cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

A ̶l ̶ ̶a ̶e ̶r ̶a ̶f

Al åěraf ye hadra jemeå

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استزبان مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
پست‌های تبلیغاتی
141
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

Ramadan kharim😍 ረመዳን ከሪም💚👌
نمایش همه...
1.57 MB
❤ ኢስራዕ ወል ሚዕራጅ ❤ 💚ኢማም ሆኖ አሰገደ በበይተል መቅዲስ 💚ደግሞም ወደ ሰማይ ሙንተሀ ድረስ 💚ከጂብሪል ጋር ሆኖ ሄደ ገሰገሰ 💚መለኮች ጀመሩ እሱን ማወደስ 💚 አሏህ ጋር መጅሊስ ረፍረፍ አስቀመጠው ❤@mewlied
نمایش همه...
የኢስራእና የሚዕራጅ ለይል!! ✦✦✦ ይሄ ለይል የተባረከ የዱዓ ለይል ነው። ✦✦✦ መቼስ ከቀን እና ከለይል የትኛው ይበልጣል የሚል አይጠፋም።አላህን ሳታምፅ ያሳለፍከው ቀንም ይሁን ለይል ከሁሉም የተሻለ ቢሆንም ደጋጎቹ ግን ከቀን ይልቅ ለይሉን ያስበልጣሉ።በአፈጣጠርም ቢሆን ከቀን ቀድሞ የተኸለቀው ለይሉ ነው።ቀን ላይ የማናገኛት የስቲጀባ ሰአት ሁሌም የሌሊቱ አንድ ሶስተኛ ሲቀረው እናገኛታለን። ✦✦✦ "የንዚሉ ረቡና" የሚለው ሐዲሰ በቀጥታ ከለይሉ ጋር ነው ቁርኝቱ።የንዚሉ ሲል ሙዷፉ ሐዝፍ ሆኖ እንጂ "የንዚሉ መለኩ ረቢና"ለማለት ነው።ይህንንም ታላቁ ሙፈሲር አል ኢማሙል ቁርጡቢይ ተፍሲራቸው ላይ በግልፅ አስቀምጠዋል። ሙዷፍ፣ ሙዷፍ ኢለይሂ እና ሓዝፍ የሚሏቸው ቃላት የነሕው ጉዳዮች ናቸው። ✦✦✦ ታላቁ ሐፊዝ ኢብኑ ሐጀር አል ዓስቀላኒይ ቡኻሪን ከሚተነትኑበት ፈትሑል ባሪ ላይ "የንዚሉ"ከሚለው ቃል ያለቸው "የ" "ዩ" ተብላ መነበብ እንዳለባት ኢብኑ ፉረክን ጠቅሰው ዘግበዋል።ማለትም የንዚሉ ሳይሆን "ዩንዚሉ"። የንዚሉ ማለት "ይወርዳል" ሲሆን "ዩንዚሉ" ከሆነ ደግሞ ያወርዳል ማለት ነው።ይወርዳል ሲል የተፈለገበት መላኢካ በአላህ ትእዛዝ ወደ ቅርቢቱ ሰማይ ይወርዳል ማለት ሲሆን "ያወርዳል" ከሆነ ደግሞ አላህ መላኢካውን ወደ ቅርቢቱ ሰማይ ያወርዳል ማለት ነው። የአሏህ መላኢካ የሌሊቱ አንድ ሶስተኛ ሲቀረው ወደ አንደኛው ሰማይ ይወርድና "ሃል ሚን ዳዒን ፈዩስተጃበ ለህ፣ሃል ሚን ሙስተጝፊሪን ፈዩጝፈረ ለህ፣ሃል ሚን ሳኢሊን ፈዩዕጧ....." እያለ እንዲለፍፍ ጀሊሉ ያዘዋል። "ማን ነው የሚለምን