fa
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

رفتن به کانال در Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

کانال Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 396 مشترک است و جایگاه 5 567 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 182 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 396 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 28 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 15 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 5 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 21.32% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 10.24% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 282 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 576 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 17 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 29 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

15 396
مشترکین
+524 ساعت
+287 روز
+1530 روز
آرشیو پست ها
ግንቦት_16 ተዛካር ዮሐንስ ፍቁረ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ በእንተ ስብከቱ ቅዳሴ ቤቱ ውስተ ሀገረ እስክንድርያ ወሶበ ጽሕፈቱ ወዕረገቱ ውስተ ሰማያት ወርእዮቱ ለሠራዊተ ሰማያውያነ ፡፡ ✤ወደ ሰማይ ወጥቶ በሰማይ የሚኖሩ የመላእክት ሰራዊትን ሥራዓታቸውን አይቶ አቡቀለምሲስ የሚባለውን ጻፈ፡፡ ✤ለስብከቱም የበዓሉ መታሰቢያ ነው ፡፡ ✤በእስክንድርያም ሀገር ቤተክርስቲያን የከበረችበት ዕለት ነው ፡፡ ሰላም ለቅደሴ ቤትከ በእለ እስክንድርያ ሀገር ፡፡ እለ ሐነፅዋ ኬነውት ወጠበብታ ምክር፡፡ ወእንዘ ትበውእ ዮሐንስ ውስተ መቃብር ፡፡ ተኀባዕከ ወተሠወርከ በሥልጣን ኀይል መንክር ፡፡ ባሕቱ ልብሰከ ዘተተፈ ለዝክር ፡፡ #በተለያዩ_ቅጽል_ስሞች_የሚጠራ፤ (100 አካባቢ ከሚጠጉ ስሞቹ ጥቂቶቹን /21ዱን ስሞች ከጽሑፍ በስተመጨረሻ ይመልከቱ) #ሰዓሊ_የኾነ፤ የጌታችንን ስነ ስቅለት የሳለ፡፡ #ከ81ዱ_የመጽሐፍ_ቅዱስ_ክፍሎች_5ቱንና_ሌሎች_መጻሕፍትንም_(ነገረ ማርያምን ..) የደረሰ፤ #ብዙ_ደቀ_መዛሙርትን_ያስተማረ፤ ወደ ሰማይ ወጥቶ በሰማይ የሚኖሩ የመላእክት ሰራዊትን ሥራዓታቸውን አይቶ አቡቀለምሲስ የሚባለውን ጻፈ፡፡ ለስብከቱም የበዓሉ መታሰቢያ ነው ፡፡ በእስክንድርያም ሀገር ቤተክርስቲያን የከበረችበት ዕለት ነው ፡፡ #share እና #Like ማድረግ እንዳይረሱ ጌታ እናቱንም እነሆ ልጅሽ ያላት እርሱን ደቀ መዝሙሩንም እነኋት እናትህ ያለው ነው፡፡ ✤ዮሐንስ ንጹሕ በአምሳለ ትጉሃን፤ (#ዮሐንስ_እንደ_መላእክት_ንጹሕ_ነው፤) ✤ዮሐንስ ድንግል ምክሐ ቅዱሳን፤ (#ዮሐንስ_ድንግል_የቅዱሳን_መመኪያ_ነው፤) ✤ዮሐንስ ስርግው በቀጸላ ሥን በሜላተ ብርሃን፤ (#ዮሐንስ_በብርሃን_መጐናጸፊያና_ሻሽ_የተጌጠ_ነው፤) ✤ዮሐንስ አርጋኖነ ዘቤተ ክርስቲያን፤ (#ዮሐንስ_የቤተ_ክርስቲያን_በገና_ነው፤) ✤ወበቃለ ቀርን ዘይኬልህ በኤፌሶን፥ ይስአል ለነ ስርየተ ለኀጥኣን፡፡ (#በኤፌሶን_ዐዋጅ_የሚናገር_ዮሐንስ_ኀጥኣን_ለምንሆን_ለኛ_ይቅርታን_ይለምንልን፡፡ /እመጽሐፈ ሰዐታት/ ፨ ‹‹ሰላም ለአፉከ ለዮሐንስ ዘሰዓሞ፤ ንጽሐ ኅሊናሁ ወልቡ ለዐይነ ፍትወትከ ሶበ አደሞ›› /መልክአ ኢየሱስ/ ፨ ሰላም ለሥዕልኪ ወለሥዕለ ወልድኪ ዘሰዓሞ፤ ዮሐንስ ርኄ ዮሐንስ ቀናንሞ፤ ለዝ ወልድኪ መሐሪ ኅሩመ በቀል ወተቀይሞ፤ ማርያም ሀብኒ በእዴኪ እንዘ ትጼውዒ ስሞ፤ ሥጋሁ ቅዱሰ ወክቡረ ደሞ፡፡ /መልክአ ሥዕል/ ፨#100_አካባቢ_ከሚጠጉ_ስሞቹ_ጥቂቶቹን_21ዱን_ስሞች_እነኾ፤ #ሐዋርያው_ቅዱስ_ዮሐንስ፤ ዮሐንስ #ፍቁረ እግዚእ፥ (የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ለጌታ በጣም ቀራቢ ከነበሩት ሦስት የምሥጢር ሐዋርያት (ጴጥሮስ ፣ ናያዕቆብ ) ዮሐንስ ቀዳሚዉ ነዉ፡፡ ጌታችን ምሥጢረ ተአምራትን በኢያኢሮስ ቤት ፣ ምሥጢረ መንግስትን (መለኮትን) በደብረ ታቦር፣ ምሥጢረ ምጽአትን በደብረ ዘይት ፣ ምሥጢረ ጸሎትን በጌቴ ሴማኒ ሲገልጽና ሲያሳይ አብሮ የተመለከተ በመሆኑና ለጌታ በጣም ቀራቢ በመሆኑና በወንጌልም ‹‹ጌታ ይወደዉ የነበረ ደቀ መዝሙር ››ተብሎ ስለ ተጠቀሰ የጌታ ወዳጅ ፍቁረ እግዚእ ይባላል፡፡ዮሐ 13፡ 23 ፡፡ ወልደ #ዘብድዮስ ፥ ዮሐንስ #ነባቤ መለኮት ፥ ዮሐንስ #ቦኦርኔጌስ ፥ ዮሐንስ #አብቀለምሲስ ፥ (ፍጥሞ በምትባል ደሴት ላይም ወደ ፊት የሚሆነዉን ነገር በራእይ ስለተገለጸለት በግሪክ ቋንቋ አቡቀለምሲስ ተብሏል፡፡ትጉሙም የራዕይ አባት ማለት ነዉ፡፡) ዮሐንስ #ወንጌላዊ ፥ ዮሐንስ #ድንግል ዮሐንስ #ታዎሎጎስ ቅዱስ ዮሐንስ ምሥጢረ ሥላሴንና ምሥጢረ ሥጋዌን አስፍቶ በመጻፉ (ታዎሎጎስ) ተብሏል፡፡ትርጉሙም ነባቤ መለኮት (የመለኮትን ነገር የሚናገር)ማለት ነዉ፡፡ 1. #ዮሐንስ_ብፁዕ (ብፁዕ ዮሐንስ) 2. ዮሐንስ ድንግል 3. #ዮሐንስ_ፍንው 4. #ዮሐንስ_ካህን 5. #ዮሐንስ_ኅሩይ 6. ዮሐንስ ሥርግው 7. #ዮሐንስ_ምዑዝ 8. ዮሐንስ ቅኑይ 9. #ዮሐንስ_ማኅቶት 10. ዮሐንስ ቤዛ ሰማይ 11. #ዮሐንስ_ክቡር 12. ዮሐንስ ጻድቅ 13. #ዮሐንስ_ረድእ 14. ዮሐንስ ማኅቶት 15. #ዮሐንስ_ድንግል 16. ዮሐንስ ንጹሕ 17. #ዮሐንስ_ለባዊ 18. ዮሐንስ መረግድ 19. #ዮሐንስ_ዕንቈ 20. ዮሐንስ መልአክ 21. #ዮሐንስ_ኪሩብ 22. #ቁጽረ ገጽ ቅዱስ ዮሐንስ እስከ መስቀል ድረስ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተቀበለዉን መከራ በማየቱ ከዚያ ዕለት ጀምሮ 70 ዘመን ሙሉ ፊቱ በኅዘን የተቋጠረ በመሆኑ (ቁጽረ ገጽ) ሆኖ ኖሯል፡ በዚህ በከበረ ሐዋርያ ጸሎት ይማረን አሜን

