የስንኝ ቋጠሮ
رفتن به کانال در Telegram
የዚህ ቻናል ዋና አላማ የተለያዩ ወጣቶች የግጥም ችሎታቸውን የሚዳብሩበት እና የሚያወጡበት ቻናል ነው። ግጥሞችን ለመላክ @mogea ይጠቀሙ መልሰን ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል!!
نمایش بیشتر2 046
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
2 046
ሽል
ምን ይሆን ጥቅሙ ምን ይሆን ማመሱ
ገና ብቅ ሳይሉ መተረማመሱ
ከተመሰረተ ፅንስ ሆኖ ከቀረ
አሁን አሁን ሳይሆን ድሮም ከነበረ
በጊዜያዊ ስሜት ታስሮ ካላበረ
ብናኝ ሳታነሳ ሌተቀን ያይላል
ታይታን ሳትሻ ሽል ከሆነ ይገፋል!!
ፅንሱ ይወለዳል!!
2 046
ጥንትስ ያለወትሮ ብዙ አመት
አርግዤ
ሰው ሆኖ ሰው ላይሆን ጭንቅ
ምጥ ተይዤ
ጉዴ ሳይሰማ መስከረም
አልጠባም
መቼ አደለኝና አቅፌ ለመሳም።
በሆዴ ውስጥ ያለው ያረገዝኩት
🤰ልጄ
ልምሻ የመሰለኝ ስዳብሰው በጄ።
አሁን ከኔ ወጥቶ
ምን ሊረባ ከቶ🤔
ግዴለም, ባይወለድ ይቅር
ተወልዶ ላይረባ ኖሮ ላይጠነክር
ደሞ .... አባት የሌለው ልጅ
ኧረ ለማን ሊበጅ!?
ስለዚህ እዛው ሁን ልጄ አትወለድ
ቆመህ ላትራመድ።
በማህፀን ሳለ ስመኘው የኖርኩት
የማልወልደው ልጄን ስነ-ፅሑፍ
አልኩት።
ወይንሃረግ
2 046
የካድኩት ልጅ አለኝ
ወልጄ 'ማላቀው አሱም የማያቀኝ።
ግሩም ድንቅ ፍጡር
ከሱ በላይ ላሳር።
አይኖቹ ከዋክብት ጠይም አሳ
መሳይ
እኔን እናቱን ሲሆን አይኑ ዞሮ 'ማያይ
ምጡቅ አንጎል አለው
አለም ያደነቀው
ግንሳ.... ብልሀት ጎደለው።
አንጀቱ እንስፍስፍ
ማየት የማይችል ግፍ።
ግንሳ ለናቱ....
አይራራ አንደበቱ።
እናትህ ትቃጠል እናትህ እንዲ
ትሁን
እናትህ..... እናትህ.....የስድብ
ውርጂብኝ።
የካድኩት ልጅ አለኝ
እሱም የማያቀኝ
ስድብ የሚያረገኝ
አስር ጣት እያለው...
ሁለቱን ሦስቱን ካልቆረጥኩ
የሚለኝ።
2 046
ኢትዮጵያዊ ነኝ!
(በእውቀቱ ስዩም)
.
.
ኑሮ ቢገፋኝ የማልወድቅለት፣
እንደ አክሱም ድንጋይ እንደሮሃ አለት፣
የጊዜ ሞገድ ያልነቀነቀኝ፣
የመከራ ዶፍ ያላደቀቀኝ፣
ለሙሾ ሲያጩኝ ቅኔ የምቀኝ፣
በግራ ሲሉኝ የምገኝ በቀኝ፣
ኢትዮጵያዊ ነኝ!
።።።።።
ከዋርካ ባጥር ከዕምቧይ ተልቄ፣
ከፀሐይ ባንስም ከኩራዝ ልቄ፣
ከምድረበዳ ጅረት አፍልቄ፣
ጥሜን የምቆርጥ በእፍኝ ጠልቄ፣
ኢትዮጵያዊ ነኝ!
።።።።።።
ልክ እንደቻይናው የትም ሳልረባ፣
እንደ እንግሊዙ ሳልሰራ ደባ፣
እንደ አሜሪካው በቁም ሳልሰባ፣
በመጠን ኑሬ አፈር 'ምገባ፣
ኢትዮጵያዊ ነኝ!
ግትር ጠላቴን በአጭር አንካሴ፣
ራስምታቴን በዳማከሴ፣
ነቅዬ 'ምጥል፣
አገር በነገር የማብጠለጥል፣
ነገር በነገር የማብጠለጥል
ኢትዮጵያዊ ነኝ!
