fa
Feedback
የስንኝ ቋጠሮ

የስንኝ ቋጠሮ

رفتن به کانال در Telegram

የዚህ ቻናል ዋና አላማ የተለያዩ ወጣቶች የግጥም ችሎታቸውን የሚዳብሩበት እና የሚያወጡበት ቻናል ነው። ግጥሞችን ለመላክ @mogea ይጠቀሙ መልሰን ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል!!

نمایش بیشتر
2 046
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
ሽል ምን ይሆን ጥቅሙ ምን ይሆን ማመሱ ገና ብቅ ሳይሉ መተረማመሱ ከተመሰረተ ፅንስ ሆኖ ከቀረ አሁን አሁን ሳይሆን ድሮም ከነበረ በጊዜያዊ ስሜት ታስሮ ካላበረ ብናኝ ሳታነሳ ሌተቀን ያይላል ከ እህል ከዘለለ ሽል ከሆነ ይገፋል!! ፅንሱ ይወለዳል!! ሼር ላይክ @gitmv @Mogea

ሽል ምን ይሆን ጥቅሙ ምን ይሆን ማመሱ ገና ብቅ ሳይሉ መተረማመሱ ከተመሰረተ ፅንስ ሆኖ ከቀረ አሁን አሁን ሳይሆን ድሮም ከነበረ በጊዜያዊ ስሜት ታስሮ ካላበረ ብናኝ ሳታነሳ ሌተቀን ያይላል ታይታን ሳትሻ ሽል ከሆነ ይገፋል!! ፅንሱ ይወለዳል!!

ጥንትስ ያለወትሮ ብዙ አመት አርግዤ ሰው ሆኖ ሰው ላይሆን ጭንቅ ምጥ ተይዤ ጉዴ ሳይሰማ መስከረም አልጠባም መቼ አደለኝና አቅፌ ለመሳም። በሆዴ ውስጥ ያለው ያረገዝኩት 🤰ልጄ ልምሻ የመሰለኝ ስዳብሰው በጄ። አሁን ከኔ ወጥቶ ምን ሊረባ ከቶ🤔 ግዴለም, ባይወለድ ይቅር ተወልዶ ላይረባ ኖሮ ላይጠነክር ደሞ .... አባት የሌለው ልጅ ኧረ ለማን ሊበጅ!? ስለዚህ እዛው ሁን ልጄ አትወለድ ቆመህ ላትራመድ። በማህፀን ሳለ ስመኘው የኖርኩት የማልወልደው ልጄን ስነ-ፅሑፍ አልኩት። ወይንሃረግ

የካድኩት ልጅ አለኝ ወልጄ 'ማላቀው አሱም የማያቀኝ። ግሩም ድንቅ ፍጡር ከሱ በላይ ላሳር። አይኖቹ ከዋክብት ጠይም አሳ መሳይ እኔን እናቱን ሲሆን አይኑ ዞሮ 'ማያይ ምጡቅ አንጎል አለው አለም ያደነቀው ግንሳ.... ብልሀት ጎደለው። አንጀቱ እንስፍስፍ ማየት የማይችል ግፍ። ግንሳ ለናቱ.... አይራራ አንደበቱ። እናትህ ትቃጠል እናትህ እንዲ ትሁን እናትህ..... እናትህ.....የስድብ ውርጂብኝ። የካድኩት ልጅ አለኝ እሱም የማያቀኝ ስድብ የሚያረገኝ አስር ጣት እያለው... ሁለቱን ሦስቱን ካልቆረጥኩ የሚለኝ።

