cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

የኦርቶዶክስ መዝሙሮች እና ጥቅሶች (pp)🙏🙏

የ ኦርቶዶክስ ጥቅሶች ብቻ⛪💒💒 እየሱስም። አባት ሆይ፥ የሚያደርጉትን አይውቁምና ይቅር በላቸው አለ። ልብሱንም ተከፋፍለው እጣ ተጣጣሉበት።😭 🙏🙏🙏 የሉቃስ ወንጌ. 23:34

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استزبان مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
Advertising posts
364مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

ወቀሳ ከብዶህ ባቆምስ ብለሀል? በጣም ለፍተህ እየሰራህ ባለህበት ሁኔታ ውስጥ ባለማወቅ ትንሽ ስህተት ብትፈጠርና በሷ ምክንያት ከፍተኛ ወቀሳ ቢደርስብህ ወቀሳው በጣም ያማል አይደል? ምክንያቱም አውቀህ አይደለም ያጠፋኸው ፣ ጥፋቱ በመከናወኑ አንተ ራስህ ከፍቶሀል በዚያ ላይ ደግሞ በጣም ወጥረህ ከልብህ እየሰራህ ነው ስለዚህ መወቀስ አይገባህም አይደል? ግን ሰው ነህና ሁሌ ትክክል አትሆንም ትሳሳታለህ፣ ሰዋች ይናደዱብሀል የደከምክበት ሁሉ ባዶ እንደሆነ አስኪሰማህ ድረስ ትደርሳለህ እነዚህን ሁሉ ነገሮች ልትቆጣጠራቸው አትችልም ስለዚህ ወደምትቆጣጠረው አተኩር ስህተትህ ስላስተማረህ ነገር በልፋትህ ያገኘኸውን ውጤት ጥፋቶችኽን የምታስተካክልበትን ጥበብ ለማስተዋል ሞክር! ለምን እንዲህ ሆነብኝ አይገባኝም እኮ በሚል ጥቅም የለሽ ሀሳብ ጊዜህን አታባክን ወንድሜ አንተ ብቻ አይደለህም አለም ላይ ያለ ሰው በሙሉ ይሄ ነገር ያጋጥመዋል ታድያ ግን ልዩነቱ ሁሉም የሚቀበሉበት መንገድ ነው! መልካም ቀን ተመኘን 🙏 @Inspire_Ethiopia የእናንተው ምርጥ ጓደኛ ☺️
نمایش همه...
نمایش همه...
የዘማሪ አብርሃም ተገኔ/Zemari Abraham Tegene የጉዞ ላይ አስደናቂ ዝማሪዎች ከከተማው ወጣጣቶች ጋር: Timeket/Ketera/ kanazegelila

ዛሬም ሌላ ልዩ ቀን በባሌ ጎባ ጥር 13 ቀን 2014 ዓ.ም የእግዚአብሔር አብን የቃል ኪዳን ታቦት ስናስገባ የነበረውን ልዩ ደስታ ተመልከቱልኝ።በእውነት ገና ትደመማላችሁ እናንተ ብቻ ሰብስክራይብ ላይክና ሼር እያደረጋችሁ መከታተሉን አትዘንጉ።

እንዳሰብነው ባይ ሆን እንኻን እንዳሰበልን አኑሮናል ከዘመን ዘመን አድርሶናል መጪውንም እሱ አብሮን ይሁን 😍 ፈጣሪ 🙇🏽 ይህቺ የጳግሜ ቀናት የይቅርታ እና የምስጋና ቀናት ናቸው ስለሆነም ❣ሳላውቅ በስህተት❤ 💙አውቄ በእህል💔 አስቀይሜ አሳዝኜ አስከፍቼ 💜ከሆነ ከጉልበቴ በርከክ ብዬ💗 💞ይ 💞ቅ 💞ር 💞ታ ጠይቃለው💕 🖤በችግሬ በሃዘኔ ስከፋ ተከፋታችው ሳዝን አዝናችው💘 💖በደስታዬ ተደስታችው ሃሳቤን በመካፈል መፍትሄ ለሰጣችውኝ❣ 💚ስሜታዊ ሆኜም 💙መታግስትን ላስተማራችውኝ💜💗 💖💕💞በዙሪያየ 💓💗💖ያላችው 💙💜❤ሁሉ 💝አ 💝መ 💝ሰ 💝ግ 💝ና 💝ለ 💝ው ❣💝💕💞💓💗 መልካም አዲስ አመት 🌻🌻🌻🌻💐💐💐🌼🌼🌼ላንተ/ቺ ይሁንላችሁ ለጓደኞቻቹ ኣድርሱ እኔም🙋🙌 ከነዛ ውስጥ ከሆንኩ forward ኣድሩጉልኝ😙💕💕💕💕💕💕💕💕💕
نمایش همه...
