fa
Feedback
ብሩህ ተስፋ

ብሩህ ተስፋ

رفتن به کانال در Telegram

Gefa ወደላይ

نمایش بیشتر
6 971
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-367 روز
-20230 روز
آرشیو پست ها
ፈጣሪያችንን እናስብ! ነፍሳችን ሰላምን ትሻለች፣ ውስጣችን መረጋጋትን ይመኛል፣ ስሜታችን ሃይባይ ያስፈልገዋል። እንዳሻቸው የሚነዱንም ሆነ አንዳሻን የምንነዳ ግኡዛን አይደለንም። ፈጣሪያችን በጥበቡ የሰራን የእጆቹ ድንቅ ስራዎች ነን። መንፈሱ በውስጣችን ይመላለሳል፣ ከእርሱ የሚታደለን በረከት የሰላማችን ምንጭ ነው፣ መረጋጋታችን፣ እረፍታችን አፅናኝ ቃሉ ነው። ተስፋ ብታጡ እንኳን በእግዚአብሔር አምላካችሁ ተስፋ አትቁረጡ፣ በህይወት አቀበት ቁልቁለት ብትፈተኑ እንኳን እርሱን ተስፋ ማድረጋችሁን እንዳታቆሙ፣ ደክማችሁ፣ ዝላችሁ፣ ውስጣችሁ ታክቶ ብትገቡ እንኳን ወደ አምላካችሁ ለመጠጋት አትስነፉ። ምድር መኖሪያችን ብትሆን፣ ህይወት ፈተናችን ቢሆን እረፍትና ሰላማችን እግዚአብሔር አምላክ ሁሌም ከጎናችን አለ። አዎ! ፈጣሪያችንን እናስብ፤ ሃልዎቱን ውስጣችን እናስገባ፣ በስሙ እንድን ዘንድ፣ በፀጋው እንታነፅ ዘንድ ከልባችን እናስገባው። ምን ለማድረግ ምን እስኪታያችሁ ትጠብቃላችሁ? ምንስ ለማትረፍ ምናችሁን አሳላፋችሁ ትሰጣላችሁ? የጨለመ ዘመን ተስፋ ላይኖረው ይችላል እግዚአብሔር ባለበት ግን ከብረሃን በቀር ጨለማ ሊኖር አይችልም። ማልቀስ ካለባችሁ ለሰው ሳይሆን ለፈጣሪያችሁ አልቅሱ፣ መታደስ ካለባችሁ በምድራዊ ጌጣጌጥ ሳይሆን በአምላካችሁ ህያው ቃል ታደሱ፣ እራሳችሁን ማበርታት፣ ከችግራችሁ በላይ መሆን፣ ለሃገር ለወገን መትረፍ ከፈለጋችሁም እምነታችሁን አጠንክሩ፣ ብሩህ ተስፋን ሰንቁ። አዎ! አለም የምታድነን ይመስል አለም ላይ ብንጣበቅ፣ ሰው ይታደግን ይመስል በሰው ብንታመን፣ የዛሬ ዝናና ንብረታችን ዘላለማዊ ይመስል በእርሱ ብንመካ  መጨረሻችን መና፣ አወዳደቃችንም የከፋ ይሆናል። "ለደስታዬ ሁሉን አድርጌያለሁ፣ ስኬታማ ለመሆን የሚጠበቅብኝን ሃላፊነት በሙሉ ተወጥቼያለሁ፣ ውስጤን ለማሳረፍ መሔድ ያለብኝ ቦታ ሁሉ ሄጄያለሁ።" ልትሉ ትችላላችሁ። ነገር ግን ያጣችሁትን አንድ ወሳኝ ነገር አስታውሱ። እግዚአብሔር ያልታከለበት የደስታ ፍለጋ፣ አምላክ ያልፈቀደው የስኬት ጉዞ፣ በፈጣሪ ያልተመራ የውስጣዊ ሰላም ዳሰሳ በምንም በማንም ቢከናወን ሙሉ ሊሆን አይችልም፣ የሚያሳርፍና አስደሳች ሊሆን አይቻለውም። ብክነታችሁን ቀንሱ ከፈጣሪያችሁ ጋር ግንኙነታችሁን አጥብቁ፣ ለሰላማችሁ ቁሙ፣ እውነተኛውን ውስጣዊ ሰላም ከልባችሁ አጣጥሙ፣ ከድካማችሁ ለማረፍ ከአምላካችሁ እቅፍ ተጣበቁ።