ኢትዮጵያዊ ነኝ! (በእውቀቱ ስዩም) . . ኑሮ ቢገፋኝ የማልወድቅለት፣ እንደ አክሱም ድንጋይ እንደሮሃ አለት፣ የጊዜ ሞገድ ያልነቀነቀኝ፣ የመከራ ዶፍ ያላደቀቀኝ፣ ለሙሾ ሲያጩኝ ቅኔ የምቀኝ፣ በግራ ሲሉኝ የምገኝ በቀኝ፣ ኢትዮጵያዊ ነኝ! ።።።።። ከዋርካ ባጥር ከዕምቧይ ተልቄ፣ ከፀሐይ ባንስም ከኩራዝ ልቄ፣ ከምድረበዳ ጅረት አፍልቄ፣ ጥሜን የምቆርጥ በእፍኝ ጠልቄ፣ ኢትዮጵያዊ ነኝ! ።።።።።። ልክ እንደቻይናው የትም ሳልረባ፣ እንደ እንግሊዙ ሳልሰራ ደባ፣ እንደ አሜሪካው በቁም ሳልሰባ፣ በመጠን ኑሬ አፈር 'ምገባ፣ ኢትዮጵያዊ ነኝ! ግትር ጠላቴን በአጭር አንካሴ፣ ራስምታቴን በዳማከሴ፣ ነቅዬ 'ምጥል፣ አገር በነገር የማብጠለጥል፣ ነገር በነገር የማብጠለጥል ኢትዮጵያዊ ነኝ! ።።።።። እንደመሃረብ ቤቴን በኪሴ፣ እንደንቅሳት ተስፋን በጥርሴ፣ ይዤ የምዞር ከቦታ ቦታ፣ በዘብ በኬላ የማልገታ፣ ኢትዮጵያዊ ነኝ!!!! ።።።።።። ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር። @gitmv

'እንዳያማህ ጥራው' 'እንዳይበላ ግፋው' ይሄ ነው ሀገሬ የሆነው አንቺ ላይ አምላክሽ እስኪፈርድ እስኪመጣ ከላይ።

አለሜን በሙሉ ከአንድ ያሳነሰብኝ ፍቅር ፍቅር ይዞት አንድዬ ባሳየኝ። እናም ..... ሁሌ እኔ ብቻ አንግሱኝ የሚለው እሱንም አንደሱ ከአንድ ባሳነሰው። ወይንሃረግ✍ @gitmv

ግና ጨቅላ ሆነን በልቤ ላይ ሰርፀሽ ህመሜን አታምጭው ባክሽ ልለምንሽ ችየው መስሎኝ እንጅ የደላኝ መሠለሽ ጭራሽ ዝም ብልሽ ሩቅ !!! ሀገር ሄደሽ ታሠቃይኛለሽ፡፡ እስኪ ይሁንልሽ ብቻ ሠላም ሁኝ እግዚኣብሄር ሲፈቅድ አገኝሻለሁኝ እስከማይሽ ድረስ ሰላምሽ ይብዛልኝ አንች ጨክነሻል ላላገኘው ብለሽ ፈጣሪ እቅፍ አርጎ እጀ ላይ ያስገባሽ፡፡ ግን ይህን እወቂ ሁሌ ወድሻለሁ በልጅነት ፍቅሬ ጠባሳ ሆኛለሁ ኤልሳቤጥ✍ @gitmv

ጠብቄህ ነበረ ግንስ አልወሽህም ጠብቄህ ነበረ ስታረፍድጊዜ ለዚያ ነው የቀረ። ዘንጬ ለብሼ ሽቶ ተነስንሼ። ደግሞም .... ፍቅሬ ምነው ቀረህ? ዛሬ ምን ገጠመህ? እያልኩ ጠብቄህ ነበረ አንተ በማርፈድህ ለዚያ ነው የቀረ በሰኮንድ ልዩነት እያየሁ ሰዓቴን የስልክ ጥሪዎች ኮብራ እየመሠሉኝ ልቤ እስክትወጣ እያስደነገጡኝ። እውነቴን ልንገርህ? ጠብቄህ ነበረ ባቡር, ስታረፍድ ጊዜ ልቤ ተሰበረ ለስራ አረፈድኩ 'ቦስም' ተማረረ። ወይንሃረግ✍ @gitmv