ታዲያ ለሁሉም ሰው መርሐ ግብር  ይመራሉ። ይህንን ጉባኤ የሚለውን መዝሙር አስመርጠው አብረው ይዘምሩና አሁን ወደ መመህራችን …. እገሌ ብለው ማይክ ይሰጣሉ። (ፕሮግራም መሪ) ይሆናሉ።አንድ ቀን በአጋጣሚ መጣሁ። ማታ አስተምር አሉኝ። በሰዓቱ ተገኘሁ። አላሰብኩትም አባታችን መጡ። ዲያቆኑ ማይክ ፣ ክብ በዳንቴል የተሸፈነች አትሮንስ አወጣ ፡ ጉባኤውን ከፍተው ራሳቸው መዝሙር ዘመሩ እንዳስተምር እሰጠን የቆጡን የባጡን ብዬ ወረድኩ። የእርሳቸው ሥራ መጠቅለል ነው። እንዲህ ብለው ይነሳሉ ..” ግሩም ነው፣ ግሩም ነው ወንድማችን ዛሬ ያስተማረን ብለው…… 10 ደቂቃ ያላልከውን ፣ ያልተከሰተልህን፣ ብለህ ሰምተህ የማትውቀውን፣ ምስጢር ብጥር አድርገው ከልሰው ልክ አንተ እንዳስተማርከው አድርገው “ወንድማችን ያስተማረን ቁም ነገር ይህ ነው” ቃለ ሕይወት ያሰማልን፡ የቅዱስ እስጢፋኖስን ሥራ ነው የሰራው። ብለው ይዘጉታል። ዛሬ ላይ ሳስበው ምንም ሳይነግሩን ለካ ስብከት ዘዴ ነበር የሚስያስተምሩን። ለካ ተተኪ ነበር የሚያፈሩት። ያኔ እሳቸውን አስቀምጠን ስናስተምር ምንም አይመስለንም ነበር። ዛሬ ላይ ውስጤ ገብቶ ያሸማቅቀኛል ትኅትናቸው። ሳስበው ዕንባዬ ይመጣል። የእሳት ልጅ ዐመድ መሆናችንን ሳስብ። በስም እንደ ፎከርን እንኖራለን። ወይ ነዶ። ምንም ይሁን ምን ፍቅራቸው እጥንቱ ያልገባ ትውልደ ባሌያዊ አለ ማለት ግን አልችልም። ይኽንንም እመለስበታለሁ።ጉባኤ ካለቀ ወደ ቤት ሲገቡ በመንገዳቸው ያገኙትን ሁሉ “ና እራት ብላ” ከአንደበታቸው አትለይም፡ “ና ሻይ ጠጣ” በቃ ሰው ይወዳሉ። ሰላማ ካህናትን፣ ዲያቆናትን፣ ሰንበት ተማሪዎችን ብቻ ሳይሆን ሐዋርያ የሚያደርጉት ሴቶችንም ጭምር ነበር። ዛሬ ላይ “እግዚአብሔር ብርሃኔና መድኃኒቴ ነው” የሚል ትምህርት ያስተማረችውን ጡርዬን አልረሳም። ይኽ ያየሁትን ምስክርነት ስለሆነ የጻፍኩት። አፈሯ ላይ ቁጭ ብዬ ተምሬያለሁ። (ጎባዎች ምስክር ናቸው) አቡነ ሰላማ ለወንጌል ካላቸው ፍቅር የተነሳ ከዶዶላ፣ አዳባ፣ ሮቤ፣ ሲናና፣ ጋሰራ፣ ደሎ መና፣ ደሎ ሰብሮ፣ ጃራ፣ ጊኒር፣ ከጎሮ፣ አጋርፋ…… ወጣት መሰብሰብ ነው ሥራቸው።ወንጌል የሚያስተምር ይወዳሉ፤ ክህነት ይሰጣሉ። እኛ ሙት ብንሆን እንኳ ስለ ሃይማኖት እሳት ጭረውብን ሄዱ። አምዬ ተዋሕዶ ብረሳሽ የሰላማ አጽም ይወጋኛል። ሁሌም ሲያስተምሩ “የተዋህዶ ልጅ” ይሉ ነበርና። ++ የሰውን ስህተተን የሚይዙበት (የሚያርሙበት) ጥበብ ይኽ የታሪክ ትውስታ የራሴን ነው። ብዙዎች የየራሳቸው ትዝታ እንዳላቸው አውቃለሁ። በተለይ በቅርበት የነበሩ። በእኔ አካባቢ ተመድቤ ሥሰራ (በልጅነት ሊቀ ካህናትም) ያደረጉኝ እርሳችው ነበሩ። እንኳን ያኔ ዛሬ እንኳ ለምንም የማልበቃውን። በመሠረቱ አባታችን ሐዋርያ እንጅ የአስተዳደር ሰው አልነበሩም። ችግሮችን የሚፈቱበት መንገድ ግን በመንፈሳዊ መንገድ ነው።በተለያዩ ጊዜያት ስለተፈጸሙ ችግሮችና የአቡነ ሰላማ ችግር አፈታትን እንይ፦ በ1984 ዓ.