በዋጋ እዚህ አለህ! በመስቀሉ አዳነን፤ በሞቱ ህይወትን ዘራብን፤ የፍቅርን ሃያልነት፣ የመውደድን ጥግ እራሱን ሰውቶ፣ እራሱን ሰጥቶ ገለፀልን። ገደብ አልባው ፍቅሩ፣ ማለቂያ የሌለው መውደዱ ከዙፋኑ ሳበው፤ ወደ ምድር አወረደው፤ በወደዳቸው፣ በመረጣቸው፣ ባፈቀራቸው ልጆቹ እጅም እንዲሰቀል አበቃው። ሰቃዮቹም ሰዎች የሚድኑትም ሰዎች፣ የሚሰቀለውም አምላክ የሚያድነው፣ የሚፈውሰውም እራሱ የተሰቀለው፣ ህይወቱን የሰጠው ድንቅ መካር ኀያል ቅዱስ ጌታ። የፍቅሩ ግዝፈት እየሰቀልነው ማዳኑ፣ የመውደዱ ጫፍ እያወቀ ለመሞት መዘጋጀቱ። በእርግጥ ፍቅር የለም ቢባል እንዴት ይሆናል እራሱ ፍቅር፣ እራሱ መውደድ፣ እራሱ ትርጉሙ ለሰው ልጅ ሲል መስቀል ላይ ተቸንክሮ እየታየ። ገዳዮቹን ሊያድን የሚመጣ፣ አጥፊዎቹን ከእስራታቸው ሊፈታ፣ በደለኞችን በገባው ቃል ነፃ ሊያወጣ የሚችል ከአንድ አምላክ በቀር እርሱ ማን ሊሆን ይችላል? አዎ! በዋጋ እዚህ አለህ፤ በደሙ ህይወትን አገኘህ፤ በፍቅሩ ሃያልነት ከዘላለም ሞት አመለጥክ፤ በርህራሔው ጥግ በሰውነትህ ከበርክ። የአምላክ መውደድ በተግባር እስከሞት ነው፤ የእኛስ ፍቅር እስከምን ይሆን? እርሱ ውደዱኝ ባይል እንኳን ባልንጀራችንን ብንወድ፣ ብናከብር እርሱን እንደወደድን እንደሚቆጠር አስተምሮናል። የምታየውን፣ የምታውቀውን፣ ከጎንህ ያለውን ወዳጅህን ሳትወድ እኔን ያላየሀኝን፣ ያላወከኝን፣ ያልዳሰስከኝን እወድሃለሁ ብትል እንዴት ይሆናል? ይላል አምላክ። ቃላት ቢደረደሩ፣ ዜማ ቢረቅ፣ ጥበብ ብትኖር የአምላክን የማዳን ጥበብ አይገልፁትም። ለዚህም ነው እግዚአብሔር አለምን ከፈጠረበት አለምን ያዳነበት ጥበቡ ይበልጣል መባሉ። አዎ! ፍቅርን ከክርስቶስ እንማር፤ መሰዋትን፣ እራስን መስጠትን፣ ሳይሳሱ ለቃል መታመንን ከቸር አምላካችን እንማር። ሰላም እርሱ ነው፤ መውደድ እርሱ ነው፤ ፍቅር እርሱ ነው። በእርሱ ልኬት መሰዋት፣ በእርሱ መጠን እራስን መስጠት ባይጠበቅብን እንኳን እርስ በእርስ ብንዋደድ፣ ብንደጋገፍ፣ ብንማከር፣ ህይወት ላይ ብንተባበር ዳግም በረከቱን እንቋደሳለን። ስሙን መጥራት፣ ለምስጋና መትጋት፣ ለውዳሴ መንቃት ትንሹ ክፍያችን ነው። ስራውን መመስከር፣ ማዳኑን መናገር፣ ለአምላክነቱ ለክብሩ መስገድ ጥቂቱ ስራችን ነው። ሀጢያት ቢበዛብን፣ በደል ቢደራረብብን፣ ጥፋታችን እልፍ ቢሆን ይቅር ለማለት ህይወቱን የሰጠ አምላክ አለና እራሳችን እንስጠው፣ ውስጣችንን እናሳየው፣ ማዳኑንም በእያንዳንዳችን ህይወት እንመልከት። “ ከምርጥ ፅሁፎች የተገለበጠ”

የተሻለ አለህ! በአውሎ ንፋስ ውስጥ ብትሆን፣ ዶፍ ዝናብ ቢወርድብህ፣ ዋጋህ ያነሰበት፣ መኖርህ የማይቆጠርበት፣ አበርክቶትህ የማይታይበት፣ ስራህ የማያፈራበት፣ ማንነትህ የማይመረጥበት ስፍራ ብትኖር እንኳን እግዚአብሔር አብሮህ ካለ ሁሌም የተሻለ ከፍ ያለ ነገር አለህ። ምንም እንኳን እምነታችን ቢጎድል፣ ክፋታችን ቢበዛ፣ ሃሳባችን ቢያንስ፣ ምግባራችን የወረደ፣ ስራችንም አሳዛኝ ቢሆንም ፈጣሪ ግን ጥሎ አይጥለንም።፣ ትቶ አይተወንም ሁሌም ይመለከተናልና መቼም እንዴትም ችላ አይለንም። የተውን ሰዎች ይኖራሉ፣ ያገለሉን፣ የተጠየፉን እንዲሁ እንደዋዛም የናቁን ሰዎች ይኖራሉ ዋናው ነገር ግን በአምላካችን በእግዚአብሔር አለመናቃቸስንና በእርሱ አለመገፋታችን ነው። አዎ! ጀግናዬ..! የተሻለ አለህ! ከዛሬው የላቀ፣ ከትናንት የገዘፈ፣ ከአሁንህ ያየለና ከፍ ያለ ስፍራ ይኖርሃል። የማይቀየሩ የሚመስሉ ከባድ ሁኔታዎች ይቀየራሉ፤ ይወርዱ የማይመስሉ ሸክሞች፣ ይፈቱ ያልመሰሉ ችግሮች፣ ይስተካከሉ ያልመሰሉ ውጥንቅጦች ይወርዳሉ፣ ይፈታሉ፣ ይስተካከሉ። እምነትህ ቢፈተን ግራ አትጋባ ይልቅ ለተሻለ ክብር እንደታጨህ አስተውል፤ በፈተናህ ብዛት አትደናገር ይልቅ የድልህ ቀን ቅርብ እንደሆነ አስተውል። በጫናዎች ብዛት የማትሸበር፣ ለምድራዊ ፈተና የማትበገር፣ ከፈጣሪህ በቀር በማንም ለማንም የማትታወቅ የአንዱ አባትህ ልጅ እንደሆንክ አስተውል። እግዚአብሔር በልጆቹ ይገለጣል፤ ስራው በልጆቹ ይከናወናሉ፤ ልጆቹም በእርሱ ፍቃድ በእርሱ መንገድ ይሔዳሉ፣ መሻቱን ይፈፅሙ፣ ህጉንም ይጠብቁ ዘንድም ሃላፊነት አለባቸው። አዎ! ሁሉን የፈጠረ፣ ሁሉን የያዘ፣ በሁሉ ውስጥ ያለው አምላክህ ባንተ ውስጥ ስለመኖሩ አትጠራጠር፤ ለተሻለው ስፍራ እንደሚያበቃህ እምነት ይኑርህ። የሚሰሩ እጆች በረከትን ከአምላካቸው ይቀበላሉ፣ የሚታትሩ የሚሮጡ እግሮች ብርታትን ከፈጣሪያቸው ያገኛሉ፤ ዝቅ ብለው የሚያገለግሉ፣ አምላካቸውን በተሰበረ ልብ የሚማፀኑ፣ ፀሎታቸውን በምስጋናና በልመና የሚያቀርቡ ነፍሳት ሁሌም የተሻለውን እንደሚያገኙ ቅንጣት ጥርጣሬ የላቸውም። ማሰብ ላይ በርታ፤ መስራት ላይ ጠንክር፣ አምላክህን ይዘህ ፈተናህን ተጋፈጥ፣ በፀሎትህ ፅና፣ ምስጋናህን ደጋግመህ አቅርብ፣ ካንተ በላይ የሚሰራብህ፣ ተአምር የሚያደርግብህ እግዚአብሔር አብሮህ እንደሆነ አስብ። ብቻህን የሆንክ ቢመስልህ እርሱ ከጎንህ አለ፤ የተገፋህ ቢመስልህ በእርሱ እቅፍ ውስጥ ነህ፤ የወደክ ቢመስልህ እርሱ ያነሳሃል፤ በሚገባህ ስፍራም በክብር ያቆምሃል።

እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ! “አዲስ ትእዛዝ እሰጣችኋለሁ፤ ይኸውም እርስ በርሳችሁ እንድትዋደዱ ነው፤ እንግዲህ እኔ እንደ ወደድኋችሁ እናንተም እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ። እርስ በርሳችሁ ብትዋደዱ፣ ሰዎች ሁሉ የእኔ ደቀ መዛሙርት እንደ ሆናችሁ በዚህ ያውቃሉ።” -ቅዱስ መፅሐፍ ፍቅር ትዕዛዝ ነው፣ መውደድ የእግዚአብሔር ልጅነት መገለጫ ነው፣ መተጋገዝ፣ አብሮ ማደግ፣ ፈጣሪ በወደደን ልክ ሰዎችን መውደድ መቻል ፈጣሪን የመውደዳችን መገለጫ ነው። አምላክህን ታውቃለህ፣ ስለርሱ ፍቅር ደጋግመህ ታወራለህ፣ የታደሉህን በረከቶች ታስተጋባለህ፣ የመውደዱ ጥግ፣ የቸርነቱ መጨረሻ ያስደንቅሃል። ነገር ግን ከመደነቅና ከመገረም በላይ ያንተስ ምላሽ ምንድነው? ለርሱ ያለህን ፍቅር ለምትገልፅበት ትዕዛዝ ምንያህል ቀናኢ ነህ? የእርሱ ልጅ መሆንህን ለማስመስከር ምንያህል ትተጋለህ? የሰውን ልጅ መርዳትና ከልብ መውደድ የእግዚአብሔር አምላክ ልጅነት መገለጫ ከሆነ ስንቶቻችን ልጆቹ እንደሆንን እራሱ ፈጣሪ ያውቀዋል። ለወዳጅህ እንቅፋት እየሆንክ፣ በልብህ ጥላቻን ይዘህ፣ ለቂም በቀል እራስህን እያዘጋጀህ፣ በውስጥህ ንቀትን እያስቀመጥክ እንዴትም ስለ ፈጣሪ ልጅነት አፍህን ሞልተህ ማውራት አትችልም። አዎ! ጀግናዬ..! ደቀመዛሙርቴ፣ ተማሪዎቼ እንዲሁ ልጆቼ መሆናችሁ ይታወቅ ዘንድ እርስበርሳችሁ ተዋደዱ መባሉን ከልብህ አስገባው። ፍቅርን እየገፉ ጥላቻን እያገዘፉ፣ መውደድን ችላ እያሉ ልዩነትን እየሰበኩ፣ ይቅርታን እያንቋሸሹ ክፋትን እያጠናከሩ ስለፈጣሪ ልጅነት ማውራት አይቻልም። ወገን በችግር ውስጥ ሆኖ በረሃብ በጥማት እየተሰቃየ፣ ወንድም እህቶች የህይወት ካርታ ጠፍቶባቸው ሳለ አንድ ሰው ቢያንስ በቁስ ወይም በገንዘብ መርዳት ባይችል እንኳን ድምፅ በመሆን ህመማቸውን ሌሎች ጋር ማድረስ ሲችል ስላፈራው ንብረትና ስለደረሰበት ስኬት ደጋግሞ ቢያወራ ምንም ትርጉም የለውም። የአንዳችን መኖር ለአንዳችን ብርታት ሊሆን ይገባል፣ ያንተ ጥንካሬ ለወንድምህ ችግር መፍትሔ ማምጣት ይኖርበታል። አዎ! ለብቻ ኖሮ ማለፍ፣ የእራስን ሆድ ብቻ መሙላት፣ ፅንፍ በያዘ ጥላቻ የሰውን ልጅ ማንቋሸሽ፣ ነገ ምን እንደሚሆን በማይታወቅ ሃብትና ንብረት ከልክ በላይ መመካት በምንም መመዘኛ በእግዚአብሔር ዘንድ ሊወደድ አይችልም። ብንወድቅ የሚያነሳን ፈጣሪ ነው፣ ብንስት የሚመልሰን የዘላለም አባታችን ነው፣ በጥፋት በበደል አንገታችንን ብንደፋ በይቅርታው ቀና የሚያደርገን ቸሩ አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር ነው። ትልቁ የምድር ጌጥ ንብረት፣ ዝና፣ ሰው ወይም ገንዘብ አይደለም ትልቁ ጌጥ የእግዚአብሔር ልጅነት ነው። ሌላው ሁሉ ትርፍና ጠፊ ነው። እርስበርስ በመዋደድ የፈጣሪያችንን ልጅነት እናስመስክር፣ በመልካም ስራ ነፍሳችንን ወደ ፅድቁ መንገድ እንምራት።

ስለሁሉም አመስግኑ! ስለሆነው ስለሚሆነው ስለማይሆነው፣ ስላጣናቸው ስላገኘናቸው ፈልገንም ስላላገኘናቸው ስለተሰጠን ስለሚሰጠን፣ ስለማይሰጠን፣ ስላልተሳካልን ስለተሳካልን፣ ስለከሰርነው ስላተረፍነው ነገር በሙሉ ፈጣሪ ይመስገን። ስለሔደው በማልቀስ፣ ስለሚመጣውም በመጨነቅ ጊዜ ማጥፋት አያስፈልግም። ሁሉ ለበጎ ሁሉ ለመልካም እንደሚደረግ ማመን ከሁሉ ነገር ነፃ ያወጣል። ስለእራሳችን በሚገባ የምናውቅ ሊመስለን ይችላል ለእኛ የሚበጀንን ግን ከእኛ በተሻለ እግዚአብሔር አምላካችን እንደሚያውቅ ማስታወስ ያስፈልጋል። በህይወታችን የሚከሰቱ እያንዳንዱ ነገሮች በምክንያት የሚፈጠሩ ናቸው። ወደዳችሁም ጠላችሁም ከትናንት ጥፋታችሁና ከዛሬ ተግባራችሁ ጀርባ በቂ ምክንያት ነበረ፣ አለም። አዎ! ስለሁሉም ምስጋና ይገባልና ምስጋናን አትሰስት፣ ነገሮች ሁሉ ለበጎ እንደሆኑ ለማሰብ ብዙ አትቸገር። ቅዱስ መፅሐፍ ይህን ይላል፦ "እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደ ሃሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን፡፡" ምንም ክፉ ነገር ቢከሰትብን፣ ምንም ለጊዜው የሚያሸማቅቅና አንገት የሚያስደፋ ሁነት ውስጥ ብንገኘ ሁኔታው ነገ ምን ይዞ እንደሚመጣ አናውቅምና ለበጎ እንደሆነ ማሰቡ ብዙ በረከትን ይዞልን ይመጣል። በማጣት ውስጥ መረጋጋት፣ በማግኘት ውስጥ መረጋጋት። በችግር መሃል ማመስገኛ ምክንያት መፈለግ፣ በደስታ መሃልም እንዲሁ ምስጋናን ማስቀደም ተገቢ ነው። በማማረር የሚገኝ ነገር ቢኖር ሌላ ተጨማሪ የሚያማርር ነገር ነው፤ ከማመስገንም እንዲሁ ሌላ ማመስገኛ ነገር ነው። በረከትን በመቁጠር ሌላ በረከት ይገኛል፣ እርግማንን ደጋግሞ በማሰብም እንዲሁ ተጨማሪ ችግርን ወደእራሳችን እንጠራለን። አዎ! ፈጣሪን የምታመሰግኑት ሁሉን የሚያደርግላችሁ እርሱ ስለሆነ ነው፤ ሰዎችን የምታበረታቱት፣ ሰዎችን የምታደንቁት ብሎም ደስተኛ እንዲሆኑ የምትጥሩት እናንተም ይሔ ነገር እንዲደረግላችሁ በምትፈልጉት መጠን ነው። ክፉ ሰው መልካም ነገር ከሰዎች አይጠብቅም፤ ውሸታም ሰው ማንም እውነት የሚያወራ አይመስለውም፤ አቃቂር በማውጣት የተጠመደ ሰው ምንም በጎ ስራ አይታየውም። ከእናንተ የተሻለ ህይወት የሚኖሩ የሚመስሏችሁን ሰዎች እየተመለከታችሁ ከአመስጋኝነት አትራቁ፣ የሌላችሁን እየቆጠራችሁ ለጭንቀትና ለብቸኝነት እራሳችሁን አታጋልጡ። እያንዳንዱ ችላ የምትሉት ትንሽ ልማዳችሁ እያደር ዋጋ እንደሚያስከፍላችሁ አትርሱ። ከምስጋና የራቀ ሰው ከታሰበለት በረከቱም እንዲሁ እየራቀ ይሔዳል። ስለሁሉም አመስግኑ፣ እለት እለት በልባዊ ምስጋና ውስጣችሁን አድሱ፣ በረከታችሁን ጨምሩ፣ ደስታችሁንም እራሳችሁ ፍጠሩት። ከምርጥ ፅሁፎች የተቀዳ

አዛምድ 1. ሁሉን a. ውደዱ 2. ወንድሞችን b. አክብሩ 3. እግዚአብሔርን c. ፍሩ 4. ንጉሥን መልስዎን ከ1ኛጴጥሮስ 2:17 ጋር ያዛምዱ
አዛምድ 1. ሁሉን a. ውደዱ 2. ወንድሞችን b. አክብሩ 3. እግዚአብሔርን c. ፍሩ 4. ንጉሥን መልስዎን ከ1ኛጴጥሮስ 2:17 ጋር ያዛምዱ

የጌታን ነገር እንትን በል ዛሬ ጠዋት ከጓደኛዬ ጋር ስልክ ተደዋወልንና እሱ በሚኖርበት አካባቢ ስላለው ሃይለኛ ቅዝቃዜ አውርቶኝ ልንለያይ ስንል ስለ ስራ አነሳንና እኛ አካባቢ አየሩ ደህና ነው ስራው
የጌታን ነገር እንትን በል ዛሬ ጠዋት ከጓደኛዬ ጋር ስልክ ተደዋወልንና እሱ በሚኖርበት አካባቢ ስላለው ሃይለኛ ቅዝቃዜ አውርቶኝ ልንለያይ ስንል ስለ ስራ አነሳንና እኛ አካባቢ አየሩ ደህና ነው ስራው ግን ቀዝቅዟል ስለው እንግዲያውስ ስራው እስኪመጣ "አንተ የጌታን ነገር እንትን በል" አለኝ። ለማለት የፈለገው ገብቶኛል ግን "እንትን" ምን አልኩት። ያው ጸልይ፣ ቃሉን አንብብ አለኝ። እሺ አልኩኝና ብዕሬን አንስቼ ይህችን ጽሑፍ እንትን አልኩኝ። አንተስ/አንቺስ ፋታ ስታገኙ ትርፍ ጊዜያችሁን በምን እንትን ታደርጋላችሁ? ፍራሽ አነጥፎ ቀኝ እግር አጣጥፎ የበሰለ እያማሰሉ ያረረውን እየቆሉ ጊዜውን ለመግደል ወሬ ሲቃበሉ ሃሜት ጥይት ባርቆ ጊዜ ወጥቶ ሲሄድ ሊገድሉ የፈረሹት ክፉኛ ቆሰሉ። ስለ ንጉስ ዳዊት በሐዋ 13:36 የተነገረ አባባል አለ:- “ዳዊትም በራሱ ዘመን የእግዚአብሔርን አሳብ ካገለገለ በኋላ አንቀላፋ.." አይምጣብኝ ብትልም የማይቀረው የእንቅልፍ ሰዓት ሲመጣ እስከወዲያኛው ታንቀላፋለህና እስከዚያው ግን የጌታን ነገር እንትን እንድትል እግዚአብሔር ይርዳህ።

