fa
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

رفتن به کانال در Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

کانال Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 327 مشترک است و جایگاه 5 647 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 194 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 327 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 17 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -87 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -13 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 21.14% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 9.89% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 240 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 515 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 23 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 18 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

15 327
مشترکین
-1324 ساعت
-147 روز
-8730 روز
آرشیو پست ها
/በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

ያለመሰልቸት መድኃኔዓለምን ሲያገለግሉ የኖሩት መምሬ ዋለ አረፍተ ዘመን ገታቸው በዛሬው እለት ሥርዓተ ቀብራቸው ተፈጽሟል። "እግዚኦ አዕርፍ ነፍሰ መምህርነ " ለቤተሰቦቻቸው እንዲሁም ለወዳጅ ዘመዶቻቸ
ያለመሰልቸት መድኃኔዓለምን ሲያገለግሉ የኖሩት መምሬ ዋለ አረፍተ ዘመን ገታቸው በዛሬው እለት ሥርዓተ ቀብራቸው ተፈጽሟል።     "እግዚኦ አዕርፍ ነፍሰ መምህርነ " ለቤተሰቦቻቸው እንዲሁም ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን ያድልልን የአባታችንንም ነፍስ ከደጋግ አባቶች ጋር ያሳርፍልን።

እንኳን አደረሳችኁ ! #ልደቱ_ለእግዚእነ_ኢየሱስ_ክርስቶስ #ጌና_እና_ልደት ጌና እና ልደት ዋዜማና ክብረ በዓል /የተለያዩ ቀናት/ ቢኾኑም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ግን ጌና ልደትን እየተካ እንጠቀምበታለን፤ ነገር ግን ይህ ሊስተካከል ይገባዋል፡፡ ልዩነት ስላለውም የኢትዮጵያ ብርሃን የተባለው አፈ ጳዝዮን አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ለጌናና ለልደት ለ2ቱም በዓላት ለየብቻቸው በመጽሐፈ ምሥጢር ድርሰት ደርሶላቸዋል፡፡ #ጌና፤ የልደት በዓል ዋዜማ ቀን ሲኾን በዚህ ቀን ‹‹በገና ጨዋታ አይቆጡም ጌታ›› የተባለለትን ‹‹የገና ጨዋታ›› እንጫወታለን፤ የምንጫወትበት የኳሱ ስያሜ ‹‹ሩር›› ሲባል ስያሜውን ያገኘው፤ ሰብዓ ሰገል እልፍ እልፍ ሠራዊት አስከትለው የተወለደውን አይሁድ ንጉሥ ፍለጋ ወደ ንጉሡ ሔሮድስ ደርሰው ነበርና፤ ሔሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ፈልጎና በውስጡ ሸሽጎ ለሰብዓ ሰገል ሂዱ ሕፃኑን ፈልጉ ስታገኙትም ንገሩኝ ብሎ ሰድዷቸዋል፤ ነገር ግን በዚያው ሳይነግሩኝ እንዳይሄዱ በማለት እነርሱ ሳያውቁ ‹‹ሩር›› የተባለ ሰላይ በመሃላቸው አስገብቶ ነበርና ሰብዓ ሰገልን ይመራቸው የነበረው ኰከብ ተሠውሮባቸዋል፤ ሰብዓ ሰገል ሠራዊታቸውን ቢያጣሩ ከመሃከላቸው የተቀላቀለ ሩር የተባለ የሔሮድስን ሰላይ አገኙ ይህንንም ሰላይ የሰብዓ ሰገል ሠራዊት አንገቱን በሰይፍ ቀልተውታልና ያን ለማስታወስ ዛሬ በገና ጨዋታ ላይ ሩር የተባለው ኳስ የሔሮድስ ሰላይን ‹‹ሩር›› እንዲያስታውስ አባቶች ሥርዐትን ሠሩ፡፡ #ልደቱ_ለእግዚእነ_ኢየሱስ_ክርስቶስ #‹‹ቤዛ ኩሉ ዓለም ዮም ተወልደ::›› /#ቅዱስ_ያሬድ/ ጌታችን ለሰው ልጆች ብሎ፤ የሰው ልጆች ፍቅር አገብሮት ንጽሕትና ቅድስት ከኾነች ከእመቤታችን ያለ ወንድ ዘር በመጋቢት 29 ተጸንሶ ታኅሣሥ 29 በ1ዓ.ም. (ዓለም ከተፈጠረ፥ ዘመን ከተቈጠረ በ5,500 ዓመት) በበረት ተወልደ፡፡ ሰማይና ምድር የማይወስኑትን በረት ቻለው፤ ወሰነውም በሌሊት መንጋቸውን የሚጠብቁ እረኞች ነበሩ፡፡ መልአኩ መጥቶ እንዲህ አላቸው፡- ‹‹እነሆ! ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኀኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና፡፡ ይህም ምልክት ይሆንላችኋል፤ ሕፃን ተጠቅልሎ በግርግምም ተኝቶ ታገኛላችሁ›› አላቸው፡፡ ሉቃ2፡10-12፡፡ ከመለአኩም ጋራ ሠራዊተ መላእክት መጥተው ‹‹ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ወሰላም በምድር ለዕጓለ እመሕያው /ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ/›› አሉ፡፡ ቅዱሳን መላእክትም ከእነርሱ ተለይተው ወደ ሰማይ በወጡ ጊዜ እረኞቹ እርስ በርሳቸው ‹‹እንግዲህ እስከ ቤተ ልሔም ድረስ እንሂድ፣ እግዚአብሔርም የገለጠልንን ይህን የሆነውን ነገር እንይ›› ተባባሉና ፈጥነው መጡ፡፡ ማርያምንና ዮሴፍን ሕፃኑንም በግርግም ተኝቶ አገኙ፡፡ አይተውም ስለዚህ ሕፃን የተነገረላቸውን ነገር ገለጡ፤ የሰሙትን ሁሉ እረኞቹ በነገሯቸው ነገር አደነቁ፤ የብርሃን እናቱ እመ አምላክ ግን ይህን ነገር ሁሉ በልብዋ እያሰበች ትጠብቀው ነበር፡፡ ሉቃ 2፡13-19፡፡ መላእክትም ሰማይ መንበሩ ምድር የእግሩ መረገጫ የሆኑለት አምላክ በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ በጎል ተኝቶ በጨርቅ ተጠቅልሎ አይተውት ደስ ብሏቸው ወደ ሰማይ ቢያርጉ ከባሕርይ አባቱ ከአብ ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በዕሪና ከመንበሩ አይተውት ‹‹ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት›› ብለው አመስግነውት በጣዕም ላይ ጣዕም፤ በጸጋ ላይ ጸጋ ተጨምሮላቸው ደስ ብሏቸዋል፡፡ ልደቱን ይሹታልና፤ መላእክትም ብቻ አይደሉም እንስሳትም አራዊትም ደስ ብሏቸዋል፡፡ #ይህም_ሊታወቅ_አንድ_ባሕታዊ_በቋራ_/_ኋላ_ማኅበረ_ሥላሴ_ገዳም/_ቋርፍ_ሲምስ_ቶራ_ሚዳቋ_ዮም_ተወልደ_ መድኀኔ_ዓለም_ዮም_ተወልደ_ቤዛ_ኵሉ_ዓለም_ዮም_ተወልደ_ከሣቴ_ብርሃን፡፡ እያለች ስትዘል አይቷል። በጌታችን በልደቱ የባሕር ውኃ ወተትና ማር ተራሮች እንጀራ እንጨቶችም የበረከት ፍሬ ሆነዋል፡፡ ልደቱንም በኮከብ ተረድተው ሰብአ ሰገል (የጥበብ ሰዎች) ስማቸውም ማንቱሲማር፣ ሜልኩ በዲዳስፋ የተባሉ የፋርስ ነገሥታት ከገነት የተገኘ ወርቅ፣ ዕጣን ከርቤ አምጥተው ገብረውለታል፡፡ /ዘኅ 20፡17፡፡ ‹‹ሰው ሆይ! ፈጽመህ ደስ ይበልህ፣ እግዚአብሔር ዓለሙን ወዶታልና አንድ ልጁንም የሚያምንበት ሁሉ እስከ ዘለዓለም ፈጽሞ ይድን ዘንድ አሳልፎ ሰጥቷልና ልዑል ክንዱን ሰደደልን፡፡›› ‹‹በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩ ሰዎች