የስንኝ ቋጠሮ
رفتن به کانال در Telegram
የዚህ ቻናል ዋና አላማ የተለያዩ ወጣቶች የግጥም ችሎታቸውን የሚዳብሩበት እና የሚያወጡበት ቻናል ነው። ግጥሞችን ለመላክ @mogea ይጠቀሙ መልሰን ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል!!
نمایش بیشتر2 046
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
2 046
":እናት ሀገሬ :"
ጣጣሽ ይተካ
እንቁ ልበሺ
ማልቀሱ ይብቃሽ
ፍቅርን አንግሺ
ጨለማዉ ይንጋ
እንደ ዘመኑ
ትንሳኤዉ ይምጣ
የደስታሽ ቀኑ
ጣጣሽ ይወገድ
እንቁ ለጣጣሽ እንበል ልጆችሽ
ጦቢያ ሀገሬ
ይንጋ ለሊትሽ
ደምሽ ይታጠብ
ዉስጥሽ ይደሰት እንደ አበቦችሽ
ይፍካ ይደሰት
መላዉ አካልሽ
ዉስጥሽ ይታደስ
እንደ ዘመንሽ
©✍ @tamiru_mosisa
2 046
መቼም የማይረሳን-የዓለማት ጌታ
ልጆቹ ነንና-ማይተወን ቀን ማታ
ካለፈው እድሜ ላይ-ሌላ ዓመት ጨምሮ
ምንም ብንበድለው-በይቅርታ ምሮ
.
.
አዲሱ ዓመት ላይ-ሰናይ ያድርግልን
ዲግሪ ላለው ማስተርስ-ትንሽ ላለው ትልቅ-አብዝቶ ይስጥልን
ስጋት ችግሮችን-ከኢትዮጵያ ምድር-ፈፅሞ ያጥፋልን
.
.
አምና ያየነውን- ችግራቱን ሁሉ
መልካም ይተካቸው-ይረሱ ይጣሉ
ትህትና በርክቶ-ሃዘን እንዲጠፋ-እስኪ አሜን በሉ
2015🌼🌼🌼
✍✍ሮቤል
2 046
ሰላም ውድ የ ስንኝ ቋጠሮ አባሎች እንዴት ቆያችሁ? ዛሬ ማታ ድንቅ የግጥም ውድድር ይኖረናል
ስለሆነም ከታች ያሉ መስፈርቶችን በመከተል እንድትወዳደሩ አሳስባለው!!
👉"አዲስ አመትን በተመለከተ"
👉 ከስምንት እስከ አስር ስንኝ
👉 60 like ቀድሞ የሞላ 25 birr Card ይሸለማል
👉ቀጥሎ ሁለተኛ የወጣ 15 birr Card
👉 ሶስተኛ ላይ 60 like የደረሰ 10 birr Card ይሸለማል
ከ ከአሁን ጀምሮ ግጥሞቻችሁን @abebekasu እና @mogea ላይ ላኩልን
እስከ ምሽት 3:00 ድረስ ግጥሞቻችሁን ላኩልን ልክ ሶስት ሰአት እንደሞላ ግጥም መቀበል እናቆማለን ስለዚህ ተሳተፉ
ግጥም ለመላክ 👉 @mogea @abebekasu ይጠቀሙ!!
የግጥም ችሎታችሁንም አሳድጉ በተጨማሪ ተወዳድራችሁ አሸንፉ ተሸለሙ !! በስንኝ ቋጠሮ ብቻ!
2 046
ውድ አባሎቻችን ረጅም ጊዜ እንደጠፋን እናውቃለን ይቅርታ ይደረግልን እንጠይቃለን። ስለዚህ ታላቁን የግጥም ውድድር ልንጀምር ስላሰብን "ነገ" ምሽት የግጥም ውድድር ይኑር የምትሉ…
2 046
ውድ አባሎቻችን ረጅም ጊዜ እንደጠፋን እናውቃለን ይቅርታ ይደረግልን እንጠይቃለን። ስለዚህ ታላቁን የግጥም ውድድር ልንጀምር ስላሰብን ዛሬ ምሽት የግጥም ውድድር ይኑር የምትሉ…
2 046
ውድ አባሎቻችን ረጅም ጊዜ እንደጠፋን እናውቃለን ይቅርታ ይደረግልን እንጠይቃለን። ስለዚህ ታላቁን የግጥም ውድድር ልንጀምር ስላሰብን ዛሬ ምሽት የግጥም ውድድር ይኑር የምትሉ…
2 046
ክረምት እና ናፍቆት
በክረምት መግቢያ እፈልግሻለሁ
ምን ባስከፋሽ እንኳን ይቅርታን እሻለሁ
እዚህ ያለሁበት ክረምቱ ይረዝማል
ቆፈኑ ብርቱ ነው አንድ ሆኖ ይከብዳል
እዚህ ያለሁበት ውርጩ አያላውስም
ለብቻ ተሁኖ እርምጃ አይሰምርም
እዚህ ያለሁበት ዝናቡ ያይላል
ከንጋት እስከ-ሌት እዬዬን ያቀልጣል
እዚህ ያለሁበት አንቺን መሳይ የታል
እቅፍን አሙቆ ሀሴት መች ያድላል
እዚህ ያለሁበት አንቺስ የታል ያለሽ
በበጋ እኝደራቅሺኝ እንደሸሺኝ ነሽ
እዚህ ያለሁበት ትዝታሽ ብቻ ነው ውል ሲል ሚታየኝ
ከክረምት አብሮ ቆፈናም ያረገኝ
እዚህ ያለሁበት መች እንደሆን እንጃ መጥተሽ ያገኘሁሽ
ትውስታዬን ሁሉ ከክረምቱ ጋራ አጥቦት የረሳሁሽ
በክረምት...
