናል ጊዜዉ የተራቀቀ ነዉ በፊት ቤተሰብ ይቆጣጠረን ነበር አሁን ግን በስልክ ሁኗል ስራዉ በስልክ ያልቃል ወንጀል ለመፈፀም አንቺ እሱ እና ጌታሽ ብቻ የሚያቃቸዉ ብዙ የዚና መስሪያ ቦታዎች ምን ይሰራ ማን ይግባ ማን ይዉጣ የማይታይበት የወንጀል መስሪያ ቦታዎች በሁላችንም የመኖሪያ ሰፈሮች ቦታዎች እናገኛለን ፡፡  የሂክማ ነገር አላለቀም                   #እስኪ #ፈገግ #እንበል  .....አንዷ ሁሌ ላይብረሪ እያለች ትሄዳለች አቧቱ ሲጠይቃት ሁሌ ላይብረሪ እያለች ስታስቸግር ..አንድ ቀን አባቷ ማታ ስትመጣ በብትር ይገርፋታል የት ነዉ የምትሄጅዉ ??ሲሏት ላይብረሪ ስትል...አባቷ አልተማሩም ነበር ላይም ብረሪ ታችም ብረሪ የሄድሽበትን ብቻ ተናገሪ እንዳሉት አባት ትክክለኛ መሆን መቻል አለብን፡፡  መቼም ቀን በቀን ይፈራረቃል አንድ ቀን ባሳለፍን ቁጥር ወደ ሽምግልና እየሄድን እና ወደ ሞት እየተጠጋን መሆኑን እረስተናል፡፡ እኛ ሞትን ብንረሳም ሞት ግን እኛን አይረሳም፡፡ ካልተሳፈሩበት ቶሎ ተሽቀዳድሞ ጊዜ ታክሲ አይደለም አይጠብቅም ቁሞ ተብሏል፡፡ ግን አሁን ጊዜ ሰዉ ታክሲ ተሰልፎ ይጠብቃል እንጂ ታክሲ ተሰልፎ ሰዉ መጠበቅ አቁሟል፡፡ ምን ለማለት ነዉ አንተም አንቺም እሱም እሷም ሞት ቁሞ እየጠበቀን ስለሆነ ጥርት ያለ ተዉበት አድርገን ሞትን እንጠብቀዉ፡፡ ነግቶ ፊርዶስ ጋር ተገናኘን ከበፊቱ በበለጠ ፍካቷ እየጨመረ ለኔ ያላት አመለካከት እየጨመረ ሄደ ፡፡ በቃ ምን ልበላችሁ እስከዛሬ በመደበቄ እኔ ስጨናነቅ እንደኖሩኩ አወኩኝ ቢሆንም አልሀምዱሊላህ አሁንም እፎይ ማለቱ በጣም ደስታ ፈጠረልኝ፡፡ ፊርዶስ እኛ ቤት እየመጣች አንድ ላይ እንሆናለን ፡፡ አንድ ቀን እናቴ ለፊርዶስ ምንድን ነዉ አታገቡም እንዴ ፊርዱ??? ሴት ልጅ ትዳር የሚያምረዉ በልጅነት ነዉ፡፡ እኔ ያገባሁት በ19 አመቴ ነዉ ፡፡ ከሁለት አንዳችሁ አግቡ እና በሰርጋችሁ እንልፋ አለቻት፡፡ ለፊርዶስ ..ፊርዱም ኢንሻ አላህ አይቀርም እኔ የማመቻቸዉ ስላለ ነዉ እንጂ በቤተሰብ የመጣልኝ አለ ታጭቻለሁ  ሆነም ቀረ የሂክማ ይቀድማል ተዘጋጂ አለች ሳቅ እያለች .....እናቴም ማሻ አላህ ብያለሁ👇
نمایش همه...
እዉነተኛ ታሪክ  😢 #አስለቃሽ #የቴሌግራም               #ፕሮፋይል       🌀 #Part 1⃣6⃣ ✍ ፀሀፊ #አሚር #ሰይድ     ለፊርዶስ ምን ልበላት እንደባለፈዉ በቤተሰብ የመጣ አለ ብየ ልዋሻት እንዴ  ??? ወይስ እዉነቱን ልንገራት እያልኩ ሁለት ልብ ሆንክ ብዙ ካሰብኩ ቡሀላ በመጨረሻም አንድ ዉሳኔ ወሰንኩ ነገ....ፊርዶስን ሳገኛት ጓደኛየ ናት ለኔም ለወንድሟም እያሰበች አንድ ከጎኔ ላለችዉ ፊርዶስ የኔን ማንነት ከመጀመሪያዉ እስከመጨረሻዉ ልነግራት ወሰንኩ፡፡    እንደምንም ብሎ የወፎቸ ጫጫታ ንጋትን ሊያበስር ብቅ አለ ፡፡ እኔም ቁርሴን በልቼ እናቴ የምታቃቸዉ ሰዎች ስለሞቱ ለቅሶ ደርሼ ልምጣ ቤት ጠብቂኝ ብላ ከቤት ወጣች፡፡ እኔም ጊዜ መግደል አልፈለኩም እኔ ለዙበይር እንደማልሆነዉ እራሴን እንደረከሰ ሴት ስለምቆጥር ....በእኔ ፍቅር ሳይጎዳ በጊዜ እኔን እንዲረሳ እኔን እንዳያስታዉስ ለእህቱ ፊርዶስ ልነግራት ወሰንኩ፡፡         ስልኬን ማታ እንዳጠፋሁት ነበር ወዳዉ ስልኬን አብርቼ ለፊርዶስ ደወልኩ ....ፊርዶስም ሂኩ ዛሬ አዳሬን ስጨነቅ እንቅልፍ ሳይወስደኝ አደረ ትናንት ለሰራሁት ስራ አዉፍ በይኝ ዙበይር ጋር ለማገናኘት መጀመሪያ አንቺን ማስፈቀድ ነበረብኝ ብላ እንባ እየተናነቃት ጠየቀችኝ ......እኔም ፊርዱ አንቺ ምንም ጥፋት የለብሽም ስታጠፊ ነዉ አዉፍ የምልሽ ...አንድ ነገር ላማክርሽ ነዉ አሁን የደወልኩልሽ ....ፊርዱ አንቺን የማይሽ እንደእህቴ ነዉ ደስታየንም ሀዘኔንም ልትካፈይኝ በምነግርሽ ነገር ላትርቂኝ በሆዴ አፍኜ የያዝኩትን የሆድ እሳት የሆነብኝ ሚስጥር ልነግርሽ ወስኛለሁ  እኔን ልታዳምጪኝ ልትረጂኝ ዝግጁ ነሽ??? አልኳት ......ፊርዶስም እንደመደንገጥ ብላ እሺ ዝግጁ ነኝ አለችኝ ......አሁን ከተመቸሽ እቤት መምጣት ትችያለሽ ???አልኳት ......እሷም እሺ ሂኩ አሁን መጣሁ አለችኝ፡፡     ፊርዶስም ጊዜ ሳትፈጅ በፍጥነት እኛ ቤት ከተወሰኑ ደቂቃዎች ቡሀላ መጣች፡፡ ስገባ ሂኩ አሰላሙ አለይኩም ትናንትና አንቺን ሳላስፈቅድ በሰራሁት ስራ አዉፍ በይኝ ጥፋተኛ ነኝ ይቅር በይኝ እያለች እኔን መለመን ጀመረቸ፡፡ ...... ወላሂ ከአንቺ ምንም ጥፋት የለም በራሴ ችግር ነዉ እንደዚህ የሆንኩት ዛሬ ኢንሻ አላህ ትረጂኛለሽ ብየ አስባለሁ ....   