fa
Feedback
ቃሉን እንማር

ቃሉን እንማር

رفتن به کانال در Telegram

ይህ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርት እና ስብከት የሚቀርብበት ቻናል ነው። ቃሉን በመፈለግ በመኖር እና በማስተማር እንትጋ! Find me on my YouTube Channel: https://www.youtube.com/channel/UCNz7MqCOz-nl0B5SITmKMHQ/featured

نمایش بیشتر
3 575
مشترکین
+124 ساعت
+47 روز
-1130 روز

در حال بارگیری داده...

ابر برچسب‌ها
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
ژوئیه '26
ژوئیه '26
+62
در 0 کانال‌ها
ژوئن '26
+26
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '26
+18
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '26
+34
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '26
+31
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '26
+22
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '26
+19
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '25
+40
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '25
+23
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '25
+28
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '25
+80
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '25
+31
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '25
+16
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '25
+13
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '25
+37
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '25
+25
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '25
+33
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '25
+32
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '25
+27
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '24
+57
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '24
+94
در 1 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '24
+38
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '24
+46
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '24
+29
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '24
+42
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '24
+38
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '24
+39
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '24
+41
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '24
+39
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '24
+42
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '24
+58
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '23
+89
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '23
+62
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '23
+50
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '23
+53
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '23
+37
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '23
+30
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '23
+26
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '23
+36
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '23
+46
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '23
+54
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '23
+40
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '23
+66
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '22
+69
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '22
+93
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '22
+434
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '22
+118
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '22
+65
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '22
+28
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '22
+42
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '22
+209
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '22
+15
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '22
+24
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '22
+8
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '22
+4
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '21
+9
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '21
+136
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '21
+55
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '21
+136
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '21
+187
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '21
+178
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '21
+349
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '21
+218
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '21
+47
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '21
+228
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '21
+579
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '21
+908
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '20
+10 262
در 0 کانال‌ها
تاریخ
رشد مشترکین
اشارات
کانال‌ها
31 ژوئیه+1
30 ژوئیه+2
29 ژوئیه+3
28 ژوئیه+2
27 ژوئیه+1
26 ژوئیه+1
25 ژوئیه+1
24 ژوئیه+3
23 ژوئیه+2
22 ژوئیه+2
21 ژوئیه+2
20 ژوئیه+1
19 ژوئیه+3
18 ژوئیه+3
17 ژوئیه+1
16 ژوئیه+1
15 ژوئیه+2
14 ژوئیه+1
13 ژوئیه+3
12 ژوئیه+2
11 ژوئیه0
10 ژوئیه+2
09 ژوئیه+2
08 ژوئیه+3
07 ژوئیه+2
06 ژوئیه+2
05 ژوئیه+4
04 ژوئیه+4
03 ژوئیه+2
02 ژوئیه+3
01 ژوئیه+1
پست‌های کانال
ሮሜ 4-6 እና 7-9
+1
ሮሜ 4-6 እና 7-9

2
የጥናት ክፍል፡- ሮሜ 1፣ 2 እና 3   ዋና ዋና ነጥቦች፡- ሮሜ 1፤ መግቢያው ጸሐፊው ጳውሎስ የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ፣ ሐዋርያ ሊሆን የተጠራና ለእግዚአብሔር ወንጌል የተለየ መሆኑን፣ ወንጌል አስቀድሞ ተስፋ የተሰጠና ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑን፣ እንዲሁም ተደራሲያኑ በሮም ያሉ ቅዱሳን መሆናቸውን ይገልጻል። ጰውሎስ ወደ ሮም ለመሄድና ወንጌልን ለመስበክ፣ የሚያጸናቸውን መንፈሳዊ ስጦታ ያካፍላቸው ዘንድ፣ ያለውን ጉጉት ያስታውቃል፤ የእግዚአብሔር ኀይል በሆነው ወንጌል እንደማያፍር ይናገራል። በመጨረሻም የእግዚአብሔር ቁጣ በሰዎች ሁሉ ላይ እንደሚገለጥ ያስረዳል።   ሮሜ 2፤ የእግዚአብሔር ፍርድ ትክክለኛነት፣ በሌሎች ላይ እየፈረዱ ራሳቸው ግን ያንኑ የሚያደርጉ ከእግዚአብሔር ጻድቅ ፍርድ አያመልጡም፤ ሕግ ሳይኖራቸው ኀጢአት የሠሩ ሁሉ ያለ ሕግ ይጠፋሉ (በኅሊናቸው ምስክርነት መሠረት ይጠየቃሉ)፤ ሕግ እያላቸው ኀጢአት የሠሩ በሕግ ይፈረድባቸዋል። በመጨረሻም አይሁድን እና ሕግን በተመለከተ ይናገራል፤ አንድ ሰው ይሁዲ የሚሆነው በውስጣዊ ማንነቱ ይሁዲ ሆኖ ሲገኝ ነው።     ሮሜ 3፤ የእግዚአብሔር ታማኝነትና እውነተኛነት በሰዎች አለማመን ዋጋ አያጣም። ሁሉም ኀጢአትን ሠርተዋል፤ የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል፤ ጽድቅ የሚገኘው የእግዚአብሔር ጽድቅ የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን በማመን ብቻ፣ በጸጋ ነው።    ከተማርኩት፡-  ·         ጳውሎስ የእግዚአብሔር ባሪያ፣ ሐዋርያ ሊሆን የተጠራና ለእግዚአብሔር ወንጌል የተለየ ሰው ነው! ·         ወንጌል አስቀድሞ በነቢያቱ በኩል በቅዱሳት መጻሕፍት ተስፋ የተሰጠ፣ የእግዚአብሔር ወንጌል ነው፤ ወንጌል ስለ ልጁ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው! ·         ጳውሎስ ወደ ሮም ሄዶ ለማገልገል መንገድ/በር እንዲከፈትለት ይጸልይ ነበር፤ እጅግም ይናፍቅ/ይጓጓ ነበር! ·         “እንድትጸኑ የሚያስችላችሁን መንፈሳዊ ስጦታ ላካፍላችሁ … እርስ በርሳችን እንድንበረታታ …” ·         በወንጌል አላፍርም፤ ምክንያቱም ለሚያምን ሁሉ ለድነት የሚሆን የእግዚአብሔር ኀይል ነው! አሜን! ·         እግዚአብሔርን ባልፈለጉትና ባላከበሩት መጠን ለማይረባ አእምሮ አሳልፎ ሰጣቸው። ·         እግዚአብሔር ለእያንዳንዱ እንደ ሥራው ይሰጠዋል፤ በሌሎች ላይ እየፈረደ ያንኑ የሚያደርግ ከፍርድ አያመልጥም! ·         አንድ ሰው ለይምሰል በውጫዊው ብቻ ይሁዲ ልሁን ቢል ይሁዲ አይሆንም! በመንፈስ የልብ ግዝረት ያስፈልጋል! ·         የሰዎች አለማመን የእግዚአብሔርን ታማኝነት ዋጋ አያሳጣውም! ·         ሁሉ ኀጢአትን ሠርተዋል፤ የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል! ·         የተገለጠው የእግዚአብሔር ጽድቅ የሚገኘው ኢየሱስ ክርስቶስን በማመን ብቻ ነው! እግዚአብሔር ኢየሱስን የማስተሰረያ መሥዋዕት አድርጎ አቅርቦታል!   ቃሉን እንጸልይ፡- ·         የአገልግሎት በር እንዲከፈትልን እንጸልይ። ·         በወንጌል ሳናፍር በድፍረት መመስከር እና ብዙዎን መድረስ እንድንችል እንጸልይ። ·         በክርስቶስ በማመን የሆነልንን እያሰብን ጌታን እናመስግን።   ወንጌል የእግዚአብሔር ኀይል ነው፤ ወንጌል ነጻ ያወጣል! በወንጌል አንፈር! ጸጋው ይብዛልን!
269
3
የጥናት ክፍል፡- የሐዋርያት ሥራ 25፣ 26፣ 27 እና 28 ዋና ዋና ነጥቦች፡- የሐዋርያት ሥራ 25፤ ጳውሎስ በፊስጦስ ፊት ቀረበ፤ በማስረጃ ያልተደገፉ ብዙ ከባድ ክሶች ቀረቡበት፤ ጳውሎስ ክሱ መሠረተ ቢስ መሆኑን በመግለጽ ራሱን ተከላከለ። ፊስጦስ ከንጉሥ አግሪጳ ምክር ጠየቀ፤ ጳውሎስ በንጉሥ አግሪጳ ፊት ቀርቦ እንዲናገር ተጠራ።   የሐዋርያት ሥራ 26፤ ጳውሎስ በአግሪጳ ፊት ቀርቦ በልጅነቱ የነበረውን ሁኔታ፣ በደማስቆ መንገድ ላይ ከኢየሱስ ጋር የተገናኘበትን መንገድ፣ አገልግሎቱን በዝርዝር አስረዳ። አግሪጳ ንግግሩን ከሰማ በኋላ “… አእምሮህን ስተሃል፤ የትምህርትህ ብዛት አሳብዶሃል” ባለው ጊዜ ጳውሎስ ንግግሩን በመቀጠል ሁሉም እንዲያምኑ ምኞቱ መሆኑን ገለጸ። ንጉሡም ሆነ አገረ ገዥው እንኳን ለሞት ለእስራት የሚያበቃ ነገር አለማድረጉን መሰከሩ።   የሐዋርያት ሥራ 27፤ ይህ ምእራፍ ጳውሎስ በመርከብ ወደ ሮም የተወሰደበትን መንገድ እና በመርከቢቷ እና በተጓዦቹ ላይ የደረሰውን ጉዳት ይተርካል። ጳውሎስ ጉዞው አደገኛ መሆኑን አስቀድሞ ቢገልጽም አልሰሙትም። ጳውሎስ መርከቧ እንጂ አንዳቸውም እንደማይጎዱ እግዚአብሔር የላከው መልአክ እንደ ተናገረው እና እግዚአብሔር እንደ ተናገረው እንደሚሆን እንደሚያምን ገለጸ። ሁለት መቶ ሰባ ስድስቱም ሰዎች በደኅና ደረሱ።   የሐዋርያት ሥራ 28፤ የመላጥያ ደሴት ነዋሪዎች የሚያስገርም ደግነት አሳዩአቸው፤ ጳውሎስ የነደፈችውን እፉኝት ወደ እሳት አራገፋት፤ ብዙ ሕመምተኞችም ተፈወሱ። ጳውሎስ ወደ ሮም ደረሰ፤ በጥበቃ ሥር ሆኖ የእግዚአብሔርን መንግሥት እየሰበከ፣ ስለ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በፍጹም ግልጽነት ያስተምር ነበር።   ከተማርኩት፡- ·         ጳውሎስ ራሱን የተከላከለበትና የቀረበበት ክስ መሠረተ ቢስ መሆኑን ያስረዳበት መንገድ አስተማሪ ነው። ተገቢ ያልሆነ ውንጀላን በመጋፈጥ ራስን መከላከል ከመንፈሳዊነት መጉደል አይደለም! ·         ጳውሎስ ምስክርነቱን (በሕይወቱ የተከሰተውን ለውጥ) የሚያቀርብበት መንገድ አስደናቂ ነው! ·         “የእግዚአብሔር ርዳታ እስከ ዛሬ ስላልተለየኝ እነሆ እዚህ ቆሜ ለትንሹም ለትልቁም እመሰክራለሁ …” ሃሌሉያ ብዬ ልለፍ መቼስ ልሳን አይጻፍም! ርዳታው እስከ ዛሬ ስላልተለየን …   ·         ጳውሎስ መስበክ፣ ማስተማር፣ ድንቅና ታምራት ማድረግ ብቻ ሳይሆን ሊሆን ያለው የሚታየው ሐዋርያም ነበር - “… ጉዳት እንደሚደርስ ይታየኛል” በማለት አስጠንቅቋል! በእርግጥ በየትም ስፍራ ራሱን ነቢይ ብሎ አላስተዋወቀም፤ የሚታየው ሁሉ ነቢይ አይደለምና!       ·         ጳውሎስ በመርከቧ ላይ ለነበሩ ሰዎች ያስተላለፈው መልእክት ድንቅ ነው። የእርሱ የሆነውና የሚያመልከው እግዚአብሔር የላከው መልአክ በአጠገቡ ቆሞ የተጓዦቹን ሕይወት እግዚአብሔር እንዳተረፈለት እንደ ተናገረው ገልጾ “እርሱ እንደ ነገረኝ እንደዚያው እንደሚሆን በእግዚአብሔር አምናለሁና! አላቸው! እውነትም እርሱ እንደ ተናገረው እንደዚያው ሆነለት! ሃሌሉያ! ·         ጳውሎስ በእፉኝት በተነደፈ ጊዜ “ይህ ሰው በእርግጥ ነፍሰ ገዳይ ነው፤ ከባሕር ቢያመልጥ እንኳ የፍርድ አምላክ በሕይወት እንዲኖር አልፈቀደለትም” እያሉ ሲናገሩ ጳውሎስ እባቢቱን ወደ እሳቱ አራገፋት፤ አንዳችም ጉዳት አልደረሰበትም። ·         በትኩሳትና በተቅማጥ ሕመም ተይዞ የነበረው የፑፕልዮስ አባት እና ብዙ ሕመምተኞች ተፈወሱ! ·         “እርሱም ከጧት ጀምሮ እስከ ማታ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት እየመሰከረ ያብራራላቸው ነበር … ማንም ሳይከለክለው የእግዚአብሔርን መንግሥት እየሰበከ፣ ስለ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በፍጹም ግልጽነት ያስተምር ነበር” - በጳውሎስ በመደነቅና በመደመም ውስጥ መሆኔን አለመግለጽ አልችልም!   ቃሉን እንጸልይ፡- ·         ርዳታው እስከ ዛሬ ያልተለየንን እግዚአብሔርን እናመስግን! ·         እግዚአብሔር የተናገረውን የሚፈጽም አምላክ ነው፤ በእርሱ መታመናችንን እንግለጽ። ·         ከጌታ የተቀበልነውን አገልግሎት በትጋት መፈጸም እንድንችል እንጸልይ።   እንደ ውልብታ በሆነችው ዘመናችን ጌታን አገልግለን እንለፍ! ነፍሱን ለሰጠን ጌታ ራሳችንን እንስጥ! ጸጋው ይብዛልን!