።።።።።
እንደመሃረብ ቤቴን በኪሴ፣
እንደንቅሳት ተስፋን በጥርሴ፣
ይዤ የምዞር ከቦታ ቦታ፣
በዘብ በኬላ የማልገታ፣
ኢትዮጵያዊ ነኝ!!!!
።።።።።።
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር።
@gitmv
2 046
መቼ ትመጣለህ
ፀሀይ ስትዘቀዝቅ ስታዞረው ፊቷን
ጨረቃ ስትስቅ ስናይ ፈገግታዋን
ሲከፋኝ ስታመም ስምህን ሳነሳ
ስላንተ ሳወጋ ፍቅርህን ሳወሳ
አልበላ ሲለኝ ባር ባር ሲለው ሆዴን
ንገረኝ መቼ ነው እማየው አይንህን
ለሊት አልጋዬ ላይ ሆኜ እንቅልፌ ሲጠፋ
መኖር አስጠልቶኝ ልቤ ሲቆርጥ ተስፋ
ስልኬን አነሳ እና ፎቶህን አያለሁ
ትመጣለህ እያልኩ በርበሩን አያለሁ
ከቀጠርከኝ ቦታ ቀድሜ ብደርስም
ቆሜ ብጠብቅም አንተ ግን የለህም
ትመጣለህ አደል አትቀርም ልጠብቅ
ዝናቡ ቢዘንብ ቢወርድብኝ መብረቅ
ነይ ካልከኝ ቦታ ላይ ቆሜ አንተን ስጠብቅ
ጎርፍ ወስዶ ቢጥለኝ ባካል ካንተ ብርቅ
ስቃዩ ቢበዛ ቢከብድም ንፋሱ
ሳትስመኝ አልሞትም ከንፈሬን በስሱ
ባንተ ሳልታቀፍ ህሜን ሳልነግርህ
አትቀርም ልጠብቅ መቼ ትመጣለህ
🤔🤔
@nitsuhti1419
2 046
ውድ ቤተሰቦቻችን እንደምን ከረማችሁ፤የዚህ ቻናል ዋንኛ አላማ የጀማሪ ገጣሚያንን የግጥም ስራዎች በይበልጥ መውጣት እንዲችሉ መርዳት ነውና ገጣሚያን በየትኛውም ሰዓት የግጥም ስራዎቻችሁን @Abebekasu እና @mogea ላይ ብትልኩልን የምንቀበል ይሆናል።
2 046
ለኔ...
የድፍን አፍሪካ ኩራት፤የሀያላን ሀገራት ውርደት
የመላው ዓለም ውዥምብር ፤የጣሊያን ቅስም ስብራት
የጥቁር ህዝቦች መመኪያ፤የአፍሪካ ነጻነት ብስራት
ተንቀው ወድቀው ለታዩ፤የዕሳት ትንታግ አለኝታ
የ ኢ ት ዮ ጵ ያ ዋርድያ፤የጥቁር ዘር መከታ...
ሚኒሊክ ዕኮ ሀገር ነው...
ግርማው ከተራራ የገዘፈ፤ወኔው ነጭን የረታ
በድፍረት የደነደነ ፤ልቡ የማይፈታ
ጨካኝ አትለው እምዬ ፤ ልቡ የሴት ቦርቧራ
እኖር ባይ አይደለ ቆራጥ፤ የሚቀበል መከራ
ጀግንነት ዕኮ እዳ አለው ፤ ለፈሪ ግን ቀብድ ነው
ዛሬ ጀግናነኝ የሚል ፤ ለሀገር ጥሎሽ ብድር ነው
ለኔ...