ፊርዱ በማወራሽ ሚስጥር እኔ እና አላህ ነን የምናቀዉ አሁን አንቺን የዚህ ሚስጥር የምታቂዉ ከአላህ ከእኔ ቀጥሎ አንቺን ላማክርሽ ልነግርሽ ነዉ ግን ስነግርሽ ጠንካራ ልትሆኝ ይገባል እንደ አጋጣሚ እንባየ ቢፈስ አንቺም ማልቀስ የለብሽም አደራ አልኳት ፊርዶስም በመደናገጥ እሺ አለችኝ        እኔም ከረጅም ዝማታ ቡሀላ በፊት ስለትምህርቴ ስለጉብዝናየ .. ስለtelegram profile አርጌ......ሀይደር የሚባል ተዋወቄ......አምኘዉ እስከ ደብረዘይት ያሳለፍነዉን በመንታ እንባ የታጀበ እያወረሆት እንባየ ልብሴን እስከሚያርሰዉ አንድ ባንድ ነገርኳት ቂርአትም የገባሁት በዚሁ ምክንያት እንደሆነ ሁሉንም እያለቀስኩ ለፊርዶስ ነገርኳት ፊርዶስም አብራኝ ታለቅሳለች....    ባለፈዉ ሲሀም ዘመዴ ነዉ ያለችኝ ቁጥሬን የሰጠነዉ ቢክራ ነሽ ወይ ???ብሎ ሲጠይቀኝ ይሄ በሆዴ ያፈንኩት ሚስጥር ስላለኝ በመዋሸት በቤተሰቦቼ የመጣ ትዳር አለ ብየ መለስኩኝ ..አሁንም ይህን ሁላ የነገርኩሽ ያለምክንያት አይደለም እኔ ለወንድምሽ ለዙበይር የትዳር አጋር መሆን አልችልም የቆሸሸ ማንነት ነዉ ያለኝ ዙበይር ከአሁን ቡሀላ እኔን ይወደኝ እንደሆነ ከአሁን ቡሀላ ከኔ ተስፋ ይቁረጥ ፡፡      እኔ ማለት ይህን ነገር ደብቄ ቤተሰቦቼ ሲጨናነቁ አንዱ ከአንዱ ከአንዱ ሀገር ወደ ሌላ ሀገር በዚሁ የተነሳ ቁርአን ይቀራብሽ ተብየ ደሴ ከተማ ድረስ እንደሄድኩ ....እናቴ ስታለቅስ ስትዉል አጎቶቼን አስጨንቄ ነዉ የኖርኩት አላህ ይምረኝ ይሆን ?? ደግሞ በሀይደር ተናድጄ ከቅርብ ቀናት በፊት ሚስቱን በFace book አግኝቻት ልነግራት የእሱንም ሂወት ላበላሽበት ወስኜ ስልኳን እስከ መቀበል የደረሰ ተግባብተን ደዉየ ልነግራት ብየ ለወለደቻቸዉ ልጆች እና የወደፊት የእሷ ሂወት አሳዝኖኝ ተዉኩት ፡፡ ፊርዶስ የኔ ወንጀል ብዙ ነዉ አላህ ይምረኝ ይሆን?? አላህ ይምረኝ ይሆን ??    አላህ ያለልኝን እጠብቃለሁ ግን እኔ ለዙበይር የምገባ ሴት አይደለሁም ለዙበይር ሌላ ፈልጊለት እኔ መፈቀር የሚገባኝ ሰዉ አይደለሁም እኔ ማለት ከአንዱ ወንጀል ወደ አንዱ ስረማመድ አሁን ድረስ እኔ በማንነቴ የማፍር..........ብየ ንግግሬን ለፊርዶስ አስረድቼ እምባየን እየጠረኩ ከፊርዶስ ጎን ተነሳሁ፡፡ ፊርዶስ አብራኝ ተነስታ ........ #part 17......louding
نمایش همه...
#Iklaasa ➛ Waan dalagaa turte tokko namaaf jecha dhiisuun #Riyaa'a/na argaa jedhama . ➛ waan dura hin dalagne tokko namaaf jecha dalaguun #Shirkii jedhama . ➛ kanneen lamaan irraahuu qulqullaa’uun #Iklaasa jedhama . Iklaasa Rabbiin nuuf haa kennu . Share👇 @tafak_or @tafak_or
نمایش همه...
እዉነተኛ ታሪክ  😢 #አስለቃሽ #የቴሌግራም               #ፕሮፋይል       🌀 #Part 1⃣5⃣ ✍ ፀሀፊ #አሚር #ሰይድ      ስልኬን አዉጥቼ ለኢክራም ደዉየ ልነግራት ወስንኩ ግን ጨነቀኝ የኔ ሂወት አንዴ ተበላሽቷል ግን የሶስት ሰዉ ሒወት ላበላሽ እንደሆነ ተሰማኝ፡፡  ሁለት ልጆቿ እና ኢክራም ..ደግሞ ወደ ፍች ከሄዱ ልጆቹ ካለቤተሰብ ፍቅር ተለያይተዉ ኢክራም ወደ ቤተሰቦቻ ትሄዳለች ሌላም ችግር ፈጠርኩ ማለት ነዉ ..ቤተሰቦች ፀብ ብዙ ነገር  ስልኬን ይዤ ማሰብ ጀመርኩኝ .... ግን ሀይደር የሰራኝ ስራ መልሶ አእምሮየ ጋር ብልጭ ይልብኛል፡፡ ግን ምን ይደረጋል የእኔነ በደል ብሸከም ይሻለኛል የሌላ ሰዉ ሒወት ከማበላሽ....ሁሉንም ነገር ለፈጣሪየ ለአላህ ሰጠሁኝ፡፡  ስልኬን አቅፌ እንደ ወራጅ ወንዝ ማልቀስ ሆነ ያረቢ እርዳኝ ያረቢ እርዳኝ እያልኩ ........የኢክራምን ስልክ ለወደፊት እንደዚህ አይነት ዉሳኔ እንዳልወስን ብየ ከContact ላይ አጠፋሁ፡ Facebook ላልጠቀም ከአሁን ቡሀላ የሀይደርን ሚስት ኢክራምን ላላወራ ብየ ለራሴ ቃል ገባሁ፡፡ በአላህ ተወከልኩ እስከአሁንም የሰራሁትን ስራ አላህ ይማረኝ..