fa
Feedback
የስንኝ ቋጠሮ

የስንኝ ቋጠሮ

رفتن به کانال در Telegram

የዚህ ቻናል ዋና አላማ የተለያዩ ወጣቶች የግጥም ችሎታቸውን የሚዳብሩበት እና የሚያወጡበት ቻናል ነው። ግጥሞችን ለመላክ @mogea ይጠቀሙ መልሰን ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል!!

نمایش بیشتر
2 046
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
ሰላም ውድ "የስንኝ ቋጠሮ" ቻናል ቤተሰቦቻችን በዚህ ሳምንት እንደከዚህ ቀደም ሁሉ አርብ እለት የግጥም ውድድር ይኖረናል። የግጥሙም ሀሳብ "በሀገራችን ታሪክ የሀገር ባለውለታ ጀግና ነው ለምትሉት ግለሰብ ስንኝ መቋጠር" በተጠቀሰው ሀሳብ ብቻ የግጥም ስራችሁን @Abebekasu እና @mogea ላይ ከነገ ሀሙስ ማለዳ ጀምሮ ውድድሩ እስከሚካሄድበት አርብ ምሽት 3 ሰዓት ድረስ እንድትልኩልን እንሻለን። ማሳሰቢያ 1.በተጠቀሰው የግጥም ሀሳብ ብቻ እንዲሆን የምትልኩልን ግጥም 2.ከ 12 ስንኝ ያልበለጠ ግጥም 👉እንደሁልግዜው ሌሎች ወዳጆቻችሁንም ወደ ቻናላችን መጋበዝ አትረሱ።

✅ አሁን online ላላችሁ ብቻ ጥያቄ ና መልስ ልንጀምር ነው❗️ 1⃣ ለወጣ 500 ብር ካርድ 2⃣ ለወጣ 250 ብር ካርድ 3⃣ ለወጣ 100 ብር ካርድ 👉 ዝግጁ ከሆናችሁ ጀምር የሚለውን ይጫኑ 👇👇👇👇👇

እንዲህ ነው ያገኛት እንዲህ ነው ያገኛት ኖሮ በራሱ ቤት የኛን ሊያይ ሲመጣ አዝኖ በስራችን ሲወረድ በቁጣ እንዲህ ነው ያገኛት እሱ የሰራትን አለም እኛ አበላሽተናት በሀጢያት ውቂያኖስ በዛ ሰፊ ባህር ጥላቻ እና ቅናት ገዝፎብን ከፍቅር ሴት ከሴት ተጋብተው ትዕዛዙን ተላልፈው ቃየሎች ተነስተው አቤሎችን ገድለው እንዲህ ነው ያገኛት ድብልቅልቋ ወጦ ምድር ተሸበራ የሰዉ ህይወት ቀሎ ሁሉም ሆኖ ተራ ፈጣሪ መኖሩን ሁሉ ሰው ዘንግቶ ከነፍስ ደስታ ይልቅ ለስጋው አድልቶ መፅም መፀለዩ ተለውጦ አየህው በስካር በዝሙት ብታይ ተጨማልቀው እንዲህ ነው ያገኛት መሬቷ ረጥባ የሠው ደም ሞልቶባት ህዝብ በህዝብ ላይ ይነሳል እንዳለው ትንቢቱ ሲፈፀም ጊዜው ደርሶ ባለው እንዲህ ነው ያገኛት ወደ ምድር ወረዶ ባልታሰበው እለት ✍✍ራኬብ✍✍

ሀገሬ አርቧ ነው ! ተነሺ እናት ዓለም ይብቃ ያንቺ ህማም ትንሣኤሽ ይሰማ ድል ንሺ ጠላትን ውጪና ከማማ ሀገሬ አርቧ ነው ! ብዙ ንፁህ ነፍሶች ደም የሚሸትበት እንደ አንድዬ ያ'ብ ልጅ ምንም ያላጠፋ ህዝብ ሚቀጣበት ስቅለት ላይ ላለችው ይሁዶች ለከዱአት ዕጣ ተጣጥለው ለሚቀራመቷት ፈራጅ እንደ አይሁዶች ሞልተው ለሚፈስዋት ሀገሬ አርቧ ነው! ኤሎሄ ኤሎሄ ብላ እንዳጠራው ያልተዋትን አምላክ ምን ብላ ትክሰሰው ወንድም ለከዳነው ወገን ላቆሰልነው ራስ ለወደድነው ዘር ጎጥ ለወረሰን ገንዘብ ለሚገዛን ለየቱ ተማፅና የትኛውን ትተው ለስቅለት ያበቃት ሁሉ ሕማሟ ነው አባት ሆይ ታረቀን መከፈል መገረፍ መገደሉ ይብቃን የእናት ኢትዮጵያን እንይ ትንሣኤዋን አሜን !! ሰርክ አዲስ @gitmv

የሳመውን ከንፈር ~ያቀፈውን ገላ ፅድቅነቱን ትቶ~ ለጥቅሙ ያደላ ይሁዳ ነው እሱ~ ጌታውን የሸጠ ለሰላሳ ዲናር ~እምነቱን የለወጠ . . . እየተባለ ቡዙ ~ተወራ ተፃፈ ግን ግን እንደኔ እንደኔ ይሁዳ ባይከዳው ኑሮ ባይለውጠው በዲናር እሄኔ ተሰቀለ ተገረፈ እያለ ማን ያመልከው ነበር? @gitmv #ተፃፈ በbluefish

የህይወት እኩሌታ ከሰማይ ጠቀሱ :ለእግዜር ከቀረበው ...... ደሞም ከእምድሩ ከተራጎዳናው :ሸራከለበሰው ቢሆን ........ ማደራዬ ልብን ካምላክ አርጎ :አካልን ካሸሸው አካሌን አቅርቦ :ልቤን ካሸፈተው ቢሆን መገኛዬ :ከሁለት ባንዳቸው ምንም ለውጥ የለው :የሁለቱም ነፍሶች በስተመጨረሻ አፈር ነው ቤታቸው። አዲስአለም አብርሃም

አፍቃሪ ልብ አፍቃሪ ልብ ይዤ እንጎራደዳለሁ፣ ማፍቀሬን እያወኩ ብዙውን አያለሁ። ልቦቼ ትንንሽ ቶሎ ይሰበራሉ፣ ቢተርፉ ቢተርፉ ይሸራረፋሉ። አፍቃሪ ልብ ይዤ ወዲህ ወዲያ እላለሁ ወይ ግሩም ማንነት፣ ወይ መርሳት ወይ ማጣት። ስንቱን አፈቀርኩኝ፣ ልቤ ግን ስንት ነው እያጠያየኩኝ። የመውደድ ማህተቤ መቼም አልበጥስም ትልቅ ሀይል አለው ይህንን አልክድም። የወደድኩት ከድቶኝ ብሰቃይ ባነባ ፣ ህይወት ይቀጥላል ይፈስና እንባ። ስትል እየሰሟት ባሽሙር ሲስቁባት፣ እኔ ብቻ ገባኝ ፍቅርን እንደራባት። በምድር ቢሞላ የወንድ ጋጋታ ሴትን ዝቅ የሚያረግ ስሜት የሚነካ ተወልዶ ያላደገ ስነ ምግባር ተራ፣ ጥበቡን ሲጀምር አምላኩን ያልፈራ ፍቅርን እያስራበ ሆዷንም ካባባ፣ ዛሬም ትጮሀለች ፍቅርን ተርባ። ምህረት ወርቁ 5/8/2013