ጀግብናዬ እሱ ነው ፤ ስሙን እንደ ዕሾህ ዓለም የፈራው
ጀግና የጀግና ጀግና፤ሚኒሊክ የኛ ሀገር ነው።
@ s@m! d@n
🇪🇹🇪🇹🙏🙏
2 046
*የኔ ጀግና አንተው ነህ*
ሀገር ምስቅልቅል ወርሷት
የምጥ አመቷ በዝቶባት
የመሃል ሀገር ረመጥ ትኩሳትዋን ሽሮላት
ቅጥርዋን ከአለት ገንብቶት ስቃይዋን ያሳጠረላት
ቴዎድሮስ ነው የቋራው ጀግና ሀዘኗን ያበረደላት
የኔ ጀግና አንተው ነህ
መቅደላ ላይ ሁነህ የሽጉጥ አረር የጠጣህ
በነገስክበት አመታት ለጦቢያ ታትረህ ራስህንው የሰዋህ
የጀግና ሞትን ሞተህ ስምክን በደማቅ የፃፍክ።
✍Ab
2 046
ሁሉ ለኔ
ላይሆነንአንድ እጅ፡ቢፈለግ ጭብጨባው
አንድ ጀግና የለኝ ፡ለብቻ ማወሳው
ከአፍ በዘለለ አስከመሆን አፈር
ጥልቀቱ ባየለ በእውነተኛ ፍቅር
ባራቱም መሀዘን የተሰው ነፍሶች
ነጋቸውን ለኛ የለገሱ ሰዎች
ሁሉም ለኔ ጀግና ፡ሁሉም የኔ ጀግኖች።
አዲስአለም አብረሃም
2 046
ጀግና
አንጀቷን ቢወጋ በሆድ ኑሮ ባን'ዳ ፣
አብሮ ከጠላት የእናት ቤት ሲከዳ ፣
ተነሳ ተቆጣ!፦
ልክ ግብሩን ሊያሳይ ነቅቶ በማለዳ ፤
ነጆ ያበቀለው እትብተ ወለጋ ፣
ምሎ ለኪዳኗ ጎህ ሲገፍ ሲውጋጋ ፣
ተነሳ ማለዳ ጠላቷን ፍለጋ ፤
በማለዳው ነቅቶ ፣
የጠላቱን ዱካ ካለበት አሽትቶ ፣
ኦኔ እያ'ነሳሳ በአጀብ በቀረርቶ ፤
ድል እያደረገ ቢያ'ዝም በጠላት ፣
እኛን ምሰል ቢሉት ቢሰጡት ዜግነት ፣
መሞት የመረጠ ክዶ ለባርነት ፤
እሱ...
የማይደራደር ከቶ ባገር ጉዳይ ፣
እትዮጵያን ከፍ አርጎ በሮም አደባባይ ፣
ከፎቅ ያመለጠ በእራፊ ትልታይ ፤
ጀግናው
አብዲሳ አጋ !።
ከሻምበል ዋቅጋሪ
ከ ጅማ
20/08/2014
2 046
ማነው ጀግና የሀገርህ?
ከሁሉ በላይ ክብር የሚሰጥህ
እስኪ ንገረኝ ወገኔ ማን ይሆን ጀግናህ?
በህይወት እንድትኖር ጊዜ፣ ጉልበቱን ደግሞም ገንዘቡን የከሰከሰልህ
ሀገርህም እንዳትፈርስ ነፍሱን የገበረልህ
በፈጠረህ ንገረኝ ማን ይሆን ጀግናህ?
እኔ ግን እላለሁ ጀግናዬ ገበሬ
አርሶ በጉልበቱ ማዕድ ያቀረበላት ለሀገሬ
አርብቶም ያበላን ተዋግቶ ከአውሬ
ደግሜ ደግሜ እኔ ግን አላለሁ ጀግናዬ ገበሬ
ዋጋው ያልታየለት
በቃ እሱ ነው ጀግናዬ ለሀገሩ የሞተላት
ዳር ድንበሩአንም ያስከበረላት
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።✍B. T
2 046
ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች ውድድራችንን ለማካሄድ አንድ ሰዓት ገደማ ይቀረናል።አሁንም ግጥሞችን መቀበል ስለምንችል @Abebekasu እና @mogea ላኩልን።
2 046
ምሽት ላይ ለሚኖረን የግጥም ውድድር አሁንም ግጥሞቻችሁን እየተቀበልን እንገኛለን።
ማን ነው ጀግናችሁ?ስንኝ እስኪ ቋጥሩለት፤እንዲሁም ላኩልን።
2 046
ውድ ቤተሰቦቻችን ግጥሞቻችሁን ነገ ምሽት 3 ሰዓት ድረስ እየተቀበልን እንቆይና ወደ ውድድሩ እናመራለን። ከዚህ በፊት የነበሩት ህጎች ቀጣይነት ያላቸው ሲሆን ቀድሞ 60 ላይክ የደረሰ ተወዳዳሪ አሸናፊ ሲሆን ሁለተኛ እና ሶስተኛ 60 ላይክ የሚደርሱም ተወዳዳሪዎች በቅደም ተከተል የሚሸለሙ ይሆናል።አሁንም ከላይ በጠቀስነው ሀሳብ የግጥም ስራችሁን @Abebekasu እና @mogea ላይ ላኩልን።