ሀይደርን ከነቤተሰቦቹ  ልጎዳዉ ነበር ይቅርብኝ አላህ እሱንም ያስተካክለዉ እኔንም አላህ የተሻለ ይስጠኝ ብየ ዱአየን አርጌ ለመጨረሻ ጊዜ ከሀይደር ለመበቀል ያሰብኩት ሀሳብ ሰረዝኩኝ፡፡       Face book መጠቀም አቆምኩ ግን ሀይደር የሰራኝ ጉድ ለማን ሰዉ እንደምተነፍሰዉ አላቅም ብቻየን ማታ ተኛሁ ብየ  አዳሬን ብቻ ማልቀስ ሁኗል ስራየ ፡፡    የማይነጋ የለም የወፊት ጫጫታ መንጋቱን አበሰረኝ......ወደ ቂርአት ሄድኩ ፊርዶስን አገኘሇት፡፡  ዛሬ እናንተ ቤት ሂጄ  እናትሽን መተዋወቅ እፈልጋለሁ አለችኝ ..እኔም ከቂርአት መልስ እቤት ወስጃት ከእናቴ ጋር አስተዋወኳት፡፡ እናቴን ካስተዋወኳት ቡሀላ  ፊርዶስ በረፍት ሰአቷ እኛ ቤት እየመጣች ቤተሰብም ጓደኛም ሆነች አላህ የሰጠኝ የዲን እህቴ ፊርዶስ ነች..... ፊርዶስ እሁድ እንደምትጋብዘኝ ነገረችኝ .......ሸገር ላይ በሚገኘዉ ታላቁ ወበሪ ሆቴል....ከአሱር ቡሀላ እንሄዳለን አለችኝ፡፡ .....እኔም እሺ ፊርዱ አልኳት፡፡ ቀናቶች በተቆጠሩ ቁጥር እሁድ ደረሰ ፊርዶስ አሱር ሶላት አካባቢ እኛ ቤት መጥታ ሰግደን አብረን ወደ ወበሪ ሆቴል ሔድን፡፡  እዛ ስደርስ ያየሁትን ማመን አቃተኝ የፊርዶስ ወንድም ዙበይር ቀድሞን መጥቶ  ቁጭ ብሎ እየጠበቀን ነዉ፡፡   ዙበይርን በፊርዶስ ስልክ በፎቶ  አንዴ ስላየሁት እሱ እንደሆነ ጠረጠርኩ፡፡ ፊርዶስ ግን ዙበይርም ነዉም አይደለምም አላለችኝም...እሷ ሶስት ወንድሞች ስላሏት ዙበይር  ላይሆን ይችላል ብየ ጠረጠርኩ፡፡ ትኩስ ነገር አዘን አንዳንድ ወሬ እያነሳን ተጨዋዉተን  ተጠቀምን ስንጨርስ እኔን ወደ ቤቴ ሸኝተዉኝ እነሱም ወደ ቤታችን ተመለሱ ግን ማን ይሆን??? እያልኩ ሳስብ ሳስብ ....ዙበይር ይሆን እንዴ እያልኩ ብቻየን ባዶ ቤት ቁጭ ብየ እኔዉ  ስከራከር.... ዳኛ ከሌለዉ ክርክር ዉስጥ ስልኬ ጮኸ ስልኬም ከክርክሩ ገላገለኝ...ስልኬን ሳየዉ የደወለችዉ ፊርዶስ ነበረች ,,...አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱሏሂ ወበረካትሁ አለች ......እኔም ወአለይኩም ሰላም ፊርዱ ደህና ነሽ .......አልሀምዱሊላህ በሰላም እቤት ገባሽ??? አለችኝ .....እኔም አዎ ገብቻለሁ ፊርዱ ብዙ ተራ ወሬዎች ካወራን ቡሀላ ....ሂኩየ ቅድም አብሮኝ የመጣዉ ማን እነንደሆነ አዉቀሽዋል ????አለችኝ .....እኔም መቼም አንቺ ከአጂ ነብይ ጋር እንደማትሄጅ አቃለሁ፡፡ ከሶስት ወንድሞችሽ አንዱ ይሆናል ፊርዱ አልኳት፡፡ .....አዎ አልተሳሳትሽም ዙበይር ነዉ ፡፡ በአካል አገናኚኝ እያለ ረበሸኝ ምን ላድርግ ፡፡ ፊርዱ አንቺ  ለኔ እኮ አይቴ(የወንድሜ ሚስት ለማለት ነዉ) ዙበይርም ወንድሜ ነዉ ፡፡ ዙበይር ናፈቀችኝ ናፈቀችኝ ሲለኝ ነዉ እስከዛሬ በሩቅ ነበር የሚያይሽ ዛሬ ፊት ለፊት እንዲያይሽ ያረኩት አለችኝ ፊርዱ .....እሷ ባለችኝ ነገር ደርቄ ቀረሁ የምመልሰዉ አጣሁ መልሴ ዝም ሆነ ... ....ፊርዶስም ሄሎ ሄሎ ሄሎ ሂክማ ምነዉ ዝም አልሽ ...አረ በአላህ አጥፍቼ ከሆነ ይቅርታ እንደዚህ ይከፋሻል አላልኩም ሂክማ ..አረ አናግሪኝ አስጨነቅሽኝ .....ሂክማ አረ ሂክማ እያለች እሰማታለሁ ስልኩን አልዘጋሁትም ነበር፡፡ እኔ ምንም የምመልሰዉ መልስ የለም ብቻ እንባየ ቁልቁል ሲወርድ ይታወሰኛል ፊርዱም ሄሎ ሄሎዉ ማለቷን አላቆመችም በድንጋጤ ..እኔም ስልኩን ዘጋሁት መልሳ ፊርዶ ደወለች እኔም አላነሳሁኝ.....ፊርዶስ በመደወል ትደጋግም ይዛለች.....እኔም በtext ነገ የማወራሽ ነገር አለ ብየ በmessgae ልኬ..ስልኬን አጠፋሁት፡፡ ለፊርዶስ ምን ልበላት እንደባለፈዉ በቤተሰብ የመጣ አለ ብየ ልዋሻት እንዴ  ??? ወይስ እዉነቱን ልንገራት እያልኩ ሁለት ልብ ሆንኩ ብዙ ካሰብኩ ቡሀላ በመጨረሻም አንድ ዉሳኔ ወሰንኩ ነገ....ፊርዶስን ሳገኛት......... ለፊርዶስ በሆዷ ያፈነችዉን ሚስጥር ለሂክማ ትነግራት ይሆን ??? ለሂክማ ነገረች ማለት ዙበይር ሊርቃት ይችላል እናንተ ምን ትላላችሁ ?? በቀጣዩ ክፍል እናየዋለን፡፡ #Part 1⃣6⃣ ይ.............,......ቀ...... ............,ጥ..........,ላ........ል JOIN👇👇👇  @rayyan @rayyan
نمایش همه...