295
4
የትላንትናው የንባብ ክፍል የሐዋርያት ሥራ 19፣ 20 እና 21 መሆኑ ይታወቃል የዛሬው የንባብ ክፍል፡- የሐዋርያት ሥራ 22፣ 23 እና 24 ነው   ዋና ዋና ነጥቦች፡- የሐዋርያት ሥራ 22፤ ጳውሎስ የጦር አዛዡን አስፈቅዶ በዕብራይስጥ ቋንቋ ንግግር አደረገ። በንግግሩም በጠርሴስ የተወለደ አይሁዳሁ መሆኑን፣ በገማልያል እግር ሥር ተቀምጦ መማሩን፣ ለእግዚአብሔር በመቅናት ክርስቲያኖችን ሲያሳድድ መኖሩን እና ጌታ በደማስቆ መንገድ ላይ ተገናኝቶት የወንጌል ሰባኪ እንዳደረገው ተረከ። ንግግሩን የሰሙት ሁሉ ከምድረ ገጽ መወገድ አለበት በማለት ጮኹ፣ የጦር አዛዡ ጳውሎስ እየተገረፈ እንዲመረመር ባዘዘ ጊዜ ጳውሎስ የሮም ዜጋ መሆኑን በመናገሩ ተረፈ። በመጨረሻም ጳውሎስ በአይሁድ ሸንጎ ፊት ቀረበ።   የሐዋርያት ሥራ 23፤ ጳውሎስ በሸንጎ ፊት ቀርቦ ንግግር ሲጀምር አፉን ያስመታውን ሐናንያ የተባለ ሊቀ ካህን “አንተ በኖራ የተለሰንክ ግድግድ” በማለት ከተናገረ በኋላ ሊቀ ካህናት መሆኑን ሳያውቅ መሆኑን ገለጸ፤ ፈሪሳውያንን እና ሰዱቃውያንን አጋጨ፤ ጠባቸው ከማየሉ የተነሣ አዛዡ ጳውሎስን እንዳይገነጣጥሉት ወደ ጦር ሰፈር እንዲያዝገቡት አዘዘ። ጌታ በጳውሎስ አጠገብ ቆሞ፣ “ጳውሎስ ሆይ አይዞህ! በኢየሩሳሌም እንደ መሰከርህልኝ በሮምም ደግሞ ልትመሰክርልኝ ይገባሃል አለው!” አይሁድ ጳውሎስን ለመግደል አሤሩ፤ ከዐርባ በላይ የሚሆኑት ጳውሎስን ሳይገድሉ እህል እንደማይበሉ በተማማሉ ጊዜ የእኅቱ ልጅ ስለ ሤራው ለጦር አዛዡ በመንገሩ ጳውሎስ በጥንቃቄ ወደ ቂሳርያ እንዲወሰድ ተደረገ።   የሐዋርያት ሥራ 24፤ ጳውሎስ በፊልክስ ፊት ቀረበ፤ ጠርጠሉስ በጳውሎስ ላይ ክስ ባቀረበ ጊዜ ሕዝቡብ ክሱን የሚደግፉ መሆናቸውን ገለጹ። ጳውሎስ የቀረበበት ክስ መሠረተ ቢሲ መሆኑን እና እምነቱን በሚገባ አስረዳ። ፊልክስ የጌታን መንገድ በሚገባ ዐውቆ ስለ ነበረ የጦር አዛዡ ሉስዮስ ሲመጣ ይታያል በማለት ጉዳዩን በቀጠሮ አሳደረው። ፊልክስ ከአይሁዳዊ ሚስቱ ከድሩሲላ ጋር በመሆን ጳውሎስን አስጠርቶ በኢየሱስ ስለ ማመን ሲናገር ሰማሁ፤ ጉቦ ለመቀበል ፈልጎ በተደጋጋሚ እያስጠራ ቢያነጋግረውም ያሰበው ስላልተሳካ እንዲሁም አይሁድን ለማስሰደሰት እንደ ታሰረ ትቶት በጶርቅዮስ ተተካ።   ከተማርኩት፡- ·         ጳውሎስ ማንነቱን እና ጌታ ሕይወቱን ለውጦ የወንጌል ሰባኪ እንዳደረገው ያስረዳበት መንገድ አስገራሚ ነው! ጳውሎስ ንግግሩን ሲጨርስ የሰሙት ሁሉ “ይህስ ከምድረ ገጽ ይወገድ! በሕይወት መኖር አይገባውም! ብለው በታላቅ ድምጽ መጮሃቸውም እንዲሁ የሚገርም ነው! ·         ጳውሎስ የገጠመውን ፈተና ለማለፍ ወይም ለመከላከል የወሰዳቸው ርምጃዎች አስተማሪ ናቸው። ማንነቱን በመግለጽ፣ እርስ በርሳቸው የሚያጋጫቸው ንግግር በማድረግ፣ የክሳቸውን መሠረተ ቢስነት በመግለጽ፣ ወዘተ. ራሱን ተከላክሏል! በዚህ ሁሉ ውስጥ ግን እምነቱን አላመቻመቸም! ተገቢ ያልሆነን ውንጀላ/ክስ በተገቢ መንገድ መከላከል ብልህነት ነው! ·         “ጳውሎስ ሆይ አይዞህ! በኢየሩሳሌም እንደ መሰከርህልኝ፣ በሮምም ደግሞ ልትመሰክርልኝ ይገባሃል!” - ጳውሎስ በሚጓዝባቸው መንገዶች ሁሉ ጌታ በአጠገቡ ቆሞ ያበረታታው ነበር! ምስክሮቹን ያበረታታል! ·         እግዚአብሔር የጳውሎስን የእኅቱን ልጅ የተጠቀመበት መንገድ ድንቅ ነው! እግዚአብሔር ሰው ፈቃዱን፣ ሐሳቡን የሚፈጽምበት ሰው ወይም መንገድ አያልቅበትም! ·         “ይሁን እንጂ እነርሱ ኑፋቄ በሚሉት በጌታ መንገድ የአባቶቻችንን አምላክ አመልካለሁ፤ በሕጉ የታዘዘውንና በነቢያት የተጻፈውን ሁሉ አምናለሁ … ስለዚህ በእግዚአብሔርና በሰው ፊት ንጹሕ ኅሊና እንዲኖረኝ ሁልጊዜ እጥራለሁ” - ይህ ጳውሎስ ምን ዓይነት አስገራሚ እና ደፋር ሰው ነው? ·         ፊልክስ በአንድ በኩል የጌታን መንገድ በሚገባ ማወቁ፣ በጌታ ስለ ማመን ይበልጥ ለመረዳት መሞከሩ፣ ሚስቱም ከእርሱ ጋር እንድትሰማ ማድረጉ መልካም ሆኖ ሳለ በሌላ በኩል ደግሞ ጉቦ ፈልጎ ደጋግሞ እየጠራ ጳውሎስን ማነጋገሩ እና አይሁድን ለማስደሰት እንደ ታሰረ መተው እርስ በርሱ ይጋጫል!   ቃሉን እንጸልይ፡- ·         በእግዚአብሔርና በሰው ፊት ንጹሕ ሕሊና ኖሮን መኖር፣ ማገልገል እንድንችል እንጸልይ። ·         በምናልፍባቸው ውጣ ውረዶች ሁሉ ከጎናችን ሆኖ የሚያበረታንን ጌታ እናመስግን። ·         የጌታን ፈቃድ በመረዳት መመላለስ እንድንችል፣ በሚፈልገን ቦታ መሆን እንድንችል እንጸልይ።   በእግዚአብሔርና በሰው ፊት ንጹሕ ኅሊና እንዲኖረን ሁልጊዜ ራሳችንን እየመረመርን እንመላለስ! ጸጋው ይብዛልን!
315
5
የንባብ ክፍል፡ የሐዋርያት ሥራ 16፣ 17 እና 18 ዋና ዋና ነጥቦች፡- የሐዋርያት ሥራ 16፤ ጳውሎስ ወደ ደርቤንና ወደ ልስጥራን እንደ ደረሰና አባቱ የግሪክ ሰው የነበረው ጢሞቴዎስ ከእርሱ ጋር እንዲሄድ ፈልጎ እንደ ገረዘው በመግለጽ ይጀምራል። ጳውሎስ ስለ መቄዶንያው ሰው “ተሻግረህ ርዳን” የሚል ራእይ አየ። በፊልጵስዩስ ልድያ በጌታ አመነች። በመጨረሻም ጳውሎስና ሲላስ በወህኒ ቤት ሆነው በእኩለ ሌሊት እየጸለዩና እየዘመሩ ታምር ሆነ፤ የወህኒ ቤት ጠባቂ ከነቤተሰቡ አመነ፤ ጳውሎስና ሲላስ ተፈቱ።   የሐዋርያት ሥራ 17፤ ጳውሎስና ሲላስ በተሰሎንቄ የሰበኩት ስብከትና የተፈጠረው ሁከት፤ ጳውሎስና ሲላስ በቤርያ፤ የቤርያ ሰዎች ከተሰሎንቄ ሰዎች ይልቅ ቃሉን ዕለት ዕለት የሚመረምሩና በታላቅ ጉጉት የሚቀበሉ መሆናቸው፤ ጳውሎስ በአቴና “ለማይታወቅ አምላክ” የሚልን ጽሑፍ እንደ መነሻ አድርጎ ኢየሱስን ሰበከ።   የሐዋርያት ሥራ 18፤ ጳውሎስ በቆሮንቶስ የእግዚአብሔርን ቃል እያስተማረ አንድ ዓመት ተኩል ቆየ። ከዚያም ከጵርስቅላና ከአቂላ ጋር ወደ ሶርያ ሄደ፤ ጵርስቅላንና አቂላን በኤፌሶን ትቶ በተለያዩ ስፍራዎች ሲዘዋወር የእስክንድርያ ተወላጅ የሆነውን፣ የጌታን መንገድ በትክክል የሚናገረውንና በመንፈስ እየተቃጠለ የሚያስተምረውን አጵሎስን አገኘ።   ከተማርኩት፡-  ·         መልካም ምስክርነት የነበረውንና ግሪካዊ አባት የነበረውን ጢሞቴዎስ አይሁዶች እንዳይሰናከሉ ገረዘው። ስለ ጢሞቴዎስ የነበረው ምስክርነት እና የጳውሎስ ጥንቃቄ አስተማሪ ነው! ·         “አብያተ ክርስቲያናትም በእምነት እየበረቱና ዕለት ዕለትም በቁጥር እየጨመሩ ይሄዱ ነበር” - ቀናሁ! ·         “… የኢየሱስ መንፈስ አልፈቀደላቸውም …ተሻግረህ ርዳን …” በመንፈስ በመመራት ማገልገል! ·         ጳውሎስ የሚናገረውን በማስተዋል ትሰማ ዘንድ ጌታ የልድያን ልብ ከፈተ - ለቃሉ ልባችን ይከፈት! ·         በጥንቆላ መንፈስ ትንቢት የምትናገር አንዲት የቤት አገልጋይ እየተከታተለች ስታስቸግር ጳውሎስ መንፈሱ ከእርሷ እንዲወጣ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አዘዘ። በጥንቆላ መንፈስ ትንቢት! ·         ጳውሎስና ሲላስ በእስር ላይ ሆነው ሲጸልዩና ሲዘምር የተከሰተው ታምር ድንቅ ነው! እስር ከጌታ ጋር የነበራቸውን ግንኙነት አላቋረጠውም! ·         በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ እመን አንተም ቤተሰቦችህም ትድናላችሁ! ·         የቤርያ ሰዎች ከተሰሎንቄ ሰዎች ይልቅ መጻሕፍትን በየዕለቱ በመመርመር ቃሉን በታላቅ ጉጉት ተቀበሉ! ይጋባብን አልኩ! ·         ጳውሎስ በአቴና ሳለ ከተማይቱ በጣዖት የተሞላች መሆኗን በማየት መንፈሱ ተበሳጨ! ·         ጳውሎስ “ለማይታወቅ አምላክ” የሚለውን ተጠቅሞ ክርስቶስን የሰበከበት መንገድ አስተማሪ ነው! ·         “አትፍራ ተናገር፣ ዝምም አትበል፤ እኔ ካንተ ጋር ነኝና ማንም በአንተ ላይ ተነሥቶ ሊጎዳህ አይችልም፤ በዚች ከተማ ብዙ ሰዎች አሉኝና” ·         አጵሎስ የተማረና ቅዱሳትን መጻሕፍት ጠንቅቆ የሚያውቅ፣ ስለ ኢየሱስ በትክክል የሚናገርና በመንፈስ እየተቃጠለ የሚያስተምር ሰው …! ጠንቅቆ ማወቅ፣ በትክክል መናገር፣ በመንፈስ ተቀጣጥሎ ማስተማር! ዋው!   ቃሉን እንጸልይ፡- ·         ሰዎች ለእግዚአብሔር ቃል ልባቸው እንዲከፈት እንጸልይ። ·         እንደ አጵሎስ ቅዱሳት መጻሕፍትን ጠንቅቀን የምናውቅ፣ በትክክል የምናስተምር እንድንሆን እንጸልይ። ·         በጥንቆላ መንፈስ ትንቢት የሚናገሩ፣ ለእግዚአብሔር ሥራ እንቅፋት የሆነን ተግባር በመቃወም እንጸልይ።   ስለ ጌታ ለመመስከር እንዘጋጅ፤ እንነሣ፤ ጌታ እንዲመራንና እንዲረዳን እንጸልይ። ኢየሱስ ያድናል! ጸጋው ይብዛልን!