Watch "አትስጡኝ አልወስድም!!" on YouTube https://youtu.be/1likOe9AnhE

ለ ሰው ሞት አነሰው ያለችው ቀበሮ ምን ተሰምቷት ይሆን? የራሱን አዳፋ የራሱን መጥፎ ሃሳብ በሰው ላይ ለመፍረድ በሰው ለማሳበብ አብሮት ያለውንም አብሮት እንደሌለ መካድ መካካዱን መጥላት መጥላላቱን ለራሱ አላብሶ ውስጡ እያኖረ ይሄኔ እኮ እሷ እኛን ከኛ በላይ አውቃን ኖሮ ይሆናል እኛም በኛ ቤት ላይ ይሄን ተሳልቀናል ቀበሮ አለች አሉ ምን አውቃ ለራሷ ምንም የማታስብ እንስሳ ናት እሷ አዬ እንስሳ እቴ እኛም ሰው ተባልን እሷን ኖረን ሆኖ እንደሷ ባወቅን ሰው ተብሎ መለየት ለማሰቡ ነበር እኛ ላለማሰብ የማልን ይመስል ለማያስበው ነው የሚሰጠው ክብር እንዲህ ያለችውን ቀበሮን ባወኩዋት እንዴት እንዳወቀች ቀርቤ ባዋያት ያውም እኮ ያኔ በደናው ጊዜ ነው እሷ የነበረች አሁን ብትኖርማ አነሰውም ሳይሆን ይገባዋል ብላ ገድላ በጨረሰች:: ሰርክ አዲስ

ሸልመናቸዋል!! በስንኝ ቋጠሮ ብቻ!! @gitmv

photo content

photo content

እስከ ነገ ድረስ ሶስተኛውን እንጠብቅና ከሌለ አንደኛ እና ሁለተኛ የወጡትን ነገ እንሸልማለን!! @gitmv 👈 ይቀላቀሉን

ሶስተኛውን እንጠብቃለን

ሁለተኛ ፍስሃ 🏆🏆🏆🏆

ሁለተኛውን እየጠበቅን ነው

አንደኛ ሮቤል ከ አለም ገና 🏆🏆🏆🏆🏆🏆

ሀገሬ ኢትዮጵያ ፣ሞኝ ነሽ ተላላ ፣እንዳለው ገጣሚ፣ እኔም ልወቅስሽ ነው፣ ልብ ብለሽ ስሚ፣ እውነትም ሞኝ ነሽ ፣ሕዝብሽም ሞኝ ነው፣ የሄደው የመጣው ፣እንደልብ ሚነዳው፣ እውነትም ሞኝ ነሽ፣ ሕዝብሽም ሞኝ ነው፣ አምላኩን ረስቶ፣ ንጉስ የሚያመልከው፣ እኔ ግን ልንገርሽ ፣እኔ ግን ልውቀስሽ፣ ፈጣሪን ማስታወስ ፣ፈጣሪን መጥራት ነው፣ ላንቺ የሚበጅሽ፣ እንደ ቀደም ጊዜ ፣ልክ እንደ በፊትሽ ኢትዮጵያ ታበፅ ፣እሱ ነው ሚያምርብሽ ፣ ✍✍ ሮቤል አድራሻ : ዓለም ገና

Shambel Wakgari: ፈተና ነው ክንደ ብርቱዋኑ ሀያል የተባሉ ሉአላዊ ሀገር ያፈርሳሉ አሉ ዲሞክራሲ ሚሉት በዳቦ ስማቸው ቆይቶአል አሉ አለም ካወቃቸው ድሮ እዛ ያልነው ዛሬ እዚህ ደርሶ ባይኔ አይቻለሁ ወገን አስለቅሶ ሀገሬን ቢጎዱዋት አለሙ አብሮ ውስጥ-ውጩ ባንድት ፍፁም ተተባብሮ ቢጎሿሽማትም...! አለየሚረዳት ከፀባዖት ሆኖ ማያልፍ የለም እና ያልፋል ተፈትኖ ያልፋል። ያልፈሉ! ብቻ ክብር ለሀገር! @*** 18 በጅማ ዞን ጎማ ወረዳ ሊሙ ሻይ ከተማ ቀበሌ ሻምበል ዋቅጋሪ ጃለታ

ለኢትዮጵያ እንቁም🇪🇹🇪🇹🇪🇹 ለሰላም እንዘምር ፍቅር እናስፋፋ የጦርነት መአት ከሀገራችን ይጥፋ መዝፈን ብቻ ሳይሆን በጋራ እንታገል ካለ ቆራጥ ትግል ሰላም አይታደል ዝም ማለትማ ለበግም አልበጄ ሺዉን የበግ መንጋ አንድ ነብር ፈጄ በጋራ ተነስተን በአንድነት ተሳስረን ኢትዮጵያን እናድን እንደ አባቶቻችን ታሪክ እንደሰማን ታሪክ እንሰራለን ፍሥሃ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