ልመናው የሚሰማለት፣ማነው ምህረትን ጠይቆ ምህረትን የሚያገኝ፣ ማነው የሚጠይቅና የሚሰጠው ...." እንደማለት ነው። ወዳጄ! በደንብ የሚገባህ ነሕውን በደንብ ስትቀራው ነውና አትቦዝን። ✦✦✦ እናማ "ያገኘም አገኘ ያጣም ያን ቀን አጣው" እንዳሉት የዘቡራ ልጅ ሰይድ ጫሊ በለይሉ ተነስቶ እጁን አሏህን ለመለመን የዘረጋ በብዙ ማትረፉ አይቀሬ ሲሆን እንዲሁ ተኝቶ ያሳለፈው ደግሞ ይቀርበታል።በለይሉ ጀሊሉን መለመን ብዙ ትርፍ አለውና።እንዴታ! ለይሉኮ የጀግኖች ሜዳ ነው። የሰው ልጅ ቀን ሲባዝን ውሎ ለሊቱን በእረፍት ሊያሳልፍ ጋደም ሲል እንደርሱ ሲባዝኑ የዋሉ ግን ደግሞ የለይሉን ምስጢር የተገነዘቡ ድንቅ የአሏህ ባሮች ገላቸውን ከምንጣፉ አርቀው ሰርክ ዒባዳ ሲያደርጉ ያነጋሉ። ✦✦✦ ወዳጄ! ይሄ ለይሉ የሚሉት ሌላ ተአምርንም አስተናግዷል። ለሰማይ ለመሬት የከበደ "ኢስራእና ሚዕራጅ" የሚሉትን አጃኢበኛ ትእይንት ተንፀባርቆበት አልፏል።ክስተቱ ለኛ ነብይ ብቻ የተሰጠ የልህቀት ማሳያ ምልክት ነው። መገን ለይሉ! ✦✦✦ የክስተቱ መንስኤ የነብዩ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ ሃዘን ነው።መቼስ ነብዩ እንደኛው ሁሉ የሰው ልጅ ናቸውና በወቅቱ ከመከራ ላይ መከራ ተጨማምሮባቸው በጭንቀት ተከበው ነበር። ﺃﺷﺪ ﺍﻟﻨﺎﺱ ﺑﻼﺀ ﺍﻷﻧﺒﻴﺎﺀ ﺛﻢ ﺍﻷﻣﺜﻞ ﻓﺎﻷﻣﺜﻞ . እንዳለው ሐዲሱ ።ከሰዎች ከባድ በላእ የሚደርስባቸው ቀዳሚዎቹ ነብያቶች ናቸው።አንዳንዱ የኔ ብጤ ትንሽ ነገር ስትነካው እየየውን ያቀልጠዋል።በላኡንም የመጠላት ምልክት አድርጎ ያስበዋል።ነገሩ ግን በተቃራኒው ነው። ✦✦✦ የኛ ነብይ የመከራ ዶፍ ላያቸው ላይ እንደ መብረቅ እያጓራ በነበረበት በዚያ ጭንቅ ሰአት ይባስ ብሎ የቅርብ ደጋፊ የነበሩ በጣም ወሳኝ ሰዎቻቸውን በሞት ተነጠቁ።አቡ ጧሊብን እና እመት ኺዲጃህን[ረዲየሏሁ ዓንሃ] የኛ ነብይ ይሻል እንደሁ ብለው ወደ ጧኢፍ ቢያቀኑም ጭራሽ የወቅቱ የጧኢፍ ሰዎች "ውሻ በቤቱ ይኮራል" እንዲሉ ለአለማት እዝነት የተላኩትን ያን ሰላማዊ ነብይ ከሃገራችን ውጣልን ብለው ድንጋይ ውርውሮሽ ጀመሩ። አሁን በኛ ዘመንም "አንተ የኛ ዘር አይደለህምና ሃገራችንን ለቀህ ውጣ" የሚሉ መንጋዎችን ሳይ በጧኢፍ የነበሩትን ያስታውሱኛል።ጥሎት ለሚሄደው፣ለዛውም ንብረቱ ላልሆነው የአላህ መሬት "ውጣልኝ" ማለቱ መሃይምነት እንጂ ሌላ ምን ሊሆን ይችላል?! ✦✦✦ ሐቢባችን በዚህ ሁሉ መከራ ውስጥ ሆነው አንድም የማማረር ቃል አላወጡም።