Go away from me! ሰውን ከዘላለም ጥፋት ለማዳን እግዚአብሔር ሰው ሆኖ ወደ ወደ ዓለም መጣ፣ ዓለሙም አላወቀውም (reject)። ቁ.10 ወደ ወገኖቹ መጣ (አይሁድ)፣ የገዛ ወገኖቹም አልተቀበ
Go away from me! ሰውን ከዘላለም ጥፋት ለማዳን እግዚአብሔር ሰው ሆኖ ወደ ወደ ዓለም መጣ፣ ዓለሙም አላወቀውም (reject)። ቁ.10 ወደ ወገኖቹ መጣ (አይሁድ)፣ የገዛ ወገኖቹም አልተቀበሉትም። ቁ.11 መምጣቱን ዛሬም አላቆመምና ዛሬ ያንተ ተራ ሆኖ አንተ ጋ ደግሞ መጥቷል። አላውቅህም ወይንም አልቀበልም ለማለት መብት ነው። ምላሽህ ግን ምን ይሆን? "ነገር ግን ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው።" ዮሐንስ ወንጌል 1:12 ጥያቄ ቢኖርዎ ይላኩልን። Share @Bruh_Tesfa

የተሳትፎ ጥያቄ "እርሱ (1) እውነተኛ አምላክ እና (2) የዘላለም ህይወት ነው።" . ይህ ጥቅስ የት ይገኛል? . "እርሱ..." የተባለውስ ማን ነው? (ለመልስዎ ማስረጃ ምንጭ ይጥቀሱ) . ይህ ጥቅስ ብዙዎች ለሚያነሱት ሙግት ቀጥተኛና ግልጽ መልስ የሚሆነው እንዴት ነው? ተሳተፉ!

ሁልጊዜ አንብበው ሲጨርሱ ከእነዚህ ቢያንስ አንዱን ያድርጉ፥ - ይህ የመዳን መልዕክት ለሚያስፈልጋ ቸው እንዲደርስ ቻነሉን ያጋሩ - እርስዎም ከጽሁፉ የተረዱትን ሃሳብ በጥቂት ቃላትም ቢሆን ያካፍሉን ያስታውሱ፣ መልእክቱን ለሌሎች ሲያጋሩ ለሰዎች ህይወት መለወጥ ምክንያት ከመሆን ያለፈ ለእርስዎም ሆነ ለኛ ለአዘጋጆች ሌላ ጥቅምም ሆነ ድርሻ የለንም።

ብቸኝነት 3 አይነቶች 1ኛ. አጠገባችን እኛን የሚመስል አቻ ሳይኖር ሲቀር የሚሰማን ብቸኝነት። አዳም ዙሪያውን የከበቡት እጅግ ብዙ እንስሳት ቢኖሩም እነ አንበሳና ጉሬዛ ግን ከብቸኝነቱ ሊያወጡት አል
ብቸኝነት 3 አይነቶች 1ኛ. አጠገባችን እኛን የሚመስል አቻ ሳይኖር ሲቀር የሚሰማን ብቸኝነት። አዳም ዙሪያውን የከበቡት እጅግ ብዙ እንስሳት ቢኖሩም እነ አንበሳና ጉሬዛ ግን ከብቸኝነቱ ሊያወጡት አልቻሉም። መፍትሄ:- እግዚአብሔር የሚመቸውን ረዳት እንፍጠርለት ብሎ ገላገለው፣ እኛም እንጠይቀው። 2ኛ. በብዙ ሰዎች ተከብበን ነገር ግን ህመማችንን የማይረዱ ወይም የማያማቸው መሆኑን ስናውቅ የሚሰማን ብቸኝነት። ኢየሱስ በጌተሰማኔ የደም ላብ እያላበው ሲያጣጥር ደቀ መዛሙርቱ በከባድ እንቅልፍ ውስጥ ሆነው የሚናገሩትን እንኳን አያውቁም ነበር። ማቴ 26:36 መፍትሄ:- የእግዚአብሔር አብሮነት። ኢየሱስ እንዲህ አለ "እያንዳንዳችሁ... እኔንም ለብቻዬ የምትተዉበት ሰዓት ይመጣል...ነገር ግን አብ ከእኔ ጋር ስለሆነ ብቻዬን አይደለሁም። ዮሐ 16:32 እግዚአብሔር ከአንተ ጋር መሆኑን እርግጠኛ ሁን። 3ኛ. ማንም የማንንም ጥሪና ጩኸት በማይሰማበት ሥፍራ የሚከሰት ብቸኝነት። ይሄኛው ከሁሉ የከፋ ነው ያ ባለ ጠጋ ሰው በሲኦል ነበልባል ሲሰቃይ ምላሱን እንዲያበርድለት የጠየቀውን አንዲት ጠብታ ውሃ የሚሰጠው ማንም አጠገቡ የለም፣ ሁሉም በራሳቸው ሰቆቃ ተጠምደዋልና። መፍትሄ:- "በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና። ዮሐ 3:16 ዛሬ በኢየሱስ አምነህ ከእግዚአብሔር ጋር ወደምትኖርበት የዘላለም ህይወት ግባ እንጂ በዛ የጥፋት ሥፍራ በዘላለም ብቸኝነት እንዳትሰቃይ። ጥያቄ ቢኖርዎ ይላኩልን። Share @Bruh_Tesfa

የቅርብ እሩቅ በከተማው መካከል በከፍተኛ ፍጥነትና ኃይል ቤቶችን አመድ እያደረገ ስላለው የሎስ አንጀለሱ እሳት አደጋ ዜና ሰምተዋል። እግዚአብሔር ለከተማዋና ለህዝቡ ምህረትን ያድርግ! እስካሁን የእሳ
የቅርብ እሩቅ በከተማው መካከል በከፍተኛ ፍጥነትና ኃይል ቤቶችን አመድ እያደረገ ስላለው የሎስ አንጀለሱ እሳት አደጋ ዜና ሰምተዋል። እግዚአብሔር ለከተማዋና ለህዝቡ ምህረትን ያድርግ! እስካሁን የእሳቱ ሰለባ ሆነው ወደ አመድነት ከተቀየሩት 12 ሺህ ቤቶች ውስጥ ከላይ የተለጠፈው ፎቶ ግን ትኩረትን ይስባል። ምክንያቱም ቤቶቹ ከግዙፉ ፓስፊክ ውቅያኖስ ያላቸውን ርቀት ሲመለከቱ ከጥፋቱ አለመትረፋቸው እጅግ ያስገርማል። ቅርብ ሆነው ግን ቅርበታቸው አላዳናቸውምና። እግዚአብሔር የዓለማት ፈጣሪ መሆኑን፣ እየሱስ ክርስቶስ ታላቅ ነብይ መሆኑን ወይንም ደግሞ ለሰዎች ልጆች መዳን ወደ ምድር መምጣቱን፣ መሞቱንና ትንሣኤውንም ማወቅ፣ ማሳወቅ እና በዓላትንም ማክበር እጅግ መልካምና ለወንጌል ያለንን ቅርበት ያሳያል ሊባል ይችላል። ሆኖም በባህሩ ዳር የነበሩት ቤቶች ከእሳቱ እንዲተርፉ ከቅርበት ባለፈ የባህሩን ውሃ ወደ ግቢአቸው ማስገባት ይጠበቅባቸው እንደነበር ሁሉ "በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚለኝ ሁሉ ወደ መንግስተ ሰማያት የሚገባ አይደለም" ማቴ 7:21 የሚለው ቅርብ ከመሆን ባለፈ ለመዳን የእግዚአብሔርን ፍቃድ ማድረግ ግድ እንደሆነ ያሳያል። ታዲያ እግዚአብሔር ፈቃድ ምንድነው? "ልጅንም (እየሱስን) አይቶ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወትን እንዲያገኝ የአባቴ ፈቃድ ይህ ነው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።” ዮሐ 6:40 ማወቅ መልካም ነው ልጅ ለመሆን ግን መቀበልን ይጠይቃል። "ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው" ዮሐ 1:12 ጥያቄ ቢኖርዎ ይላኩልን! Please share @Bruh_Tesfas

ደሞዝህ ስንት ነው? ባለፈው ወር የተቀበልከው ደሞዝ እያንዳንዷ ሽርፍራፊ ሳንቲም የላብህ ወዝ ዋጋ እንደሆነች እንደምታውቅ አውቃለሁ። ደሞዝ ሠራተኛ በሰራው መጠን ለድካሙ በአሰሪው የሚከፈለው ክፍያ ስ
ደሞዝህ ስንት ነው? ባለፈው ወር የተቀበልከው ደሞዝ እያንዳንዷ ሽርፍራፊ ሳንቲም የላብህ ወዝ ዋጋ እንደሆነች እንደምታውቅ አውቃለሁ። ደሞዝ ሠራተኛ በሰራው መጠን ለድካሙ በአሰሪው የሚከፈለው ክፍያ ስለሆነ አንድ ስራውን ፈጽሞ የሰራ ሰራተኛ የሚጠይቀው መብቱ ነው። ፀጋ ደግሞ ፍጹም የደሞዝ ተቃራኒ ነው። • መብቴ ተብሎ የማይጠየቅ፣ • ሰው ሰርቶ ለድካሙ ተመጣጣኝ ዋጋ ነው ተብሎ ሊሰጠው እንዳይችል እጅግ ውድ የሆነ፣ • ተቀባዩ ጠይቆ ሳይሆን ሰጪው ለመስጠት ስለወደደ የሚሰጥ ነፃ ስጦታ ነው። ለምሳሌ አየር፣ ውሃ፣ ማዕድናት፣ ምድር፣ ሰማይ፣ ፀሐይ... በደመወዝ ለማግኘት እንስራ ብንል፣ ምን ስራ ለስንት ዘመን ብንሰራ ይበቃል? አይታሰብም። አንተ ከዘላለም ሞት /ገሃነም እሳት/ አምልጠህ የዘላለምን ህይወት እንድታገኝ ምን የሚበቃ ስራ ልትሰራ ትችላለህ? የተሰጠህን ነፃ ስጦታ አምነህ ከመቀበል ዉጪ ምንም በቂ ስራ ልትሰራ አትችልም። "የኃጢአት ደመወዝ ሞት ነውና፤ የእግዚአብሔር የጸጋ ስጦታ ግን በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን የዘላለም ሕይወት ነው።" ሮሜ 6:23 ጥያቄ ቢኖርዎ ይላኩልን! Please share @Bruh_Tesfa

የእግዜር ሞኝ አንድ ቀኑን ሁሉ በታማኝነት የሚወጣና የሚገባ ሰው እንደሚኖርበት አካባቢ ግንዛቤ 'ሞኝ' ተብሎ ሊታወቅ ሲችል፣ በተቃራኒው በዓለም ሚዛን 'ጥበበኛ' በሚል መጠሪያ የሚታወቅ ደግሞ በእግዚ
የእግዜር ሞኝ አንድ ቀኑን ሁሉ በታማኝነት የሚወጣና የሚገባ ሰው እንደሚኖርበት አካባቢ ግንዛቤ 'ሞኝ' ተብሎ ሊታወቅ ሲችል፣ በተቃራኒው በዓለም ሚዛን 'ጥበበኛ' በሚል መጠሪያ የሚታወቅ ደግሞ በእግዚአብሔር አቆጣጠር 'ሞኝ' ተብሎ ሊጠራ ይችላል። ለምሳሌ "የጌታ ፈቃድ ምን እንደሆነ አስተውሉ እንጂ ሞኞች አትሁኑ።" ኤፌ 5:17 የሚለው ቃል የጌታን ፈቃድ የማያስተውል በእግዚአብሔር ዘንድ 'ሞኝ' ነው ማለት ነው። ምክንያቱም "ፍጥረታዊ ሰው የእግዚአብሔር መንፈስ ነገር ሞኝነት ስለሚሆንበትና ስለማይቀበለው" በእግዚአብሔር ፊት ጥበብ የሆነውን ሞኝነት አድርጎ ይቆጥራል። 1ቆሮ 2:11 እንዲሁም በእርሱ ፊት ሞኝነት የሆነውን ሰዎች እንደ ትልቅ ጥበብ ቆጥረውት ሊያገኙት በነፍሳቸው እንኳን ይወራረዳሉ። ጠቢቡ ሰለሞን "ጥበብንና እብደትን ሞኝነትንም አውቅ ዘንድ ልቤን ሰጠሁ። ይህም ደግሞ ንፋስን እንደመከተል እንደሆነ አስተዋልኩ" በማለት በዘመኑ መጨረሻ በዕድሜው የማይጨበጥ ባዶነትን የሚከተል ሞኝ እንደነበር ተረዳ። መክብብ 1:17 "የመስቀሉ ቃል (መልዕክት) ለሚጠፉት ሞኝነት ለኛ ለምንድን የእግዚአብሔር ኃይል ነው።" አይገርምም? እንደተቀባዩ አንድ ዓይነት ነገር ሞኝነት ወይንም የኃይል ምንጭ መሆን መቻሉ? ለአንተ የቱ ይሻልሃል? "ከእናንተ ማንም በዚች ዓለም ጥበበኛ የሆነ ቢመስለው ጥበበኛ ይሆን ዘንድ ሞኝ ይሁን። የዚች ዓለም ጥበብ በእግዚአብሔር ፊት ሞኝነት ነውና።" 1ቆሮ 3:18-19 ጥያቄ ቢኖርዎ ይላኩልን! Please share @Bruh_Tesfa