ም ከጊኒር መድኅኔ ዓለም ቤ/ክ ጽላት ይሰወራል(ይጠፋል)። ወቅቱ መንግስት የተቀየረበት ወቅት ነበር። ሁለቱ ቀዳሽ ካህናት በጥርጣሬ ይያዛሉ። እስር ቤት ገቡ። ጉዳዩን ካላሳጠርኩ ብቻውን ሌላ ረጅም ታሪክ ነው። ታቦት “ሰረቁ” ተብለው ታሙ ተያዙ። ካህናቱ በመደበኛ ፍርድ ቤት ሳይሆን በየወቅቱ ሕዝቡ እየተሰበሰበ በሚደረግ ውይይት ወታደሮቹ ይዘዋቸው እየመጡ በዐደባባይ ነበር የሚሞገቱት። በአንድ ወቅት በሕዝብ ፊት ይገደሉ ሁሉ ተብሎ ነበር። እጅግ ያን ቀን ሳስበው ይዘገንነኛል። እጅግ ትንንሾች በመሆናችን የምናውቃቸው ካህናት ሲሞቱ ማየት ከባድ ነበር። ጉዳዩ ወደ አቡነ ሰላማ ሲደርስ ጉዳዩ የሃይማኖት፤ የቤተ ክርስቲያን ስለሆነ እራሴ እመጣለሁ ብለው ወደ እኛ ከተማ ጊኒር ይዘልቃሉ። ሁለት ቀን የፈጀ ውይይት ከከተማው ሽማግሌች ጋር አድርገው አሳማኝ መረጃ ይጠፋል። ከዚያም ካህናቱ ከእስር እንዲፈቱ፣ ቤተሰባቸውን ይምሩ፣ ቅዳሴ እንዳይቀድሱ ብለው ይወስናሉ። በቃ ምንም ማስረጃ ስላልነበረ ተለቀቁ። ሰላማዬ ባይገቡበት ኖሮ ምን ሊሆን እንደሚችል አስቡት። ካህናቱ ሁለቱም እጅግ ጎበዝ ጎበዝ ነበሩ። ካህናቱ በሁኔታው በስነ ልቡና ተጎድተው ስለ ነበረ ወደ ቤተ ክርስቲያን መምጣትን እንቢ አሉ። መድኃኔ ዓለም ካልፈረደልን ወደ ግቢው አንገባም ብለው ቀሩ ቀሩ። ከ 8 -10 ዓመት በኋላ በቦታው ካህናት እጥረት ያጋጥማልና። ሁለት ቤተ ክርስቲያናት ካህን በማጣት ይዘጋል። ጫንጮ ሥላሴ እና ኤቢሳ ባለወልድ። ታዲያ አባታችንን አማከርኳቸው። “ዲ/ን ግሩም ኅሳብ ነው አሉ። እነዚህ ሰዎች እኮ ምንም ማስረጃ ሳይኖር ነው የተሰቃዩት ሕዝብ እንዳይቆጣ ነው እንጂ ከሆነማ ጥሩ ነው” ይሉኛል።ባይሆን ከተማው ላይ ሊከብድ ይችላል። ሕዝብ እንዳይቆጣ ተጠንቀቅ ይላሉ። ሁለቱንም ገጠር የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናት ላይ ሕዝቡም ተስማምቶ ተቀጠሩ። እጅግ ደስ በሚል ፍቅርና ትጋት ሁለቱም ከ 18 ዓመት በላይ አገለገሉ።ዛሬ ላይ አንዱ ካህን በሕይወት የሉም (መምሬ ተሰማ በቅጽል ስማቸው (መብረቁ) የድምጻቸው ማማርና ከሩቅ መሰማቱ ነው ስሙን ያሰጣቸው ። አንዱም አረጋዊ አባ ተክለ ማርያም በእድሜ ብዛት ደክመው ቤት ቢውሉም። ወገኖቼ እስቲ እኛ ብንሆን እንዴት እናልፍ ይሆን? ዛሬ ምንም ሳናይ ሳንሰማ የገደልነው ብዙ አይደል??? ለራሳችሁ አስቡት … ብንማርበት ይበጃል። ++ ሌላው ትዝታዬ፦ በ “ዝሙት” ተያዙ ስለተባሉ አባት ነው ስምና ቦታ ለመጥቀስ ሕግም፣ ሞራልም፣ ክርስትናም ይከለክላል። ገመና ድራማ እንጂ ገመና በፌስቡክ አይሰለቅም (የማይቀየር አቋሜ ነው)። ወደ ጉዳዬ ልሂድ፦መነኩሴው ድቀት እገኛቸው ተብሎ ሐሜት ተሰማች። ወሬዋ ተናፈሰች፣ ተራገበች፣ ቡና መጠጫ ሆነች። ጉዳዩ ሰላማ ጆሮ ገባች። ጉዳዩ ጠንከር እያለ መጣ። ማስረጃ አምጡ ቢባል። እገሌ እገሊት ብቻ መባባል ሆነ። እርሳቸውም መነኩሴውን ጠርተው “አባታችን ጉዳዩ ምንድን ነው የምሰማው” ብለው ይጠይቃሉ። የተነጋገሩትን አላውቅም። በማግስቱ “አባታችን ልብን እና ኩላሊትን የሚፈትን እግዚአብሔር ብቻ ነው። ሕዝብ ካልወደደ መሰናከያ ነው የሚሆነው። ለርስዎም በረከት አይሆንም። የቅዱሳን አምላክ ይከተልዎ። እንዳይራቡ እንዳይጠሙ እኔ የትራንስፖርት እሰጥዎታለሁ። ለእረፍትም እንዲሆንዎ ገዳም ይሂዱ መቼስ መነኩሴ ሌላ ቤት የለውም። እኔስ ማነኝ የምፈርደው” በማለት ሸኟቸው።መነኩሴው በኋላ ላይ ለብፁእነታቸው ጃንደረባ እንደሆኑ ነግረዋቸዋል የሚል ወሬ ሰምቻለሁ። ሰላማን የሚያህል ከባቴ አበሳ አላየሁም። በተለይ ካህንን የሚይዙበት ጥበብ። ++ሁለት አስቂኝ ገጠመኞቼን ላውጋችሁ         ከካህናትን ማሰልጠኛ እንደተመለስኩ ትምህርተ አበ ነፍስ ስልጠና ሰጠሁና ሪፖርት አቀረብኩ “አባታችን ካህናቱን አሰለጠንኩ አስተማርኩ” አልኳቸው እርሳቸውም ምን አልካቸው? አሉኝ ቀለል አድርገው። ድርሻቸው ምን እንደሆነ፣ ምን እንደሚያስነቅፍ፣ ካሕናቱ በምን እየተተቸን እንዳለን፣ ጠበል ሲረጩ አብረው ወንጌል እንዲያስተምሩና፣ መስበክ እንዲያውቁ ነገርኳቸው ስላቸው በአንድ ቃል ” ካናትን እመኑ እንጂ እወቁ አትበላቸው ካልሆነ ይናደዱብሐል አንተ ልጅ ስለሆንክ ” አሉኝ። እንተ የምትለውን አኮ ያውቁታል የካህናት ችግር የሚያውቁትን አምነው አይተገብሩም አሉኝ። እርፍ አልኩት። ይሕው በዚህ ቃል እራሴው ስሟገት እኖራለሁ። የማውቀውን ለማመን በመጣር ውስጥ። “የምታውቀውን እመነው፤ ካመንከው ታደርገዋለህና። ያወከውን ካላደረከው አላመንክም ማለት ነው”
نمایش همه...
++መጨራሻ አካባቢ አንድ ሸምገል ያሉ የቀድሞ ሰራዊት ወታደር የነበሩ ሰው ሹፌር ነበሯቸው። በጣም ቀልጣፋ ናቸው። በጣም ታዛዥ ናቸው። እሺ አባታችን ብሎ መታዘዝ ብቻ ነው የሚያውቁት። ጠዋት ቀድመው መጥተው መኪና አዘጋጅተው ይጠብቃሉ። መቋሚያ ተቀብለው ቦታ ያመቻቻሉ። አንድ ቀን ጠዋት ላይ ወደ አዲስ አበባ ልንሸኝ ቆመናል። የሰውየውን መዘጋጀት አይተው። ሊሸኙ ለተሰበሰቡትን ካህናት “አንድ ካህን ከመምራት መቶ ወታደር መምራት ይቀላል” አሉ። ካህናቱ ሳቁ። አይደል እንዴ አባቶች አሉ። ካህናቱም በራሳቸው አዝነው አዎን አባታችን ትክክል ነው አሉ። ሰላማ ማብራሪያ ጨመሩበት ቆም ብለው። ወታደር ወደፊት ሲባል ወደፊት ነው። ተቀመጥ ሲባል ተቀመጥ ነው፤ ሩጥ ሲባል ሩጥ ነው። እኛኮ ስንታዘዝ እንደ ግመል ሽንት ግራ ነን። ብለው በር ዘጉ። ታዲያ ይህ አይነት ተግሳጽ እንዴት ከአዕምሮ ይጠፋል። ሁሌም የሚገርመኝ አባባል ይናገራሉ “አንድ ተራ መነኩሴ ነኝ አኮ” ሰላማን የሚያህል ተጫዋችም አላየሁም። ትልቅ፤ ትንሽ፣ ተማረ፣ አልተማረ የለም ከኔቢጤው ጋር ቆመው ነው የሚያወሩት። እንደ ዮሐንስ አፈወርቅ የድሃ ጠበቃ ነበሩ። ጊንር ላይ ሲያስተምሩ “እግዚአብሔር በሐብታም አድሮ ይሰጣል፤ በደሃ አድሮ ይቀበላል” “ለድሆች መመጽወት በሰማይ ቤት ባንክ መክፈት ነው” ብለው አስተማሩን። ዛሬ ላይ የድሆች መርጃ ማኅበር በሰንበት ትምህርት ቤቱ ከተቋቋመ 218 ዓመቱን አስቆጥሯል። ++ሰላማና ንባብ አቡነ ሰላማን እኔ ለማየት እንደታደልኩት ትልቁ መጽሐፏቸው አዘውትረው የሚመረምሩት መጽሐፍ ቅዱስ እና ሃይማኖተ አበው ነው። ምንም ቢሆን ለንባብ አይቦዝኑም። ++ሰላማና መታሰቢያቸው * መታሰቢያ አንድ ብፁዕነታቸው ብዙ ወዳጅ እንዳላቸው አውቃለሁ። መታሰቢያም ለማድረግ ብዙ የተጣረ ይመስለኛል። በተለይም ባቋቋሙት ገዳም አካባቢ። ወደ ገዳሙ ከሔድኩ ከ 14 ዓመት በላይ ስለሆነኝ ምንም መረጃ የለኝም። ከዚህ ጽሑፍ በኋላ የማገኝ ከሆነ እጠብቃለሁ። ነገር ግን እጅግ ደስ የሚለኝ ቆራጥ መንፈሰ ጠንካራ ትጉህ ባህታዊ፣ ገዳማዊው አባት ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የደብረ ሊባኖሱ መናኝ። ዛሬ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ናቸው። ወደ ሀገረ ስብከቱ እንደመጡ ምንም የልማት ሥራ እንዳልተሰራ ሲያዩ በማዘናቸው ለመስራት ወጠኑ። እኔም እንደተመደቡ ቡራኬ ልቀበል ቤታቸው ስሄድ መስራት እንደሚፈልጉ ነገሩኝ። ደስ አለኝ እኛም እናስተባብራለን አልኳቸው። በቃ የሰላማን ልጆች ያዙ። ከአቡነ ባስልዮስ ጀምሮ ምንም ያልተለወጠውን ያረጀ መንበረ ጵጵስና ለመስራት አሰቡ። በተለይም ታላላቆቹ አባቶች የኖሩበት ቤት እንዲህ ሆኖ ማየት አልሻም በማለት ቁጭት ፈጠሩ። ጎባ ላይ የቢሮ ሰራተኛውን አዘጋጁ። ሥራ አስኪያጁን ሊቀ ስዮማን ንጋቱ ዘውዴ፣ ቀሲስ ፍቃዱ ለገሰ፣ መ/ር ወጋየሁን በተርታ አሰለፉ… (ሁሉም የሰላማ ልጆች የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ምሩቃን ናቸው ፣የሀገረ ስብከቱ ሰራተኞች ናቸው)። ወደ ወረዳ ዘመቱ፣ አዲስ አበባ ሊቀ ትጉሃን ኃይለ ጊዮርጊስ ዳኜ፣ እኔ አሰተባባሪ ሆንን። ሰላማ መታሰቢያ መንበረ ጵጵስና ተገነባላቸው። የሰላማ መታሰቢያ ክፍል ይሰየማል። ያገለገሉበት ንዋያተ ቅድሳት፣ ልብስ፣ መስቀል ይቀመጣል። አሁን ሥራው ተጠናቋል። አቡነ ዮሴፍ የስራ አባት ናቸው። ሁለቱም የደብረ ሊባኖስ ፍሬ ናቸው። (ባሌ ጎባ) * መታሰቢያ ሁለት ሁሌም ለአቡነ ሰላማ መታሰቢያ አመታዊ ጉባኤ በጎባ መድኅኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ይደረጋል። ይዘከራሉ። ደስ ሲል። ዘንድሮ በኮቪድ ምክንያት የሚኖር አይመስለኝም። * መታሰቢያ ሦስት የጎባ መድኅኔ ዓለም ሰንበት ትምህርት ቤት እጅግ ዘመናዊና ትልቅ የስብከተ ወንጌል አዳራሽ አሰርቷል። ይህ የስብከተ ወንጌልም መታሰቢያነቱ ለአቡነ ሰላማ ነው። *መታሰቢያ አራት በእረፍታቸው ዕለት አዲስ አበባ ያሉ ልጆቻቸው በቦታው እንደሚሄዱና እንደሚዘክሯቸው አውቃለሁ። ዘንድሮን ባላውቅም። በቀጣይ ጽሑፍ ሰላማና የሕመማቸው ወቅት፣ ሞትና ቀብራቸው በተለይም ከአቡነ ጳውሎስ ጋር የነበራቻው ጉዳይን እንዳስሳለን። በረከታቸው አይለየን!!!