ምንም እንኳ በበላእ ባህር ቢዋጡም "የጧኢፍ ህዝቦችን ጠራርገህ አጥፋልኝ" ብለው ግን ዱዓ አላደረጉም።የአለማት እዝነት ተደርገው ተልከዋልና። ጀሊሉ! "ጭንቅን ደስታ ይተካዋል፣ ከመካራ በኋላ ተድላ ይመጣል" እንዳለው ያን ሁሉ ጭንቀት የሚያስረሳ ነገር በዚህች አሁን እኔና አንተ በምናወጋባት ለይል ተመሳሳይ ሰይዱና ጅብሪል ከሰማየ ሰማያት ተልኮ ወደ ምድር ነብዩን ፍለጋ ወረደ።ነብዩ ያኔ በጃዕፈርና በሐምዛ መሃል ተኝተው ነበር።ጅብሪል በጣሪያው በኩል ነበር የገባው።ጅብሪል ጠጋ ሲሉ ጣሪያው በአሏህ ቁድራ ጋ ብሎ ተከፈተ።ጀብሪል ገቡና ነብዩን ይዘው ወጡ። ✦✦✦ በዚያ ውድቅት ለሊት ጀብሪል ነብዩን ከቤት ካስወጣቸው በኋላ ካዕባ ወስዶ ደረታቸውን ሰነጠቀውና በረቀቀ ዘዴ ልባቸውን አውጥቶ በዘምዘም ውኃ አጠበው።ከዚያም "ሒክመተን ወኢማና"የሚባሉ እጅግ ውድ ነገሮች ልባቸው ውስጥ አንዠቀዠቀውና ሞላው።ዑለማኦች ይሔን ነገር ሲተነትኑ ለአስገራሚው ጉዞ ቅድመ ዝግጅት ነው ይላሉ። የትኛውም ነብይ ያልሄደውን አለም ሊጎበኙ ስለሆነ ያንን የሚቋቋም የማይነጥፍ አቅም ያስፈልጋቸው ነበር። ከዚያማ በኋላ .... ለጉዞው ማሳለጫ ይሆን ዘንድ ሰማየ ሰማያትን አቋርጦ የመጣው የተሽቆጠቆጠው ቡራቅ ቀረበ።ውጣበት አላቸው ጀብሪል ለነብዩ .... ነብዩ ቡራቁ ላይ ሊወጡ ሲሞክሩ ቡራቅ ደስታው አስክሮት መቅበጥበጥ አበዛ። ጅብሪል እንዲረጋጋ ነካ አደረጉት ቀጥ አለ።መገን ጅብሪል ባለ ስድስት መቶው አክናፍ! አንዱን ክንፍ ሲዘረጉት ማበይነሰማኢ ወል አርድ ከፀሃይ መውጫ እስከ መግቢያው እፍፍፍን አድርጎት ይሞላል።አጃኢብ ነውኮ። በዚህች ለይል የኛ ነብይ ጅብሪልን በትክክለኛ አፈጣጠሩ አዩት።ባለ ስድስት መቶ ክንፉ አስገራሚ ፍጥረት ሰይዱና ጅብሪል በዚያ አፈጣጠር ማየት አስቡት .... በነገራችን ላይ ነብዩ ጅብሪልን በትክክለኛው አፈጣጠር ያዩት ሁለት ጊዜ ሲሆን በመጀመሪያው ራሳቸውን ስተው ወድቀዋል።በሁለተኛው ግን የተገጠመላቸው ልዩ አቅም ስለነበር አልወደቁም።ተቋቋሙት። ✦✦✦ በጅብሪል የተነካው ቡራቅ መቅጥበጡን አቆመ።ነብዩ ቡራቁ ላይ ወጡ።ጉደኛው ቡራቅ አይኑ ያየበት ድረስ እንዲወነጨፍ ተደርጎ የተሰራ ተአምረኛ ሰንጋ ነው።አሁን ሁሉም ነገር ዝግጁ ነው። እናም ጉዞው ለይሉ ላይ ጀመረ... ለይሉ!!! እንኳን አደረሳችሁ! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @mewlied @mewlied @mewlied @mewlied @mewlied @mewlied @mewlied @mewlied
نمایش همه...
