fa
Feedback
Gurage Zone Government Communication Affairs

Gurage Zone Government Communication Affairs

رفتن به کانال در Telegram

Gurage Zone Government Communication Affairs

نمایش بیشتر
1 573
مشترکین
+224 ساعت
+47 روز
-130 روز
آرشیو پست ها
በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች ያነጋገርናቸው የሀገር ሽማግሌዎች ድምጻቸው ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ መስጠታቸው ገልጹ። ግንቦት 24/2018(ወልቂጤ ) በጉራጌ ዞን እዣ ቁጥር 2 ምርጫ ክልል ምሁር አክሊል ወረዳ በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች ያነጋገርናቸው የሀገር ሽማግሌዎች፣ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸው፣ በነጻነት ድምፃቸውን በመስጠታቸው ደስተኞች መሆናቸውን ተናግረዋል። በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች ያነጋገርናቸው የሀገር ሽማግሌዎች፣ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በነቃ ተሳትፎ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል። የሀገር ሽማግሌዎቹ እንደገለጹት፣ ምርጫው ሰላማዊ፣ ፍትሃዊና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እየተካሄደ ሲሆን፣ የህብረተሰብ ክፍሎች ያለምንም ጫና በነጻነት ድምፃቸውን እየሰጡ ነው ብለዋል። ምርጫ መምረጥ ለሀገር ልማት፣ ለዴሞክራሲ ግንባታ እና ለህዝብ ተሳትፎ መጠናከር ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፣ ዜጎች የዜግነት ግዴታቸውን በመወጣት በምርጫው እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል። በተጨማሪም የምርጫውን ውጤት በጸጋ እንደሚቀበሉ ገልጸው፣ የሀገሪቱ የዴሞክራሲ ጉዞ እንዲጠናከር ሁሉም ወገኖች ሰላምንና መቻቻልን ሊያስቀድሙ ይገባል ብለዋል።

ሕዝቦች በልማትና በመልካም አስተዳደር ተሳትፎ እንዲኖራቸው ዲሞክራሲያዊ ምርጫ አስፈላጊ መሆኑን በጉራጌ ዞን የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ታደለ በቀለ ገለፁ ። ግንቦት24/18(ወልቂጤ)በጉራጌ ዞን የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ታደለ በቀለ ድምጻቸውን ሰጥተው ሲወጡ እንደገለፁት ሕዝቦች በልማትና በመልካም አስተዳደር ተሳትፎ እንዲኖራቸው ዲሞክራሲያዊ ምርጫ አስፈላጊ ነው። ሀገሪቱም በየአምስት አመቱ ጠቅላላ ምርጫ በማድረግ ህዝቦች በመረጡት መንግሥት እንዲተዳደሩ እንደሚደረግ ገልፀው ምርጫው ሰላማዊ ፍትሀዊና ተአማኒ እንዲሆን ሁሉም ሀላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል። በከተማው ምርጫው ሠላማዊ በሆነ መልኩ እየተካሄደ መሆኑን የገለፁት አቶ ታደለ ዜጎች መብታቸውን በመጠቀም የሚፈልጉትን ፓርቲ መምረጥ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል ። @top fans

በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን በእዣ ቁጥር ሁለት ምርጫ ክልል ድድጋር ምርጫ ጣቢያ ድምጽ አሰጣጥ ሂደት ።

“ልጄን አቅፌ ድምፄን ሰጥቻለሁ” የመስከረም ሀብቴ የምርጫ ተሳትፎ በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ መቆርቆር ቀበሌ ነዋሪ የሆነችው መስከረም ሀብቴ፣ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ድምፅዋን ለመስጠት ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በመቆርቆር ምርጫ ጣቢያ ተገኝታለች። መስከረም የ7 ወር ሕፃን እናት ሲሆን፣ ልጇን አቅፋ በመምጣት በሰላማዊና ሥርዓት በተጠበቀ ሁኔታ የምርጫ መብቷን ተጠቅማለች። እንደገለጸችው፣ በምርጫው መሳተፍ የዜግነት ኃላፊነቷን ከመወጣት ባለፈ በሀገሯ የወደፊት እጣ ፈንታ ላይ የራሷን አስተዋጽኦ ለማድረግ እድል እንደሚሰጣት ገልጻለች። መስከረም ዘንድሮ ለ3ኛ ጊዜ ድምፅዋን የሰጠች ሲሆን፣ ምርጫው በሰላምና በጥሩ አደረጃጀት መካሄዱ ደስታ እንደፈጠረባት ተናግራለች። እናቶችና ሌሎች ዜጎችም የምርጫ መብታቸውን በመጠቀም በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተሳትፎአቸውን እንዲያጠናክሩ ጥሪ አቅርባለች።