نمایش همه...
ብጹዕ አቡነ ሰላማ ዘባሌ በረከታቸው አይለየን!!!
نمایش همه...
"እነዚህ ሁሉ አምነው ሞቱ" ዕብ 11:13 ዛሬ ማለዳ ወደ ፌስ ቡክ መንደር ጎራ ስል መጀመሪያ ያየሁት የወንድሜን የመምህሬን የትጉሁን አገልጋይ የመጋቤ ሐዲስ አስራት አያንሳ ዜና እረፍትን ነበር። በእውነት ካለው የአገልግሎት ፍቅር ከነበረው ትጋት በተለይ ክፍለ ሀገር ላይ ከከተማ እስከ ገጠሪቱ አንዲት ቤተክርስቲያን የነበረው ወንጌልን ለሕዝብ ሁሉ የማድረስን ተልዕኮ ስለማውቅ ቤተክርስቲያን ድምጿ ሚሰማበት ወንጌልን የምታዳርስበት አንዱንና ምርጡን የክርስቶስ አገልጋይ ማጣቷን ስረዳ አዘንኩ። ሆኖም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ አምነውና አገልግለው ስላለፉት ቅዱሳን ምስክርነት በሰጠበት ኃይለ ቃል "እነዚህ ሁሉ አምነው ሞቱ" ያለውን እያሰብኩ ተጽናናው። ወንድሜ አስራት እንዳመነ : ክርስቶስን እንደገለጠ : እንዳገለገለ ሞተ!!! ምን መታደል ነው እንዳመኑ እንዳገለገሉ መሞት??? እንዴ እየሰረቁም መሞት እየገደሉም መሞት እንደካዱም መሞት አለ እኮ ጎበዝ! ስንቱ ከነኃጢአቱ ከነበደሉ ሊሞት ወረፋ እየተጠባበቀ ይሆን? ስንቱ እንደካደ ሊሞት ተራውን እየጠበቀ ይሆን? ቸሩ መድኃኔዓለም የወንድሜንስ ሞት ተመኘሁት ለንስሐ ሞት በቅቼ እንዳመንኩህ እያገለገልኩህ እየሰበኩህ ልሙት!!! ነፍስ ይማርልን! ለቤተሰቦቹና ለወዳጆቹ ሁሉ መጽናናትን ተመኘሁ! ለቤተክርስቲያንም ተተኪዎችን ያብዛልሽ አልሁ!!! ዲያቆን መሰለ ሞላ ከባሌ ጎባ
نمایش همه...
ስለነበሩበት ገዳም ሲናገሩ ማኅበረ ሥላሴ ጥሬ በጸሐይ የሚበስልበት፡ የእንስሳ እንስት ፆታ እንኳ የማይገባበት፡ ላሞችና አንበሶች አብረው የሚኖሩበት ነው ራሳቸው ሲሉ ሰምቻለው።አቡነ ሰላማን የተከተሏቸው ብዙ መናንያን አሉ። በዚያ ጊዜ እርሳቸው በመሰረቱት ጎለ ብሕንሳ ገዳም ውስጥ የመነኮሱ ወጣንያን ዛሬ ብርቱ ብርቱ ዐሠረ ፍኖታቸውን የተከተሉ አባቶች (መነኮሳት) አሏቸው። በግሩም መምህርነታቸው የሚመስሏቸውንም አባቶችም ለማየት እድሉን አግኝቻለሁ (አባ ጌዴዎንን ) ። የመሰሉ አባቶችን። አሁን ሲያትል ያሉ አባት። ቦታውን ገዳሙን ለመርዳት የምትሹ አዲስ ቤተ ክርስቲያን እየተሰራ በመሆኑ ልታግዙ ትችላላችሁ። ሰላማ በሕይወት ዐሠረ  ፍሎታቸውን የተከተሉ ብዙ ልጆቸ አሏቸው። አክብረው ያስከበሩ። ፍጻሜያቸውን ያሳምርልን። አብዝተው መነኩሴ ይወዱ ነበር። አንድ ወቅት እጅግ ተቆጪ ተማቺ መነኩሴ ሥራ አስኪያጅ ነበራቸው(አባ ገብረ ሥላሴ) ። ከወረዳ ለሥራ ስመጣ ብፁዕነታቸው ቢሮአቸው ተቀምጬ ሳለ አንድ አባት ገብተው አባ ገብረ ሥላሴ (ሥራ አስኪያጁን) ባናግራቸው ሰዳቡኝ ውጣ ከፊቴ ዞር በል ከዚህ ብለው አባራሩኝ ብለው ለሰላማ ሲነግሯቸው አንገታቸውን አቀርቅረው “አይ እንደው አመክሮ ያልነካው ምንኩስና ይኽው እኮ ነው ችግሩ” ሲሉ ሰማኋቸው። ++ ትምህርታቸው ሰላማ እጅግ የሚያስገርም ስጦታቸው የማስተማር