fa
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

رفتن به کانال در Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

کانال Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 381 مشترک است و جایگاه 5 584 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 199 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 381 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 03 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 21 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -7 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 21.13% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 9.50% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 250 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 462 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 16 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 04 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

15 381
مشترکین
-724 ساعت
+117 روز
+2130 روز
آرشیو پست ها
ሚያዝያ 7 ፤ ከአያቶች ሁሉ የሚልጠው ፤ የጌታችን አያት የሆነው የቅዱስ ኢያቄም ዕረፍት:: ቅዱስ አባታችን ኢያቄም በሌላ ስሙ ዮናኮር ተብሎ ይጠራል ሳዶቅም ይባላል፡፡ ትውልዱ ከነገረ ይሁዳ ከቤተ ዳዊት ነው ፡፡ አባቱ ቅስራ ይባላል ፡፡ ከነገደ ሌዊ የሆነች ቅድስት ሐናን አግብቶ በይሁዳ ከተማ ይኖር ነበር፡፡እጅግ ባለጸጋም ነበሩ ነገር ግን ቅድስት እናታችን ሐና ዕፁተ ማኀፀን ሆና፤ ልጅ አጥቶ ልክ እንደ ሐና አያቶች ብዙ ዘመን ሲያዝን ኖሯል፡፡/ፍ.ሕ.ሰ.ት.ቤት/ ለፈጣሪም ከተሳሉ ቦኃላ ፤ ሃዘኑን አይቶ ሙቀትም ከተለየው በኃላ በሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ብሥራት ፤ እመቤታቻንን ሰጥቶታል፡፡ እመቤታችን ማርያም በተወለደች ጊዜ፤ ታድሶ እንደሠላሳ ዓመት ጎልማሳ ሆኖ ሕማም እና ድካም ሳይሰማው ኖሮ ሚያዝያ 7 ዐርፉል ፡፡ ዕረፍቱም እመቤታችን ድንግል ማርያም በቤተ መቅድስ እያለች ነው፡፡ #ድንግል_ማርያም ከእናቶች ሁሉ እንደምትበልጥ ቅዱስ #ኢያቄም እና ቅድስት #ሐና በምድር ላያ ካሉ አያቶች ይበልጣሉ፤ የአምላካችን #የክርሰቶስ_አያቶች ናቸውና ፡፡ ምልጃቸው አይለየን! /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ #በዓሉ ከሚከብሩባቸው ቦታዎች መካካል 1. #ኮተቤ መካነ ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና ቤ.ክ :: የምታውቋቸው ካሉ ይጻፉልን! /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ #share Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem Finotehiwotsundayschool.com

የቅዱስ ያሬድ ልደትና የስሙ ትርጓሜ ꔰ ኢትዮጵያዊው ቅዱስ ያሬድ #ሚያዚያ 5 ቀን በ505 ዓ.ም. ከአባቱ ይስሐቅ(አብድዩ) ከእናቱ ክርስቲና (ታውክልያ) በአኵሱም ከተማ ተወለደ፡፡ (አንዳንዶች ልደቱ
የቅዱስ ያሬድ ልደትና የስሙ ትርጓሜ ꔰ ኢትዮጵያዊው ቅዱስ ያሬድ #ሚያዚያ 5 ቀን በ505 ዓ.ም. ከአባቱ ይስሐቅ(አብድዩ) ከእናቱ ክርስቲና (ታውክልያ) በአኵሱም ከተማ ተወለደ፡፡ (አንዳንዶች ልደቱን 493 ዓ.ም. ነው ይላሉ፤ እንዲሁም አባቱ ኖኅ ነው ይሉና መሪጌታ ይስሐቅ የቀለም አባቱ /መምህሩ/ ነው ይላሉ፡፡) ꔰ የስሙም ትርጓሜም ያሬድ ማለት #እንዚራ፣ በገና፣ መሰንቆ ማለት ነው ፡፡ እነዚህ መሣሪያዎች በስልት በስልት ሲመቱ ለሚሰማቸው ደስ እንዲያሰኙ የያሬድም ዜማ በንጉሠ ነገሥቱ ክርስቶስ አደባባይ በቤተ ክርስቲያን ሲሰማ መላእክትን፥ ሰውንና እንስሳትን ደስ ያሰኛልና፡፡ አንድም ያሬድ ርደት፣ ወሪድ፤ መውረድ ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ያሬድ ሰማያዊውን ልዩ ጣዕመ ዜማ ወደ #ኢትዮጵያ አውርዷልና፡፡ / ፍኖተ ሕይወት ሰ. ት. ቤት/ * አንድም ያሬድ ማለት ንብ ማለት ነው፤ ንብ የማይቀስመው አበባ እንደሌለ ሁሉ ቅዱስ ያሬድም ከመጻሕፍት የማይጠቅሰው የማይቀሰመው የለም፤ አንድም ያሬድ ማለት ረአዬ ምሥጢር፥ ነጻሬ ኅቡአት ማለት ነው፤ የመላእክት ምሥጢራት የነበሩትን ጸዋትወ ዜማ አምልቶ አስፍቶ ተናግሯልና፣ ነጻሬ ኅቡአት አለ፥ ኅቡእ (ስውር) የሆነ የጻድቃን፣ የሰማዕታት የነቢያት የሐዋርያትን ገድል አምልቶ አስፍቶም ይናገራልና፡፡ * አፄ ካሌብ ቤተ እስራኤል፣ ገብረክርስቶስና ገብረ መስቀል የሚባሉ ልጆች ነበሩት፤ ቅዱስ ያሬድ የተነሳው ከእነዚህ ውስጥ በአፄ #ገብረመስቀል ዘመን ነው፡፡ #ጥቆማ በቅርቡ በሊቀ ማእምራን አባይ አጥሌ ለንባብ በተሰራጨው ‹‹ቅዱስ ያሬድ በዓለም መድረክ›› የሚለውን መጽሐፍ ያንብቡ ፡፡ /የቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት/ ከልደቱ ረድኤት፣ በረከትን ያሳትፈን፡፡

#ስድስተኛው_ሳምንት ገብርኄር ይባላል፡፡ ገብርኄር ማለት ታማኝ አገልጋይ ማለት ነው፡፡ በዚህ ሳምንት ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለኄር (ስለታማኝ) አገልጋይ ያስተማረው ትምህርት ይነገራል ፡፡ ይኸውም ማቴ 25፥14-30 ላይ ይገኛል፡፡ (ይህም ክፍል ጌታችን በማቴዎስ ወንጌል በምሳሌ ካስተማራቸው ትምህርቶች አንዱ ነው)፡፡ ወደ ሌላ አገር የሚሄድ ሰው ባሮቹን ጠርቶ ያለውን ገንዘብ እንደ ሰጣቸው እንዲሁ ይሆናልና፤ ለእያንዳንዱ እንደ ዐቅሙ፡ ለአንዱ #አምስት መክሊት፥ ለአንዱ #ሁለት፥ ለአንዱም #አንድ ሰጠና ወደ ሌላ አገር ወዲያው ሄደ፡፡ መክሊት የወርቅ መለኪያ (መስፈሪያ) ነው፡፡ #፭ት መክሊትም የተቀበለው ሄዶ ነገደበት ሌላም ፭ት አተረፈ፡፡ እንዲሁም #፪ት የተቀበለው ሌላ ፪ት አተረፈ ፡፡ #፩ድ የተቀበለው ግን ሄዶ ምድርን ቆፈረና የጌታውን ገንዘብ ቀበረ፡፡ ከብዙ ዘመንም በኋላ የእነዚያ ባሮች ጌታ መጣና ተቈጣጠራቸው፡፡ #፭ት መክሊት የተቀበለውም