photo content

ካደረገልን በላይ የሆነልን አምላክ ሰው ሆኖ ወደ ምድር የመጣበት ብርሃነ ልደቱ ለኛ የደስታና ፌሽታ ጊዜ ቢሆንም ለሰማይ ግን ከዚህ ፍፁም የተለየ ነው። ምክንያቱም በኃጢያት አዘቅት ውስጥ የወደቀውን
ካደረገልን በላይ የሆነልን አምላክ ሰው ሆኖ ወደ ምድር የመጣበት ብርሃነ ልደቱ ለኛ የደስታና ፌሽታ ጊዜ ቢሆንም ለሰማይ ግን ከዚህ ፍፁም የተለየ ነው። ምክንያቱም በኃጢያት አዘቅት ውስጥ የወደቀውን ሰው ወደ ቀድሞ ከፍታው ለመመለስ አምላክ ወደ ማይወረድበት ዝቅታ ዝቅ ያለበት በመሆኑ። ለመሆኑ እየሱስ ሰው ሆኖ ሲመጣ የወረደበት ዝቅታ ምን ያህል ነው? በጥቂቱ እንመልከት። ፈጣሪ ሆኖ ሳለ ፍጡሩን ሰው ሆኖ መወለዱ፣ ገደብ የለሽ አምላክ ሆኖ ሳለ በማርያም ማህፀን መወሰኑ፣ መጀመሪያና መጨረሻ የሌለው አልፋ-ኦሜጋ ሆኖ ሳለ እንደ ሰው በዕድሜ ገደብ መወሰኑ፣ ንጉስ ሆኖ ሳለ ምስኪን የሚባሉ ሰዎች እንኳን ከማይወለዱበት በረት መወለዱ፣ የዘላለም አባት ሆኖ ሳለ በአባትና እናት ስር ሊያድግ ዝቅ ማለቱ (ኢሳ 9:6)፣ • ሰው መሆን ብቻ ሳይሆን ከሰው ደረጃ ዝቅ ብሎ ባሪያ ሆኖ ለማገልገል መፍቀዱ፣ እንኳን ለሞት ለክስ የሚያበቃ ጥፋት የሌለበት ነው እየተባለ ለመስቀል ሞት አልፎ መሰጠቱ፣ ጻድቅ ሆኖ ሳለ በእኛ ምትክ የመስቀልን የእርግማን ሞት መሞቱ፣ ፈውስ ከእጁ በተቀበሉ ሰዎች መመታቱና በምስማር መቸንከሩ፣ ኃጢያት የማያውቀው ስለእኛ ኃጢአት መደረጉ (እኛ በእርሱ ሆነን የእግዚአብሔር ጽድቅ እንሆን ዘንድ ኃጢአት ያላወቀውን እርሱን ስለ እኛ ኃጢአት አደረገው፣ 2ኛ ቆሮ 5:21) "ነገር ግን የባሪያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አደረገ፥ በምስሉም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ፥ ለሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ። በዚህ ምክንያት ደግሞ እግዚአብሔር ያለ ልክ ከፍ ከፍ አደረገው፥ ከስምም ሁሉ በላይ ያለውን ስም ሰጠው፤ ፊልጵስዩስ 2:7 ጥያቄ ቢኖርዎ ይላኩልን! Please share @Bruh_Tesfa

-2147483648_-210356.webp3.19 KB

በእንቢተኝነት ታዝዘህ ታውቃለህ? በእሺታ የምንታዘዘውን ያህል በእንቢታችንም ታዛዥነታችንን ልናሳይ ይገባናል። ጽድቅ ያልሆነውንና እግዚአብሔር የማይወደውን እንድናደርግ አማላይ ጥሪ በየጊዜው ይቀርብልና
በእንቢተኝነት ታዝዘህ ታውቃለህ? በእሺታ የምንታዘዘውን ያህል በእንቢታችንም ታዛዥነታችንን ልናሳይ ይገባናል። ጽድቅ ያልሆነውንና እግዚአብሔር የማይወደውን እንድናደርግ አማላይ ጥሪ በየጊዜው ይቀርብልናል። እንቢ ማለት ደግሞ ብዙ ዋጋ ያስከፍላል። ከሚሰርቁ መሃል ቆሞ አልሰርቅም ማለት፣ ከሃሰተኞት መሃል የተገኘ አንድ እውነተኛ መከራው ብዙ ነው። ስለዚህም አዕምሮአችን ግብዣውን እሺ ብሎ በመቀበል ከመከራ የማምለጥ ሂሳቡን በፍጥነት ያሰላል። ዮሴፍ ግን የአለቃው ሚስት ላቀረበችለት ግብዣ ምላሹ እምቢ ነበር - ወህኒ ቢያስጥለውም። እነ ዳንኤል ንጉሡ ላቀረበላቸው ጮማና መጠጥ የሰጡት ምላሽ እምቢ ነበር - በምትኩ ጥሬ ሲቆረጥሙ ቢሰነበቱም። ሲድራቅ ሚሳቅ አብደናጎ ለተቀረበላቸው ለተቀረፀው ምስል ስገዱ ጥያቄ መልሳቸው እምቢ ነበር - ከእቶን እሳት ቢያስወረውራቸውም። ዋናው ቁም ነገር ይሄ ሁሉ የትላንት አባቶች ታሪክ ብቻ ሳይሆን ዛሬም ላንተ ባለህበት ሁኔታ ከዓለም ግብዣ በየቀኑ ይቀርብልሃል። የቱን ትመርጣለህ? ከብዙሃኑ ተስማምቶ እሺ ብሎ ከመከራው ሹልክ ብለው ማምለጥ ወይስ እምቢ ብሎ በብቸኝነት የሚመጣውን መቀበል። እንቢ ያሉት ሰዎች ለጊዜው በመከራ ውስጥ ቢያልፉም ፍፃሜአቸው ግን ከትላንትናቸው የበለጠ ክብር ሆኖላቸዋልና በእንቢታህ እግዚአብሔርን ታዘዝ። ጥያቄ ቢኖርዎ ይላኩልን! Please share @Bruh_Tesfa