ታላቅ ብርሃን ወጣላቸው፤ በቅዱሳን ላይ የሚያድር እግዚአብሔር እኛን ለማዳን ልዩ ከሆነች ድንግል ሰው ሆኗልና ኑ ይህን ድንቅ እዩ፤ ስለተገለጠልን ምሥጢር ምስጋና አቅርቡ፤ ሰው የማይሆን ሰው ሆኗልና ቃል ተዋሕዷልና ጥንት የሌለው ሥጋ ጥንታዊ ቀዳማዊ ሆነ፣ ዘመን የማይቆጠርለት መለኮት ዘመን ተቆጠረለት፡፡ የማይታወቅ ተገለጠ፣ የማይታይ ታየ፣ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ በእርግጥ ሰው ሆነ፡፡›› ‹‹ከቅድስት ሥለሴ አንዱ ወልድ መዋረዳችንን አይቶ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ባሕርዩን ዝቅ አደረገና መጥቶ በድንግል ማኅፀን አደረ፤ ከብቻዋ ከኃጢአት በቀርም እንደ እኛ ሰው ሆነ፡፡ ነቢያት ትንቢት እንደተናገሩለት በቤተልሔም ተወለደ፤ ፈጽሞ አዳነን፣ ወገኖቹም አደረገን፡፡›› ይህችም ዕለት፤  ነቢዩ ኢሳይያስ እንዲህ ብሎ ትንቢት የተናገረላት ናት፡- ‹‹እነሆ ድንግል ፀንሳ ወንድ ልጅ ትወልዳለች፣ ስሙንም ዐማኑኤል ትለዋለች፣ ትርጓሜውም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ ማለት ነው፡፡ /ት.ኢሳ. 7፥14/ **ነቢይ ሕዝቅኤል ‹‹እግዚአብሔርም አለኝ ‹ይህች በር ተዘግታ ትኖራለች፣ አትከፈትም፣ የሚገባበትም የለም የእስራኤል ፈጣሪ እግዚአብሔር እንደተዘጋች ይገባባታልና ተዘግታ ትኑር››› አለ፡፡ **ነቢዩ ዳንኤልም ‹‹ሌሊት በራእይ አየሁ ‹እነሆ ታላቁ እንደ ሰው ልጅ በሰማይ ደመና መጣ፤ ዘመኑን ወደሚያስረጅ ደረሰ፣ ከፊቱም አቀረቡት፣ የዘላለም አገዛዝ፣ ጌትነት፣ መንግሥት ተሰጠው፡፡ ሕዝቡና አሕዛቡ ሁሉ መንደር መንድረው የሚኖሩትና ነገዱም ነገሥታቱም ሁሉ ይገዙለታል፤ አገዛዙም የዘላለም አገዛዝ ነው፤ መንግሥቱም የማያልፍ የማይጠፋ ነው››› አለ፡፡ **ዳግመኛም ኢሳይያስ ‹‹እግዚአብሔር እንደ እኔ የሥጋ መጋረጃ በመጋረድ ተገለጠልኝ›› አለ፡፡ አሁንም ደግሞ ‹‹አዲስ ሰማይ አዲስ ምድር እሠራ ዘንድ አለኝ›› አለ፡፡ ሁለተኛም ‹‹በእሴይ ሥር በትር ትወጣለች፣ ከእርሷም ጽጌ አበባ ይወጣል›› አለ፡፡ ዳግመኛም ‹‹ሕፃን ተወልዶልናልና ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና ይኸውም ሥልጣን በጫንቃው የሆነ ክርስቶስ ነው፣ ስሙም ድንቅ መካር፣ ኃያል አምላክ፣ የዘላለም አባት፣ የሰላም አለቃ ይባላል›› አለ፡፡ **ነቢዩ ኤርምያስም ስለ እግዚአብሔር ‹‹በዚያን ወራት ለዳዊት ብርሃንን አወጣለሁ፣ በምድርም የቀና ፍርድን ያደርጋል፣ እግዚአብሔርም ያመኑትን ያድናቸዋል›› አለ፡፡ **ኤልሳም ‹‹እግዚአብሔር ከሰማይ ይወርዳል፣ በእስራኤል ልጆች አደባባይም በመመላለስ ለሕዝቡ ዕውነትን ያስተምራቸዋል፡፡ ከአብርሃም ልጅነት ልዩ ከሆኑ ወገኖች በቀር አሕዛብ ሁሉ ይታዘዙለታል›› አለ፡፡ **ናሆምም ‹‹እግዚአብሔር በእኔ አርአያ ይመጣል፣ ልብሱም እንደልብሴ ነው›› አለ፡፡ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott

በፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤታችን ፤ በቀን 26/04/2017 ዓ.ም ፡ ከቀኑ 10:30 በተደረገ ጠቅላላ ጉባኤ  በካህናት አባቶች ፀሎተ ኪዳን ተደርሶ የተጀመረ ሲሆን ፡ አዲስ የተመረጡ የሥራ አመራርና ሥራ አስፈፃሚ አባላት ፡ ከነባሩ ሥራ አመራር ይፋዊ የሥራ ርክክብ ፣ የኦዲትና ኢንስፔክሽን ጉባኤ አባላት መምረጥ እንዲሁም የአጋፔ መርኃግብር በማድረግ በታላቅ ድምቀት ተካሂዷል። /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