"ወገኖቼ! ከፈጣሪ በታች የኔ ህይወት በእጃችሁ ላይ ይገኛል፡፡ እያያችሁ አሳልፋችሁ ለሞት አትስጡኝ!" ሀያት ኢብራሂም #አስቸኳይ_የእርዳታ_ጥሪ_ለእህታችን_ሀያት_ኢብራሂም እህታችን ሀያት ኢብራሂም የ11ኛ ክፍል ተማሪ ስትሆን ኩላሊቷን በመታመሟ ምክንያት በአዲስ አበባ ግሩም ሆስፒታል (Girum Hospital) ለ3 ወር ስትታከም ቆይታለች። በአሁን ሰዓት በጣም በሚያሳዝን መልኩ የህመሟ ሁኔታ ወደ መጨረሻው ደረጃ የኩላሊት ህመም (End-Stage Renal Failure) በመቀየሩ ምክንያት ሁለቱም ኩላሊቷ ስራ ስላቆመ በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ውጪ ሀገር በመሄድ የኩላሊት ንቅለ ተከላ (RENAL TRANSPLANT OR KIDNEY TRANSPLANT) እንድታዳርግ በዶክተሮቿ ተወስኗል፡፡ለዚህ ህክምና ሁሉንም ሂደት (Process) ጨምሮ እስከ ሁለት ሚልዮን (2,000,000) ብር የምያስፈልግ ሲሆን ቤተሰቦቿ ይህን ሁሉ ወጪ ለብቻቸው መሸፈን ስለማይችሉ ሁላችንም የእህታችንን ህይወት ለማዳን የበኩላችንን የወንድማማችነት; የእህትማማችነት; የሰብዓዊነት እንዲሁም የዜግነት ግዴታ እንወጣ ስንል እንጠይቃለን:: ህመሟ ግዜ የማይሰጥና አስቸኳይ ህክምና የሚፈልግ ሲሆን ከቀን ወደ ቀን እህታችንን እያዳከመ ህይወቷ ሊነጥቅ ስለሆነ እህታችን ሳትደክም እና ህይወቷን ሳናጣ በቻልነው አቅም ትንሽም ብትሆን ፈጣር ያገራልንን ያህል እርዳት እናድርግላት። የባንክ አካውንት - የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE) 1000353443147 Hayat Ebrahim & Sada Sultan - የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ (COOP) 1000089014135 Hayat Ebrahim Umer - አዋሽ ባንክ 01425853981500 Hayat Ebrahim Umer ሰልክ ቁጥር 0983676776 0920942369 0912823605 👉 @mewlied
نمایش همه...
#በአንድ ወቅት #ስለመውሊድ ምን ይላሉ? ተብለው ሲጠየቁ: <<መውሊድን ለማክበር ጥያቄ ማንሳት ማለት ፀሐይና ጨርቃን አሉ ወይ? ብሎ ጥያቄ ማንሳት እደማለት ነው።>>ብለው መልሰዋል። #ረጅም ሐያት ከአፊያ ጋር ለተቀዳሚ #ሙፍቲ ዶ/ር ሐጅ ዑመር እድሪስ ተመኘን! 👇👇👇👇 👇👇👇👇 @mewlied @mewlied @mewlied @mewlied @mewlied @mewlied @mewlied
نمایش همه...
petitionu የተጀመረው ትላንት ነው በአንድ ወር ውስጥ በትንሹ 100,000 ሰው ፈርሞ ለ white house gov't (ለ ኮንግረስ አባላት)መግባት አለበት ያለበዚያ ዋጋ የለውም , ተብሏል የ profile pic ከማድረጋችን በተሻለ ይሄን petition መፈረም then share ብናደርግ የተሻለ ነው ባረከሏሁፊኩም 👇👇👇👇👇 @mewlied @mewlied