7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለዲሞክራሲ ስርአት ግንባታ ከፍተኛ አስተዋፅዖ እንዳለው በወልቂጤ ምርጫ ክልል የኢዜማ ፓርቲ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተመራጭና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ደምስ ገብሬ ገለፁ። ግንቦት 24/18(ወልቂጤ)በወልቂጤ ምርጫ ክልል የኢዜማ ፓርቲ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተመራጭና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ደምስ ገብሬ በምርጫው ወቅት እንደገለፁት 7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለዲሞክራሲ ስርአት ግንባታ ከፍተኛ አስተዋፆ አለው። ህዝቡ በነቂስ በመውጣት ለአምስት አመት የሚመራውን ፓርቲ በመምረጥ ላይ መሆኑን ገልጸው የምርጫ አስፈጻሚዎች የፀጥታ አካላትና የሚመለከታቸው አካላት ነጻና ገለልተኛ ምርጫ እንዲሆን መስራት እንደሚኖርባቸው ተናግረዋል ። በክልሉ በፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ምርጫው ሠላማዊና ዲሞክራሲያዊ እንዲሆን ከቅድመ ዝግጅት ጀምሮ መሰራቱን የገለፁት አቶ ደምስ የምርጫ ሂደት በሰላማዊ ሁኔታ እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል ። Fm Wolkite 89.2 Radio

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!! 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምጽ አሰጣጥ ስነ ስርአት ከማለደው 12:00 ሰዓት ጀምሮ በጉራጌ ዞን እዣ ቁ.1 ምርጫ ክልል በእዣ ወረዳ በሚገኙ የተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች በይፋ ተጀምሯል። የጉራጌ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪና የፓርቲው የክልል ምክር ቤት እጩ አቶ ናስር ሀሰን ጨምሮ የእዣ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪና የምርጫ ክልሉ የክልል ምክር ቤት እጩ አቶ ዘውዱ ዱላ፣ የጉራጌ ዞን ምክር ቤት ምክትል አፈጉባኤና የክልል ምክር ቤት እጩ ክብርት ወይዘሮ ከድጃ ተማም በምርጫ ጣበያቸው በመገኘት ድምጽ ሰጥተዋል። ይህ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለዴሞክራሲ ስርአትና ለሀገረ መንግስት ግንባታ ፋይዳው ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል። በወረዳው በርካታ ዜጎች ማልደው በመነሳት በወሰዱትን ካርድ ቀጣይ የሚመራቸውን ፓርቲ በሰላማዊ መልኩ እየመረጡ መሆኑን አንስተው ሌሎችም ያልመረጡት ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው እንዲመርጡም አሳስበዋል።

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው ግንቦት 24/2018ዓ.ም(ወልቂጤ) ወይዘሮ ዘርፍነሽ ቀድሩ፣ አቶ ገረመው መልስና ወርቅነሽ ቲመርጋ በጉራጌ ዞን እዣ ቁ.1 ምርጫ ክልል በወድበር ምርጫ ጣቢያ ድምጻቸውን ሲሰጡ አግኝተን ያነጋገራቸው ነዋሪዎች ናቸው። ነዋሪዎቹ እንዳሉት ጠዋት 12 ሰዓት ካርዳቸው በመያዝ በነቂስ ወጥተው መምረጣቸውን አንስተው በዚህም ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል። ምርጫውም ያለምን የጸጥታ ችግር በሰላማዊ መልኩ በነጻነት ድምጻቸን እየሰጡ መሆኑንም ተናግረዋል። ሁሉም ዜጋ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም በወሰዱት ካርድ ቀጣይ ይበጀኛል፣ ያስደዳድረኛል የሚሉትን ፓርቲ መምረጥ እንዳለባቸውም ነዋሪዎቹ መክረዋል።

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!! 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምጽ አሰጣጥ ስነ ስርአት ከማለደው 12:00 ሰዓት ጀምሮ በጉራጌ ዞን እኖር ኤነር ቁጥር 1 ምርጨ ክልል ጉንችሬ ከተማ በሚገኙ የተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች በይፋ ተጀምሯል። በርካታ ዜጎች በወሰዱትን ካርድ የሚመራቸውን ፓርቲ ለመምረጥ ማልደው በምርጫ ጣቢያዎቹ ተገኝተዋል።

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!! 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምጽ አሰጣጥ ስነ ስርአት ከማለደው 12:00 ሰዓት ጀምሮ በጉራጌ ዞን ኮኪር ምርጫ ክልል በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በሚገኙ የተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች በይፋ ተጀምሯል። በርካታ ዜጎች በወሰዱትን ካርድ የሚመራቸውን ፓርቲ ለመምረጥ ማልደው በምርጫ ጣቢያዎቹ ተገኝተዋል።