383
6
የሐዋርያት ሥራ 13-15
የሐዋርያት ሥራ 13-15
370
7
የንባብ ክፍል፡- የሐዋርያት ሥራ 10፣ 11 እና 12 ዋና ዋና ነጥቦች፡- የሐዋርያት ሥራ 10፤ ከመላ ቤተሰቡ ጋር በመንፈሳዊ ነገር የተጋና እግዚአብሔርን የሚፈራ፣ ለሰዎች ምጽዋት የሚሰጥ፣ አዘውትሮ ወደ እግዚአብሔር የሚጸልይ ሰው ለነበረው ለቆርኔሌዎስ መልአክ በራእይ ተገልጦ ጴጥሮስን እንዲጠራ በነገረው መሠረት ሁለት አገልጋዮቹን ልኮ አስጠራው። የተላኩት ሰዎች ከመድረሳቸው በፊት ጴጥሮስ ራእይ አየ፤ በማግስቱም ከመልእክተኞቹ ጋር ወደ ቆርኔሌዎስ ቤት በሄደ ጊዜ ዘመዶቹንና የቅርብ ወዳጆቹን ሰብስቦ የጠበቀው ቆርኔሌዎስ በጸሎት ሳለ ያየውን ራእይ ለጴጥሮስ ከተናገረ በኋላ ጴጥሮስ ስለ ኢየሱስ እየተናገረ ሳለ ቃሉን በሰሙት ሁሉ ላይ መንፈስ ቅዱስ ወረደ፤ ይህን የተመለከተው ጴጥሮስ በኢየሱስ ስም እንዲጠመቁ አዘዛቸው።   የሐዋርያት ሥራ  11፤ ጴጥሮስ ወደ ኢየሩሳሌም በወጣ ጊዜ “ወዳልተገረዙ ሰዎች ገብተህ ከእነርሱ ጋር በላህ” በሚል ለተነሳበት ነቀፌታ የተከሰተውን ነገር በቅደም ተከተል፣ በዝርዝር አስረዳቸው። የጰጥሮስን ገለጻ የሰሙ ሁሉ የሚሉትን በማጣት እግዚአብሔር ለአሕዛብም ንስሓን እንደ ሰጠ በመጥቀስ እግዚአብሔርን አመሰገኑ። በስደት ምክንያት የተበተኑት አይሁዶች በተለያዩ ስፍራዎች፣ ለግሪኮች ጭምር ወንጌልን ሰበኩ፤ ቁጥራቸው እጅግ ብዙ የሆኑ ሰዎች አመኑ። በኢየሩሳሌም የነበረችው ቤተ ክርስቲያን መንፈስ ቅዱስንና እምነትን የተሞላውን ደግ ሰው በርናባስን ላኩላቸው። በርናባስ ባየው ነገር በመደሰት እንዲጸኑ ከመከራቸው በኋላ ሳውልን ፍለጋ ወደ ጤርሴስ ሄዶ ባገኘው ጊዜ ወደ አንጾኪያ አመጣው። በርናባስና ሳውል በአንጾኪያ ለአንድ ዓመት ያህል ብዙ ሕዝብ አስተማሩ፤ ደቀ መዛሙርቱም ለመጀመሪያ ጊዜ በአንጾኪያ ክርስቲያን ተብለው ተጠሩ። ነቢያትም ወደ አንጾኪያ ወረዱ፤ ከመካከላቸው አጋቦስ የተባለው ሊመጣ ስላለው ራብ ተናግሮ ተፈጸመ፤ በይሁዳ የሚኖሩትን ወንድሞች ለመርዳት ያሰባሰቡትን በበርናባስና በሳውል ላኩ።   የሐዋርያት ሥራ  12፤ ሄሮድስ የዮሐንስን ወንድም ያዕቆብን በሰይፍ ማስገደሉ ብዙዎችን ደስ ማሰኘቱን ባየ ጊዜ ጴጥሮስንም ለመጨመር ወደ ወህኒ ቤት አስገባው። ቤተ ክርስቲያን ግን ስለ ጴጥሮስ አጥብቃ ትጸልይ ነበር። ጴጥሮስ የሚሰየፍበት ዕለት በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር በአስደናቂ ታምር ጴጥሮስን አስወጣው። እርሱም ወደሚጸለይበት ስፍራ በመሄድ ጌታ ከእስር ቤት እንዴት እንዳስወጣው አስረዳቸው። በማግስቱ እርሱን ሊገድሉት ፈልገው ሲያጡ ጠባቂዎቹ እንዲገደሉ ታዘዘ። ሄሮድስ ወደ ቂሣርያ ወርዶ ልብሰ መንግሥቱን ለብሶ በዙፋን ተቀምጦ ለሕዝቡ ንግግር ባደረገ ጊዜ ሕዝቡ “ይህስ የአምላክ ድምፅ እንጂ የሰው አይደለም” በማለት በጮኹ ጊዜ ሄሮድስ ለእግዚአብሔር ክብር ስላልሰጠ የጌታ መልአክ ወዲያው መታው፤ በትል ተበልቶ ሞተ። የእግዚአብሔር ቃል ግን እያደገና እየሰፋ ሄደ! በርናባስና ሳውል ተልኮአቸውን ጨርሰው ማርቆስ የተባለውን ዮሐንስን ይዘው ከኢየሩሳሌም ተመለሱ።   ከተማርኩት፡-  ·         ቆርኔሌዎስ የተገለጸበት መንገድ እጅግ የሚያስቀና እና የሚሞግት ነው (ከመላ ቤተሰቡ ጋር በመንፈሳዊ ነገር የሚተጋ፣ እግዚአብሔር የሚፈራ፣ እጅግ ምጽዋት የሚሰጥ፣ አዘውትሮ የሚጸልይ፣ ጸሎቱና ምጽዋቱ በእግዚአብሔር ፊት ያረገለት፣ ጻድቅ፣ በአይሁድ ሁሉ ዘንድ የተከበረ፣ ወዘተ.!) ዋው!  ·         ቆርኔሌዎስ ከሁለቱ አገልጋዮች ጋር በመንፈሳዊ ነገር የሚተጋና ለእርሱ ታማኝ የሆነ አንድ ወታደር ወደ ጴጥሮስ መላኩን ተጽፏል። ይህ ወታደርም የተገለጸበት መንገድ ገርሞኛል! ·         ቆርኔሌዎስ በጴጥሮስ እግር ላይ ወድቆ በሰገደለት ጊዜ “እኔም እንዳንተው ሰው ነኝና ተነሥ!” በማለት አስነሣው። ሰው መሆኑን ከረሳ አገልጋይ እግዚአብሔር ሕዝቡን ይጠብቅ! እኛም ራሳችንን እንጠብቅ! ·         “እግዚአብሔር ለማንም እንደማያዳላ በእርግጥ ተረድቻለሁ፤ ነገር ግን እርሱን የሚፈሩትንና ጽድቅን የሚያደርጉትን ሁሉ ከየትኛውም ወገን ቢሆን ይቀበላቸዋል …” ·         ወንጌል የሰላም የምሥራች መልእክት ነው! ·         እግዚአብሔር የናዝሬቱን ኢየሱስ በመንፈስ ቅዱስና በኀይል ቀባው … በእርሱም የሚያምን ሁሉ በስሙ የኀጢአትን ስርየት እንደሚቀበል ነቢያት ሁሉ ይመሰክሩለታል! የኀጢአት መድኀኒት እርሱ ነው! ·         ቃሉን በሰሙት አሕዛብ ሁሉ ላይ መንፈስ ቅዱስ ወረደባቸው! አመኑ፤ በኢየሱስ ስም ተጠመቁ! “ይህማ ከሆነ አሕዛብም ወደ ሕይወት ይመጡ ዘንድ እግዚአብሔር ንስሓን ሰጥቶአል ማለት ነዋ!” አዎ! ·         አማኞች “የጌታን የኢየሱስን ወንጌል” ሰበኩ፤ የጌታ እጅ ከእነርሱ ጋር ነበረ፤ የሚያምኑት ቁጥር ጨመረ! ·         የበርናባስ ማንነትና ተግባር አስተማሪ ነው (መንፈስ ቅዱስንና እምነትን የተሞላ ደግ ሰው፤ ሳውልን ፈልጎ መጥቶ በአንጾኪያ ከእርሱ ጋር እንዲያገለግል ያደረገ፣ ወዘተ.)። የበርናባስ ያለ? ·         ደቀ መዛሙርቱም ለመጀመሪያ ጊዜ በአንጾያ ክርስቲያን ተብለው ተጠሩ! ·         የነቢያት አገልግሎት በግልጽ ይታያል - ነቢያት ወደ አንጾኪያ ወረዱ፤ አጋቦስ የተናገረው ተፈጸመ፤ መልእክቱ ስግብግብ እንዲሆኑ ሳይሆን እንዲያካፍሉ አደረጋቸው! ·         ያዕቆብ ስለ ወንጌል ተሰየፈ፤ ጴጥሮስ ግን በአስደናቂ ታምር ከእስር ቤት ወጣ! ሉዓላዊ የሆነው እግዚአብሔር በሕይወታችን የሚሠራበት/የሚከብርበት መንገድ ልዩ ልዩ ነው! ጅምላ ክርስትና የለም! ·         እግዚአብሔር በሕይወታችን ላይ ያለው ዓላማ ካላለቀ ማንም ሊጨርሰው አይችልም! ጴጥሮስ የተፈታበት መንገድ ድንቅ ነው! እግዚአብሔር ከሞት መካከል ማውጣት ይችላል! ·         የጸሎት ጉልበት! ቤተ ክርስቲያን ለጴጥሮስ ትጸልይ ነበር! በጸሎት መትጋት ከዘመን ጋር አይሻሻልም! ·         ለእግዚአብሔር ክብር ያልሰጠው ሄሮድስ የሞተበት መንገድ አስገራሚ ነው! ሰዎች እንደ እግዚአብሔር የሚያዩት ሰው በትንሽዬ ትል ተበልቶ ሞተ!   ቃሉን እንጸልይ፡- ·         እግዚአብሔር እንደ በርናባስ ያሉ ሰዎችን እንዲያበዛልን እንጸልይ። ·         ቤተ ክርስቲያን በትክክልም የጸሎት ቤት እንዲትሆን እንለምን። ·         እግዚአብሔር በእውነተኛ አገልጋዮች ቤተ ክርስቲያንን እንዲባርክ እንጸልይ።   የእግዚአብሔር ቅጣት ልክ ያስገባል! ጸጋው ይብዛልን!
401
8
የንባብ ክፍል፡- የሐዋርያት ሥራ 7፣ 8 እና 9 ዋና ዋና ነጥቦች፡- የሐዋርያት ሥራ 7፤ እስጢፋኖስ የቀረበበት ክስ እውነት መሆኑን በተጠየቀ ጊዜ ከአብርሃም መጠራት በመጀመር እስከ ንጉሥ ሰለሞን ድረስ ያለውን ታሪክ በሚያስደንቅ መልኩ በአጭሩ ከተረከ በኋላ “እናንት ልባችሁና ጆሮአችሁ ያልተገረዘ፣ አንገተ ደንዳኖች! ልክ እንደ አባቶቻችሁ መንፈስ ቅዱስን ሁል ጊዜ ትቃወማላችሁ …” አላቸው። የእስጢፋኖስን ንግግር የሰሙ ሁሉ እጅግ ተቆጡ፣ ጥርሳቸውን አፏጩበት፤ እርሱ ግን የእግዚአብሔርን ክብር፣ እንዲሁም ኢየሱስ በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ ማየቱን በተናገረ ጊዜ ሁሉም ወደ እርሱ በመሮጥ ይዘው ከከተማ ውጪ በመጣል ወገሩት፤ ነፍሴን ተቀበላት ብሎ ከጸለየና ይህ ኀጢአት አትቁጠርባቸው ብሎ ከጮኸ በኋላ አንቀላፋ። ሳውል ልብስ ያዥ ነበረ።   የሐዋርያት ሥራ  8፤ ሳውሎ በእስጢፋኖስ ሞት ተስማምቶ ነበር። በኢየሩሳሌም በነበረችሁ ቤተ ክርስቲያን ታላቅ ስደት በመነሣቱ ከሐዋርያት በስተቀር አማኞች በይሁዳና በሰማርያ አውራጃዎች ሁሉ ተበተኑ። ፊልጶስ ወደ አንዲት ሰማርያ ከተማ ወርዶ ክርስቶስን ሰበከ፤ ብዙ ሰዎች ተፈወሱ እንዲሁም ከርኩሳን መናፍስት ነጻ ወጡ። ቃሉን የሰሙ አምነው ተጠመቁ፤ ጠንቋዩ ሲሞንን አመነ፤ ሐዋርያት በሰማርያ የሆነውን ሲሰሙ ጴጥሮስንና ዮሐንስን ላኩ፤ እነርሱም ላመኑት በጸለዩ ጊዜ መንፈስ ቅዱስን ተቀበሉ። ሲሞን ገንዘብ በማምጣት እንደ እነርሱ እጁን የምጭንበት ሁሉ መንፈስ ቅዱስን እንዲቀበል ሥልጣን እንዲሰጡት በጠየቀ ጊዜ ጴጥሮስ “አንተም ገንዘብህም አብራችሁ ጥፉ” በማለት ንስሓ እንዲገባ ተናገረው። ፊልጶስ የነቢዩ ኢሳይያስን መጽሐፍ ያነብ ወደ ነበረው ኢትዮጵያዊ ጃንደረባ ተልኮ ስለ ኢየሱስ ወንጌል ሰበከለት፤ ጃንደረባውም አምኖ ተጠመቀ፤ የጌታ መንፈስ ፊልጶስን ወደ ሌላ ስፍራ ወሰደው።   የሐዋርያት ሥራ  9፤ በደማስቆ መንገድ ላይ ሳለ ኢየሱስ ለአሳዳጅ ሳውል ተገለጠ፤ ሳውል ለሦስት ቀን ዐይኑ ታወረ፤ ሐናንያ ወደ ሳውል ተላከ፤ እጁን ጭኖ ለሳውል በጸለየ ጊዜ እንደ ቅርፊት ያለ ነገር ከዐይኑ ላይ ወድቆ ማየት ቻለ። ሳውል በደማስቆ መስበክ ጀመረ፤ ሊገድሉት ባሰቡ ጊዜ በሌሊት በከተማዋ ቅጥር ቀዳዳ አሹልከው በቅርጫት አወረዱት። ሳውል ወደ ኢየሩሳሌም በመጣ ጊዜ ፈሩት፤ በርናባስ ግን ከሐዋርያት ጋር አቀላቀለው፤ ሳውል በድፍረት ስለ ኢየሱስ መናገር ቀጠለ። ጴጥሮስ ኤንያ የተባለ ለስምንት ዐመት የዐልጋ ቁራኛ የነበረ ሰው በፈወሰ ጊዜ ብዙዎች ወደ ጌታ መጡ። በኢዮጴ ጣቢታ የተባለችውን አንዲት ደቀ መዝሙር (ዶርቃን) ከሞት አስነሣ፤ ብዙ ሰዎች በጌታ አመኑ።   ከተማርኩት፡- ·         እስጢፋኖስ ብሉይ ኪዳንን በአጭሩ የተረከበት መንገድ እጅግ ያስደንቃል። ·         “… ልክ እንደ አባቶቻችሁ መንፈስ ቅዱስን ሁል ጊዜ ትቃወማላችሁ … ሕግ ተቀበላችሁ እንጂ አልጠበቃችሁትም” ·         እስጢፋኖስ ልክ እንደ ኢየሱስ “ይህን ኀጢአት አትቁጠርባቸው” በማለት ለወገሩት ጸለየ። ·         በስደት ምክንያት ወንጌል ከኢየሩሳሌም ወደ ይሁዳና ሰማርያ ሄደ። ·         ጠንቋዩ ሲሞን የእግዚአብሔርን ኀይል በገንዘቡ ለመግዛት የሞከረበት መንገድ እና ጴጥሮስ የሰጠው ምላሽ አስተማሪ ነው! የእግዚአብሔር ስጦታ በገንዘብ አይገዛም! እንዲህ ዓይነት ሰዎች ቅን ልብ የሌላቸው እና በእግዚአብሔር አገልግሎት ውስጥ ዕድል ፈንታ የላቸውም! ·         ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ የነቢዩ ኢሳይያስን መጽሐፍ እያነበበ ቢሆንም ስለ ምን እንደ ሆነ አልተረዳም ነበር፤ የፊልጶስን ርዳር ካገኘ በኋላ ግን አምኖ ተጠመቀ። ኢትዮጵያዊው በወንጌል አመኖ ተጠመቀ። ·         አሳዳጅ የነበረው ሳውል በኢየሱስ ተለውጦ ተሰዳጅ ሆነ! በአሕዛብና በነገሥታት ፊት እንዲሁም በእስራኤል ሕዝብ ፊት የኢየሱስን ስም የሚሸከም የተመረጠ ዕቃ ሆነ! ጌታ የሰዎችን ሕይወት ለውጦ ለሌሎች ለውጥ ምክንያት ያደርጋል። ·         በጴጥሮስ እጅ ድንቅና ታምራት ይሆን ነበር፤ ብዙ ሰዎችም በጌታ ያምኑ ነበር! ድንቅና ታምራቱ ብዙዎችን ወደ ክርስቶስ ለማምጣት እንደ መሣሪያ ሆኖ ነበር።   ቃሉን እንጸልይ፡- ·         ጌታ ዛሬም የጳውሎስ ዐይነት ሰዎችን አንበርክኮ የራሱ አገልጋዮች እንዲያደርግ እንጸልይ። ·         አገልግሎታችን በድንቅና ታምራት የታጀበ እንዲሆን ጌታን እንለምን። ·         የእግዚአብሔርን ነገር በገንዘብ ከሚገዙ ሰዎች እንዲጠብቀን እንጸልይ።   ስደት ወንጌልን ያሰፋው ይሆናል እንጂ ሊያስቆመው እንደማይችል ሊታወቅ ይገባል። ጸጋው ይብዛልን!
