cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

Ethiopia Customs Commission

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
4 957
مشترکین
+1024 ساعت
+307 روز
+7830 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

Photo unavailableShow in Telegram
👍 8 1
👍 5 1
በንቅናቄው የታክስ እና የጉምሩክ ህግ ተገዥነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ በውጤት የታጀቡ ስራዎች መከናወናቸው ተገለጸ ********************************************* (ጉምሩክ ኮሚሽን፣ ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ.ም) የገቢዎች ሚኒስቴር እና የጉምሩክ ኮሚሽን ግብር ለሀገር ክብር በሚል መሪ ቃል የታክስ እና የጉምሩክ ህግ ተገዥነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል የንቅናቄ መድረክ በተለያዩ ሁነቶች ሲያካሂዱ ቆይተዋል፡፡ የዚህ የንቅናቄ መድረክ የማጠቃለያ መርሀግብር እና የተገኙ ስኬቶችን አስመልክቶ የገቢዎች ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሴ እና የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ ለሚዲያ ባለሙያዎች መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ ወ/ሮ ዓይናለም በመግለጫቸው፣ ዘመናዊ የታክስ ስርዓትን የገነቡ ሀገራት ጠንካራ የህግ ተገዥነት ስርዓት እንዳላቸው ጠቅሰው እንደ እንደበለጸጉ ሀገራት የታክስ እና የጉምሩክ ህግ ተገዥነትን ለማሳደግ ባለፉት ዓመታት በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን አስረድተዋል፡፡ ንቅናቄው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ(ዶ/ር) ይፋ ከሆነበት ጊዜ አንስቶ ከትምህርት ቤቶች ፣ ከኃይማኖት ተቋት፣ ከምሁራን ፣ ከግብር ከፋዮች እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይቶች እና የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል፡፡ በተለያዩ ሁነቶች በተካሄደው የንቅናቄ መድረክም የታክስ እና የጉምሩክ ህግ ተገዥነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ በውጤት የታጀቡ ስራዎች መከናወናቸውንም ሚኒስትሯ አክለዋል፡፡ ወ/ሮ ዓይናለም አክለውም፣ ግብር ከፋዩ በእውቀት ላይ የተመሰረተ የግብር አከፋፈል ስርዓትን እንዲከተል ለማድረግም ለ4ሺህ 79 ግብር ከፋዮች በታክስ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ተገቢውን ስልጠና መሰጠቱን ጠቁመዋል፡፡ ግብራቸውን በወቅቱ እና በታማኝነት ለከፈሉ ለ500 ግብር ከፋዮችም የእውቅና ሽልማት መሰጠቱን ያስታወሱት ሚኒስትሯ ከዚህ በተቃራኒ ህግን በተላለፉ አካላት ላይም አስፈላጊውን አስተማሪ እርምጃ መወሰዱን ሚኒስትሯ ተናግረዋል፡፡ የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ በበኩላቸው፣ ኮንትሮባንድ እና ህገወጥ ንግድ ቁጥጥር በማጠናከር በንቅናቄው በተሰራው ስራም የኮሚሽኑን ህግ የማስከበር ዓቅም ማሳደግ ተችሏል ብለዋል፡፡ ባለፉት 11 ወራት ብቻ 14 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር የሚገመቱ የወጭ እና የገቢ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስረድተው በአጠቃላይ በኮንትሮባንድ እና በህገወጥ ንግድ ሀገር ልታጣ የነበረውን 106 ቢሊዮን ብር ማዳን መቻሉን ጠቁመዋል፡፡ የንቅናቄ መድረኩ የህግ ተገዥነትን ለማስፈን አስተዋጽኦ ከማበርከቱ በተጨማሪ ለዘላቂ ተቋም ግንባታ መሰረት ለመጣል የሚያስችል ዓቅም የተፈጠረበት እንደሆነም ኮሚሽነር ደበሌ አስገንዝበዋል፡፡ የጉምሩክ ኮሚሽንን የተመለከቱ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ecczena በድረ ገጽ፦ www.ecc.gov.et በቴሌግራም፦ https://t.me/EthiopianCustomsCommission
نمایش همه...
Log in or sign up to view

See posts, photos and more on Facebook.