ቀረበና፤ ‹‹ጌታ ሆይ ፭ት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ ሌላ ፭ት መክሊት አተረፍሁበት›› አለ፡፡ ጌታውም፦ ‹‹መልካም አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ (ገብር ኄር)፤ በጥቂቱ ታምነሃል በቡዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ፡፡›› አለው፡፡ #፪ት መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፡፡ ‹‹ጌታ ሆይ ፪ት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ ሌላ ፪ት መክሊት አተረፍሁበት፡፡›› አለ፡፡ ጌታውም፡፡ መልካም፡ ‹‹ አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ (ገብር ምዕመን) በጥቂቱ ታምነሃልና በብዙ እሾምሃለሁ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው፡፡ #፩ድ መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፡፡ ‹‹ጌታ ሆይ ካልዘራህባት የምታጭድ፥ ካልበተንህበትም የምትሰበስብ፥ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ፤ ሌቦች እንዳይሠርቁኝ አታላዮች እንዳይቀሙኝ፤ ሄጄም መክሊትህን በምድር ቀበርሁት፤ መክሊትህ እነሆ›› አለው፡፡ ጌታውም መልሶ እንዲህ አለው፡- ‹‹አንተ ክፋና ሃኬተኛ ባሪያ (#ገብር_ሀካይ) ካልዘራሁበት እንደማጭድ ፥ ካልበተንሁበትም እንድሰበስብ ታውቃለህን? ስለዚህ ገንዘቤን ለለዋጮች አደራ ልትሰጠው በተገባህ ነበር፤ እኔም መጥቼ ያለኝን ከትርፉ ጋር እወስደው ነበር፡፡ ስለዚህ መክሊቱን ውሰዱበት ፲ር መክሊትም ላለው ስጡት፤ እሱን ደግሞ ወደ ዘለዓለም ሐዘንና መከራ ወዳለብት ወደ ጨለማው አውጥታችሁ ጣሉት›› አላቸው፡፡ ላለው ሁሉ ይሰጠዋልና ይበዛለትማል፤ ከሌለው ግን ያው ያለው እንኳ ይወስድበታል፡፡ አገልጋዮችም ይህንን ክፉ አገልጋይ ወደ ጨለማው አውጥተው ጣሉት፡፡ በዚህ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል፡፡ † መክሊት የተባለ ጸጋ ስጦታ ሲሆን፤ እግዚአብሔር ለእያንዳንዳችን የተለያየ ስጦታ ሰጥቶናል፤ በተሰጠንም ስጦታ ልናገለግልበት ያስፈልጋል፡፡ † በተጨማሪ መክሊት ቃለ እግዚአብሔር ነው፤ የሰማነውን ቃለ እግዚአብሔር ለመተግበር እየበረታን ለሌላው ማሰማት ይገባናል፤ ከእኛ የሚጠበቀው ማሰማቱ ብቻ ነው፤ በልቡናው አድሮ ሥራ የሚያሠራ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ነውና፡፡ እኛም በሃይማኖት ጠንክረን በምግባር በርትተን ታማኝ ባርያ ልንሆን ይገባል፡፡ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ #share Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem Finotehiwotsundayschool.com finotehiwotsundayschool.com