፳፭. ሆሳዕና ደብረ ምሕረት ቅዱስ በዓለ ወልድ፤ አድራሻ፤ ጉራጌ ሀገረ ስብከት፤ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ሆሳዕና ፳፮. ቡኢ ደብረ ሰላም በዓለ ወልድ ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ደቡብ ሃገረ ስብከት፥ ቡኢ፤ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ቡኢ ፳፯. ባሕር ዳር በዓለ ወልድ (በዐለ እግዚአብሔር) ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ባሕር ዳር ሃገረ ስብከት፥ ባሕር ዳር ከተማ፥ ቀበሌ 13፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ባሕር ዳር፡፡ ፳፰. ወለንጪቲ ጨመሪ በዓለ ወልድ ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ደቡብ ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ወለንጪቲ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ወለጪቲ፡፡ ፳፱. ወንዶ ገነት በዓለ ወልድ ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ሳዲማ ሃገረ ስብከት፥ ወንዶ ገነት፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ወንዶ ገነት፡፡ ፴. ደብረ ምሕረት ዱና በዓለ ወልድ ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ዱና፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አውቶቡስ ተራ → ዱና፡፡ ፴፩. ደብረ ገነት በዓለ ወልድ ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ሃገረ ስብከት፥ ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አውቶቡስ ተራ → ደብረ ገነት፡፡ ፴፪. ጫንቋ በዓለ እግዚአብሔር፤ (ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት፤ ደምቢያ ቆላ ድባ አጠገብ፡፡) ፴፫. ባርጫ ኢየሱስ፤ (ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት፤ ከቆላድባ አጠገብ፡፡) ፴፬. ገምበራ ኢየሱስ፤ (ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት፤ በጯሂትና በጣና አጠገብ፡፡) ፴፭. ጉቢያ ኢየሱስ፤ (ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት፤ ደምቢያ፡፡) ፴፮. ማክሰኚት በዓለ ኢየሱስ፤ (ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት፤ ጎንደር ዙሪያ ወረዳ፡፡) ፴፯. ዘንተራ ኢየሱስ፤ (ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት፤ ጎንደር ዙሪያ ወረዳ፤ ማክሰኚት፤ በግራኝ በርና በጎንድ ገዳም መሃል፡፡) ፴፰. ደባርቅ በዓለ እግዚአብሔር፤ (ሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት፤ ደባርቅ ከተማ ወረዳ) #ከኢትዮጵያ_ውጪ_የሚከበርበት_፩ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. ደብረ ገሊላ ቅዱስ በዓለ ወልድ ወሩፋኤል ቤተ ክርስቲያን፤ አድራሻ፤ አሜሪካ ሃገረ ስብክት፥ ሲያትል ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ ቦሌ አየር መንገድ (በአውሮፕላን)→ አሜሪካን (ሲያትል) / #ክብረ_በዓላት #Feasts / / #ገዳማትና_አድባራት #Monasteries_and_Churches / /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot • YouTube 👉 m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#ታኅሣሥ ፳፱፤ #ልደተ_እግዚእነ_ኢየሱስ_ክርስቶስ_፡፡ #በአዲስ_አበባ_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_ #የጌታችን_ልደት_የበዓለ_ወልድ_የገና_ክብረ_በዓል_የሚከብርባቸው ፵፯ ገዳማትና አድባራት፡፡ (ያልጠቀስናቸው ካሉ አሳውቁን) #ዮም_ተወልደ_ መድኀኔ_ዓለም፤ #ዮም_ተወልደ_ቤዛ_ኵሉ_ዓለም፤ #ዮም_ተወልደ_ከሣቴ_ብርሃን፡፡ ✧ ክብረ በዓሉ የሚከበርበት ምክንያት፤ የጌታችንና የአምላካችን የመድኀኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት፤ ልዩ ማስታወሻ፤ ከቅዱሳንም ሆነ ከእመቤታችን በላይ የጌታችን በዓል ከዋለ የጌታችን በዓል በዋነኛነት ስለሚከበር፤ ጾምም ከሆነ ጾሙ ቀርቶ በዓል ስለሚደረግ፤ በዓላቸው በዚህ ቀን የኾኑ ቅዱሳን በዓላቸው በሌላ ቀን ቅያሬ ሲከበር ነገር ግን በቦታቸው ላይ የጌታችን ልደት በልዩ ሁኔታ ይከበራል፡፡ ✧ ነገር ግን የጌታችን ልደት፤ ከ9ኙ ዐበይት የጌታችን በዓላት አንዱ በመኾኑ፤ በሁሉም ገዳማትና አድባራት ዋይዜማ ተዚሞ፥ ማኅሌት ተቁሞ፥ ሰዐታት ተቁሞ፥ ኪዳን ተደርሶ፥ ቅዳሴ ተቀድሶ ይከበራል፡፡ #በመዲናችን_በአዲስ_አበባ_የሚከብርባቸው_፰ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. አዲስ አበባ መካነ ሥላሴ ቅዱስ በዓለ ወልድ (አዲስ አበባ ላይ በ1883 ዓ.ም. የተመሠረተ፤ ነገር ግን ታቦቱ ቀድሞ የነበረና ከ600 ዓመታት በላይ ታሪክ ያለው) አድራሻ፤ አራዳ ከተማ ክፍለ ከተማ፤ 4ኪሎ ታክሲ፤ ከፒያሳ → አራት ኪሎ ፪. ለቡ ደብረ ታቦር በዓለ ወልድና አበ ብዙኃን አብርሃም ገዳም አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ለቡ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ለቡ ፫. ጽርሐ ንግሥት ቅድስት ሐና ቤ/ክ አድራሻው፤ ሐና፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሐና፡፡ ፬. አንቀፀ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (የቅዱስ ላሊበላ ታቦት በድርብነት ይወጣል) አድራሻ፤ የካ_ክፍለ_ከተማ፥ ራስ ካሣ ታክሲ፤ ከ4 ኪሎ → ፈረንሳይ → አንቀጸ ምሕረት (ራሳ ካሣ ሚካአል) ፭. ፊሊዶሮ መድኀኔዓለም ቅዱስ ላሊበላ፡፡ አድራሻው፤ ፊሊዶሮ፡፡ ታክሲ፤ ከመርካቶ → ኮልፌ(ፊሊዶሮ)፡፡ ፮. አዲስ አምባ ደብረ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕትና ደብረ ፍስሐ ቅዱስ ገብርኤል አድራሻው፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ሳሪስ አዲስ ሰፈር፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሳሪስ አዲስ ሰፈር፡፡ ፯. መካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል (ቅዱስ በዓለ ወልድ በድርብነት ይከብራል) አድራሻው፤ መካኒሳ፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ → መካኒሳ ፰. ኮልፌ ቀራንዮ (ታቦት ማደርያ) ደብረ ተአምራት ዳግማዊ ጻድቃኔ ማርያም፡፡ (ቅዱስ በዓለ ወልድ በድርብነት ይከብራል) አድራሻ፤ ዘነበወርቅ ታቦት ማደሪያ ጀርባ፤ ከዘነበወርቅ ወደ ታቦት ማደሪያ በሚወስደው መንገድ ላይ፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ጦር ኃይሎች → ዘነበ ወርቅ፡፡ #በሃገራችን_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከበርባቸው_፳፩ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. ቤተልሔም፥ እስራኤል፥ ኢየሩሳሌም (ጌተችን የተወለደባት) አድራሻ፤ እስራኤል፥ ኢየሩሳሌም፤ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ ቦሌ አየር መንገድ (በአውሮፕላን) → እስራኤል ፪. ማኅበረ ሥላሴ ገዳም (የሺዎች ገዳም)፤ (ለመጀመሪያ ጊዜ ጌታ በተወለደባት ዕለት የጌታችን መወለድ በኢትዮጵያ የተበሠረባት) አድራሻ፤ ምዕራብ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ቋራና (መተማ) ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ጎንደር → ሸዲ/መተማ/ ፫. ደብረ ሮሐ ላስታ ቅዱስ ላሊበላ (ዳግማዊት /አምሳለ/ ኢየሩሳሌም) አድራሻው፤ ሰሜን ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ላስታ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ላሊበላ ፬. መንበረ ልዑል ደብረ መጕና አቡነ አብሳዲ ወቅድስት ኪዳነ ምሕረት ወማኅበረ በኵር ገዳም፡፡ አድራሻ፤ ምዕራብ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ትራንስፖርት፤ ከጎንደር ከተማ → ዳንሻ መስመር ላይ → በበው /አሸሬ/ የምትባል መንደር ላይ ተወርዶ → የእግር ጕዞ ፭. ዞዝ አንባ አቡነ አብሳዲ (ቅዱስ ላሊበላ ከፈለፈላቸው አንዱ) አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ በለሳ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ማክሰኚት → በለሳ (ዞዝ አንባ) ፮. ምድረ ከብድ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አድራሻ፤ ጉራጌ ስልጤ ሃገረ ስብከት፥ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ምደረ ከብድ ፯. ዲጎ ኢየሱስ፡፡ አድራሻ፤ ሰሜን ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ወልድያን አልፎ፥ ዶሮ ግብር፤ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ ላምበረት አውቶቡስ ተራ → ወልድያ፡፡ ፰. ገሀ ኢየሱስ፤ (ሰሜን ወሎ ሃገረ ስብከት፥) ፱. ኬላ ኢየሱስ፤ (ሰሜን ወሎ ሃገረ ስብከት፥) ፲. ደንቀዝ ኢየሱስ፡፡ አድራሻ፤ ጉራጌ ስልጤ ሃገረ ስብከት፥ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ምደረ ከብድ ፲፩. ርዕሰ አድባራት አደባባይ ኢየሱስ ቤ.ክ.፤ /ጽላቱ ከደበቡ ኢትዮጵያ የሄደ፥ እጅግ ጥንታዊ ታሪክ ያለው፥ ኋላ ላይ ቊጥሩ ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ የሆነ/ አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፥ አራዳ፥ ጃንተከል ወርካ ጋር ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር ፲፪. እስቴ መካነ ኢየሱስ አድራሻ፤ ደቡብ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ እስቴ፤ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ → እስቴ፡፡ ፲፫. ደብረ ታቦር ኢየሱስ አድራሻ፤ ደቡብ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ደቡብ ጎንደር