👍 4
👍 8 2
1
ለታክስ እና ለጉምሩክ ህጎች ተገዥ የሆነ ፣ ሌብነትን የሚፀየፍ ትውልድ እና ግብሩን በአግባቡ የሚከፍል ማህበረሰብ ለመገንባት በሚደረገው ጥረት የትምህርት ተቋማት ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸ ********* ( ጉምሩክ ኮሚሽን፣ ሰኔ 24 ቀን 2016 ዓ.ም) በታክስ እና ቀረጥ ላይ ትኩረት በማድረግ በአስር ክላስተር እና በ240 ት/ቤቶች መካከል ሲካሄድ የነበረው የተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር የማጠቃለያ በዛሬው እለት በስካይላይት ሆቴል ተካሂዷል፡፡ በዚህ ሀገር አቀፍ የተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር ተማሪ ህሊና ተ/ማርያም ከመቀሌ ክላስተር ከመርሲ ፉል ፓራዳይዝ አካዳሚ፣ ተማሪ ሲቲና መሀመድ ከኮምቦልቻ ክላስተር ኩታበር አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት እና ተማሪ ሲና አበራ ከጅግጅጋ ክላስተር ከስፓርክ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል፡፡ በማጠቃለያ መርሀግብሩ የተገኙት የገቢዎች ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሴ፣ ለታክስ እና ለጉምሩክ ህጎች ተገዥ የሆነ ፣ ሌብነትን የሚጸየፍ ትውልድ እና ግብሩን በአግባቡ የሚከፍል ማህበረሰብ ለመገንባት በሚደረገው ጥረት የትምህርት ተቋማት ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ታክስን በፈቃደኝነት እና በታማኝነት መክፈል የሀገር ፍቅር አንዱ መገለጫ ነው ያሉት ሚኒስትሯ ሀገር የሰጠችውን መልሶ በአግባቡ የሚከፍል ትውልድ ለመፍጠር የተጀመሩት ስራዎች ቀጣይነት ባለው መንገድ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስረድተዋል፡፡ ወ/ሮ ዓይናለም አክለውም፣ ኢትዮጵያ የበርካታ ህዝቦች መኖሪያ እና ከፍተኛ ኢኮኖሚ የምታንቀሳቅስ ሀገር መሆኗን ጠቁመው የሀገር እድገትን ታሳቢ ያደረገ እና የህዝብ የመልማት ፍላጎትን በአግባቡ የሚመልስ ገቢን ከማመንጨት አንጻር ክፍተቶች እንዳሉ አስረድተው ይህ የተማሪዎች ጥያቄና መልስ ውድድር በቀጣይ ለውጥ ለማምጣት እንደሚረዳ ገልፀዋል፡፡ በውድድሩ ከአንደኛ አስከ ሶስተኛ ደረጃን ይዘው ላጠናቀቁ የላፕቶፕ፣ ከአራተኛ አስከ አስረኛ ደረጃ ላጠናቀቁ ተማሪዎች የታብሌት እና የሞባይል ስልክ እንዲሁም ለትምህርት ቤቶች እና ድጋፍ እና ክትትል ላደረጉ መምህራን የዴስክ ቶፕ ኮምፒውተር እና የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡ የጉምሩክ ኮሚሽንን የተመለከቱ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ecczena በድረ ገጽ፦ www.ecc.gov.et በቴሌግራም፦ https://t.me/EthiopiaCustomsCommission
نمایش همه...
Log in or sign up to view

See posts, photos and more on Facebook.

👍 4
👍 2🎄 1
ሃገር አቀፍ የታክስ እና ቀረጥ የተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር የማጠቃለያ መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው ********** (ጉምሩክ ኮሚሽን፣ ሰኔ 24 ቀን 2016 ዓ.ም ) በታክስ እና ቀረጥ ላይ ትኩረት በማድረግ በአስር ክላስተር እና በ240 ት/ቤቶች ሲካሄድ የነበረው የተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር የማጠቃለያ መርሃ ግብር በስካይ ላይት ሆቴል እየተካሄደ ይገኛል። በዚህ የአሸናፊዎች አሸናፊ የጥያቄና መልስ ውድድር የገቢዎች ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሴ ፣ የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ ምክትል ኮሚሽነሮች ፣ ዳይሬክተሮች ፣ መምህራን ፣ ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች ተገኝተዋል ። በዚህ የማጠቃለያ መርሃግብር የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ ፤ " ግብር ለሃገር ክብር " በሚል መሪ ቃል ከፌደራል እስከ ታችኛው የመንግስት መዋቅር ድረስ የታክስ እና የጉምሩክ ህግ ተገዥነት የንቅናቄ መድረክ ሲካሄድ መቆየቱን ገልጸዋል ። ኮሚሽነር ደበሌ አክለውም ፣ በኃይማኖት ተቋማት ፣ በትምህርት ቤቶች እና በሌሎች ህዝባዊ ተቋማት የታክስ ስርጸትን ለማሳደግ የሚያስችሉ በርካታ ውይይቶች እና የንቅናቄ መድረኮች መከናወናቸውን አስረድተዋል ። የተማሪዎች ጥያቄና መልስ ውድድሩ የዚህ ንቅናቄ አንዱ አካል መሆኑን የጠቀሱት ኮሚሽነር ደበሌ ፣ ውድድሩ ስለ ታክስና የጉምሩክ ህጎች በቂ ግንዛቤ ያለው ትውልድ ለማፍራት ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል ። ከአንድ ዓመት በላይ በቆየው በዚህ የንቅናቄ መድረክ የታክስ እና የጉምሩክ ህግ ተገዥነትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸውንም ኮሚሽነር ደበሌ ጠቁመዋል ። ጉምሩክ ኮሚሽንን የተመለከቱ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት :- ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ecczena በድረ ገጽ፦ www.ecc.gov.et በቴሌግራም፦ https://t.me/EthiopianCustomsommission
نمایش همه...
Log in or sign up to view