#እንኳን ለጌታቸን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ፅንሰት እና ለጥንተ ትንሣኤ በሰላም አደረሳቹህ #እግዚአብሔር_ዓለምን_ከፈጠረበት_ጥበቡ_ይልቅ_ከድንግል_ማርያም_ሰው_ሆኖ_ዓለምን_ያዳነበት_ጥበቡ_ይበልጣል፡፡ ምክንያቱም፤ ፠ እግዚአብሔር ዓለምን የፈጠረበት ጥበቡ፤ 7ቱ ዕለታትን፣ 20ው ዓለማትን፣ 22ት ሥነ ፍጥረታትን ካለመኖር ወደ መኖር፤ ከፈጠራቸውም ላይ አሻሽሎ አስገኘ ፠ ዓለምን ያዳነበት ጥበብ፤ሰማይና ምድር የማይወስኑት፤ ከጽርሐ አርያም በላይ ጠፈሩ፥ ከበርባሮስ በታች መሠረቱ፥ ለአድማስና ለናጌብ ዳርቻቸው የኾነ አምላክ በአጭር ቁመትና በጠባብ ደረት ለሰው ልጅ ቤዛ ለመሆን ወደ ፈጠረው ምድር በፈጠረው አካል ላይ የሰማይ ዙፋኑን ሳይለይ መጥታል #ብስራትና (#Annunciation_to_the_Blessed_Virgin_Mary) ፅንሰት በአንድ ዕለት ነው የተከናወኑት፡፡ #ኢየሱስ ክርስቶስ በማህፀነ #ማርያም የተፀነሰው ልክ ቅዱስ #ገብርኤል ‹‹ ትፀንሺያለሽ ›› ሲላት እርሷም “ይኩነኒ በከመ ትቤለኒ” ‹‹ እንደቃልህ ይደረግልኝ ›› ብላ በተቀበለች ጊዜ የእግዚአበሔር ቃል በማህፀነ ድንግል ማርያም ተፀነሰ፡፡ አብ አፀናት መንፈስቅዱስ አነፃት ወልድ በተለየ አካሉ ከሥጋዋ ስጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ተዋሐደ (ሉቃ 1፤33)፡: እመቤታችን እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም ንጽሕት መቅደሱ ናትና ፤ ነገሩን አስቀድማ ጠንቅቃ ትወቅ ሲል ቅዱስ ገብርኤልን ልኮታል ( ሉቃ ፩፥፳፮ -፳፷) ብስራቱን የነገራት መጋቢት 29 ቀን በዕለተ እሁድ ከቀኑ ሦስት ሰዓት ላይ ነው፡:ቅዱስ ገብርኤልም ብርሃናዊ መልአክ መሆኑን ለማጠየቅ እና የሥላሴ ማደርያ መኾኗን ለማስረዳት 3 ጊዜ ተመላልሷል ፡፡ ሉቃ 1 ፥33 ማቴ 18፥ 16:: #ሊቀ_መላእክት ቅዱስ ገብርኤልም በደስታ ተውጦ ለመላእክት ጉባኤ “በቅድስት ድንግል ማርያም የይሁንታ ቃል ምክንያት ዓለም ዳነች” ብሎ የምስራች አላቸው፡፡ ነቢዩ ሕዝቅኤል “… በዙፋኑም አምሳያ ላይ እንደ ሰው መልክ አምሳያ ነበረ” (ሕዝ.1፡26) ብሎ እንደገለጠው እግዚአብሔር አምላክ ለመላእክት በሰው ምሳሌ ተገልጦ ይታያቸው ነበር እንጂ እርሱን ገጽ በገጽ አያዩም ነበር፡፡ ነገር ግን ቅዱስ ገብርኤል የፀንሰቱን ነገር ለመላእክት በነገራቸው ጊዜ ፈጣሪያቸው እግዚአብሔር ቃል ሰው በመሆን በአካል ሊያዩት እንደተቃረቡ ተረድተው ከዚህ በፊት ተሰምቶ የማያውቅ ታላቅ የሆነ የደስታ ዝማሬ ዘመሩ፡፡ በዚያን ጊዜ ቅዱሳን መላእክት ደስታቸው ድርብ ነበር፡፡ የመጀመሪያው ደስታቸው የሰው ልጆች መዳን ሲሆን ሁለተኛው ግን አምላካቸውን በጠባብ ደረት በአጭር ቁመት ተወስኖ ለማየት በመብቃታቸው ነበር፡፡ ቅዱስ ገብርኤል ለማብሰር የተመረጠውም #_1 #በማብሠር የታወቀ ስለሆነ(መሳ 13) ሊቃ 1 #_2 #የስሙ ትርጓሜ ሥራውን ስለሚገልጽ ፡፡ ገብር ሰው ማለት ሲሆን ኤል ደሞ አምላክ ማለት ነው ስለዚህ አምላክ ወሰብእ ማለት ነው (አምላክም ሰውም) ስለዚህ የአምላክ ሰው የመሆንን ምሥጢር እንዲያበስር ተልኳል ፡፡ #_3.