ኃጢያቷን የምትፅፈዋ ሴት
አንዲት ሴት ነበረች ኃጢአቷን የምትፅፍ ልቧ በኃጢአት የሰከረ ለኃጢአቷም ተገዢ የሆነች ይች ሴት የተለያየ ኃጢአት የምትሰራ ናት ትዘሙታለች፣ ትዋሻለች፣ ታማለች ፣ ትሰርቃለች ፣ ትገድላለች ፣ በዓል ትሽራለች ፣ በትእቢት የተሞላች ሴት ናት ልቧ ኃጢአት ነበር። ነገር ግን አንድ ቀን ንስሐ እገባበታለው ብላ የምትሰራውን ኃጢአቷን ሁሉ እየጻፈች ታስቀምጥ ነበር።
ከዕለታት በአንድ ቀን የጻፈችውን ኃጢአቷን ብታየው ስንክሳር አክሎ ተመለከተችው ስንክሳር ማለት በ365 ቀኖች የሚለው የቅዱሳን ታሪክ ሰብስቦ የያዘ ትልቅ መጽሐፍ ነው። የዚች ሴትም ኃጢአትም ይህን አክሎ ነበር እንዳየችው ደነገጠችና ኃጢአቷን ተሸክማ አባት ወደ አለበት ወደ አንጾኪያ ሄደች
ባስልዮስን አገኘችው አባቴ በዚህ ያለው ኃጢአትሽ ይፋቅልሽ በለኝ አለችው።
አባ ባስልዮስም ይፋቅልሽ አላት ገልጣ ብታሳየው ሁሉ ተፍቆ አንዲት ኃጢአት ብቻ ቀርታ አየቻት። በጣም ከባድ ኃጢአት ነበረች ሊሰሩዋት የምትከብድ ሊነግሯት የምታሳፍር ነበረች ይቺን ኃጢአትሽንስ ማስተሰረይ የሚችል ልጄ
ቅዱስ ኤፍሬም ነው ሂደሽ ለእርሱ ንገረው አላት።
አባ ባስልዮስ ይሄን ያላት ኃጢአቷን መፋቅ አቅቶት አይደለም የራሱ ክብር ከሚገልጥ
የቅዱስ ኤፍሬም ክብር እንዲገለጥ ፈልጎ ነው። ደግሞም ስትመላለስ ንስሐ እንዲሆናት ጭምር ነው።
እሷም
አባ ባስልዮስ እንዳላት
ቅዱስ ኤፍኤም ወዳለበት ወደ ሶሪያ ሄደች በባዶ እግሯ እንቅፋት እየመታት እሾሁ እየወጋት እግሯ ሲደማ ልብሷን ቀዳ እየጠመጠመች ተጉዛ
ከቅዱስ ኤፍኤም ደረሰች።
አባቴ በዚህ ያለው ኃጢአትሽ ይፋቅልሽ በለኝ አለችው
ቅዱስ ኤፍሬም ግን ይሄ ለኔ አይቻለኝም ለአባቴ
ለአባ ባስልዮስ እንጂ አላት
ቅዱስ ኤፍሬም ግን ኃጢአቷን መደምሰስ አቅቶት አይደለም በፈሊጥ ቀኖና ሲሰጣት እንጂ ስትመላለስ ኃጢአቷ እንዲቀልላትም ነው። ሄደሽ
ለአባ ባስልዮስ ንገሪው ይደመሰስልሻል አላት እሷም አግኝቼው እኮ አይሆንልኝም ብሎ ወደ አንተ ልኮኛል ሳትል እሽ ብላ መንገድ ስትጀምር እንደ ቀድሞው በህይወት አታገኝውም መቶ ካህናት ሊቀብሩት ወደ ቤተክርስቲያን ይዘውት ሲሄዱ ታገኝዋለሽ ሳትጠራጠሪ የተጻፈው ኃጢአትሽን ከአስክሬኑ ላይ ጣይው አላት እሷም እሽ ብላ ሄደች የቀኑ ሙቀት የሌሊቱ ብርድ እያሰቃያት ደረሰች ሙቶ ካህናት ፍትሐት እየፈቱ አየች።
የእግዚአብሔር አገልጋይ ባስልዮስ ሆይ የባሪያህን ኃጢአት ደምስስልኝ ብላ ከአስክሬኑ ላይ ጣለችው አስክሬኑም ድምፅ አውጥቶ ኃጢአትሽ ተደምስሶልሻል አላት ገለልጠ ስታየው ተደምስሶላታል።
አምላኳን አመሰገነች በደስታ ዘመረች በዚህ በኋላ ዓለምን ንቃ ገዳም ገብታ መኖር ጀመረች።
ቅዱሳን ሞተውም ያማልዳሉ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እውነተኛዋ ሀይማኖት
እንደዚች ሴት ኃጢአቱን የሚያስታውስ ማን ነው?
ወደ ካህን ሄዶ ንስሐ የገባስ ስንቱ ነው?
ስለ ኃጢአቱ በረሃ የተንከራተተ ማን ይሆን?
የዚችን ሴት መጨረሻ ያሳመረ የሁላችንም መጨረሻ ያሳምርልን ኃጢአቷን የደመሰሰ የሁላችንም ኃጢአት ይደምስስልን!
ለንስሐ የሚሆን ፍሬ አድርጉ
ምን ተረዳችሁ? ሀሳብ መስጫው ላይ አጋሩን እንማማርበት🙏
ቻናሉ👇
https://t.me/eotcy
መወያያ👇
https://t.me/eotcy_comment