402
9
የንባብ ክፍል፡- የሐዋርያት ሥራ 4፣ 5 እና 6 ዋና ዋና ነጥቦች፡- የሐዋርያት ሥራ  4፤ ካህናትና የቤተ መቅደሱ ጥበቃ ኀላፊ እንዲሁም ሰዱቃውያን ጴጥሮስና ዮሐንስን ያዟቸው፤ በወህኒ ቤት አሳደሯቸው፤ ይሁን እንጂ ቃሉን ከሰሙት መካከል ወደ አምስት ሺህ የሚሆኑት አመኑ። በነጋታውም በአይሁድ ሸንጎ ፊት ቀርበው በምን ኀይል ወይም በማን ስም ሽባውን እንደ ፈወሱ በተጠየቁ ጊዜ ጴጥሮስ በመንፈስ ቅዱስ ኀይል ተሞልቶ እነርሱ በሰቀሉት እግዚአብሔር ግን ከሙታን ባስነሣው በናዝሬቱ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም መሆኑን፣ ከዚህ ስም በስተቀር ድነት በሌላ በማንም አለመኖሩን ተናገረ። መሪዎቹም በኢየሱስ ስም ፈጽሞ እንዳይናገሩና እንዳያስተምሩ ባስጠነቀቋቸው ጊዜ “ከእግዚአብሔር ይልቅ ለእናንተ መታዘዝ በእግዚአብሔር ፊት ይገባ እንደ ሆነ እስቲ እናንተው ፍረዱ፤ እኛስ ያየነውንና የሰማነውን ከመናገር ወደ ኋላ አንልም” በማለት መለሱላቸው። ጴጥሮስና ዮሐንስ ከተፈቱ በኋላ ወደ ወገኖቻቸው ተመልሰው የሆነውን በተናገሩ ጊዜ እግዚአብሔር ዛቻቸውን እንዲመለከት፣ ቃሉን በድፍረት መናገር እንዲችሉና እጁን ዘርግቶ ድንቅና ታምራት እንዲያደርግ ጸለዩ፤ ሥፍራው ተናወጠ በመንፈስ ቅዱስ ተሞሉ፤ ቃሉንም በድፍረት ተናገሩ። ያመኑት ሁሉ በአንድ ልብና በአንድ ሐሳብ ተስማምተው ያላቸውን ሁሉ በጋራ ይጠቀሙ ነበር፤ በርናባስም መሬቱን ሽጦ ገንዘቡን በሐዋርያት እግር ሥር እኖረ።   የሐዋርያት ሥራ  5፤ ሐናንያና ሲጳራ መንፈስ ቅዱስን በመዋሸታቸው የእግዚአብሔር ፍርድ አገኛቸው። ሐዋርያት በሕዝቡ መካከል ብዙ ታምራዊ ምልክቶችንና ድንቅ ሥራዎችን አደረጉ። የጴጥሮስ ጥላው እንኳ እንዲያርፍባቸው ብዙ ሕመምተኞችን በመንገድ ላይ ያስተኙ ነበር፤ የሚመጡት ሁሉ ይፈወሱ ነበር። ሊቀ ካህናቱና አብረውት የነበሩት ሰዱቃውያን በቅናት ባሳሯቸው ጊዜ የጌታ መልአክ በሌሊት አስወጣቸው። እስር ቤት ሲፈለጉ በቤተ መቅደስ አደባባይ ቆመው ሕዝቡን እያስተማሩ ነበር። ተይዘው እንዲቀርቡ ከሆነ በኋላ በኢየሱስ ስም ስላደረጉት ነገር ሲጠየቁ እንደሚቀጥሉ በማስታወቃቸው ሊገድሏቸው አሰቡ፤ ገማልያል የተባለው የተከበረ የሕግ በሰጠው ሐሳብ ምክንያት መግደሉን ተው፤ ገርፈው በኢየሱስ ስም እንዳያስተምሩ አስጠንቅቀው ለቀቋቸው፤ እነርሱ ግን ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ መሆኑን ማስተማርና መስበክ አላቋረጡም።   የሐዋርያት ሥራ  6፤ የደቀ መዛሙርቱ ቁጥር እየጨመረ በመሄዱ ከግሪክ አገር በመጡ አይሁድና በይሁዳ በነበሩ አይሁድ መካከል በምግብ ዕደላ ጉዳይ አለመግባባት በተፈጠረ ጊዜ ይህን የሚያስተባብሩ በእምነትና በመንፈስ ቅዱስ የተሞሉ ሰባት ሰዎች ተመረጡ። ከተመረጡትም መካከል እስጢፋኖስ የተባለው ጸጋንና ኀይልን ተሞልቶ በሕዝቡ መካከል ድንቅ ነገሮችንና ታምራዊ ምልክቶችን ያደርግ ነበር። እስጢፋኖስን በመቃወም ከእርሱ ጋር ቢከራከሩም ይናገርበት የነበረውን ጥበብና መንፈስ መቋቋም ባለመቻላቸው የሐሰት ምስክሮች አቁመው በሸንጎ ፊት ከሰሱት። በሸንጎ ተቀምጠው የነበሩት የእስጢፋኖስን ፊት ሲመለኩቱ የመልአክ ፊት መስሎ ታያቸው።   ከተማርኩት፡-  ·         ቃሉን ከሰሙት መካከል አምስት ሺህ አመኑ - የስብከታቸው ትኩረት፣ ፍሬ ዛሬስ? የሚያስብል ነው! ·         “እናንተ በሰቀላችሁት እግዚአብሔር ግን ከሙታን ባስነሣው በናዝሬቱ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም መዳኑን …” - እግዚአብሔር አስነሥቶታል፤ ስሙ ያድናል! ·         “ድነት በሌላ በማንም አይገኝም፤ እንድንበት ዘንድ ለሰዎች የተሰጠ ከዚህ ስም በስተቀር ሌላ ስም ከሰማይ በታች የለምና” - በቃ አራት ነጥብ! ·         ጴጥሮስና ዮሐንስ በኢየሱስ ስም እንዳይናገሩ በታዘዙ ጊዜ ከእግዚአብሔር ይልቅ ሰዎችን መታዘዝ እንደማይገባ በመግለጽ “እኛስ ያየነውንና የሰማነውን ከመናገር ወደ ኋላ አንልም” ብለው የመለሱበት መንገድ የጌታን ሥራ ለመመስከር/ለመናገር የሚያነሣሣ፣ የሚያነቃቃ፣ የሚያደፋፍር ነው! ·         በጋራ ሆነው የጸለዩት ጸሎት ይዘት አስተማሪ ነው። የተቃዋሚዎቻቸውን ዛቻ እንዲመለከት፣ ቃሉን በድፍረት መናገር እንዲችሉ እንዲረዳቸው፣ እጁን ዘርግቶ ድንቅና ታምራት እንዲያደርግ፣ ወዘተ. ·         ሐዋርያት በአንድ ልብና በአንድ ሐሳብ ተስማምተው ያላቸውን እየተካፈሉ ያገለግሉ ነበር። በመካከላቸው የነበረው ሁኔታ እውነተኛ ኅብረት ምን እንደሚመስል ይጠቁማል።     ·         መንፈስ ቅዱስን መዋሸት እግዚአብሔርን መዋሸት ነው፤ ምክንያቱም መንፈስ ቅዱስ አምላክ ነው! ·         በሐዋርያት እጅ ይፈጸም የነበረው ድንቅና ታምራት አስገራሚ ነው፤ የጴጥሮስ ጥላ እንዲያርፍባቸው ሕመምተኞችን በመንገድ ላይ ያስቀምጡ የነበረበት መንገድ ድንቅ ነው! ዛሬስ? ለምን? … ·         “ከሰው ይልቅ ለእግዚአብሔር ልንታዘዝ ይገባል! እናንተ በዕንጨት ላይ ሰቀላችሁ የገደላችሁትን ኢየሱስን የአባቶቻችን አምላክ ከሙታን አስነሣው፤ እርሱም ለእስራኤል ንስሓንና የኀጢአትን ስርየት ይሰጥ ዘንድ እግዚአብሔር የሁሉ ራስና አዳኝ አድርጎ በቀኙ ከፍ ከፍ አደረገው።” ምን ዓይነት አስገራሚና ጥልቅ ምላሸ ነው! ·         ሐዋርያት ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ መሆኑን ከመስበክና ከማስተማር አልታቀቡም! ·         ማእድ ለማስተናገድ የእግዚአብሔርን ቃል አገልግሎት እንደማይተው በመግለጽ ለሰባት ሰዎች ኀላፊነት በመስጠት፣ “እኛ ግን በጸሎትና በቃ አገልግሎት እንተጋለን” ማለታቸው ሞጋች ነው! ትኩረት ማድረግ በሚገባ ላይ ማተኮር! ·         ሰባቱ ሰዎች የተመረጡበት መሥፈርት - በመንፈስ ቅዱስና በጥበብ የተሞሉ መሆናቸው ነው። ·         ፊቱ እንደ መላእክ ያበራው የእስጢፋኖስ ጉዳይ ይቀጥላል …   ቃሉን እንጸልይ፡- ·         ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ በመስበክና በማስተማር እንድንተጋ እንጸልይ። ·         ከኢየሱስ ውጪ ከሰማይ በታች እንዲድኑበት የተሰጠ ሌላ ስም አለመኖሩን ሰዎች እንዲረዱ እንጸልይ።  ·         በዘመናችን፣ በአገልግሎታችን ድንቅና ታምራት እንዲሆን እንጸልይ።   ተመሳስለው የሚሠሩ “ፎርጅድ ፈውሶች” ቢበዙም መንፈስ ቅዱስ ዛሬም በትክክል ይሠራል! ክብሩ ይገለጥልን!