#ሳጥናኤል አምላክ እኔ ነኝ ብሎ መላእክትን ባሸበራቸውጊዜ ‹‹ነቁም በበህላዌነ እስከ ነአምሮ ለአምላክነ (የፈጠረን ይህ አይደለምና ፈጣሪያችንን እስክናውቅ ድረስ በያለንበት እንጽና ) ብሏል፡፡ ይህን ያለበት አንደበቱየአምላክን ሥጋዌ ለእመቤታቸን ለመንገር አብቅቶታል :: ይህ በቅዱስ ገብርኤል ብሥራት አምላክ በማኅፀነ ማርያም ያደረበትን የፅንሰቱን በዓል ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በታላቅ ድምቀት በማኅሌት፣ በቅዳሴ፣ በትምህርት መጋቢት ፳፱ ቀን ስታስብ ከጌታችን ዘጠኙ ዐበይት በዓላት ውስጥ አንደኛውና የመጀመሪያው አድርጋ ታስበዋለች፡፡ መጋቢት መድኀኔዓለም፤ ጥቅምት 27 እንደሚከበር ሁሉ ይህ በዓል በፆም ወቅት ሰለሚውል መጋቢት 29 ለዋጭ በዓሉን ታኀሣሥ 22 በድምቀት እንድናከበር አባቶች ስርዐትን ሰሩልን ፡፡ ፍትሐ ነ አነድምት አ.15 #ጥንተ ትንሣኤ «ትንሣኤ» የሚለው ቃል የግእዝ ቋንቋ ነው፡፡ መገኛ ቃሉም «ተንሥአ» = ተነሣ የሚለው ግስ ሲሆን፡፡ «ትንሣኤ» ማለት = መነሣት፥ አነሣሥ፥ ሐዲስ ሕይወት ማግኘት ማለትን ያመለክታል፡፡ «ትንሣኤ» በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በየመልኩ፣ በየዓይነቱ ሲተረጐም ፭ት ክፍል አለው፡፡ ፩ኛ) «ትንሣኤ» ማለት ኅሊና ማለት ነው፡፡ ይህም ማለት ተዘክሮተ እግዚአብሔር ነው፡፡ ፪ኛ) «ትንሣኤ» ማለት ልቡና ማለት ነው፡፡ የዚህም ምሥጢሩ ቃለ እግዘብሔርን መስማትና በንስሐ እየታደሱ በሕይወት መኖር ነው፡፡ ፫ኛ) «ትንሣኤ» ለጊዜው የሙታን በሥጋ መነሣት ይሆናል፡፡ ነገር ግን ድጋሚ ሞት ይከተለዋል፡፡ ፬ኛ) «ትንሣኤ» የክርስቶስ በገዛ የባሕርይ ሥልጣኑ ሞትን ድል አድርጎ መነሣት ነው፡፡ የዛሬው ትምህርታችንም ይህንን መሠረት ያደረገ ነው፡፡ ፭ኛው)ና የመጨረሻው «የትንሣኤ» ደረጃም የባሕርይ አምላክ የጌታችን የመድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን «ትንሣኤ» መሠረት ያደረገ «ትንሣኤ ዘጕባኤ» ነው፡፡ ይህም ከዓለም ኅልፈት በኋላ ሰው ሁሉ እንደየሥራው ለክብርና ለውርደት፥ ለጽድቅና ለኩነኔ በአንድነት የሚነሣው የዘለዓለም ትንሣኤ ይሆናል፡፡ ጌታችን በመስቀል ላይ ተሰቆል በሥጋ ከሞተበት ቀን መጋቢት 27 ፤ ሦስተኛው ቀን መጋቢት 29 ነውና ይህች ዕለት ቅድስት ትንሣኤው ውሎባታል በከበረች ልዩ የሆነች ትንሣኤው የዓለም ድኀነት ሆነ ፡፡ በረቀቀ ጥበቡ በዚህች ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሥቷል ፡፡ የጽንሰቱ በዓል ተደርቦባት ነው እንጂ ልናስበው የሚገባ ትልቅ ዕለት ነው :: /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ #share Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem Finotehiwotsundayschool.com

#መጋቢት_28 #ጻድቅ _ንጉሥ_ቆስጠንጢኖስ_ዕረፍቱ_ነው ፡፡ እናቱ ዕሌኒ አባቱ ቊንስጣ ይባላሉ ፡፡ አባቱ ቊንስጣ አረማዊ ቢሆነም በልቡ ግን ይቅርታን እና ርኀራኀን የተሞላ ነበር ፡፡ ዕሌኒን ካገባ
#መጋቢት_28 #ጻድቅ _ንጉሥ_ቆስጠንጢኖስ_ዕረፍቱ_ነው ፡፡ እናቱ ዕሌኒ አባቱ ቊንስጣ ይባላሉ ፡፡ አባቱ ቊንስጣ አረማዊ ቢሆነም በልቡ ግን ይቅርታን እና ርኀራኀን የተሞላ ነበር ፡፡ ዕሌኒን ካገባ ቦኃላ ቆስጠንጢኖስን ወለዱ ፡፡ ቆስጠንጢኖስ ማለት ዠንጉርጉር ማለት ነው ይህም ነበር ይተባለው እርሷ ክርስቲያን በሏ ደግሞ አረማዊ ሰለሆነ ነው ፡፡ እናቱ ቅድስት ዕሌኒ ይቅርታን እና ርኀራሄን በልቡ እንዲኖር ዘውትር ታስተምረው ነበር ፡፡አባቱ አርፎ መንግስቱን ከተረከበ በኃላ ክርስቲያኖች ላይ የተጫኑትን ክፉ አገዛዞች አስወገደ፡፡ ስለደረሰባቸውም መከራ ተክዞ ሲያስብ በ 6 ሰዓት ላይ እንደ ከዋክብት የሆነ #መስቀል ታየው በላዩ ላይም በዮናኒ ቋንቋ #ኒኮስጣጣን የሚል ጽሑፍ ነበረበት ትርጉሙም #በዚህ_ጠላትህን_ድል_ታደርጋለህ ማለት ነው፡፡ እናቱ ቅድስት ዕሌኒ መስቀሉን ስትፈልግ ሰራዊቱን በመላክ ፣ ሃብት በመስጠት እና በመሳሰሉት ረድቷል ፣ ታሳትፏል ፣ አፋልጓል ፡፡ለተጨማሪ ( መስከረም 17 እና መጋቢት 10 የፃፍናቸውን ያንብቡ ) በስሙ #ቊስጠንጥንያ (Constantinople) የተባለችም ከተማም ገንብቷል በውስጣም #የእመቤታንን ቅድስት ድንግል ማርያምን ስም ፣ በአግያና ስም ፣ በሶፋያ ስም ታላቅ ቤተ ክርስቲያን ሰርቷል ፡፡በእነርሱም ውስጥ #አጽመ ቅድሳንን እያፈላለገ ያኖር ነበር፡፡ አምላክን ደስ ካሰኝ ቦኀላ ተጋድሎውን ፈጽሞ በኒቆምድያ ከተማ ታሞ አረፈ፡፡ ወደ ቊስጠንጥንያ መልሰው በከበሩ ሐዋርያት ቤተ መቅድስ በምስጋና አኑረውታል ፡፡ የፃድቃን ነገሥታት በረከታቸው ይደርብን አሜን! /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/

#መጋቢት_27_ኢትዮጵያዊው_ንጉሥ_ገላውዴዎስ_አንገቱን_የተቆረጠበት_ዕለት ፤ #አጼ_ገላውዴዎስ የልደት ቀኑና የሞት ዕለቱ ፤ ሁለት ታላላቅ የመድኀኔዓለም በዓል በሚከብሩበት ዕለት ነው ፡፡ ይህም ልደቱ
#መጋቢት_27_ኢትዮጵያዊው_ንጉሥ_ገላውዴዎስ_አንገቱን_የተቆረጠበት_ዕለት ፤ #አጼ_ገላውዴዎስ የልደት ቀኑና የሞት ዕለቱ ፤ ሁለት ታላላቅ የመድኀኔዓለም በዓል በሚከብሩበት ዕለት ነው ፡፡ ይህም ልደቱ #ጥቅምት ፳፯ ቀን ፲፭፻፴፫ ዓ/ም ፤ ዕረፍቱ ደግም መጋቢት ፳፯(መጋቢት 27 #ጥንተ_ስቅለት (ጥንተ ስቅለት) ቀን ፲፭፻፶፩ ዓ/ም ነው፡፡ ንገሥ ገላዴዎስ #የአጼ_ልብነ_ድንግል_ልጅ ሲሆን እናቱ ደግም ሰብለ ወንጌል ትባል ነበር፡፡ ግራኝ ተነሥቶ ክርስቲየኖችን ሲያሳድድ ፣ሲያጠፋ ፣አብያተ ክርስቲያናትን ሲያቃጥል ፤ እግዚብሔር ያስነሳው ንጉሥ ነው፡፡ ከነገሠም ቦኃላ ጠላት ሃይሎችን አጠፋቸው አሰደዳቸው ይህንን ግራኝ ሲሰማ እጅግ ተቆጥቶ ከቱርክ እና ከመሳስሉት ጦሮች ጋር በሕብርት ገጠመው ንጉሥ ገላዴዎስም ግራኝን ገደለው ፣ አብያት ክርስቲያናትም ተመልሰው ታነፁ ፣ ክርስቲያኖችም ከተሰደዱበት ተመለሱ ፤ ክርስትና ሃይማኖትም በድጋሚ ቀናች፡፡ ንጉሥ ገላውዴዎስ የስቅለት በዓልን በሚያከብርብት ጌዜ ከእስላሞች ወገን አንዱ (አዳሉ አሚር ኑር )ከነጦሩ መጣ፤ ይህንን ባዩ ጊዜ የንጉሡ የጦር መኳንንቶች ፈቀቅ እንበል ቢሉት ዓይኔ እያየ አብያተ ክርስቲያናት አይቃጠሉም ብሎ ጦር ገጠማቸው ፤ እስላሞቹም ከበውት በጎራዴ ጨፈጨፉት የከበረች አንገቱን በሰይፈ ቆረጡት ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ፡፡በዚሁ ጦርነት ላይ የደብረ ሊባኖስ እጨጌ ዮሐንስም ሕይወታቸውን እንዳጡ መጻሕፍት ይናገራሉ፡፡:: የአባቶቻችን ጻድቃን ነገስታት በረከታቸው ይደርብን አሜን! /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ #share Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት - آمار و تحلیل کانال تلگرام @finotehiwott