ዘያቸው እና ለማስተማር ያላቸው ፍቅር ነው። የመጀመሪያው አንድም ሁለትም ሰው ይኑር ያስተምራሉ። የሰው መሰብሰብ መብዛት ማነስ ጉዳያቸው አይደለም። ጠዋት በአዘቦት ኪዳን ላይ መጥተው ወንጌል ያስተምራሉ። ጎባ መድኅኔ ዓለም ጠዋት ከኪዳን በኋላ አጠር ያለ ትምህርት ይሰጣል። በዓል ሆኖ ለኪዳን ከመጡ ያስተምራሉ። ከጊኒር ስመጣ እንዳደረሰኝ እሳተፋለሁ። ርዕስ እዚያው መድረክ ላይ የሚሰጡ ይመስለኛል። አንድ ቀን በኪዳን ሰዓት ዕለቱ ሐሙስ ነበር ታድያ “ሐሙስ የቀን ቅዱስ” የሚለውን ትምሕርት ያስተማሩትን ከ 18 ዓመት በኋላ ዛሬም አስታውሳለሁ።       + ሁለተኛው አይረሴነቱ በዚህች ሚጢጢዮ ጽሑፌ ላይ ያስተዋልኩት አስተያያየት እንኳ ሰው ትምህርቱን ምክሩን አለመርሳቱ ነው። በቃ የሰላማ ትምህርት አይረሳም። ዘልቆ የሚገባ ዝናም ነው። ታዲያ ያለ መንፈስ ቅዱስ ስጦታ ይኽ እንዴት ይሆናል። “አንተ ልጅ” የሁል ጊዜ ጥሪያቸው ናት። ዛሬ ከደቂቃ በፊት የተጣሩ እስኪመስል ድረስ ይሰማኛል። ድምጻቸው ልዩ በመሆኑ ፍንትው ብሎ ይሰማል። ትምህርታቸው በየትኛውም ዘመን ቢሆን ማስታወሻ ሳይያዝ እንኳ ከነድምጻቸው፣ ከነ ሰውነት እንቅስቃሴያቸው፣ ከነፈገግታቸው ምንም አይጠፋም። አይረሴ ነው። ሙቀት ፈጥሮ አስቆ የሚያልፍ ትምህርት የለም።   የሚያወጡት ቃላት ጥንካሬው በአንድ ወቅት የጎባ መድኅኔ ዓለም ሰንበት ትምህርት ቤት ዓመታዊ መጽሔት ላይ ይህንን ቃል ተጠይቀው ነበር። እነዚህን እያስተማሩ የሚናገሯቸው ንግግሮቸ ከየት ነው የሚያመጡት ተብለው። ዛሬ ሼክስፒር፣ ፕላቶ፣ አርስቶትል፣ አብርሃም ሊንከን …..ተናገሯቸው የምንለው ቃላት ይልቅ ሰላማ በትምህርታቸው ውስጥ እንደ ውሃ ያዝጎደጎዱታል።ንግግራቸው ሁሉ ልዩ ቃል አለው። ሰምተህ የምትሄደው ሳይሆን ተሸክመህ የምትኖረው ነው። በጎባ ተክለ ሃይማኖት ገዳሙ የታተመውን ታሪካቸውን የያዘ መጽሔት ፈልጎ ማንበበ ይሻላል በአጭሩ። +                                                በሁሉም ሰው ልክ ማስተማራቸው ሰላማ የሁሉንም ሰው ልክ ያውቁታል። ሕጻናት ሰንበት ትምህርት ቤት ገብተው ያስተምራሉ አምስቱ አዕማደ ሚስጢርን በ 30 ደቂቃ ሳይሞላ ያስተማሩንን ሳስብ ግርም እሰኛለሁ። በጥያቄ ይጀምራሉ እያሳሳቁ ቁም ነገሯን ይግታሉ። ለምሳሌ። ጥምቀት ማለት ምን ማለት ነው? ለምን እንጠመቃለን? ባንጠመቅ ምን እንሆናለን? ማነው ተጠመቁ ያለን? ለምን እንቆርባለን? ባልቆርብ ምን እንሆናለን? በፍጹም የማይረሳ ትልቅ መነሻ ማዕዘን ነው የሚመሰርቱት። ከዚያ በኋላ ምንም ብትማር ያንንው ነው የምታስፋፋው።   + የትምህርቱ ስሜት ሰላማ በትምህርት የሚያስለቅሱት ተናግረው ሳይሆን አልቅሰው ነው። ትዝታዬን ላጋራችሁ። ወርኅ ታኃሳስ ዓመተ ምሕረቱን እርግጠኛ አልሆንኩም በ90-92 ዓ.