نمایش همه...
نمایش همه...

Learn how the Biden-Harris Administration is tackling our nation’s challenges and building our country back better from this crisis.

ልብ የሚነካው የረሱል ሞት ሳያነቡ እንዳያልፋት ነብያችን (ሰ.ዓ.ወ) ወደ አኺራ ሲሄዱ የነበረው ሁኔታ ሰሀቦች ሁሉ ቀኑ የጨለመባቸው ያህል ነበር ። መለከል መውት አሰላሙዓለይኩም ብሎ ገባ ወዓለይኩሙሰላም አሉ ነብያችን (ሰ.ዓ.ወ) ለዝያራ መጣህ ወይስ ሩሕ ለማውጣት ብለው ጠየቁት ለዝያራም ሩሕም ለማውጣት ከፈቀድክልኝ ካልሆነ እመለሳለሁ አላቸው አንተ መለከል መውት ሆይ ጅብሪልን የት ተውከው ኣሉት በመጀመርያው ሰማይ መላኢኮች እያጽናኑት ነው አላቸው ከዛ ብዙ አልቆየም ወድያው መጣ ከራስጌያቸው በኩል ተቀመጠ የአላህ አምር መቅረቡን አውቅክ ኣሉት ኣዎን ኣላቸው እስቲ አበስረኝ ኣላህ ምን ኣይነት መስተንግዶ ነው ያዘጋጀልኝ ኣሉት ጅብሪልም ኣላቸው የሰማይ በሮች ሁሉም የጀነት በሮች ተከፍተዋል መላኢኮች ሶፍ ሶፍ ሁነው ያንቱን ሩሕ እየጠበቁ ነው ሑረልዓይኖችም የሩሕዎን መምጣት እየተጠባበቁ ነው አልሓምዱሊላህ እስቲ ደግሞ አበስረኝ ኡመቴ ከኔ በኋላ እንዴት ይሆናሉ ~~~~{ፊዳከ ሩሒ ያሓቢበላህ} ~{[ በዚች ቅጽበት ሩሓቸው ሊወጣ ተዘጋጅቶ የራሳቸውን መስተንግዶ የተዘጋጀላቸው ተነግሮዋቸው ሌላው ስራው ያውጣው አላሉም ሁሌም ጭንቀታቸው ለኡመታቸው ነበር ። ሓያታቸው ሙሉ ያኣላህ ምን ኣይነት ነብይ ናቸው ሶሓቦች እንዴት ሁነው ይሆን በእድሚያቸው ማለቂያ?} ጅብሪልምኣላቸው ኣላህ ጀነት ሓራም ኣድርጓል ለሌሎች ነብዮች አንተ ከመግባትህ በፊት እንዲሁም ያንተ ኡመት ከመግባታቸው በፊት ሓራም ድርጎታል ለሌሎች ነብዮች ኡመት ኣሁን ልቤ ተረጋጋ ጭንቀቴም ተውገደልኝ ኣሉ ኣንተ መለከል መውት ሆይ ኣሁን ቅረብና ሩሔን ኣውጣ ኣሉት ቀርቦ ሩሓቸው ማውጣት ጀመረ ሩሓቸው እምብርታቸው ኣካባቢ ሲደርስ ያጅብሪል የሞት ህመም እንዴት ይመራል አሉት ጅብሪልም ፊቱን ኣዞረ ነብያችን (ሰ.ዓ.ወ) ፊቴን ማየት አስጠላህ ወይ ኣሉት ጅብሪልም ያሓቢበላህ {በሰክራት ጭንቀት ላይ ሁነህ ኣንተን ማየት ልቡ የሚረጋለት ማነው} ኣላቸው {ኣነስ ረ.ዓ እንዲህ ይላሉ ሩሓቸው ደረታቸው ኣካባቢ ስትደርስ ኣደራቹ በሶላትና በናንተ ቁጥጥር ያሉት ሰራተኞች} ሩሓቸው ልትወጣ ቀርባ እንኳን ስለ ሶላት ማውሳታቸው አልተዉም ዓልይ ረ.ዓ እንዲህ ይላሉ ረሱል (ሰ.ዓ.ወ) በመጨረሻው እስትንፋሳቸው ልትቋረጥ ስትል ከንፈራቸው ኣንቀሳቀሱ ጠጋ ብዬ ሰማኋቸው ድምጻቸው ደክሞ ኡመቴ ኡመቴ እያሉ ሩሓቸው ወጣ ... ሰለዋቱ ረቢ ወሰላሙሁ ዓለይሂ እስኪ አንተ / አንቺ እሄንን መልክት እንኳን ሼር አድርጉት https://telegram.me/mewlied
نمایش همه...