እዉነተኛ ታሪክ  😢 #አስለቃሽ #የቴሌግራም               #ፕሮፋይል       🦋 #Part 1⃣4⃣ ✍ ፀሀፊ #አሚር #ሰይድ     በጣም ተናደድኩ ሀይደር የራሱን ኑሮ እየኖረ የኔን ሂወት አበላሽቶ ጨለማ አድርጎ እኔ በሂወት እያለሁ መኖር አይችልም ብየ ወሰንኩኝ አንድ ሀሳብ መጣልኝ የእሱን ሂወት ማበላሻ ......ሀይደርን ለመበቀል በጣም ቀላል ዘዴ አገኘሁ     Face book ገብቼ  የሀይደርን የfb ጓደኞች እያየሁኝ ነዉ፡፡ ሚስቱን በprofile ስላየሆት የfb ጓደኛዉ እንደሆነች ብየ መፈለግ ጀመርኩኝ፡፡ ጓደኞችን ስመለከት ብዙዎቹ ጓደኞቼ ሴት ነበሩ ገረመኝ፡፡ Fb ላይ ከ3000 በላይ ጓደኞቼ ነበሩት በስንት ድካም ልፋት ቡሀላ አንድ ፎቶ አየሁ የእሱ እና የእሷ profie የሆነ፡፡ time line ገብቼ ስመለከት የእሷ የብቻ ፎቶም አለ ፡፡ ሲጋቡ የተነሱ ፎቶዉ ላይ መብሩክ በሉኝ ብላ ፅፋለች፡፡      ያሰብኩት ተሳካ አሁን frind አርጌ የእኔን ሂወት እንዳበላሸብኝ የእሱን ላበላሽበት ወሰንኩኝ፡፡ እኔ እያለቀስኩ እሱ ስቆ እንደማይኖር ወሰንኩኝ ...frind request ላኩላት ከአንድ ቀን ቡሀላ ተቀበለችኝ ...በጣም ደስ አለኝ ሀይደር የእኔ ሂወት አበላሽቶታል የእሱንም ሒወት አበላሸዋለሁ እያልኩ ብቻየን እየዛትኩ ነዉ፡፡   face book ላይ online ቀን ቀን አትጠፋም  ፡፡ ነገሮችን ሁሉ ሳስበዉ እሱ ማታ ማታ በስልኩ ይጀናጀናል እሷም ቀን ላይ ታወራለች ብየ አሰብኩ በትዳር በመሀላቸዉ የሆነ ክፍተት እንዳለ ያስታዉቃል፡፡ እኔም  እያወረሇት ነዉ በሂደት  ተዋወቅን ግን ለክፉም ለደጉም ብየ ትክክለኛ ስሜን አልነገርኳትም ፡፡ ሚስቱ የአዲስ አበባ የመርካቶ ሰፈር ልጅ እንደሆነች ስሟም ኢክራም እንደምትባልና የባሏም ስም ሀይደር እንደሚባል እና የሁለት ልጆች እናት እንደሆነች ..... ቤተሰቦቿ ባለሀብት እንደሆኑ እና ..የባሏ ስም ሀይደር እንደሆነ  በጣም እንደምወደዉና ፡፡ በፊት ሹፌር ነበር ተዋወቅን ተዋደን ተጋባን ....ከዛም አባቴ ሀይደርን ከሹፍርና ስራ አቁም ብሎት አሁን  መርካቶ ሱቅ ከፈተልን ከዛም የቤት መኪናም ዶልፊን አባቴ ገዝቶ እንደሰጠዉ አጫወተችኝ፡፡       ኢክራም በጣም ግልፅ ልጅ ናት ሁለ ነገሯ ተመቸችኝ ፡፡ አንቺስ ??ብላ ጠየቀችኝ ....እኔ ቂርአት እየቀራሁ እንደሆነ ነገርኳት፡፡ ስለ ሀይደር ምንም አላነሳሁ፡፡ ግን በጣም ገረመኝ ወንድ ልጅ ሴትን ልጅ ለማጥመድ በእጁ አድርጎ የሚፈልገዉን ለመዉሰድ የማይፈነቅለዉ ድንጋይ የለም ዉሸታቸዉ ከባድ እንደሆነ ተረዳሁ ፡፡ ጥፋቱ የኔ ነዉ የነገረኝን ማመኔ ብቻ ወደ ጆሮየ የገባዉ ሁሉ እዉነት ይመስለኝ ነበር ፡፡ ሚስጥሩ እያደር ገባኝ ማታ ማታ ስደዉል አይመችም ስልክ ለማንሳት በtelegram እናወራለን የሚለኝ ሚስቱ ኢክራም  ሲያወራ እንዳትሰማዉ እንደሆነ ገባኝ፡፡      ግን ለምን ?? አረ ለምን?? ኢክራም ፍቅር ያሸንፋል  ከሹፍርና ኑሮ ገላግላዉ በቤተሰቦቿ ጥረት ሱቅ ተከፍቶለት መኪና ተገዝቶለት.... እሷ ባለዉለታዉ ሁና በመኪናዉ ሴት ሲሸወድ እንደ እኔ ያለዉን የተዘነጋ በማዘናጋት እንደዚህ መሆኑ ለኢክራም አዘንኩ፡፡ ወይ ጎራ ሁን ወይ ጎራ ተጠጋ አይደል የሚባለዉ ሀይደር ጎራ ተጠግቶ ይሄዉ በኢክራም ጥረት እና በቤተሰቦቻ ሀብት ለሌላ ለሀራም አላማ እየተጠቀመበት በመሆኑ ያሳፍራል፡፡ ደግሞ ለኔ የዋሸኝ ዉሸት ፊቴ ላይ ድቅን አለብኝ፡፡ ምነዉ ሀይደር ዉሸታም ነዉ ብየ ንገሪያት ንገሪያት የሚል መንፈስ ከጀርባየ አለ፡፡ ሀይደር ዉሸታም ነዉ ብየ ፅፌዉ ልልከዉ ብየ ቆይ ለሁሉም ሰአት አለዉ አልኩና   ባልሽን ትወጅዋለሽ ???ብየ ጠየኳት ....በጣም እንጂ ሀይደር ሁለ ነገሬ ነዉ በጣም እወደዋለሁ ያለ እሱ መኖር አልችልም በስራም ጎበዝ ነዉ ዉይ ሲወደኝ እኮ ብላ ታወራኝ ይዛለች በfb ......ግን ስለ እሱ መጥፎ ነገር ብሰሚ..ትጠይዋለሽ?? ወይስ አጠይዉም?? ብየ ጠየኳት .....እሷም እንዴ ሀይደር መጥፎ ነገር የለዉም የሚሰራዉን የሆነዉን ሁሉን ይነግረኛል እኔን ሳያማክር ፈፅሞ አያቅም ፡፡ በህይወቴ እሱ ነዉ የመጀመሪያየ ወንድ በጣም ነዉ የምወደዉ፡፡ ምንም መጥፎ አይሰራም እተማመንበታለሁ አለችኝ፡፡ ...እኔም አይ ግን ሰርቶ ብታገኝዉስ?? አልኳት .......ጭራሽ አያረገዉም ጥያቄዉ መልስ የለዉም ሁሌም ቢሆን በሀይደር የምተማመንበት ጨዋ ልጅ ነዉ፡፡አላህ በስንት ዱአ መሰለሽ የሰጠኝ አለችኝ፡፡ በጣም ደስ የምትል ሚስት አለችዉ ግልፅ ናት እኔም ማንነቴን ደብቄ እናወራ ይዘናል ከመግባባት ብዛት ስልክ ቁጥሯን ተቀበልኳት፡፡  ስልክ ቁጥሯም0911....2372 ብላ በfb text አረገችልኝ ፡፡  እቤቴ ሁኜ ማሰብ ጀመርኩኝ ሀይደር የእኔን ሂወት እንዳበላሸ ላበላሽበት??? ወይስ እኔን አላህ አለኝ ቶብቻለሁ  ለሚስቱ እና ለሁለት ልጆቹ ሒወት ብየ ልተወዉ?? እያልኩ ተወዛገብኩ፡፡ ያሳለፍኳቸዉ የደብረዘይት ጊዚያቶች እና አሁን ትዳር ሲመጣ የምጨነቃቸዉ ጭንቀቶች ፊቴ ላይ ድቅን ይላሉ፡፡  ይህን ጉዳይ ለፊርዶስ አላማከርኳትም ...ፊርዶስ ብሰማ ምን ትለኝ ይሆን ? ስልኬን አንስቼ ቀጥታ ለኢክራም ልደዉል ቁጥሯን አዉጥቼ የሀይደርን ጉድ ልነግራት ወሰንኩ፡፡ ሀይደር እኔን እንደሸወደ ሚስቱን ሲሸዉድ አይኖርም ...ስልኬን አንስቼ ወደ ሀይደር ሚስት ኢክራም ልደዉል ስልክ ቁጥሯን አወጣሁ....ከዛም #part 1⃣5⃣ ይ.........ቀ...... ........ጥ.............ላ..............ል @rayyan @rayyan @join @join
نمایش همه...