በክረምት ፍቅራችን ጠሃይን ይሆናል
ሙቀት ተጓናፅፎ ከብርሃን ይፈካል
በክረምት ፍቅራችን ከቁር ይዛመዳል
በጠፈጠፍ መሃል ውብ ሙቀት ይወልዳል
በክረምት ፍቅራችን እርጥበት ያረግፋል
ግግር በረዶንም አቅልጦ ያከስማል
በክረምት ለዛሽ እጅግ ይጥመኛል
ከበጋ ከማውቀው እጅግ ያድግብኛል
በክረምት
ተፈጥሮሽ ውበቱ ተአምር ሲያሰኝ
ከቁሩ ገላግሎ ለፀደይ ሲያቆየኝ
ሳልጠግበው ያልፈኛል
አዲስ አመት ከቶ መምጫው እስኪደርስ እንደሁለመናሽ ሀምሌ ይናፍቀኛል።
እናም...
በክረምት አትቀሪ በውርጩ መባቻ
ከብርዱ መግቢያ ላይ ግንቦት መከተቻ
ሀምሌ ላይ አልጣሽ ክረምት ከመበርቻው
ልክ እንደ በፊቱ ልክ እንደ ካችአምናው።
✍Ab
2 046
በክረምት............
በክረምት በብርዱ፥ በናፍቆት ረመጥ፤
በሞኝ አበስብስ ውስጥ፥ ሞኝ ልቤ ሲሰምጥ፤
ከንፋስ ሽውታ፥ከመብረቅ ብልጭታ፤
በሀሣብ ትመጫለሽ፥ እንደ ድንገት ለአፍታ።
በአል እስኪመጣ፥ ዘመን ተቀይሮ፤
በአጥር እስክንዘል፥በጀርባ በጓሮ፤
ደግሞ እስክንጠራ፥ ት/ቤት ቢሮ ፤
እንዴት አድርጎሻል፥በክረምቱ ኑሮ፤
ትዝ አላለሽም ወይ፥የመምህሩ እሮሮ፤
እኔ.............….........
ባይኖረኝም ፍቅር፥ለትምህርቱ ከቶ፤
ቀኑን እጠብቃለሁ፥እስኪነጋ መሽቶ፤
በጋው እስኪመጣ፥ክረምቱን ረቶ፤
እንችን እስኪያሳየኝ፥አምላኬ ራርቶ።
ተፃፈ በ አቅሌስያ ፋንታሁን (@eyulka፣@akli03)
2 046
የብሄ ብርሃን ለኛም በራልን×፪
እያልክ ብሄ በሉ የደብረ ታቦርን ተአምር ስታውጅ
በድምፅክ ብለ'ይ መሆንክን የኔ ወዳጅ
ስትል ብሰማ ክፈት በለው በሩን
እንኳን አደረሳቹ ልትል እንኳን አደረሰክ ብዬ ከፈትኩልህ ልቤን
ለኔም መጥተሃልና ሆነህልኝ ብርሃን
ጅራፋን ስታጮህ ፡ እዚ ቤቶች እያልክ ሰፈር ስታካልል
ፍቅርህን ልታደርስ እኔም ቤት ደርሰሃል
እዚ ማዶ አንድ አብሽ እዛም ማዶ አንድ አብሽ
የዚህ ቤት ጌታ ወርቅ ለባሽ .......................... እያልክ
የቤቶቼን ጌታ አንተ ስታሞግስ ..........እኔን እያማለልክ
በስርቆሽ ጨዋታ በአይን ተግባቦት
በብሄ ሙልሙል በሆያ ሆዬ ዜማ
የፍቅርህን ድርሳን ከልቤ ብታደርስ ልቤን ልታሸፍት
አባዬ እማዬ እህት ወንድሞቼ
መላው ሳይገባቸው ፍቅርን ተቋደስን
ሆያ ሆዬ ብለውን
ሆይሼ ሆይሼ
ልምጣ ወይ ተመልሼ
በአመት አንድ ቀን ብቅ ብትልልን
ተመኘሁ ሁልጊዜ ብሄ አንዲሆን
ተመላልሰክ አንድትመጣ ሆያ ሆዬ እያልክ
ከልቤ ሙዳይ ከቤቴ ደጃፍ እንዳይክ
እንድትመርቅ
አመት አውደአመትን
የብሄ ብርሃንን
የኔና ያንተን ፍቅርን
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ተጻፈ በ
፡ Metadel_Amel
መልካም ብሄ ;)
2 046
❤ አንቺ ጋር ስመጣ ❤
""""""""""""""""""""""""""""""
ዣንጥላም አልሻም.....