መቼ ትመጣለህ ፀሀይ ስትዘቀዝቅ ስታዞረው ፊቷን ጨረቃ ስትስቅ ስናይ ፈገግታዋን ሲከፋኝ ስታመም ስምህን ሳነሳ ስላንተ ሳወጋ ፍቅርህን ሳወሳ አልበላ ሲለኝ ባር ባር ሲለው ሆዴን ንገረኝ መቼ ነው እማየው አይንህን ለሊት አልጋዬ ላይ ሆኜ እንቅልፌ ሲጠፋ መኖር አስጠልቶኝ ልቤ ሲቆርጥ ተስፋ ስልኬን አነሳ እና ፎቶህን አያለሁ ትመጣለህ እያልኩ በርበሩን አያለሁ ከቀጠርከኝ ቦታ ቀድሜ ብደርስም ቆሜ ብጠብቅም አንተ ግን የለህም ትመጣለህ አደል አትቀርም ልጠብቅ ዝናቡ ቢዘንብ ቢወርድብኝ መብረቅ ነይ ካልከኝ ቦታ ላይ ቆሜ አንተን ስጠብቅ ጎርፍ ወስዶ ቢጥለኝ ባካል ካንተ ብርቅ ስቃዩ ቢበዛ ቢከብድም ንፋሱ ሳትስመኝ አልሞትም ከንፈሬን በስሱ ባንተ ሳልታቀፍ ህሜን ሳልነግርህ አትቀርም ልጠብቅ መቼ ትመጣለህ 🤔🤔 @nitsuhti1419

ውድ ቤተሰቦቻችን እንደምን ከረማችሁ፤የዚህ ቻናል ዋንኛ አላማ የጀማሪ ገጣሚያንን የግጥም ስራዎች በይበልጥ መውጣት እንዲችሉ መርዳት ነውና ገጣሚያን በየትኛውም ሰዓት የግጥም ስራዎቻችሁን @Abebekasu እና @mogea ላይ ብትልኩልን የምንቀበል ይሆናል።

ውድ ቤተሰቦቻችን ውድድራችን ቀጥሏል 60 ላይክ ቀድሞ ለደረሰ ተወዳዳሪ የምንሸልም ሲሆን የወደዷቸውን ግጥሞች ላይክ ያድርጉ፤ይሳተፉ።

ለኔ... የድፍን አፍሪካ ኩራት፤የሀያላን ሀገራት ውርደት የመላው ዓለም ውዥምብር ፤የጣሊያን ቅስም ስብራት የጥቁር ህዝቦች መመኪያ፤የአፍሪካ ነጻነት ብስራት ተንቀው ወድቀው ለታዩ፤የዕሳት ትንታግ አለኝታ የ ኢ ት ዮ ጵ ያ ዋርድያ፤የጥቁር ዘር መከታ... ሚኒሊክ ዕኮ ሀገር ነው... ግርማው ከተራራ የገዘፈ፤ወኔው ነጭን የረታ በድፍረት የደነደነ ፤ልቡ የማይፈታ ጨካኝ አትለው እምዬ ፤ ልቡ የሴት ቦርቧራ እኖር ባይ አይደለ ቆራጥ፤ የሚቀበል መከራ ጀግንነት ዕኮ እዳ አለው ፤ ለፈሪ ግን ቀብድ ነው ዛሬ ጀግናነኝ የሚል ፤ ለሀገር ጥሎሽ ብድር ነው ለኔ... ጀግብናዬ እሱ ነው ፤ ስሙን እንደ ዕሾህ ዓለም የፈራው ጀግና የጀግና ጀግና፤ሚኒሊክ የኛ ሀገር ነው። @ s@m! d@n 🇪🇹🇪🇹🙏🙏

*የኔ ጀግና አንተው ነህ* ሀገር ምስቅልቅል ወርሷት የምጥ አመቷ በዝቶባት የመሃል ሀገር ረመጥ ትኩሳትዋን ሽሮላት ቅጥርዋን ከአለት ገንብቶት ስቃይዋን ያሳጠረላት ቴዎድሮስ ነው የቋራው ጀግና ሀዘኗን ያበረደላት የኔ ጀግና አንተው ነህ መቅደላ ላይ ሁነህ የሽጉጥ አረር የጠጣህ በነገስክበት አመታት ለጦቢያ ታትረህ ራስህንው የሰዋህ የጀግና ሞትን ሞተህ ስምክን በደማቅ የፃፍክ። ✍Ab