እዉነተኛ ታሪክ  😢 #አስለቃሽ #የቴሌግራም               #ፕሮፋይል       🌀 #Part 1⃣3⃣ ✍ ፀሀፊ #አሚር #ሰይድ    ግን ለእሱ አንድ ዉሸት ዋሸሁት አላህ ይቅር ይበለኝ ደዉሎ  ምን ወሰንሽ ???ብሎ ጠየቀኝ እኔም ......በዉሸት ወንድሜዋ ከአንተ ከተለያየን ቡሀላ  እናቴን ሚስጥር ስለማልደብቃት ማታ ሁሉንም ነገርኳት...እናቴም እኛ ያዘጋጀነዉ አባትሽ የመረጠልሽ ልጅ አለ አለችኝ ....ወንድም አላህ ከኔ የተሻለ ይስጥህ ከአሁን ቡሀላ መደዋወል እና በtelegram አናወራም ለምን ብትለኝ የወደፊት የትዳር አጋሬ መሆን ስለማንችል ከቤተሰቦቼ ትእዛዝ ዉጭ መፈፀም አልፈልግም አልኩት፡፡ ...እሱም መርሀባ ብሎኝ  በዚሁ ተለያየን ክፉም ከአፌ ሳይወጣ እሱም ክፉ ሳይናገረኝ ወደድኩህ ወደድኩሽ የለአንቺ መኖር አልችልም ያለ አንተ መኖር አልችልም ሳንባባል በሀላል መንገድ ጀመርን፡፡ በሰላም ተለያየን አላህ ከእኔ የተሻለ የትዳር አጋር ይስጠዉ፡፡      ምን ላርግ የጠየቀኝ ጥያቄ ላይ ድንግል አይደለሁም ብለዉ አላህ ወንጀሉን ነዉሩን የሸፈነ እኔ እሸፍንነታለሁ ብሏል እኔ ቶብቻለሁ በወንጀሌ ተፀፅቻለሁ ግን የእሱን ሂወት ዋሽቼ ገብቼ ማበላሸት አልፈለኩም፡፡ እኔ ሀይደር ሸወደኝና ማንኛዉንም ወንድ በክፉ አላይም፡፡ ለምን  አባቴ ወንድ ልጅ ነዉ፡፡ ወንዶች ገደል ይግቡ ካልኩ እኔን ለማሳደግ ለመንከባከብ ከቤተሰብ ፍቅር ዉጭ ሁኖ የሚኖረዉ አባቴን ተሳደብኩ ማለት ነዉ ፡፡ ይህ ደግሞ የወላጆቼን ሀቅ አልተወጣሁም ማለት ነዉ፡፡ ስለሆነም ጥሩ ወንዶች አሉ በተዘዋዋሪም ጥሩ ያልሆነ ወንዶች አሉ እነሱንም ከመሳደብ አላህ ልቦና ይስጣቸዉ ግን ይህ ጭካኔ በእህቱ በእናቱ ቢሆን የማይወደዉን በሌላ ሴት ልጅ መጨዋት ግን ያሳፍራል፡፡       በየሳምንት ከጁምአ ሶላት ቡሀላ የደአዋ ዝግጅት አለ ሴቶች አሚራችን ፊርዶስ ደአዋ ታረግልናለች፡፡ እንደ አጋጣሚ እሷ አሟት ሳትመጣ ቀረች....      ከዛም አንቺ አድርጊ እያሉ ሌሎች የጀመአ አባላችን ግፊት አርጉብኝ ...እኔም እሺ ብየ  ደአዋ አደረኩኝ፡፡  የሚገርመኝ የመጀመሪያ ቢሆንም  በጣም የሚያምር ደአዋ አደረኩ የደአዋዉ ርዕስ በወንድ ተኩላዎች እንዳትሸወጅ ነበር፡፡ እኔም የተሰማኝን በደአዋዉ እያለቀስኩኝ ሀይደር የሰራኝ ስራ የሸወደኝ ትዝ እያለኝ እልክ በያዘኝ መልኩ ደአዋ አረኩላቸዉ ...የትምህርቱ ጠቃሚነት ብዙዎቹ አብረዉኝ ያለቅሱ ነበር፡፡ ደአዋዉን ሳረግ ለእህቶቼ ቢጠነቀቁ ብየ በኔ ሂወት የደረሰዉን ጠባሳ  በተለያዩ ዘዴዎች የደአዋ ሲስተም ነገርኳቸዉ  እንዲጠነቀቁ እና የtelegram group ጥቅም እና ጉዳቱን ዘርዝሬ ነገርኳቸዉ ከዛ ደአዋየን ጨርሼ ተቀመኩኝ፡፡     ከዛ ቡሀላ ጁምአ ሶላት ቡሀላ አሚራችን ፊርዶስ አንቺ አድርጊ ባለፈዉ ሳልመጣ ቀርቼ ያደረግሽዉ ደአዋ በጣም እንደሚያምር ነግረዉኛል ....እንደዚህ የደአዋ ብቃት አለሽ ማለት ነዉ ማሻ አላህ ብያለሁ አለችኝ ፊርዶስ ፡፡ እኔም እኔ ደአዋ አላደርግ አንቺ ስለቀረሽ ነዉ ያረኩት  ብላት .......እንዴ አላማችን አንቺ አንቺ ልንባባል ሳይሆን ያወቅነዉን ለማሳወቅ ነዉ ሂኩ ፡፡ እኔ ማረግ በምፈልግ ሰአት አረጋለሁ አንቺ አድርጊ አለችኝ...ፊርዶስ አበረታታችኝ ጁምአ ከሶላት ቡሀላ ተሰብስበን ደአዋ አድራጊዉ እኔ ሆንኩ ... አላህ የሰራሁትን ወንጀል እንዲምረኝ በምሰግድ ሰአት ብቻየን ስሆን ረከአተይን ከሰገድኩ ቡሀላ አላህንም ማረኝ እያልኩ ባገኘሁት አጋጣሚ እያለቀስኩ ነዉ....          እቤት ገብቼ ልተኛ አካባቢ ፊርዶስ አንድ ነገር አማክርሻለሁ ብላ ደወለችልኝ  ከአሱር ቡሀላ ልንገናኝ ተቀጣጠርን፡፡ ከአሱር ቡሀላ ከፊርዶስ ጋር ተገናኝተን አንድ  ያልጠበኩትን ነገር ነገረችኝ፡፡    ሂክማ ባለፈዉ  የነገርሽኝ ነገር ሲሀም ለትዳር የሚፈልግሽ አለ ብላ እንደነገረችሽ እኔ ሳልነግርሽ አረፈድኩና ግን ዛሬ ልነግርሽ ወስኛለሁ፡፡ ወንድሜ አብረን ስንሄድ አይቶናል አንቺ ጓደኛየ እንደሆንሽ ያቃል ለትዳር እንደሚፈልገኝ ነገረችኝ ፡፡  ሂኩ ወንድሜ  ዲን አለዉ አላህን ፈሪ አንቺን ከጓደኝነት አልፎ ለወንድሜ ዙበይር ብታገቢዉ ደስ ይለኛል ሂኩ ማስተዳደሪያም አልሀምዱሊላህ አላህ እርዚቅ ሰጥቶታል  .... አንቺን እንዲያገባሽ እፈልጋለሁ አለችኝ፡፡ ባለፈዉ የሲሀም ዘመድ ይፈልገኛል ብለሽ ስታማክሪኝ ደነገጥኩ ወንድሜ ዙበይር እሷን ማግባት እፈልጋለሁ እያለ እኔም ወንድሜን እንድታገቢ እየተመኘሁ ያንን ወሬ ስሰማ ለዙበይር ነግሬዉ እንዴት እስከ አሁን ሳነግሪያት ብሎ ተቆጣኝ አለችኝ፡፡ .....እኔም ደነገጥኩኝ እስኪ ቆይ ልሰብበት አልኳት ከዛም እቤቴ ሂጄ አሰብኩበት ለሚመጣዉ አመት ትምህርት የመማር እቅድ ነበረኝ..... እናቴም ብዙም ትምህርቴን እንድማር አትፈልግም...አባትሽ ተምሮ ለስራ የሚኖረዉ ደብረዘይት, ነዉ፡፡ የእኔን ፍቅር የልጁን ፍቅር ሳይሰጥ ይሄዉ እየኖረ ነዉ፡፡ መማር እንደዚህ ከሆነ ይቅር ትለኝ ነበር፡፡ መኝታ ክፍል ሁኜ ዙበይርስ  ቢክራ ነሽ ወይ ብሎ ቢጠይቀኝ መልሴ ምንድን ነዉ ??? እያልኩ እያሰብኩ ነዉ፡፡ በጣም ተናደድኩ ሳላስበዉ ሸይጧን ወሰወሰኝ ሀይደር የራሱን ኑሮ እየኖረ የኔን ሂወት አበላሽቶ ጨለማ አድርጎ እኔ በሂወት እያለሁመኖር አይችልም ብየ ወሰንኩኝ ፡፡ ብዙ ሀይደርን የምጎዳበት ነገሮች መኝታ ክፍሌ ሁኜ የቤታችንን ኮርኒስ  እያየሁ አንድ ሀሳብ መጣልኝ የእሱን ሂወት ማበላሻ ቀላል ዘዴ አገኘሁ ...እኛን የቸገረን ኸይር መስራቱ እንጂ ተንኮል መስራቱ መቼ ያቅተናል ......ሀይደርን ለመበቀል በጣም ቀላል ዘዴ አገኘሁ እስከአሁን ትዝ ሳይለኝ ብየ ተቆጨሁ፡፡ ...የሀይደርን ..... #Part  1⃣4⃣ ,,,,,,,,,,ይ ,,,,,,,,,,,,,,,,,ቀ ,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,ጥ ,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,ላ ,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,ል ሼር የማታረጉ የቻናል ቤተሰቦቻችን ደህንነታችሁ ሀሳብ ሁኖብናል😉 ለጓደኞቻችሁ ሼር በማድረግ አለን በሉን☺️ @rayyan @rayyan
نمایش همه...