430
10
የንባብ ክፍል፡- የሐዋርያት ሥራ 1፣ 2 እና 3   ዋና ዋና ነጥቦች፡- የሐዋርያት ሥራ  1፤ ይህ መጽሐፍ ሉቃስ ለቴውፍሎስ የጻፈው ሁለተኛው መጽሐፍ ሲሆን ኢየሱስ ወደ ሰማይ ከማረጉ በፊት ለሐዋርያት ያስተላለፈውን መልእክት በመከለስ ይጀምራል። ኀይል እስኪቀበሉ ድረስ ከኢየሩሳሌም እንዳይወጡ፣ ከጥቂት ጊዜ በኋላ በመንፈስ ቅዱስ እንደሚጠመቁ እና መንፈስ ቅዱስ በእነርሱ ላይ ሲወርድ በኢየሩሳሌም፣ በይሁዳና በሰማርያ ሁሉ እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ምስክሮች እንደሚሆኑ ከነገራቸው በኋላ እያዩት ዐረገ፤ መላእክትም ተመልሶ እንደሚመጣ ገለጹ። ሐዋርያት ከሌሎች ጋር ሆነው (ወደ 120 የሚሆኑ ሰዎች) በጸሎት ይተጉ ነበር። ማቲያስ በዕጣ በይሁዳ ምትክ ተመረጠ።   የሐዋርያት ሥራ  2፤ በበዓለ ኀምሳ ቀን በአንድነት በአንድ ሥፍራ ተሰብስበው ሳሉ መንፈስ ቅዱስ ወረደ፤ ሁሉም በመንፈስ ቅዱስ ተሞሉ፤ ከተለያዩ ሥፍራዎች የመጡ ሁሉ በራሳቸው ቋንቋ ሲሰሙ በአግራሞትና ግራ በመጋባት ይህ ምንድን ነው? በማለት ጠየቁ። ጴጥሮስ በመንፈስ ቅዱስ ኀይል የተስፋ ቃል/የዘመን ፍጻሜ መሆኑ እና ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ መሰከረ፤ ሕዝቡም በሰማው ነገር ልቡ ተነክቶ ምን እናድርግ በማለት በጠየቀ ጊዜ ንስሓ እንዲገቡና በኢየሱስ ስም እንዲጠመቁ ነገሯቸው፤ ሦስት ሺህ ያህል የሚሆኑት በእነርሱ ላይ ተጨመሩ። በመጨረሻም በአማኞች መካከል የነበረው አስደናቂ ኅብረት ተገልጽዋል።   የሐዋርያት ሥራ  3፤ ከተወለደ ጀምሮ ሽባ የሆነ ሰው ጴጥሮስና ዮሐንስ ወደ ቤተ መቅደስ ሲገቡ ምጽዋት ለመናቸው። ጴጥሮስ ግን፣ “እኔ ብርና ወርቅ የለኝም፤ ነገር ግን ያለኝን እሰጥሃለሁ፤ በናዝሬቱ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተነሥተህ በእግርህ ተመላለስ” ባለው ጊዜ ሽባው ተፈውሶ ከእነርሱ ጋር ወደ ቤተ መቅደስ አደባባይ ገባ። ጴጥሮስ በዚህ ሰው መፈወስ ለተደነቁ ሰዎች ስለ ኢየሱስ መሰከረ፤ ከኀጢአታቸው እንዲመለሱ ጥሪ አደረገላቸው።   ከተማርኩት፡- ·         “ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በሚወርድበት ጊዜ ኀይል ትቀበላላችሁ፤ በኢየሩሳሌም፣ በይሁዳና በሰማርያ ሁሉ፣ እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ” - የመንፈስ ቅዱስ ኀይል ምስክሮች ያደርጋል! ·         ልክ ወደ ሰማይ ሲወጣ እንዳያችሁት በዚሁ ሁኔታ ይመጣል - ኢየሱስ ዳግም ይመጣል! ·         በአንድነት ሆነው ያለማቋረጥ ተግተው ይጸልዩ ነበር - በአንድ ልብ በጋራ በትጋት መጸለይ! ·         የመንፈስ ቅዱስ መውረድ የዘመን ለውጥ፣ ከአሮጌው ኪዳን ወደ አዲሱ ኪዳን ሽግግር የሆነበት፣ የቤተ ክርስቲያን ልደት የሆነበት፣ ወዘተ. ነው። ·         ችኩልና ከሃዲ የነበረው ጴጥሮስ በመንፈስ ቅዱስ ኀይል ስለ ኢየሱስ የመሰከረበት መንገድ ድንቅ ነው! ·         “ንስሓ ግቡ፤ ኀጢአታችሁም እንዲሰረይላችሁ፣ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ፤ የመንፈስ ቅዱስንም ስጦታ ትቀበላላችሁ። የተስፋው ቃል ለእናንተና ለልጆቻችሁ እንዲሁም ጌታ አምላካችን ወደ ራሱ ለሚጠራቸው በሩቅ ላሉትም ሁሉ ነውና።” መፍትሔው ንስሓ መግባት/ማመን ነው! የተስፋው ቃል በሩቅ ያሉትንም ያካትታል! ·         ሐዋርያት በትምህርት፣ በኅብረት፣ እንጀራን በመቁረስ (የጌታ ራት) እና በጸሎት ይተጉ ነበር። እነዚህ የጥንቷን ቤተ ክርስቲያን ፍሬያማ ያደረጉ መሠረታዊ ነገሮች ናቸው። ·         ያመኑት ሁሉ በአንድነት ነበሩ፤ ያላቸውንም ሁሉ የጋራ አደረጉ! በመካከላቸው የነበረው አንድነት ሌሎችን ይስብ ነበረ! ·         “እኔ ብርና ወርቅ የለኝም፤ ነገር ግን ያለኝን እሰጥሃለሁ፤ በናዝሬቱ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተነሥተህ በእግርህ ተመላለስ” የተባለው ሽባ ተነሥቶ እየዘለለ፣ እግዚአብሔርን እያመሰገነ ወደ ቤተ መቅደስ አደባባይ ገባ። ደንቅ ነው! ·         “ይህ የምታዩትና የምታውቁት ሰው የበረታው በኢየሱስ ስም በማመን ነው፤ ሁላችሁም እንደምታዩት ፍጹም ፈውስ እንዲያገኝ ያደረገው የኢየሱስ ስምና በእርሱ አማካይነት የሚገኘው እምነት ነው” - የኢየሱስ ስም ኀይል/ጉልበት አለው፤ ያድናል!   ቃሉን እንጸልይ፡- ·         በመንፈስ ቅዱስ ኀይል በመመራት መመላለስ እንድንችል እንጸልይ። ·         ቃሉን በማጥናት፣ በጸሎት፣ በኅብረትና እንጀራንም በመቁረስ መትጋት እንዲሆንልን እንጸልይ። ·         በጌታ ስም ዛሬም የተለያዩ ችግሮች ያሉባቸው እንዲፈወሱ እንጸልይ።   በመንፈስ ቅዱስ ኀይል በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያችን የጌታ ምስክሮች እንድንሆን ጌታ ይርዳን! ጸጋው ይብዛልን!
413
11
የንባብ ክፍል፡- ዮሐንስ 16፣ 17 እና 18 ዋና ዋና ነጥቦች፡- ዮሐንስ 16፤ ይህ ምእራፍ በደቀ መዛሙርቱ ላይ በሚደርስ መከራ ጀምሮ የመንፈስ ቅዱስን ሥራ እና ደቀ መዛሙቱ ለጥቂት ጊዜ ቢያዝኑም ሐዘናቸው ወደ ደስታ እንደሚለወጥ በዝርዝር ያቀርባል። ኢየሱስ ካልሄደ አጽናኙ እንደማይመጣ፣ መንፈስ ቅዱስ ዓለምን ስለ ኀጢአት በመውቀስ የሚሠራው ሥራ፣ እርሱ የእውነት መንፈስ መሆኑ፣ ከኢየሱስ ሰምቶ የሚናገርና የሚያከብረው መሆኑ ተገልጽዋል። በዓለም ሳሉ መከራ ቢኖርባቸውም ኢየሱስ ዓለምን ማሸነፉን በመግለጽ አይዞአችሁ ይላቸዋል።   ዮሐንስ 17፤ በዚህ የጸሎት ምእራፍ ኢየሱስ የተሰጠውን ተልእኮ በሚገባ በማጠናቀቁ ወደ ቀድሞ ክብሩ እንዲመለስ ስለ ራሱ ጸለየ፤ በመቀጠል አንድ እንዲሆኑ፣ ከክፉ እንዲጠብቃቸውና እንዲቀድሳቸው ለደቀ መዛሙርቱ ጸለየ፤ በመጨረሻም ገና በእርሱ የሚያምኑትን ጨምሮ ስለ አማኞች ሁሉ ጸለየ።   ምእራፍ 18፤ ኢየሱስ በተቃዋሚዎቹ ተይዞ በሊቀ ካህናቱ በሐና ፊት ቀረበ፤ ጴጥሮስ ኢየሱስን ካደ፤ ኢየሱስ እንደ ገና በሊቀ ካህናቱ ፊት ከቀረበ በኋላ ጴጥሮስ ለሁለተኛና ለሦስተኛ ጊዜ ኢየሱስን ካደ፤ በመጨረሻም ኢየሱስ በጲላጦስ ፊት ቀረበ።   ዮሐንስ 19፤ ይህ ምእራፍ ኢየሱስ እንዲሰቀል እንደ ተፈረደበት፣ እንደ ተሰቀለ፣ እንደ ሞተ እና እንደ ተቀበረ ይተርካል። ጲላጦስ ኢየሱስን ሊፈታው ቢፈልግም ሕዝቡ “ራሱን የእግዚአብሔር ልጅ ስላደረገ መሞት አለበት” በማለት በከፍተኛ ድምጽ “ስቀለው” በማለት ሲጮኹ አሳልፎ ሰጣቸው። ኢየሱስም በሁለት ወንበዴዎች መካከል ተሰቀለ፤ ሞተ፤ በአርማትያሱ ዮሴፍ ጥያቄ መሠረት ማንም ባልተቀበረበት አዲስ መቃብር ቀበሩት።   ዮሐንስ 20፤ ይህ ምእራፍ ኢየሱስ ሞትን ድል አድርጎ መነሣቱን እና ለመግደላዊት ማርያም፣ ለደቀ መዛሙርቱ እና ለቶማስ መታየቱን በማብራራት ያቀርባል። ኢየሱስ በዚህ መጽሐፍ ያልተጻፉ ብዙ ታምራዊ ምልክቶች አድርጓል፤ ነገር ግን በዚህ መጽሐፍ የቀረቡት ታምራት የተጻፉት ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ በማመን በስሙ ሕይወት እንዲኖራቸው መሆኑ ተገልጽዋል።   ዮሐንስ 21፤ ኢየሱስ ከሞት ከተነሣ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ ለሦስተኛ ጊዜ ታየ፤ ዓሣ በታምር እንዲይዙ አደርጎ “ኑ ቁርስ ብሉ” በማለት እንጀራና ዓሣ ሰጣቸው። በመጨረሻም ጴጥሮስን ወደ ቀድሞ ስፍራው መልሶ ትልቅ ኀላፊነት ሰጠው። ይህ መጽሐፍ ሲጠናቀቅ ኢየሱስ ያደረጋቸው ታምራዊ ምልክቶች ሁሉ ቢጻፉ ለመጻሕፍቱ ዓለም በቂ ቦታ እንደማይኖረው ያስታውቃል።       ከተማርኩት፡-  ·         መሄዴ ይበጃችኋል፤ እኔ ካልሄድኩ አጽናኙ ወደ እናንተ አይመጣም - ድንቅ ነው! መንፈስ ቅዱስ የማያምኑትን በመውቀስ ወደ እምነት ያመጣል፤ ወደ እውነት ሁሉ የሚመራ፣ ኢየሱስን የሚያከብር የእውነት መንፈስ ነው! ·         “በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፤ ነገር ግን አይዞአችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ” - መከራ አለ ግን ደግሞ አሸናፊው ከእኛ ጋር አለ! ·         “አንተ ብቻ እውነተኛ አምላክ የሆንኸውንና የላክኸውን ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት” - እውነተኛ አምላክ የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን ማወቅ የዘላለም ሕይወት ማግኘት ነው! ·         “… እኛ አንድ እንደ ሆንን እነርሱም አንድ እንዲሆኑ …” - እኛ አንድ እንደ ሆንን አንድ ይሁኑ - ዋው! ·         ቃልህ እውነት ነው፤ በእውነትህ ቀድሳቸው! የእግዚአብሔር ቃል ይቀድሳል! ·         “ሰላም ለእናንተ ይሁን፤ አብ እኔን እንደ ላከኝ፣ እኔም እናንተን እልካችኋለሁ … መንፈስ ቅዱስን ተቀበሉ፤ የሰዎችን ኀጢአት ይቅር ብትሉ ኀጢአታችሁ ይቅር ይባልላቸዋል፤ ኀጢአታቸውን ይቅር ባትሉ ግን ይቅር አይባልላቸውም” ·         ይህ መጽሐፍ የተጻፈበት ምክንያት በ20፥30-31 ላይ በግልጽ ቀርቧል፤ “ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ፣ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ታመኑ ዘንድ አምናችሁም በስሙ ሕይወት እንዲኖራችሁ ይህ ተጽፎአል” ·         ዓሣ አልነበራቸውም፤ በየት መኩል መረባቸውን ቢጥሉ ዓሣ እንደሚያገኙ በነገራቸው መሠረት መረባቸውን በጣሉ ጊዜ ከዓሣው ብዛት የተነሣ መረቡን መጎተት አቃታቸው። እውነትም ጌታ እኮ ነው! ·         ለጴጥሮስ የተሰጠው ኀላፊነት እና ኢየሱስ ይወደው ስለ ነበረው ደቀ መዝሙር፣ “እርሱስ” በማለት በጠየቀ ጊዜ የተሰጠው አስተማሪ ነው። ·         የመጽሐፉ መዝጊያ አንዱን የትረካ መጻሕፍት ባሕርይ ያሳያል፤ ትረካ highly selective ነው። ጸሐፊው ከሚጽፍበት ዓላማ አኳያ የሚያቀርበውን ክስተት/ታሪክ ይመርጣል! ዮሐንስ ሰባት ታምራዊ ምልክቶችን እና ሰባት “እኔ ነኝ” ንግግሮችን በማቅረብ ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ፣ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ያምኑ ዘንድና አምነውም በስሙ ሕይወት ይሆንላቸው ዘንድ ይህን ወንጌል ጽፏል።   ቃሉን እንጸልይ፡- ·         በመከራ ውስጥ መጽናት እንድንችል ጸጋው እንዲበዛልን እንጸልይ። ·         ኢየሱስን የሚያከብረውን አጽናኙን መንፈስ ቅዱስን እየሰማንና እየታዘዝን መመላለስ እንድንችል እንጸልይ። ·         እግዚአብሔር በቃሉ እንዲቀድሰን እንጸልይ።   ወንጌላትን እንድናነብ እና እንድንጸልይ የረዳን፣ ያገዘን እና ያስተማረን ጌታ ስሙ የተመሰገነ ይሁን! ጸጋው ይብዛልን!