ም ይሆናል። እንዳንድ ሰዎች የይቀየሩልን ፊርማ ያሰባስባሉ። ቅዳሴ አልቆ ማስተማር ጀመሩ። የሳምንቱ መዝሙር “ብርሃን” ነበር። በትምህርት መካከል “የብርሃን ልጆች በጨለማ አይፈራረሙም፣ አያድሙም፣ አውቃለሁ ምንም እንዳልሰራሁ ለምን በዓት አጸና ነው የምትሉት? ለመነኩሴ ደግሞ ሥራው አጽንኦ በዓት ነው። ግድ የለም በፊርማ መቀየር ቢቻል እኔም ከናንተ ጋር ብፈርም ደስ ባለኝ ነበር”….. ሲሉ። ያ ሁሉ ቤተክርስቲያኒቱን የሞላው ሕዝብ በአንድነት ዕንባውን አረገፈው። ሰላማን የሚሰማ ሰው የሚያሳዝን ነገር የሚገልጡት በንግግር ቅላጼ በመሆኑ ሳታውቁት ታለቅሳላችሁ። ደስታም ከሆነ ገና ጥርሳቸውን ፍልቅ ሲያደርጉ ውስጥህ ይገባሉ። እንደ ማዕበል ወደ ሰማይም ወደ ምድርም ትጓዛለህ።ልባችን ድረስም በቁም ነገር ዓይን እንዳፈጠጠ ቅንድብ ሳይርገበገብ ትኩረት ይይዛሉ። ልብን በቁም ነገር ቀጥ ያደርጋሉ። በአንድ ወቅት መድኅኔ ዓለም በሠራተኛ ጉባኤ ላይ ሲያስተምሩ ከጀርመን እንደተመለሱ፦ የሀገራችንን ገበሬና የአውሮፓን ሰው ሲያነጻጽሩ “ የሀገራችን ገበሬ በጾም አንጀቱ በጠዋት ጠምዶ ሲያርስ ውሎ ማታ ይገባል። ፈረንጅ በጠዋት አንድ ቁና ዳቦ ጎርሶ ረፋዱ ላይ ያፋሽካል ” ይኽ ምን መሰላችሁ። ሀገሪቱ የረድኤት ናት፤ ሕዝቡ ሃይማኖተኛ ነዋ” ይሉ ነበር። ሮቤ መምህራን ማሰልጠኛ ላይም “ይኽንን አንዣቦ ቀላልቶ የመጣውን የአውሮፓ የክሕደት ደመና፤ በሃይማኖት ነፋስ ሰይፍ እያሳደድክ እየበተንክ እየበተንክ ወደ መጣበት መልሰው” እያሉ ሰንበት ተማሪውን ወጣቱን ቁጭት ይፈጥሩበት ነበር። አቤት ጥበብ። ጊኒር ለመጀመሪያ ጊዜ በ1985ዓ.ም. ወጣቶች በዝተው ሌሊቱን ሙሉ በቀድሞ ሰንበቴ ቤት አዳራሻችን ውስጥ ሲያስተምሩ ያደሩ ቀን እንዲህ አሉ፦”ከዚህ በፊት ስመጣ አዚህ ቦታ ማንቆርቆሪያ እና ኩባያ ጠላ እየተቀዳባቸው ቂጭል ቂጭል ይሉ ነበር፤ ዛሬ ደግሞ የተዋሕዶ ወጣት ሞልቶት ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እያለ ሲዘምር ማየቴ በእውነት እጅግ ደስ ያሰኛል” ታዲያ በዚያ ሌሊት ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ የሚለው መዝሙር እጅግ ለበርካታ ደቂቃዎች ያለማቋረጥ ተዘመረ። ++ መምህራንን፡ ሰባክያንን የሚያሰለጥኑበት መንገድ በእሳቸው ምኞት ሰንበት ተማሪ ሁሉ መምህር እንዲሆን ነው የሚሰሩት። ሁሌም ሰንበት ትምህርት ቤት መርሐ ግብር  ላይ ይሳተፋሉ። ሊያስተምሩ እንዳይመስላችሁ። እርሳቸው ተቀምጠው የተመደበው መምህር ያስተምራል። ያያሉ። ዓይናቸውን በጣታቸውን መካከል አድርገው በትኩረት ያያሉ። በሚያስቀው ይስቃሉ። አሜን ሲያሰኝ አሜን ይላሉ። በቃ በደንብ ይሰሙሃል። ሲሰሙህ በራሱ ይፈውሱሀል። ሲያልቅ ያሳርጋሉ ምክራቸውን ይሰጣሉ። ማስታኮት (የማት ጉባኤ) ይመጣሉ። መምህሩ ሲያስተምር ቁጭ ብለው ይሰማሉ። መምህር ስላችሁ የደብሩ አልያ ከአካባቢው ካህን፣ዲያቆን፣ አልያ ሰንበት ተማሪ ሊሆን ይችላል። የዛሬን የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅን ጨምሮ በጃቸው ያደጉ መምህራን ናቸው።
نمایش همه...