ሁሉ ለኔ ላይሆነንአንድ እጅ፡ቢፈለግ ጭብጨባው አንድ ጀግና የለኝ ፡ለብቻ ማወሳው ከአፍ በዘለለ አስከመሆን አፈር ጥልቀቱ ባየለ በእውነተኛ ፍቅር ባራቱም መሀዘን የተሰው ነፍሶች ነጋቸውን ለኛ የለገሱ ሰዎች ሁሉም ለኔ ጀግና ፡ሁሉም የኔ ጀግኖች። አዲስአለም አብረሃም

ጀግና አንጀቷን ቢወጋ በሆድ ኑሮ ባን'ዳ ፣ አብሮ ከጠላት የእናት ቤት ሲከዳ ፣ ተነሳ ተቆጣ!፦ ልክ ግብሩን ሊያሳይ ነቅቶ በማለዳ ፤ ነጆ ያበቀለው እትብተ ወለጋ ፣ ምሎ ለኪዳኗ ጎህ ሲገፍ ሲውጋጋ ፣ ተነሳ ማለዳ ጠላቷን ፍለጋ ፤ በማለዳው ነቅቶ ፣ የጠላቱን ዱካ ካለበት አሽትቶ ፣ ኦኔ እያ'ነሳሳ በአጀብ በቀረርቶ ፤ ድል እያደረገ ቢያ'ዝም በጠላት ፣ እኛን ምሰል ቢሉት ቢሰጡት ዜግነት ፣ መሞት የመረጠ ክዶ ለባርነት ፤ እሱ... የማይደራደር ከቶ ባገር ጉዳይ ፣ እትዮጵያን ከፍ አርጎ በሮም አደባባይ ፣ ከፎቅ ያመለጠ በእራፊ ትልታይ ፤ ጀግናው አብዲሳ አጋ !። ከሻምበል ዋቅጋሪ ከ ጅማ 20/08/2014

ማነው ጀግና የሀገርህ? ከሁሉ በላይ ክብር የሚሰጥህ እስኪ ንገረኝ ወገኔ ማን ይሆን ጀግናህ? በህይወት እንድትኖር ጊዜ፣ ጉልበቱን ደግሞም ገንዘቡን የከሰከሰልህ ሀገርህም እንዳትፈርስ ነፍሱን የገበረልህ በፈጠረህ ንገረኝ ማን ይሆን ጀግናህ? እኔ ግን እላለሁ ጀግናዬ ገበሬ አርሶ በጉልበቱ ማዕድ ያቀረበላት ለሀገሬ አርብቶም ያበላን ተዋግቶ ከአውሬ ደግሜ ደግሜ እኔ ግን አላለሁ ጀግናዬ ገበሬ ዋጋው ያልታየለት በቃ እሱ ነው ጀግናዬ ለሀገሩ የሞተላት ዳር ድንበሩአንም ያስከበረላት ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።✍B. T

ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች ውድድራችንን ለማካሄድ አንድ ሰዓት ገደማ ይቀረናል።አሁንም ግጥሞችን መቀበል ስለምንችል @Abebekasu እና @mogea ላኩልን።

ምሽት ላይ ለሚኖረን የግጥም ውድድር አሁንም ግጥሞቻችሁን እየተቀበልን እንገኛለን። ማን ነው ጀግናችሁ?ስንኝ እስኪ ቋጥሩለት፤እንዲሁም ላኩልን።

ውድ ቤተሰቦቻችን ግጥሞቻችሁን ነገ ምሽት 3 ሰዓት ድረስ እየተቀበልን እንቆይና ወደ ውድድሩ እናመራለን። ከዚህ በፊት የነበሩት ህጎች ቀጣይነት ያላቸው ሲሆን ቀድሞ 60 ላይክ የደረሰ ተወዳዳሪ አሸናፊ ሲሆን ሁለተኛ እና ሶስተኛ 60 ላይክ የሚደርሱም ተወዳዳሪዎች በቅደም ተከተል የሚሸለሙ ይሆናል።አሁንም ከላይ በጠቀስነው ሀሳብ የግጥም ስራችሁን @Abebekasu እና @mogea ላይ ላኩልን።