See posts, photos and more on Facebook.

👍 3
👍 5 2👎 1
ከ247 ሚሊዮን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ ************************************************ (ጉምሩክ ኮሚሽን፣ ሰኔ 18 ቀን 2016 ዓ.ም ) የጉምሩክ ኮሚሽን ከሰኔ 7 ቀን እስከ 13/ 2016 ዓ.ም ባደረገው ክትትል 233 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር የገቢ የኮንትሮባንድ እቃዎች እና 14 ሚሊዮን ብር የወጭ፤ በድምሩ 247 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ የኮንትሮባንድ እቃዎች በተለያዩ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ተይዘዋል፡፡ በቁጥጥር ስር ከዋሉት የኮንትሮባንድ እቃዎች መካከል አልባሳት፣ ነዳጅ፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ ቡና፣ መድሀኒት፣ የመዋቢያ እቃዎች፣ ጫት፣ አደንዛዥ እጾች፣ የመኪና መለዋወጫ፣ የምግብ ዘይት እና የተለያዩ ሀገር ገንዘቦች ይገኙበታል፡፡ በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ የገቢ እና የወጭ ኮንትሮባንድን በመቆጣጠር አዋሽ፣ ድሬድዋ እና ሐዋሳ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ቀዳሚውን ስፍራ ሲይዙ በቅደም ተከተላቸውም 70 ሚሊዮን፣ 56 ሚሊዮን እና 52 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ የኮንትሮባንድ እቃዎችን መያዝ ችለዋል፡፡ የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹ በጉምሩክ ኮሚሽን ሰራተኞች፣ በፌደራል ፖሊስ፣ በክልል ፖሊስ አባላትና ህብረተሰቡ ባደረጉት የጋራ ጥረት በፍተሻ፣ በበረራና በጥቆማ የተያዙ ሲሆን ኮንትሮባንዱን ሲያዘዋውሩ የተገኙ 10 ተጠርጣሪዎች እና ሰባት ተሽከርካሪዎች በቁጥጥር ስር ማዋል ተችሏል፡፡ የጉምሩክ ኮሚሽን በዚህ የህግ ማስከበር ስራ ላይ ለተሳተፉ የኮሚሽኑ ሰራተኞች ፣ የክልልና የፌደራል ፖሊስ አባላት እንዲሁም ለመላው ህዝባችን ምስጋናውን ያደርሳል፡፡ የኮንትሮባንድ እና ንግድ ማጭበርበር የአፈጻጸም ስልቱ ተለዋዋጭ በመሆኑ ድርጊቱን ለመግታትና በሀገር ኢኮኖሚ የሚያሳድረውን አሉታዊ ተጽእኖ ለመከላከል ጉምሩክ ኮሚሽን ብቻ የሚያደርገው እንቅስቃሴ በቂ ባለመሆኑ ሁሉም ባላድርሻ አካላትና ህብረተሰቡ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ የጉምሩክ ኮሚሽን ጥሪውን ያቀርባል፡፡ ጉምሩክ ኮሚሽንን የተመለከቱ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ecczena በድረ ገጽ፦ www.ecc.gov.et በቴሌግራም፦ https://t.me/EthiopianCustomsCommission
نمایش همه...
Log in or sign up to view

See posts, photos and more on Facebook.

👍 7
یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.