ዝናቡን አልፈራ፣ ከቶም አይበግረኝ
ፍቅርሽ አይደለም ወይ...
ከዝናቡ በላይ፣ የሚያረሰርሰኝ።
/ ልጅ_ወርቅነህ..✍️✍️ /
ጆይን/join/
👇👇👇👇
@lij_werkneh_gitm
@lij_werkneh_gitm
2 046
ቀጠሮ በክረምት
ጠዋት ተነስቼ ጀመርኩኝ ዝግጅት
አንድ ቀጠሮ አለኝ መቅረት ማልችልበት
የቀጠሮ ሰዓት ደርሶ እስካገኘው
ጠረኑን አሽትቼ ቀርቤ እስካቅፈው
የልጅነት ፍቅሬን አይኑን እስከማየው
እንዴት እንደ ጓጓው ትርታዬ ያወራል
እጅ እግሬ ታስሮ ውስጤ ግን ቸኩሏል
ንፁ አየር ፍለጋ መስኮቴን ከፍቼ
ሰማዩን አየሁት ሽቅብ በአይኖቼ
መብረቁ ያስፈራል ሰማዩም ጠቋቁሯል
ልክ እንደኔ ስሜት አንዳች ነገር አዝሏል
ሰዓቴን አይቼ ዘጋሁት መስኮቴን
ከቤቴ ልወጣ ጀመርኩ እርምጃዬን
ያጥቁሩ ሰማይ ደመናን ያዘለው
በእኔው ሰዓት ላይ ዝናቡን ለቀቀው
ያሁሉ ህልምና የሁሉ ዝግጅት
የልጅነት ፍቅሬን የማየቱ ጉጉት
በጓርፉ አለፈ አይ ቀጠሮ በክረምት
✍ Noa
2 046
አደራ ለቡሄ
ክረምቱ ዝናቡን ያለልክ ሲያፈሰው
በቤቱ ሲታደም ጉብል አዋቂው ሰው
ናና በፉጨትህ ጥራኝ እወጣለሁ
አረማ ጉልጉሎ ወይ እንጨት ለቀማ
በወጣሁኝ ቁጥር ባንተ ከምታማ
አንተ ብቅብለህ ድምፅን አሰማ
አባባ ሳይሰማ እማማም ሳታየኝ
አንዴ ብቅ ብለህ አይንህን አሳየኝ
ይህ ሁሉ ካልሆነ አንዱም ካልተሳካ
ፎቶህን ስደደው አቅፌው ልተኛ
ይሄም ካልሆነልህ ከጠፋህ መፍትሔ
ያው ነሀሴም አይደል እንዳትቀር ለቡሄ
የምትወደውን ሙልሙሉ ስለምሰራ
እንዳትቀርብኝ አንተ ልጅ አደራ
ሆያ ሆየ እያልክ የመጣህልኝ እለት
አይኖቼ ይበራሉ አገኛለሁ ጉልበት
ሽንሽኔን ለብሼ ደር እና አምባሬን አጌጥበታለሁ
ሆያያ ሆየ እያልክ ና እጠብቅሃለሁ
ቡሄ ምክንያቴ ነው እኔ አንተን ለማየት
ሳላይህ እንዳይልፍ እንዳይልቅ ክረምት
እመጣለሁ
ወንዙን ተራራው ባህሩን አልፌ
ለፍቅራችን ስል ውዴ ተንሰፍስፌ
እኔም ናፍቀሽኛል አይንሽን አያለሁ
ሆያሆየ ብየ እመጣልሻለሁ
አባታሽ ሳያዩኝ ወንድምሽ ሳይገለኝ
ላንቺ የምነግርሽ አንድ መልክት አለኝ
ግን አሁን አይሆንም ያኔ እነግሻለሁ
የኔ አለም ጠብቂኝ ሆ ብየ እመጣለሁ
የጌቶች ጌታየን ፍቃድ ጠይቂያለሁ
ገና ሳትነግሪኝ መንገድ ጀምሪያለሁ
ሆያሆየ ብየ እመጣልሻለሁ
✍ .... @nitsuti1419