438
12
የዕለቱ የንባብ ክፍል:- ዮሐንስ 13-15
የዕለቱ የንባብ ክፍል:- ዮሐንስ 13-15
440
13
የንባብ ክፍል፡- ዮሐንስ 10፣ 11 እና 12 ዋና ዋና ነጥቦች፡- ዮሐንስ 10፤ ኢየሱስ በጎቹ ድምፁን የሚያውቁ፣ የሚሰሙ፣ ተኩላውን ሸሽተው የሚከተሉት መልካም እረኛ፣ የበጎች በር መሆኑን ተናገረ። እርሱ በጎቹን በየስማቸው እንደሚያውቅ፣ በውጪ ያሉትን ሌሎች በጎች እንደሚያመጣ እና ሕይወቱን ስለ በጎቹ አሳልፎ እንደሚሰጥ ተገልጽዋል። ከኢየሱስ ንግግር የተነሣ በአይሁድ መካከል እንደ ገና መለያየት ተፈጠረ፤ በእርሱ ማመን አቃታቸው፤ ራሱን አምላክ በማድረጉም ሊወግሩት፣ ሊይዙት ፈለጉ፤ እርሱ ግን አለማመናቸውን ወቅሶ ከተናገረ በኋላ በእጃቸው አምልጦ ሄደ።   ዮሐንስ 11፤ ይህ ምእራፍ ኢየሱስ የሚወደውን አልዓዛር የተባለውን የማርያምንና የማርታን ወንድም እንዴት ከሞት እንዳስነሣ እና ይህን በማድረጉ እርሱን ለመግደል የተደረገውን ሤራ ይተርካል። እህትማማቾቹ ወንድማቸው አልዓዛር ሲታመም “ጌታ ሆይ የምትወደው ሰው ታሟል” በማለት መልእክት ቢልኩበትም ሕመሙ የእግዚአብሔር ልጅ የሚከብርበት መሆኑን ገልጾ ሁለት ቀን ያህል ቆይቶ በመሄድ እርሱ ትንሣኤና ሕይወት መሆኑን በመግለጽ እህቶቹን ካጽናና በኋላ ከሞተ በአራተኛው ቀን አልዓዛርን አስነሣው። ይህን ታምራት ካዩ ብዙዎች በእርሱ ቢያምኑም የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያን ሕዝብ ሁሉ በእርሱ አምኖ ችግር ውስጥ እንዳይወድቁ እርሱን ለመግደል አሤሩ።      ዮሐንስ 12፤ እነ አልዓዛር ቤት ለኢየሱስ ሲባል በተዘጋጀ ራት ላይ ማርታ እያገለገለች እና አልዓዛር ከእርሱ ጋር በማእድ ተቀምጦ ሳለ ማርያም ግማሽ ሊትር ሽቱ በኢየሱስ እግር ላይ በመድፋት በጠጉሯ አበሰችው። ሌባ ተብሎ የተገለጸው ይሁዳ ለድኾች ያሰበ በማስመሰል ተቃወመ፤ ኢየሱስ ግን ሽቱው ለቀብሩ ቀን የተዘጋጀ መሆኑን ጠቅሶ ምላሽ ሰጠ። ኢየሱስ ውርንጫ በክብር ወደ ኢየሩሳሌም ገባ። የሰው ልጅ የሚከብርበት ሰዓት ደርሷል በማለት ስለሞቱ አስቀድሞ ተናገረ፤ አይሁዳውያን ግን ባለማመናቸው ጸኑ።   ከተማርኩት፡-  ·         ኢየሱስ ሕይወቱን ስለ በጎቹ አሳልፎ የሚሰጥ መልካም እረኛ ነው! እርሱ በጎቹን በየስማቸው ያውቃቸዋል፤ ከሌባውና ከነጣቂውም ይጠብቃቸዋል! ·         ሌባው ሊሰርቅ፣ ሊገድልና ሊያጠፋ ብቻ የሚመጣ ሲሆን ኢየሱስ ግን ለበጎቹ ሕይወት እንዲሆንላቸውና እንዲትረፈረፍላቸው መጥቷል። በሩ እርሱ ነውና በእርሱ በኩል የሚገቡትን ያድናቸዋል። ·         የኢየሱስ በጎች ድምፁን ይሰማሉ፣ ለይተው ያውቃሉ፣ እርሱን ብቻ ይከተላሉ!  ·         “እኔና አብ አንድ ነን” - ኢየሱስ አምላክ ነው! ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው! ·         “ይህ ሕመም የእግዚአብሔር ልጅ በእርሱ ይከብር ዘንድ ለእግዚአብሔር ክብር ነው እንጂ ለሞት የሚያደርስ አይደለም” - ለእግዚአብሔር ክብር የሆነ ሕመም!? ድንቅ ነው! ·         ኢየሱስ ትንሣኤና ሕይወት ነው፤ በእርሱ የሚያምን ቢሞት እንኳ በሕይወት ይኖራል! ሞቶ በሕይወት መኖር መቀጠል አይገርምም! ·         ኢየሱስ ዕንባውን አፈሰሰ - እንደ ኢየሱስ ለሰው የሚያዝን፣ የሚራራ ወዳጅ የለም! ·         ቀያፋ “ሕዝብ ሁሉ ከሚጠፋ ስለ ሕዝቡ አንድ ሰው ቢሞት የሚሻላችሁ መሆኑን አታስተውሉም” በማለት የተናገረው ትንቢት አስገራሚ ነው! አንዱ ኢየሱስ ስለ ብዙዎች ሞተ! ·         ይሁዳ ስለ ሽቱ ያነሣው ሐሳብ “ሌባ ስለ ነበር እንጂ ለድኾች ተቆርቁሮ አልነበረም!” በዘመናችንም ለሌሎች የተቆረቆሩ መስለው የሚቆረቁር ሥራ የሚሠሩ ስንቶች ይሆን? አድነን ነው! ·         ኢየሱስ የሰላም ንጉሥ በመሆኑ በውርንጫ ወደ ኢየሩሳሌም ገባ።  ·         ኢየሱስ ሞቱን የሚከብርበት መንገድ አድርጎ (እንደ ክብር) የገለጸበት መንገድ አስተማሪ ነው!    ቃሉን እንጸልይ፡- ·         ከሐሰተኞች ተጠብቀን የጌታን ድምፅ እየሰማን የምንመላለስ መሆን እንድንችል እንጸልይ። ·         ለእኛ፣ ለሌሎች ያዘኑ መስለው የእግዚአብሔር ሐሳብ እንዳይፈጸም ዕንቅፋት ከሚሆኑ እንዲጠብቀን እንጸልይ። ·         ለእግዚአብሔር ክብር ወደ ሕይወታችን የሚመጡትን ነገሮች ማስተዋል እንድንችል እንጸልይ።   በጎቹን በየስማቸው የሚያውቅ ጌታ በሚገባ ያውቀናልና በእርሱ እንታመን! ጸጋው ይብዛልን!
492
14
የንባብ ክፍል፡- ዮሐንስ 7፣ 8 እና 9 ዋና ዋና ነጥቦች፡- ዮሐንስ 7፤ ኢየሱስ ትክክለኛ ጊዜው ገና እንዳልደረሰ ለደቀ መዛሙርቱ በመግለጽ ከእነርሱ ጋር ሳይሆን በስውር የዳስ በዓል ወደሚከበርበት ሄደ። በበዓሉ አጋማሽ ወደ ቤተ መቅደስ ወጥቶ ማስተማር ጀመረ። አይሁዶች በትምህርቱ ሲደነቁ እርሱ ግን ትምህርቱ ከራሱ ሳይሆን ከላከው እንደ ሆነ አስታወቀ። ኢየሱስ በቤተ መቅደስ አደባባይ ላይ ሆኖ ድምጹን ከፍ አድርጎ ማስተማር ቀጠለ፤ ሊይዙት ቢፈልጉም ጊዜው ገና ስላልደረሰ ማንም እጁን አላሳረፈበትም። በበዓሉ መጨረሻም ከፍ ባለ ድምፅ፣ “ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ፤ በእኔ የሚያምን፣ መጽሐፍ እንዳለ የሕይወት ውሃ ምንጭ ከውስጡ ይፈልቃል” በማለት ተናገረ። ከሕዝቡ አንዳንዶች ነቢይ ነው ሲሉ ሌሎች ደግሞ ክርስቶስ ነው አሉ። የአይሁድ መሪዎች ግን ባለማመን እርስ በእርስ ተናገሩ።   ዮሐንስ 8፤ የኦሪት ሕግ መምህራንና ፈሪሳውያን እርሱን የሚከሱበት ሰበብ ፈልገው በምንዝር የተያዘች ሴት ወደ እርሱ በማምጣት ከሙሴ ሕግ ጠቅሰው ጠየቁት። ከእናንተ ኀጢአት የሌለበት አስቀድሞ ድንጋይ ይወርውርባት ባላቸው ጊዜ አንድ በአንድ ወጥተው ሴትዬዋም ብቻዋን ቀረች፤ ኢየሱስም “… ከእንግዲህ ግን ኀጢአት አትሥሪ” ብሎ አሰናበታት። ኢየሱስ “እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ፤ የሚከተለኝም የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ ከቶ በጨለማ አይመላለስም” በማለት ተናገረ፤ እርሱ ስለ ራሱ የሚመሰክረው እውነት መሆኑን፣ ለዚህ ምስክሩ ደግሞ ከእርሱ በተጨማሪ የላከው አብ መሆኑን ተናገረ። “በትምህርቴ ብትጸኑ እናንተ በእውነት ደቀ መዛሙርቴ ናችሁ፤ እውነትንም ታውቃላችሁ፤ እውነትም ነጻ ያወጣችኋል” ባላቸው ጊዜ የአብርሃም ልጆች መሆናቸውንና ለማንም ባሪያ ሆነው እንደማያውቁ ጠቀሱ። እርሱ ግን ኀጢአት የሚያደርግ የኀጢአት ባሪያ መሆኑን ጠቅሶ የአባታችሁ የዲያቢሎስ ልጆች ናችሁ አላቸው። በመጨረሻም ኢየሱስ ስለ ራሱ ተናገረ፤ አብርሃም ከመወለዱ በፊት እኔ፣ እኔ ነኝ ባላቸው ጊዜ ሊወግሩት ድንጋይ አነሡ።   ዮሐንስ 9፤ ኢየሱስ ከተወለደ ጀምሮ ዐይነ ስውር የሆነ ሰው ፈወሰ። ደቀ መዛሙርቱ ይህ ሰው ዐይነ ስውር ሆኖ እንዲወለድ ኀጢአት የሠራው ማን ነው? እርሱ ራሱ ወይስ ወላጆች በማለት በጠየቁት ጊዜ እርሱ ወይም ወላጆቹ ሳይሆኑ የእግዚአብሔር ክብር በሕይወቱ እንዲገለጥ መሆኑን አስረዳቸው። ፈሪሳውያን ይህ ሰው እንዴት እንደ ተፈወሰ ማጣራት ጀመሩ፤ ፈውሱ የተፈጸመው በሰንበት ቀን መሆኑን ሲረዱ ኢየሱስ ከእግዚአብሔር አለመሆኑን ተናገሩ፤ ከተፈወሰው ሰውና ከወላጆቹ ጋር ሠፊ ንግግር ካደረጉ በኋላ የተፈወሰው ሰው “ይህ ሰው ከእግዚአብሔር ባይሆን ኖሮ ይህን ማድረግ ባልቻለ ነበር” በማለት ሞገታቸው። ኢየሱስም ስለ መንፈሳዊ ዕውርነት ተናገረ።   ከተማርኩት፡-  ·         “ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ፤ በእኔ የሚያምን፣ መጽሐፍ እንዳለ የሕይወት ውሃ ምንጭ ከውስጡ ይፈልቃል። ይህን ያለው በእርሱ የሚያምኑ ስለሚቀበሉት መንፈስ ነበር፤ ምክንያቱም ኢየሱስ ገና ስላልከበረ መንፈስ አልተሰጠም ነበር” - ይህ ቁጥር የተጠማን የሚያረካ ጌታ ለተጠማ ሁሉ የደረገውን ግብዣ፣ ወደ እርሱ መጥተው የጠጡ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ እንደሚሆኑ እና ኢየሱስ “ሲከብር” መንፈስ ቅዱስ እንደሚመጣ ያስረዳል። ·         “ከእናንተ ኀጢአት የሌለበት እርሱ አስቀድሞ ድንጋይ ይወርውርባት” በማለት ሊከሱት ሰበብ ይፈልጉበት የነበሩትን ያሳፈረበት እና በምንዝር የተያዘችውን ሴት ነጻ ያወጣበት መንገድ አስገራሚ ነው። “እኔም አልፈርድብሽም፤ በይ ሂጂ፤ ከእንግዲህ ግን ኀጢአት አትሥሪ!” ·         “እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ፤ የሚከተለኝም የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ ከቶ በጨለማ አይመላለስም” - በጨለማ አንመላለስም ምክንያቱም የሕይወት ብርሃን ሆኖልናል! ብርሃን የሆነው ጌታ በርቶልን የሕይወት ብርሃን ሰጥቶናል! ·         በትምህርቴ ብትጸኑ እናንተ በእውነት ደቀ መዛሙርቴ ናችሁ፤ እውነትንም ታውቃላችሁ፤ እውነትም ነጻ ያወጣችኋል! በትምህርቱ መጽናት! ·         ኀጢአት የሚያደርግ የኀጢአት ባሪያ ነው! ·         “አብርሃም ከመወለዱ በፊት እኔ፣ እኔ ነኝ!”  ·         “እርሱ ወይም ወላጆቹ ኀጢአት አልሠሩም፤ ይህ የሆነው ግን የእግዚአብሔር ሥራ በእርሱ ሕይወት እንዲገለጥ ነው” - የእግዚአብሔርን ክብር የሚገልጡ ችግሮች ትላንት እንደ ነበሩ ሁሉ ዛሬም አሉ! ·         የተፈወሰው ዐይነ ስውር ከፈሪሳውያን ጋር ያደረገው ንግግር መንፈሳዊ ዕውርነታቸውን የገለጠ አስደናቂ ሙግት ነው!   ቃሉን እንጸልይ፡- ·         ሰዎች የተጠማውን ሁሉ ወደሚያረካው ጌታ መምጣት እንዲችሉ፣ ከመንፈሳዊ ዕውርነት እንዲፈወሱ እንጸልይ። ·         በጌታ ትምህርት በመጽናት መኖር እንድንችል እንጸልይ። ·         በምናልፍባቸው አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ የእግዚአብሔር ክብር ተገልጦ ሌሎች እንዲያዩ እንጸልይ። ኢየሱስ አብርሃም ከመወለዱ በፊት የነበረ ዘላለማዊ አምላክ ነው። ጸጋው ይብዛልን!