A ̶l ̶ ̶a ̶e ̶r ̶a ̶f

Al aeraf ye hadra jemea

· •⊰✿ 💎✿⊱• ❀━┅┉┈ድንቅ ታሪክ ናት┈┉┅━❀ በሙሳ ዐ.ሰ ዘመን ነው....አንድ በጣም ድህነት ያጎሳቆላቸው ለዘመናት በችግር እና በረሀብ የኖሩ ባልና ሚስት ነበሩ። ይሁን እንጂ ይህን ሁሉ ዘመናት በሰብር አሳልፈዋል...። እናም አንድ ቀን እቤታቸው ጋደም ብለው ሳለ ሚስት ለባለቤትዋ፦"ሙሳ አላህን ማናገር የሚችል ነቢይ ነው አይደል?" ብላ ትጠይቀዋለች። እሱም፦"አዎን" ይላታል። "ታዲያ ለምን እሱጋ ሄደን ስለ ሁኔታችን አንነግረውም አላህንም ስለኛ ያናግረው ሀብታም እንዲያረገን ቀሪ ህይወታችንን በድሎት እንድንኖርም ይጠይቅልን።" አለችው። ባልም በሚስቱ ሀሳብ ይስማማና ሌሊቱ እንደነጋ ጉዞ ወደ ሙሳ ዐ.ሰ ቤት ጀመሩ። ሙሳንም ዐ.ሰ አገኟቸው። ስለድህነታቸው ነግረዋቸውም በዚህ ጉዳይ እሳቸው አላህን እንዲለምኑላቸው ጠየቋቸው። ሙሳም ዐ.ሰ አላህን ለመኑላቸው። አላህም፦"ሙሳ ሆይ! እኔ እነዚህን ሰዎች በችሮታዬ ለአንድ አመት ያህል ሀብታም አደርጋቸዋለሁ አንድ አመት ካለፈም ወደነበሩበት ድህነት እመልሳቸዋለሁ።"ብሎ መለሰላቸው። እሳቸውም ጥንዶቹ ጋ በመሄድ አላህ ዱዓቸውን ሙስተጃብ እንዳደረገላቸው ሀብታምም እንደሚሆኑ ነግረዋቸው እናም ግን ለ አንድ አመት ቢቻ እንደሚቆይ አክለው ነገሯቸው። እነዚህ ምስኪኖችም የሰሙትን ማመን ተሳናቸው። በአጭር ግዜ ውስጥ ካለሰቡበት መንገድ ሀብታም መሆን ጀመሩ።ማንም ከሚኖረው የተሻለ ኖሮ መኖርም ጀመሩ። እናም አንድ ቀን ይህች ብልህ ሚስት ለባሏ እንዲህ አለችው፦"ይህ ፀጋ ይህ ድሎት ለ አንድ አመት ብቻ እንደሚዘገይ ታውቃለህ አይደል? ስለዚህ በዚህ ንብረታችን አንድ መልካም ስራ እንስራ" ባልይውም በሀሳቧ ይስማማል። ከዚያም በከተማዋ ግንባር ቦታ ላይ አደባባይ መልክ አንድ ትልቅ ቤት ይገነቡና 7 በር አበጁለት። ለሰውም መተላለፊያ ሰሩ። ቤቱ ተገንብቶ ካለቀ በኋላ እዛ ቤት ውስጥ ምግብ እያዘጋጁ ለአላፊ አግዳሚ ጠዋት ማታ ምግብ ይቀልቡ ጀመር...። በዚህ ሁኔታ ሳሉ ወራት አስቆጠሩ። ሙሳም በትኩረት ይከታተሏቸው ነበር። ማይደርስ ቀን የለምና ያ የተወሰነላቸው ቀን ቀጠሮውን ጠብቆ ከች አለ። እነሱ ግን የቀጠሮ ቀኑ ሁላ ትዝ አላላቸውም በስራቸው ተጠምደዋል። ያ ቀጠሮ ቀናቸው አለፈ እነሱ ግን ያው ናቸው ምንም አልቀነሱም ብቻ በስራቸው ተጠምደዋል.... ሙሳም ዐ.ሰ ባዩት ሁኔታ ተገርመው፦ "ያ ረብ ቃል የገበኽላቸው ለ አንድ አመት ሆኖ ሳለ እንዴት እስካሁን እልደኸዩም?"ብለው አላህን ጠየቁ። /እዚጋ እሳቸው ሰዎቹን ተመቃኝተው ሳይሆን የአላህን ሂክማ ለማወቅ ነው የጠየቁት/ ቸር የሆነው አላህም፦ "ሙሳ ሆይ! ለነዚህ ጥንዶች ከፀጋ በሮቼ አንዲትን በር ስከፍትላቸው...እነሱ ደሞ 7 በር ከፍተው ባሪያዎቼን መቀለብ ጀመሩ። ሙሳ ሆይ! እነሱ ይሄን ሲያረጉ አይቼ የከፈትኩላቸውን በር መዝጋት ከበደኝ"አለው። ❀━┅┉┈ሱብሀን አላህ┈┉┅━❀ 💬 ሼር ማድረጉን አይርሱ 👇 @mewlied @mewlied @mewlied @mewlied
نمایش همه...
አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱ ይህ የማዲህ ኢብራሂም አባስ (የእናቱ) የቴሌግራም ቻናል ነው :: ለአስተያየት ወይም ጥያቄ 👉 @Yenatuuuuuu https://t.me/joinchat/AAAAAEeqT-WywiMC_arxHA 👇👇👇👇👇👇👇 Al aeraf yehadra jemea https://telegram.me/mewlied
نمایش همه...

یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.