እዉነተኛ ታሪክ  😢 #አስለቃሽ #የቴሌግራም               #ፕሮፋይል       🌀 #Part 1⃣2⃣ ✍ፀሀፊ☞ አሚር ሰይድ      አጎቴ እቤት መጥቶ አንድ መፍትሄ አለኝ  ለምን አታገባም ??? ሲል መኝታ ክፍል ሁኜ ሰማሁት .......   እኔ እኮ ተማሪ ናት እያልኩ ነዉ እጂ ብዙ ሰወች ጓደኞቼ ለራሱ  ለምን አትድረንም አግብቻት እኔ ጋር ሁና አስተምራታለሁ ያሉኝ አሉ፡፡ ግን እኔ ትምህርቷን ትጨርስ ለእናንተም ማዉራት አይሆንም ትላላችሁ ብየ ዝምታን መርጬ ነዉ ብሎ ለእናቴ ሲናገር ሰማሁት ... እናቴም እኔንም ብዙ ሰዉ ጠይቆኛል ግን ትምህርቷን ትጨርስ ብየ ነዉ፡፡ እሷም አስራሁለተኛ ክፍል ተፈትና ዉጤትም ቢመጣለት ዩኒቨርስቲ አትገባም ተነጋግረን እሺ ብላኝ ነበር፡፡ አላህ ያለዉ ሆነ እንጂ ይሄዉ ልጄ በሽታዋ ሳይታወቅ ታማለች አሁን ዱአየ አላህ እንዲያሽራት ነዉ፡፡ ጤናዋን ካገኘች ቡሃላ ስለ ሂክማ ትዳር አስብበታለሁ ብላ እናቴ እንባ እየተናነቃት ለወንድሟ ነገረችዉ ፡፡ እኔ እነሱ የሚያወሩትን  ወሬ ስሰማ እዛዉ መኝታ ክፍሌ አለቀስኩ ለምን ለትዳር ብቁ አይደለሁም...ሀይደር አዋቂ መስሎ ሸዉዶኛል የወደፊት የትዳር አጋሬ ቢክራ ነሽ ወይ ብሎ ቢጠይቀኝ ምን መልስ አለኝ????       ወደ ትምህርት እንዳልመለስ ከወር በላይ አለፈኝ ካቋረጥኩ ፡፡ አንድ የትምህርት ቤት ጓደኛየ እቤት መጥታ ትምህርቱን ዘንድሮ የማቀጥይ ከሆነ ለምን  ጃክሮስ ሰፈር አካባቢ ጃክሮስ መስጊድ አለ  እዛዉ አካባቢ ሴቶች ተሰባስበዉ ኪታብ የሚቀሩ አሉ እነሱ ጋር ኪታብ አቀሪም??? ብላ አመላከተችኝ፡፡ ከዛም ቅዳሜ ቀን ወስዳ የሚቀሩበትን ቦታ እና አልፎ አልፎም መስጊድ እንደሚቀራ ነገረችኝ፡፡ እዛ ኪታብ መቅራት ጀመርኩ እንደገና ወደ ዲኔ ለመመለስ ወሰንኩኝ ፡፡    ኪታብ እየቀራሁ አላህን ማረኝ እያልኩ እያለቀስኩኝ ነዉ፡፡ የጀመአ አሚራችን ፊርዶስ ትባላለች እሷ ጋር በጣም ተግባባን ፊርዶስ ጃክሮስ ሰፈር አለፍ ብሎ ያለዉ ጎሮ የሚባለዉ ሰፈር ነዋሪ እንደሆነች ነገረችኝ፡፡ ፊርዶስ ኪታብም ታቀራናለች በጣም ጎበዝ ዲነል ኢስላም ላይ በጣም ጠንካራ ናት ፡፡  ዲነል ኢስላም ከታዘዝንባቸዉ የዲን ወንድምህን በዘር በብሔር ሳትለይ ሙስሊም ስለሆነ  ዉደድ ሴትም ብትሆን እህትሽ ናት  ተዋደዱ ኢስላም አስተሳስሯችሇል ብሎናል፡፡ ከትምህርት ጓደኞቼ በላይ ፊርዶስን እንደእህቴ ቀረብኳት፡፡  እኔም እህት የለኝም ፊርዶስን እንደ እህቴ ነዉ የማያት ፊርዶስ ሶስት ትልቅ ወንድሞች አሏት ፡፡ ሁለቱ አግብተዋል አንዱ ወንድሟ ግን አላገባም ፡፡        እዛዉ ኪታብ በመቅራት የተዋወቀነው ሲሀም የምትባል ልጅ አለች ሁሌ ኪታብ ቀርተን በተገናኘን  ቁጥር ሂክማ አንድ የኔ ዘመድ  የአንችን ስልክ ቁጥር  ስጭኝ እያለ እያስቸገረኝ ነዉ ፡፡ አብረን ኪታብ እንደምንቀራ አይቶናል .....ቁጥሯን ስጭኝ እኔ አላማየ ቀጥታ ወደ ትዳር ብቻ ነዉ እያለ እያስቸገረኝ ነዉ ሂክማ እኔ ይተዉሻል ብየ ዝም ብለዉ አኔን መቸካቸኩን አላቆመም ያለአንቺ ፍቃድ ደግሞ ቁጥርሽን መስጠት ከበደኝ..ስልክሽን ልስጠዉ አልስጠዉ ?? እስከ ጠዋት አስበሽ ንገሪኝ አለቸኝ፡፡     ጠዋት ደረሰ ኪታብ የምቀራበት ሄድኩኝ ሲሀምን  አገኘሇት ......ምን አሰብሽ እሱ እንደሆነ በስልክ አላስቀምጠኝ አለ  ልስጠዉ እና  እናንተ አዉሩ አለችኝ .......እሺ ትንሽ ቆይቼ አሳዉቅሻለሁ ሲሀም አልኳት        ፊርዶስ ኪታብ ስጨርስ ለብቻዋ አማከርኳት፡፡ ፊርዶስም አይታወቅም የአላህ ነገር ለኸይር ይሆናል የሀራም መንገድ ሳጀምሩ ስለማንነቱ አጣርተሽ በስልክ በTelegram ሳይረብሽ ቀጥታ ወደ ሀላሉ ሊገባ ከቻለ አላህ የፃፈልሽ እሱ ጋር ሊሆን ስለሚችል ለሲሀም ቁጥርሽን እንድሰጠዉ ፍቀጅላት  አለችኝ ፡፡     ፊርዶስም ቀጠል አድርጋ  እኔም እኮ በጣም ዲነኛ የሆነ ልጅ በቤተሰብ የመጣ በጣም ጥሩ ስነምግባር ያለዉ ነዉ አይቸዉ ፈትኘዋለሁ ቤተሰቦቼ ጥሩ ባል መርጠዉልኛል እኔም የማመቻቸዉ ነገር ስላለ ነዉ እንጂ   ማግባቴ አይቀርም ...ግን አንቺ ቀድመሽኝ ካገባሽ በጣም ደስተኛ ነኝ ሂኩ አላህ ያሳካዉ ዱአ አትርሺኝ እኔም አረሳሽም አለችኝ እየተሳሳቅን፡፡ ወደ ሲሀም ሂጄ  እሺ ቁጥሬን ስጭዉ አልኳት፡፡ ......እሷም ቁጥሬን ሰጠችዉ ...    ልጁም ደወለልኝ በስነ ስርአት አወራኝ ....በአካል እንደሚያቀኝ ነገረኝ .....እኔ ግነ አላቅህም አልኩት፡፡ ከአስር ቀን በላይ ሆነን ማዉራት ከጀመርን፡፡ የግድ መገናኘት ስላለብን ተቀጣጥረን ተገናኘን ተያየን ማሻ አላህ ቆንጆ ልጅ ነዉ ፡፡   ስሙን ከተዋወቅን ቡሀላ እኔ አንቺን ለማጀዘብ ሳይሆን ለትዳር ነዉ የምፈልግሽ አለኝ ፡፡      ከዛም  እያወራን አንድ ጥያቄ ለመጠየቅ ከብዙ ዝምታ ቡሀላ  የፈራሁት ጥያቄ መጣብኝ >>>>>>>  ሂክማ ያዉ ለወደፊት የትዳር አጋሬ መርጬሻለሁ አንድ ጥያቄ ልጠይቅሽ .አለኝ ....እሺ ጠይቀኝ አልኩት ...... ግን ቢክራ ነሽ አለኝ??? ......ምን ብየ ልመልስ ዝም አልኩት,,,,ወንዶች ማግባት የምፈልጉት በቃ ድንግል የሆነች ነዉ??? አልኩት፡፡ ......እሱም የሌላዉን አላቅም ግን እኔ በአላህ እምልልሻለሁ እስከ አሁን ተጠብቄ ከሴት ፍትንያ ነፍስያየን አሸንፌያለሁ፡፡  አላማየም ማግባት የምፈልገዉ እንደ እኔዉ የሆነችዉን ክብር ያላትን ነዉ አለኝ፡፡ .....እኔም እሺ  በስልክ አሳዉቅሀለሁ ብየ ተለያየን፡፡ከዛም ወደ ቤቴ ተመለስኩኝ     እቤቴ መኝታ ክፍል ብቻየን ሁኜ.....ሀይደር የኔን ሂወት አበላሽቶብኛል ብቻየን የእንባ ዱብዳ ማጉረፍ ጀመርኩ ......ድንግል ነኝ ብየ ባገባዉ ድንግልናየን ሳያገኝብኝ ቢቀር መፋታቴ ቤተሰቦቼን ማስወቀሴ ነዉየ ......ወይም ሲሰድበኝ ሲያንቋሽሸኝ ወይም የእሱ ሞራሉ እንደተጎዳ ይኖራል፡፡የሴት ልጅ ህይወት ግድ እስከ ክብሯ መገኘቱ ወሳኝ እንደሆነ ተገነዘብኩኝ ፡...ገና ከመጀመሪያዉ የትዳር ፈተና ጀመረኝ፡፡  ስለሆነም ብቻየን መኝታ ክፍሌ አሰብኩኝ ባስበዉ ባስበዉ ምንም መፍትሄ ላገኝ አልቻልኩም  ያረቢ ብየ አለቀስኩ ፡፡ ግን ለእሱ አንድ ዉሸት ዋሸሁት አላህ ይቅር ይበለኝ ሲደዉልልኝ ምን ወሰንሽ???? ብሎ ጠየቀኝ     እኔም............ #Part 1⃣3⃣ ይ................ቀ........... .............ጥ............ላ............ል join👇👇 @rayyan
نمایش همه...
እዉነተኛ ታሪክ  😢 #አስለቃሽ #የቴሌግራም               #ፕሮፋይል       🌀 #Part 1⃣1⃣ ✍ ፀሀፊ #አሚር #ሰይድ     Face book ላይ profile pic ሳይ ደነገጥኩኝ የምናገረዉ ጠፋብኝ እክፍል ዉስጥ ወድቂያለሁኝ ......ሀኪም ቤት እራሴን ስቼ ማን እንደወሰደኝ እንኳ የማቀዉ ነገር የለም  ......የወደፊት ባሌ ብየ የሴትነት ክብሬን የወሰደዉ ሀይደር ባለ ትዳር ነዉ፡፡ ...,..,fb profile እና time line ብዙ ፎቶዉች አሉ ለሰርጋቸዉ ጊዜ አብረዉ የተነሱት ....ምን ልበል ያዉ የምናገረዉ የለኝም ብቻ በማለቀዉ ድንጋጤ እራሴን ስቼ ሀኪም ቤት ገብቻለሁ፡፡ ..... የተኛሁበትም ሆስፒታል እኛ ሰፈር ገርጂ  አቅራቢያ የሚገኘዉ  ኮርያ ሆስፒታል ነዉ፡፡ ሆስፒታል ሁኜ ልረጋጋ አልቻልኩም፡፡  አባቴም ሸዋሮቢት ከተማ የመንግስት ሰራተኛ አይደል መታመሜን ሲሰማ ጊዜ ሳይፈጅ  መጣ ፡፡ አልናገር ምግብ ለራሱ ብዙም አልበላም ግልኮስ ተተክሎልኛል፡፡ ብቻ በሁለቱም ጉንጬ እንባየ ሲረግፍ ነዉ የሚዉለዉ፡፡ እናቴም በእኔ ሁኔታ ተደናግጣለች የምትዉለዉ የምታድረዉ እኔዉ ጋር ነዉ...እኔ እያለቀስኩ የእናት ሆድ አያስችል አብራ ታለቅስ ነበር፡፡ ....እኔስ መናገር ያልቻልኩት የዋጥኩት እሳት ነዉ የሚያስለቅሰኝ.....እናቴ ግን ልጇ ስለሆንኩ መናገር ስለማልችል ሳለቅስ ብቻ ታለቅሳለች፡፡ ........ኮርያ ሆስፒታል አምስት ቀን ተኝቼ ህክምና ወስጄ ወደ ቤቴ ተመስኩ፡፡ ግን ምን እንደሆንኩ አላቅም አፌ እንደበፊቱ አቀላጥፎ ማዉራት አልቻለም ፡፡ ምን ሁነሽ ነዉ ??ምንሽን ይሰማሻል ??ይሉኛል... እኔ የሆንኩት ሌላ ለሰዉ የማይነገር ...መልስ የሌለዉ ጥያቄ ነዉ፡፡ ......አባቴም የያዛት ጅን ነዉ ተብሎ የሰፈራችን ጀመአዎች አሉ፡፡ ማታ ላይ ሳልሰማ መጥተዉ እስከ 4 ሰአት ቁርአን ቀሩብኝ፡፡ እነሱ የሆንኩትን አያቁም ...