522
15
የንባብ ክፍል፡- ዮሐንስ 4፣ 5 እና 6 ዋና ዋና ነጥቦች፡- ዮሐንስ 4፤ ኢየሱስ በሰማርያ በኩል ያልፍ ዘንድ ግድ ሆነበት። ከጉዞው የተነሣ ደክሞት በውሃ ጉድጓድ አጠገብ ተቀምጦ ሳለ ውሃ ልትቀዳ ከመጣች ከአንዲት ሳምራዊት ሴት ጋር ንግግር ጀመረ። ውሃ ጠየቃት፤ አይሁዳዊ ሆኖ ይህን ጥያቄ እንዴት እንዳቀረበላት ጠየቀች፤ ማንነቱን ብታውቅ ራሷ ጠይቃ የሕይወት ውሃ እንደምታገኝ ገለጸላት።  አንተ ከያዕቆብ ትበልጣለህ? ስትለው እርሱ ከሚሰጠው ውሃ የሚጠጣ ዳግመኛ እንደማይጠማ አስረዳት። ይህን ውሃ እንዲሰጣት በጠየቀች ጊዜ ባሏን ይዛ እንድትመጣ ጠየቃት። ባል የለኝም ስትለው እውነት መናገሯን ጠቅሶ አምስት ባሎች እንደ ነበራትና አሁንም ከእርሷ ጋር ያለው የእርሷ አለመሆኑን ነገራት።  ነቢይ እንደ ሆነ ጠቅሳ ስለ ስግደት ሥፍራ ላነሣችው ሐሳብ መንፈስ ለሆነው እግዚአብሔር በእውነትና በመንፈስ የሚሰገድበት ጊዜ እንደሚመጣ አስረዳት። ክርስቶስ የተባለ መሲሕ እንደሚመጣ እንደምታውቅ ስትገልጽ እርሱ መሆኑን ገለጸላት።  ደቀ መዛሙርቱ ተመልሰው ሲመጡ ከሴት ጋር እየተነጋገረ በማግኘታቸው ተደነቁ፤ ምግብ ብላ ባሉት ጊዜ የእርሱ ምግብ የአባቱን ፈቃድ መፈጸም መሆኑን አስታወቃቸው። ሴትዬዋ ያደረገችውን ሁሉ እንደ ነገራት በመሰከረች ጊዜ ብዙ ሳምራውያን በኢየሱስ አመኑ። በመጨረሻም ኢየሱስ ከይሁዳ ወደ ገሊላ በመምጣት የሹሙን ልጅ በመፈወስ ሁለተኛውን ታምራት አደረገ።   ዮሐንስ 5፤ ኢየሱስ በቤተ ሳይዳ በሰንበት ዕለት ለሠላሳ ስምንት ዓመት ሕመምተኛ ሆኖ የኖረ ሰው ፈወሰ። አይሁድም በሰንበት ዕለት ይህን ድርጊት በመፈጸሙ እና “አባቴ እስካሁን እየሠራ ነው፤ እኔም ደግሞ እሠራለሁ” በማለት ራሱን ከእግዚአብሔር ጋር እኩል በማድረጉ ያሳድዱትና ሊገድሉት አጥብቀው ይፈልጉ ነበር። ኢየሱስ አባቱ የሚያደርገውን ሁሉ (ለምሳሌ፣ መፍረድ፣ ሕይወት መስጠት፣ ወዘተ.) እንደሚያደርግ እና የላከውን እንጂ የራሱን ፈቃድ እንደማይሻ በግልጽ ቋንቋ በማስረዳት ቃሉን የሚሰማ፣ በላከው የሚያምን የዘላለም ሕይወት እንዳለው ገለጸ። በመጨረሻም ስለ እርሱ የሚናገሩ የተለያዩ ምስክርነቶችን በመጥቀስ የሚናገረውን ለማመን እንዳልቻሉ ያሳያል።   ዮሐንስ 6፤ ኢየሱስ አምስት እንጀራና ሁለት ዓሣ ለአመስት ሺህ ሰዎች መገበ። ኢየሱስ በውሃ ላይ እየተራመደ ወደ ደቀ መዛሙርቱ መጣ፤ ደቀ መዛሙርቱ ሲደነግጡ “እኔ ነኝ፤ አትፍሩ” አላቸው፤ በሰላም ወደሚሄዱበት ደረሱ። ኢየሱስ የሕይወት እንጀራ መሆኑን በመግለጽ ወደ እርሱ የሚመጣ ከቶ እንደማይራብ፣ በእርሱ የሚያምን በፍጹም እንደማይጠማ ተናገረ። አይሁድ ይህን ንግግሩን ሲሰሙ አባቱንና እናቱን እንደሚያውቁ ጠቅሰው እንዴት ከሰማይ ወረድሁ ይላል በማለት አጉረመረሙ። ኢየሱስ ማጉረምረማቸውን ተረድቶ አብ ያልሳበው ወደ እርሱ እንደማይመጣ በመጥቀስ በእርሱ የሚያምኑ የዘላለም ሕይወት እንዳላቸው፤ እርሱ የሕይወት እንጀራ መሆኑን እንደ ገና ተናገረ። ኢየሱስ ስለ ሥጋውና ስለ ደሙ በተናገረ ጊዜ ብዙ ደቀ መዛሙርት ኢየሱስን መከተል ተው። ኢየሱስም ከአብ ካልተሰጠው በቀር ማንም ወደ እርሱ ሊመጣ እንደማይችል ጠቅሶ ዐሥራ ሁለቱን፣ “እናንተም ደግሞ መሄድ ትፈልጋላችሁ?” በማለት ጠየቃቸው፤ ጴጥሮስም፣ “ጌታ ሆይ ወደ ማን እንሄዳለን? አንተ የዘላለም ሕይወት ቃል አለህ፤ አንተ አንድያ የእግዚአብሔር ቅዱስ እንደ ሆንህ አምነናል፤ ዐውቀናልም” በማለት መለሰ።   ከተማርኩት፡- ·         በአይሁድ እና በሳምራውያን መካከል ትብብር ባይኖርም ኢየሱስ በሰማርያ ያልፍ ዘንድ ግድ ሆነበት! ወንጌል በጠብ ድንበር አይገደብም! ·         ኢየሱስ ሳምራዊቷን ሴት የቀረበበት መንገድ እና ንግግሩን ያሳደገበት ማለትም ራሱን የገለጸበት መንገድ፣ የሴትዮዋ መረዳት እያደገ የሄደበት መንገድ ከወንጌል ሥርጭት አኳያ ትልቅ ትምህርት ይሰጣል! ·         “… እኔ ከምሰጠው ውሃ የሚጠጣ ግን ከቶ አይጠማም፤ እኔ የምሰጠው ውሃ በውስጡ የሚፈልቅ የዘላለም ሕይወት ውሃ ምንጭ ይሆናል” - በቃ ዝም ብዬ አሜን! ሃሌሉያ ብዬ ልለፍ! ·         እግዚአብሔር መንፈስ ነው፤ የሚሰግዱለትም በመንፈስና በእውነት ሊሰግዱለት ይገባል! ·         ኢየሱስ “የእኔ ምግብ የላከኝን ፈቃድ ማድረግና ሥራውን መፈጸም ነው” በማለት ተልእኮውን የገለጸበትና በተልእኮው ላይ ትኩረት ያደረገበት መንገድ አስተማሪ ነው። ·         ሳምራውያን ለሴትዮዋ የተናገሩ እውነት ድንቅ መገለጥ ነው፤ “ከእንግዲህ የምናምነው አንቺ ስለ ነገርሽን ብቻ አይደለም፤ እኛ ራሳችን ሰምተነዋል፤ ይህ ሰው በእውነት የዓለም አዳኝ እንደ ሆነ እናውቃለን!” ኢየሱስ የዓለም አዳኝ ነው! ·         ሰው የለኝም ላለው ሰው የደረሰው ጌታ ዛሬም ሰው ለሌላቸው ደርሶ ከልዩ ልዩ ችግሮች ይገላግላል! ·         “ቃሌን የሚሰማ፣ በላከኝም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ ከሞት ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም” - አሜን! ·         “… የምትፈልጉኝ እንጀራ ስለ በላችሁና ስለ ጠገባችሁ እንጂ … ለሚጠፋ እንጀራ አትሥሩ …” - ሆድ ከባድ ነው! ·         የእግዚአብሔርን ሥራ ለመሥራት ምን ማድረግ አለብን? “እርሱ በላከው ታምኑ ዘንድ፣ ይህ የእግዚአብሔር ሥራ ነው” ·         “የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ፤ ወደ እኔ የሚመጣ ከቶ አይራብም፤ በእኔም የሚያምን ፈጽሞ አይጠማም” - አሜን! ·         “ጌታ ሆይ ወደ ማን እንሄዳለን? አንተ የዘላለም ሕይወት ቃል አለህ፤ አንተ አንድያ የእግዚአብሔር ቅዱስ እንደ ሆንህ አምነናል፤ ዐውቀናልም” - ለመሆኑ ከጌታ ውጪ የዘላለም የሆነ ነገር ያለውና የሚሰጠን ማን ነው? የዘላለም ሕይወት ቃል ካለው ከእርሱ ወዴትም መሄጃ የለንም!   ቃሉን እንጸልይ፡- ·         ሰው ለሌለው የሚደርስ ጌታ እንዲደርስልን በምንፈልገው አቅጣጫ እንዲደርስልን እንጥራው። ·         በተልዕኮአችን ላይ ትኩረት ማድረግ እንድንችል ጌታ እንዲረዳን እንጸልይ። ·         ወንጌል ወዳልደረሰበት ስፍራ ለመሄድ ግድ የሚላቸው ሰዎች እንዲነሱ እንጸልይ።   በእውነትና በመንፈስ ሊሰገድለት ለሚገባው እየሰገድን እንኑር። ጸጋው ይብዛልን!