ከተማ፡፡ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ታቦር፡፡ ፲፬. ብራ ኢየሱስ (ብራ ታዴዎስ)፡፡ አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ወገራ፥ አምባ ጊዮርጊስ፤ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር → አምባ ጊዮርጊስ፡፡ ፲፭. ደብረ ስብሐት ቀሃ ኢየሱስ፤ (ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ፤ የጎንደር ላይ ቤት አቋቋም ትምህርት ቤት ማስመስከርያ) አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፥ ጥምቀተ ባሕሩ አጠገብ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር ፲፮. መንደረ ኢየሱስ አድራሻ፤ ምዕራብ ጎጃም ሃገረ ስብከት፥ አዴት፡፡ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ባሕር ዳር በሞጣ መስመር(አዴት) ፲፯. ጃንገበር ኢየሱስ አድራሻ፤ ምዕራብ ጎጃም ሃገረ ስብከት፥ አዴት አጠገብ፡፡ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ባሕር ዳር በሞጣ መስመር(አዴት) ፲፰. ሰንቀኛ በዓለ እግዚአብሔር፤ (ባሕር ዳር በሞጣ መስመር(አዴት) ፲፱. ሺገዢ ኢየሱስ፤ ባሕር ዳር በሞጣ መስመር(አዴት) ፳. አለም ገና ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (በድርብነት ይከብራል)፤ አድራሻ፤ ምዕራብ ሸዋ ሃገረ ስብከት ፥ አለም ገና ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → አለም ገና፡፡ ፳፩. ገፈርሳ(ታጠቅ) በዓለ ወልድ ወአቡነ ሳሙኤል ወአቡነ ኪሮስ፤ አድራሻው፤ ምዕራብ ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ገፈርሳ ትራንስፖርት፤ ከመርካቶ አውቶቡስ ተራ → ታጠቅ ወይም መናገሻ የሚል ትራንስፖርት ይዘው ገፈርሳ ድልድዩ ጋር በዓለ ወልድን ያገኛሉ፡፡ ፳፪. አሸዋ ሜዳ ቤሮ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ላሊበላ ቤተክርስቲያን፤ አድራሻ፤ ምዕራብ ሸዋ ሃገረ ስብከት ፥ ወልመራ ወረዳ፥ (አዲስ ዓለም አካባቢ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ → አምቦ (አዲስ ዓለም) ፳፫. ቂልጠፋት በዓለ ወልድ አድራሻ፤ ጉራጌና ስልጤ ሃገረ ስብከት፥ እንደጋይ ወረዳ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ጉራጌ ፳፬. ጉንችሬ በዓለ ወልድ፤ አድራሻ፤ ጉራጌና ስልጤ ሃገረ ስብከት፥ እነሞር ወረዳ) ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ጉራጌ

ኢቲሳ ደብረ ጽላልሽ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም እና አካባቢው - 1951 ዓ.ም ኢቲሳ በሰሜን ሸዋ በቀድሞው ቡልጋ አውራጃ የሚገኝ እና ከ800 ዓመት በፊት እ.ኤ.አ በ1215 ዓ.ም አባታችን አቡነ ተ
+8
ኢቲሳ ደብረ ጽላልሽ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም እና አካባቢው - 1951 ዓ.ም ኢቲሳ በሰሜን ሸዋ በቀድሞው ቡልጋ አውራጃ የሚገኝ እና ከ800 ዓመት በፊት እ.ኤ.አ በ1215 ዓ.ም አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት የተወለዱበት ታሪካዊ ቦታ ነው። University of Monash/Asian Collections/Forsyth, Elliott Christophe Photographs: https://repository.monash.edu