ቁርአን ቀርተዉ ምንም የጅን ምልክት ስላላገኙ ....አንዱ ቁርአን ከሚቀሩት አረ ይሄ ጅን አይደለም እናቁም ብለዉ አቁመዉ ሄዱ፡፡ ...,.ግን ጅንም ባይሆን ለኔ ቁርአን መቀራቱ ትንሽ ለዉጥ አመጣሁ ማዉራት አፌ መንቀሳቀስ ትንሽ እየከፈተልኝ ነዉ፡፡ አባቴ አላስቻለዉም እኛ ሰፈር ያለዉ ኢብኑ አባስ መስጊድ ዉስጥ ታዋቂ የጂን የሚቀሩት ልጆች አሉ ተብሎ ተነገረዉ፡፡ ማታ ላይ ከመቅሪብ ቡሀላ እቤት ይዟቸዉ መጣ ፡፡ እኔ ሁሉን በሆዴ ይዠዋለሁ ፡፡ መናገር የማልችለዉ ነገር ነዉ፡፡ ከኢብኑ አባስ መስጊድ የመጡ ጀመአዎች ማታ ላይ ሲቀሩብኝ  አመሹ ለዉጥ የለም ያዉ ነዉ፡፡ ግን ቁርአን በተቀራብኝ ቁጥር ልቤ በጭንቀት በሀሳብ አልተረጋጋም ብቻ ግን የተያያዘዉ አፌ  እየተፍታታ ነዉ፡፡ እናቴ ደግሞ ሰፈሩ አሉ የሚባሉት ትላልቅ ሴቶችን ጠርታ ቅዳሜ ቀን በግ ታርዶ ምሳቸዉን አብልታ ከምሳ ሰአት የጀመሩ እስከ መቅሪብ ድረስ ዱአ ሲደረግልኝ ዋለ፡፡ ከእኔ በላይ ቤተሰቦቼን አስቸገሪኩ፡፡ ቤተሰቦችን አስጨነኳቸዉ ለነገሩ አንድ ፍሬ ልጅ ነኝ ምን ያርጉ አባቴም የመንግስት ስራዉን ከሸዋሮቢት አስፈቅዶ መጥቷል፡፡ እናቴም ጭንቀቷ እኔ ሁኛለሁ ስታየኝ በስስት ሳለቅስ የምታለቅሰዉ ከእኔ በላይ ነዉ፡፡ እኔ ተረብሼ ቤተሰቦቼን እረበሽኩኝ በእኔ ፀባይ  መቀያር እነሱ ተረበሹ በጣም አዘንኩ፡፡ አላህ የዉመል ቂያማ ሲጠይቀኝ መልሴ ምን ይሆን???  የወላጆቻችሁ ሀቅ አደራ እያለ በቁርአን ነግሮኝ ነብዩ ሙሀመድ ሰ ዐ ወ ጀነት ከእናት እግር ስር ናት ብለዉን ....እኔ ግን ገና ሀይደር ያገባኛል ብየ አምኘዉ እሱ ጋር ወንጀል ሰርቼ ለዛዉም ባለትዳር ሆኖ በራሴ ባለመጠንቀቅ በተጎዳሁ በራሴዉ ጥፋት ቤተሰቦቼን አሰቃይ ይዣለሁ፡፡ አላህ በስንቱ ነዉ የሚቀጣኝ??? አንድ ዚና በመስራቴ ሁለት ወላጆቼን እነሱ በማያቁት ነገር ማስጨነቄ ማስቸገሬ....  ኡፍ እንኳን እንዳትሉ የተባልኩትን ወላጆች በእኔ መረበሽ ማልቀስ ከጀመሩ አንድ ወር ሆናቸዉ ፡፡ ብቻየን እያሰብኩ መኝታ ክፍሌ ገብቼ አለቅሳለሁ፡፡        አንድ የእናቴ ወንድም አለ ....ደሴ ከተማ የሚኖር ደሴ ትምጣ እዚህ ጥሩ የጂን የሚቀሩ ቁርአን ቀሪዎች አሉ ብሎ ይደዉልላታል፡፡ እናቴም ምንም ይሁን ምንም እኔ አንድ ፍሬ ልጇ ሳለቅስ ስጨነቅ ማየት አልፈለገችም ፡፡ እኔም ሁሉን በሆዴ ደብቄ እነሱ የሚሉኝን እሺ ከማለት ዉጭ ምንም አማራጭ የለኝም፡፡ እናቴ ጋር አብረን ከ አዲስ አበባ 401 ኪሎ ሜትር ወደ ምትገኘዉ የወሎእምብርት  ደሴ ከተማ ጉዟችንን ቀጠልን፡፡ ጠዋት ተነስተን 8:30 ደሴ ከተማ ገባን፡፡ አጎቴ ተቀብሎን መኖሪያ ቤቱ አረፍ አለን፡፡ ጠዋት ላይ ደሴ ከተማ የሚገኘዉ ተቋም አካባቢ የሚገኘዉ ጦለሀ መስጊድ በብዙ ጀመአ በተሰበሰበበት ቁርአን ቀሩልኝ ከአዲስ አበባ ለየት ያለ አቀራር ነበር፡፡ ግን አብረዉ የሚቀራባቸዉ ጅን የያዛቸዉ ነበሩ የእነሱ ብዙም ሳይቆይ ለቀቀ እኔ ግን ሁሌን በሄዴ ይዤ ቤተሰቦቼን ዘመዶቼን እያስቸገርኩ እያስጨነኩ ነዉ፡፡ በመነገታዉ ማታ ላይ ደግሞ ደሴ ከተማ የሚገኘዉ አሬራ አካባቢ አሬራ መስጊድ ከመቅሪብ ቡሀላ ቁርአን ተቀራልኝ ፡፡ ሁለት ቀን ከተቀራብኝ ቡሀላ አጎቴ ደሴን አሶገበኝኝ አዝናናኝ ፡፡ ደሴ ከተማን አንድ ሳምንት ቆይቼ ወደ አዲስ አበባ ተመለስኩኝ፡፡ አዲስ አበባም እንደተመለስኩኝ ጓደኛቼ የክፍል ተማሪዎችም እየመጡ ይጠይቁኝ አጫዉተዉኝ ይሄዱ ነበር፡፡ ትምህርት ካቆምኩ አንድ ወር ሆነኝ ......አዲስ አበባ የሚኖረዉ አጎቴ አልፎ አልፎ እየመጣ ይጠይቀኝ ነበር ፡፡ ዛሬ ግን እቤት መጥቶ አንድ መፍትሄ አለኝ ሲል ሰማሁት ለምን አታገባም ??? እኔ እኮ ዳረኝ ብለዉ የጠየቁኝ አሉ ሲል መኝታ ክፍል ሁኜ ሰማሁት...እኔም ደነገጥኩኝ.... #part 1⃣2⃣ ይ............ቀ................ ............ጥ..............ላ................ል ✍ ሼር በማድረግ ለሁሉም ያድርሱ
نمایش همه...
یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.