493
16
የንባብ ክፍል፡- ዮሐንስ 1፣ 2 እና 3 ዋና ዋና ነጥቦች፡- ዮሐንስ 1፤ ቃል በመጀመሪያ ነበረ፣ ከእግዚአብሔር ጋር ነበረ፣ እግዚአብሔር ነበረ፣ ሁሉ በእርሱ ተፈጠረ፣ ሕይወት በእርሱ ነበረች፣ ይህች ሕይወት የሰው ብርሃን ነበረች፣ መጥምቁ ዮሐንስ ሰዎች እንዲያምኑ ስለ ብርሃን መሰከረ፣ የገዛ ወገኖቹ አልተቀበሉም፣ ለተቀበሉትና በስሙ ላመኑት ግን የእግዚአብሔር ልጅነት መብት ተሰጠ፣ ቃል ሥጋ ሆነ፣ የማይታየውን እግዚአብሔር ገለጠ/ተረከ። መጥምቁ ዮሐንስ ክርስቶስ ሳይሆን በነቢዩ ኢሳይያስ እንደ ተነገረው “ለጌታ መንገድ አቅኑለት እያለ በምድረ በዳ የሚጮኽ ድምፅ” መሆኑን ካስታወቀ በኋላ የእግዚአብሔር በግ ስለ ሆነው ስለ ኢየሱስ መሰከረ። የመጀመሪያዎቹ የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት (እንድሪያስ፣ ስምዖን/ኬፋ/ጴጥሮስ፣ ፊልጶስ፣ ናትናኤል) ኢየሱስን የተከተሉበት መንገድ እና ኢየሱስ ከእነርሱ ጋር ያደረገው ንግግር።   ዮሐንስ 2፤ ኢየሱስ በገሊላ አውራጃ በቃና ከተማ በታደመበት ሰርግ ላይ ውሃን ወደ ወይን ጠጅ በመለወጥ የታምራዊ ምልክቶቹን መጀመሪያ አደረገ፤ ክብሩን ገለጠ፤ ደቀ መዛሙርቱም በእርሱ አመኑ። ኢየሱስ፣ “የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉት” በማለት ቤተ መቅደሱን አጠራ፤ አይሁድ ይህን ለማድረግ ሥልጣን እንዳለው የሚያረጋግጥ ምልክት በጠየቁት ጊዜ “ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፤ እኔም በሦስት ቀን መልሼ አነሣዋለሁ” በማለት እነርሱ ስለ ሕንፃ ሲያስቡ እርሱ ግን ስለ ገዛ ሰውነቱ ተናገረ። ብዙ ሰዎች ያደረገውን ታምራት እተው በስሙ አመኑ፤ ኢየሱስ ግን ሰውን ሁሉ ስለሚየውቅ አይታመንባቸውም ነበር።   ዮሐንስ 3፤ ኢየሱስ ከአይሁድ አለቆች መካከል አንዱ የሆነውንና በሌሊት ወደ እርሱ የመጣውን ኒቆዲሞስን አስተማረ፤ ዳግመኛ ያልተወለደ፣ ከውሃና ከመንፈስ ያልተወለደ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም፤ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት ሲያገኙ የማያምኑ ግን ተፈርዶባቸዋል። መጥምቁ ዮሐንስ ከመታሰሩ በፊት ለመጠመቅ ወደ እርሱ የሚመጡትን እያጠመቀ በነበረበት ጊዜ ስለ መንጻት ሥርዐት ክርክር በተነሣ ጊዜ መጥምቁ ዮሐንስ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ መሰከረ።      ከተማርኩት፡-  ·         የመጀመሪያዎቹ ዐሥራ ስምንት ቁጥሮች የክርስትና አስተምህሮ ማእከል የሆነውን ትምህርተ ክርስቶስን በአጭሩ ያስቀምጣሉ፤ የኢየሱስ ቅድመ-ሕላዌነት (pre-existence)፣ ማንነት ያለው መሆን (personality)፣ አምላክነት (divinity)፣ የሁሉ ፈጣሪ መሆን (creator)፣ ሰው መሆን (humanity) እና የማይታየውን እግዚአብሔርን የሚታይ ማድረግ (made the invisible God visible) በግሩም ሁኔታ ቀርቧል። ኢየሱስን በተመለከተ ከእነዚህ እውነቶች አንዱን የሚያጣምም ትምህርት የሐሰት ትምህርት ነው!   ·         ኢየሱስ የዓለምን ኀጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ ነው! እርሱ የእግዚአብሔር ልጅ ነው! ከላይ/ከሰማይ የሚመጣ እና ከሁሉ በላይ የሆነ ነው! በእነዚህ ምእራፎች ኢየሱስ የተገለጸበት መንገድ አስደናቂ ነው። ·         መጥምቁ ዮሐንስ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ የሰጠው ምስክርነት በብዙ መልኩ እንደ አገልጋዮች ምን እንደሚጠበቅብን ያስተምራሉ። ዮሐንስ ሰዎች ዐይናቸውን ከእርሱ ላይ በማንሳት ወደ ጌታ እንዲያደርጉ ከማድረግ ጀምሮ እርሱ ሊያንስና ኢየሱስ ሊልቅ እንደሚገባ በመግለጥ ኀላፊነቱን ተወጥቷል።  ዛሬም ቢሆን እርሱ ሊልቅ እኛ ግን ልናንስ ይገባል! ሰዎችን ወደ ጌታ ልናመጣ/ልንመራ እንጂ ትናንሽ ጌቶች እንድንሆን አልተጠራንም! ·         በኢየሱስ ሕይወት አለ፤ ይህች ሕይወት የሰው ብርሃን ናት፤ ኢየሱስ ወደ ገዛ ወገኖቹ መጣ፣ የገዛ ወገኖቹ ግን አልተቀበሉትም፤ ለተቀበሉትና በስሙ ላመኑት ሁሉ ግን የእግዚአብሔር ልጆች የመሆን መብት ተሰጣቸው። ያመኑት ሁሉ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸው! ·         በተለያዩ ክፍሎች በኢየሱስ ያመኑ እና ያላመኑ በንጽጽር የቀረቡበት መንገድ አስገራሚ ነው። በኢየሱስ ያመኑት የእግዚአብሔር ልጆች የመሆን መብት ያገኙ፣ ዳግም የተወለዱ፣ ከውሃና ከመንፈስ የተወለዱ፣ የዘላለም ሕይወት ያገኙ፣ ወዘተ. ተብለው ሲገለጹ በኢየሱስ ያላመኑት የእግዚአብሔር ቁጣ፣ የእግዚአብሔር ፍርድ፣ ወዘተ. እንደሚያገኛቸው ተገልጽዋል። ·         በጸጋ ላይ ጸጋ ተቀብለናል - የመጀመሪያውም ኪዳን (ብሉይ ኪዳን) የጸጋ ኪዳን ነው!! ·         ኢየሱስ ውሃን ወደ ወይን ጠጅ በመለወጥ አምላክነቱን የገለጠበት መንገድ ድንቅ ነው! ·         ኢየሱስ ቤተ መቅደሱን ያጸዳበት መንገድ አስተማሪ ነው! ·         በእርሱ የሚያምኑ ሁሉ የዘላለም ሕይወት አለው (ለምሳሌ፡- 3፥15፣ 16፣ 18፣ 36)!   ቃሉን እንጸልይ፡- ·         ኑሮአችን እና አገልግሎታችን ስለ ጌታ የሚመሰክር፣ ጌታን የሚያከብር እንዲሆን እንጸልይ። ·         በኢየሱስ በማመን የዘላለም ሕይወት ስላገኘት ደስ እግዚአብሔርን እናመስግን። ·         ስለ ኢየሱስ ባለን ዕውቀት ማደግ እንድንችል ጌታ እንዲረዳን እንጸልይ።   አምላክ-ሰው ሆኖ አምላክን ለሰው በሙላት የገለጠው ጌታ ኢየሱስ የተመሰገነ ይሁን! ጸጋው ይብዛልን!
506
17
ሉቃስ 22-24+1
ሉቃስ 22-24
556
18
ሉቃስ 19-21
ሉቃስ 19-21
531
19
ሉቃስ 16-18
ሉቃስ 16-18
519
20
የዕለቱ የንባብ ክፍል፡- ሊቃስ 13-15 ሉቃስ 13፤ ኢየሱስ በተለያዩ ሥፍራዎች እና ሰዎች ላይ የደረሰውን አደጋ በመጥቀስ “ንስሓ ካልገባችሁ ሁላችሁ እንደዚሁ ትጠፋላችሁ” በማለት የንስሓ ጥሪ አደረገ። ሦስት ዓመት ሙሉ ፍሬ ያልተገኘባትን በለስ ምሳሌ ነገራቸው።አንዲት ጎባጣ ሴት በሰንበት ቀን በመፈወሱ የምኩራብ አለቃው በተቆጣ ጊዜ ኢየሱስ “እናንተ ግብዞች ከእናንተ መካከል አንድ ሰው በሬውን ወይም አህያውን በሰንበት ቀን ከማደሪያው ፈትቶ ውሃ ሊያጠጣ ይወስደው የለምን?” በማለት ተቃዋሚዎቹ የሚሉትን አሳጣ። የእግዚአብሔር መንግሥት በሰናፍጭ ቅንጣትና በእርሾ በመመሰል አስተማረ፤ በጠባቧ በር ለመግባት እንዲጣጣሩ አሳሰበ፤ በመጨረሻም ኢየሱስ ስለ ኢየሩሳሌም ማዘኑን ገለጸ፤ … ዶሮ ጫጩቶቿን በክንፎቿ ሥር እንደምትሰበስብ ልጆችሽን ለመሰብሰብ ስንት ጊዜ ፈለግሁ፤ እናንተ ግን እምቢ አላችሁ…!”   ሉቃስ 14፤  ኢየሱስ በሰንበት ቀን በአንድ ፈሪሳዊ ቤት በአካል እብጠት የሚሰቃይ ሰው ፈወሰ፤ ስለ ሰንበትም ተናገረ። በክብር ስፍራ ለመቀመጥ መቸኮል እንደማይገባ በምሳሌ እያስተማረ ራሱን ከፍ የሚያደርግ ዝቅ እንደሚልና ራሱን ዝቅ የሚያደርግ ደግሞ ከፍ እንደሚል አመለከተ። ከዚሁም ጋር በማያያዝ ብድራት መመለስ ለማይችሉ መልካም ማድረግ ኋላ ላይ ዋጋ እንዳለው አስተማረ። ትልቅ ግብዣ አዘጋጅቶ ተጋባዦቹ በራሳቸው ምክንያት መገኘት ባለመቻላቸው ከየጎዳናው የተጠሩ ድኾችና አካለ ስንኩላን ድግሱን እንዲበሉ ስላደረገ ሰው ተናገረ። በመጨረሻም “… ማንም ያለውን ሁሉ የማይተው ደቀ መዝሙሬ ሊሆን አይችልም” በማለት ደቀ መዝሙር መሆን ምን ያህል ትልቅ ዋጋ እንደሚያስከፍል አስተማረ።   ሉቃስ 15፤ ፈሪሳውያንና ጸሐፍት ኢየሱስ ቀረጥ ሰብሳቢዎችን እና ኀጢአተኞችን ይቀበላል፤ ከእነርሱም ጋር ይበላል በማለት ባጉረመረሙ ጊዜ ኢየሱስ በጠፋውን በግ ምሳሌ፣ በጠፋውን ሳንቲም ምሳሌ እና ጠፍቶ በተገኘውን ልጅ ምሳሌ ጥልቅ ትምህርት ሰጣቸው። መቶ በጎች ያሉት ሰው አንዱ ቢጠፋበት ዘጠና ዘጠኙን ትቶ አንዱን ፍለጋ እንደሚሄድ ንስሓ ከማያስፈልጋቸው ከዘጠና ዘጠኝ ጻድቃን ይልቅ ንስሓ በሚገባ በአንድ ኀጢተኛ በሰማይ ደስታ ይሆናል። ከዐሥር ሳንቲሞች አንዱ ቢጠፋባት መብራት አብርታ፣ ቤቷን እየጠረገች የማትፈልግ እና ስታገኝ ከሌሎች ሰዎች ጋር ደስታዋን የማታጣጥም ሴት የለችም፤ እንዲሁ ንስሓ በሚገባ በአንድ ኀጢአተኛ በእግዚአብሔር መላእክት ፊት ደስታ ይሆናል። ሁለት ልጆች የነበሩት እና አንዱ ድርሻውን ሁሉ ወስዶ ካባከነ እና ከፍተኛ ችግር ውስጥ ከገባ በኋላ ተጸጽቶ በተመለሰ ጊዜ አባቱ ያደረገለትን አስደናቂ አቀባበል እና ቅሬታ ለተፈጠበት ወንድሙ የሰጠውን ምላሽ እንደ ምሳሌ በመጠቀም አስተማረ።   ከተማርኩት፡-  ·         በአንድ ግለ ሰብ ወይም ወገን ላይ የተለየ ሥቃይ የሚደርሰው ከሁሉ ይልቅ ኀጢአተኛ ስለ ሆነ ወይም ስለ ሆኑ አለመሆኑን እና በንስሓ በማይመለሱ ሁሉ ላይ ተመሳሳይ ችግር እንደሚደርስ ያስተማረበት መንገድ ወደ ራሳችን እንድናይ የሚያደርግ ነው! ሲጀምር ወይም እስከ አሁንም ቢሆን ራርቶልን እንጂ የተሻልን ሆነን አይደለም። ከጥፋታቸው፣ ከዐመጻቸው የማይመለሱ ግን ከቅጣት አያመልጡም! ·         የአብርሃም ልጅ ሆና ለዐሥራ ስምንት ዓመት በሰይጣን ታስራ ጎብጣ የኖረችን ሴት በፈወሰ ጊዜ በዚህች ሴት ነጻ መውጣት ከመደሰት ይልቅ ፈውሱ በሰንበት ዕለት መሆኑ ያስጨነቃቸው የሃይማኖት መሪዎች አስገራሚዎች ናቸው። ·         በጠባቧ በር ለመግባት ተጣጣሩ! ከኋለኞች መካከል ፊተኞች የሚሆኑ ከፊተኞች መካከል ኋለኞች የሚሆኑ አሉ! ·         “… ዶሮ ጫጩቶቿን በክንፎቿ ሥር እንደምትሰበስብ ልጆሽን ለመሰብሰብ ስንት ጊዜ ፈለግሁ፤ እናንተ ግን እምቢ አላችሁ” - መተላለፍ፣ አለማስተዋል፣ መግፋት ፣ ወዘተ. እንዴት አገደኛ ነው? ·         በአካል እብጠት የሚሰቃይ ሰው ፈወሰ! ኢየሱስ ያልፈታው፣ የማይፈታው ችግር የለም! እርሱ መልካምን ማድረግ የማይታክተው የሰንበት ጌታ ነው! ·         ራሱን ከፍ ከፍ የሚያደርግ ዝቅ ይላል፤ ራሱን ዝቅ ዝቅ የሚያደርግ ሁሉ ከፍ ይላል! የከፍታ መንገዱ ምንጣፍ አስነጥፎ በአጀብ መሄድ ሳይሆን የጌታን ፈለግ በመከተል በትሕትና ማገልገል ነው! ·         ድግሱ የተዘጋጀላቸው ምክንያት አብዝተው ግብዣውን ንቀው ቢቀሩም በግብዣው ላይ የሚገኙ አልጠፉም! ·         “ከእናንተ ማንም ያለውን ሁሉ የማይተው ደቀ መዝሙሬ ሊሆን አይችልም” - የኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዝሙር መሆን ዋጋ ያስከፍላል!  ·         ንስሓ ከማያስፈልጋቸው ከዘጠና ዘጠኝ ጻድቃን ይልቅ ንስሓ በሚገባ በአንድ ኀጢአተኛ በሰማይ ደስታ ይሆናል! ንስሓ በሚገባ በአንድ ኀጢአተኛ በእግዚአብሔር መላእክት ፊት ደስታ ይሆናል! የአንድ ኀጢአተኛ በንስሓ መመለስ በሰማይ የሚፈጥረው ደስታ አስገራሚ ነው! ·         የጠፋው ልጅ ወደ አባቱ ቤት ሲመለስ የተደረገለት አቀባበል፣ አባቱ ያሳየውን ፍቅርና መልካምነት የሚያሳየው ምሳሌ ልብ የሚነካ ነው! ለሚመለሱት የሚመለስ፣ ፍቅሩ ወደር የሌለው ጌታ ስሙ ይባረክ!        ቃሉን እንጸልይ፡- ·         የእግዚአብሔርን ማዳን እና ፍቅር እያሰብን እናመስግን። ·         በችግሮቻችን ላይ የእግዚአብሔር ክብር እንዲገለጥ እንጸልይ። ·         እግዚአብሔር በትሕትና እንዲባርከን እንጸልይ።   የእግዚአብሔር መንግሥት ከፍ እያለች እና እያሸነፈች ትሄዳለች! ጸጋ ይብዛልን!
583