Stowaway = በየትኛውም መጓጓዣ በሕጋዊነት ሳያስፈቅዱ በመደበቅ የሚደረግ ጉዞ ነው። Clapham ከለንደን Heathrow Airport በ24 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ ያለችና አውሮፕላኖች ለማረፍ በሚያደ
Stowaway = በየትኛውም መጓጓዣ በሕጋዊነት ሳያስፈቅዱ በመደበቅ የሚደረግ ጉዞ ነው። Clapham ከለንደን Heathrow Airport በ24 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ ያለችና አውሮፕላኖች ለማረፍ በሚያደርጉት ዝግጅት ጎማቸውን መዘርጋት የሚጀምሩባት ከተማ በመሆኗ በአውሮፕላን ጎማ ማስቀመጫ ውስጥ ተደብቀው የቆዩ አሳዛኝ ሰዎች በድን ከ430 ሜ. ከፍታ ቁልቁል ሲፈጠፈጥ በተደጋጋሚ የሚታይበት ከተማ ነች። እነዚህ ሰዎች ሊገጥማቸው ያለውን ሳያመዛዝኑ ያገኘነውን ብረት እንደምንም የሙጥኝ ብለን ለንደን እንደርሳለን ብለው ያስቡና አውሮፕላኑ ለመነሳት በፍጥነት ሲፈተለክ ከሚፈጠረው ኃይለኛ ነፋስ ብረት ምናምን ይዘው እንደምንም ይተርፋሉ። ሆኖም አውሮፕላኑ ከፍታውን ጨምሮ የሰው ልጅ ያለመሳሪያ እርዳታ መተንፈስ ወደማይችልበት ከፍታ ሲበር በኦክስጅን እጥረት ምክንያት አእምሮአቸውን ይስታሉ/ይሞታሉ። በአየር እጥረት ምክንያት እንኳን ነፍሳቸው ከሞት ቢተርፍ ከዜሮ በታች 40° ሴ.ግ. የሚወርደው ቅዝቃዜ ይገድላቸዋል። ስለዚህም አውሮፕላኑ ለማረፍ ጎማውን ለመዘርጋት በሩን ሲከፍት ተንከባለው ወጥተው እንዳይሆን ይሆናሉ። እናም መሳፈር ብቻ ሳይሆን ካሰቡበት በህይወት ለመድረስ የተቀመጠልንን መስፈርት እና መስመር ብቻ ጠብቆ መጓዝ የግድ ነው። ኢየሱስ ወደ ህይወት ከሚያደርሱ መንገዶች አንዱ ሳይሆን ብቸኛው መንገድ ነኝ ብሏል። ኢየሱስም አለው “እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።" ዮሐንስ 14:6 እባክህ ይህን እያነበብክ በሌላም መንገድ እንደምንም ተንጠላጥዬም ቢሆን ከህይወት እደርሳለሁ ብለህ አትሞክር። ጥያቄ ቢኖርዎ ይላኩልን! Please share @Bruh_Tesfa

ሰይጣንን ማሸነፍ በመንገዴ እንዳይቆም ሀሳቤን እንዳይሰርቅ እግሬን እንዳይጠልፈኝ ደስታዬን እንዳይወስድ በልቤ እንዳይሞላ እንዳይቆጣጠረኝ ነፍሴን እንዳይገዛ እንዳያንከራተኝ መላውን ንገሩኝ ምን ይሆን
ሰይጣንን ማሸነፍ በመንገዴ እንዳይቆም ሀሳቤን እንዳይሰርቅ እግሬን እንዳይጠልፈኝ ደስታዬን እንዳይወስድ በልቤ እንዳይሞላ እንዳይቆጣጠረኝ ነፍሴን እንዳይገዛ እንዳያንከራተኝ መላውን ንገሩኝ ምን ይሆን ሚያስፈራው? በምን ይሸነፋል በምን ላስደንግጠው? ምን ባደርግበት ነው ጉልበቱ የሚርደው? ድንጋይ ብወረውር ውሃ ብረጭበት መስቀል በደረቴ ወርቅ ሐብል በአንገቴ የጆሮ ጉትቻ ባስር ባንጠለጠል ግንባሬ ላይ ብነቀሰው በቀሚሴ ባስጠልፈው ከሆነልኝማ ከደጄ ካራቀው አዋቂ አሰርቼ እበሬ ላይ ባስተክለው፣ ወዴት ልግባ እያለ ይደነገጥ ይሆን? ወይስ አለ ከተባለ የሚፈራው ሃይማኖት ሄጄ ብመዘገብ ብከፍል አባልነት። መላውን ንገሩኝ ምን ይሆን ሚያስፈራው? በምን ይሸነፋል በምን ላስደንግጠው? ምን ባደርግበት ነው ጉልበቱ የሚርደው? ደግ ሰው ብንሆንም የሰውን ሀቅ ባንነካም አገር ወዳድ፣ ሰው አክባሪ ገበሬ፣ ነጋዴ፣ የአገር መሪ ማንንም አይምርም ለማንም አይራራም እና... እስቲ የእናንተን ንገሩኝ ከልምዳችሁ አካፍሉኝ እንዴት ነው የምትረቱት? ከእግራችሁ በታች የምትረጋግጡት ያንን ክፉ ሰይጣን የምታሸንፉት? መልስዎን በማጋራት ይሳተፉ Share @Bruh_Tesfa