3ኛው ዙር የመ.ዳሰሳ ይህን ይመሰል ነበር ። የተዳሰሰው. መ ፡ ውዳሴ ማርያም አቅራቢ፡ መ/ር አቢይ ዋስይሁን ።
+2
3ኛው ዙር የመ.ዳሰሳ ይህን ይመሰል ነበር ። የተዳሰሰው. መ ፡ ውዳሴ ማርያም አቅራቢ፡ መ/ር አቢይ ዋስይሁን ።

በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነው #የሊቁ_የቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ_ቤተ_ክርስቲያን_በደቡዊት_ኢትዮጵያ_ሌሾ_ማዞሪያ_፤ #ታኅሣሥ_12_ቀን 2012 ዓ.ም. የመሠረት ደንጊያ ሲቀመጥ,,,
+2
በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነው #የሊቁ_የቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ_ቤተ_ክርስቲያን_በደቡዊት_ኢትዮጵያ_ሌሾ_ማዞሪያ_፤ #ታኅሣሥ_12_ቀን 2012 ዓ.ም. የመሠረት ደንጊያ ሲቀመጥ,,,

✤✤ #በአንበሳ ላይ የምትጫነው ኢትዮጵያዊቷ ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ ዕረፍቷ ነው፡፡ * በ16ኛው መቶ ክ/ዘመን በምሥራቅ ኢትዮዽያ ደዋሮና ፈጠጋር አካባቢ ሲኾን የተወለደችው፤ አባቷ ባሕር አሰግድና እናቷ ክርስቶስ ዕበያ ይባላሉ፡፡ * በወግ በማዕረግ ባል አገባች፤ ግን ወዲያው አፄ ያዕቆብ ገደሉባት፤ ወላጆቿም ግድ ብለው ስዕለ ክርስቶስ የተባለ የሱስንዮስን የጦር መሪ አጋቧት 24 ዓመት እስኪኾናት ድረስም 3ት ልጆችን ወለደች፡፡ አፄ ሱስንዮስ ካቶሊክ በኾነ ጊዜ ባሏ ወደ ንጉሡ እምነት ወደ ካቶሊክነት ገባ፡፡ ልጆቿም እግዚአብሔርን የማያስደስቱ ከኾነ በሞት ውሰዳቸው ብላ ለፈጣሪ በመንገሯ ሦስቱም ልጇቿ ሞቱ፤ ባሏም ክዶ ወደ ካቶሊክነት ስለገባ ተለይታው ወደ ጣና ገዳማትና ወደ ታላቁ ገዳም ዋልድባ ገብታ ብዙ ተጋደለች፡፡ * ንጉሡንም በካቶሊክ እምነቱ ከሌሎች ቅዱሳን ጋራ ኾና ስለተቃወመችው 2 ጊዜ ወደ በርሃ አግዟታል፤ ወደ ጉሙዝ ባጋዛት ወቅት ወደ እሳት ውስጥ ቢከታትም እሳቱ ሳያቃጥላት ወጥታለች፡፡ * ፋሲል ነግሶ ሃይማኖት ተመልሶ ሃገር ሲረጋጋ ወደ ምጽሌ ከዚያም ወደ መንዞ መጥታ 7ት ገዳማትን አቅንታለች፡፡ ከ700 በላይ ለሚኾኑ መነኰሳትና መነኰሳይያት እመ ምኔት ኾናም አስተዳድራለች፡፡ ምግቧም የመረረ ቅጠልና ኮሶ ነበረ፡፡ በስተመጨረሻም የሬማ መድኀኔ ዓለምን አቅንታ በተወለደች በ50 ዓመቷ ብዙ ቃል ኪዳንን ተቀብላ በ1630ዎቹ መጨረሻ አካባቢ ዐርፋ በዚሁ ገዳም በክብር አርፋለች፤ በበዓለ ዕረፈቷም የብርሃን ምሰሶ ከምድር እስከ ሰማይ ተተክሎ ታይቷል፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ፤ ትምሕርት ዋና ክፍል ፥ ንዑስ ክፍል /ሕትመት እና ሚዲያ/ የተዘጋጀ :: #share Contact: https://t.me/finotehiwot1927 .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot .YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w www.finotehiwotsundayschool.com ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ት.ቤት .

በተጨማሪም፤ በሚከተሉት ስሞችም ይጠራል፡፡ ፨አፈ ወርቅ /የእመቤታችን ስዕል አፍ አውጥታ ነው ዮሐንስ አፈወርቅ ብላ የሰየመችው/፣አፈ በረከት፣ልሳነ ወርቅ ፣የዓለም ሁሉ መምህር፣ርዕሰ ሊቃውንት፣ዐምደ ብርሃን (የብርሃን ምሰሶ)፣ሐዲስ ዳንኤል፣ሊቀ ዻዻሳት ዘበርትዕ (እውነተኛው ሊቀ ጳጳሳት) ፣መምህር ወመገስጽ ዘኢያደሉ ለገጽ፣ጥዑመ ቃል ፨ምስጋና ለአምላካችን ይሁንና ንስጥሮስ በምፍቅናው የአንዲት ሴትን ኀፍረት ሥጋ ገልጦ እግዚአብሔር ወልድ በዚህ ማሕፀን ተፀንሶ አልተወለድም ብሎ በሕዝቡ ፊት ተናገረ፤ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም፤ * ‹‹እኔ እግዚአብሔር .. በዚህ ሥጋ ከሴት እንደተወለደ አምናለሁ፤ * እኔ እግዚአብሔር በመዋለጃ ማኅፀን እንደተወሰነ አምናለሁ፤ * እኔ እግዚአብሔር በድንግልና ወተት እንዳደገ፣ በሕፃናትም ሥርዐት ሕፃናትን እንደመሰላቸው፣ ከብቻዋ ከኀጢአትም በቀር የሰውን ሕግ ሁሉ እንደፈጸመ አምናለሁ፡፡›› ብሎ የዚህችን ሴት ኀፍረተ ሥጋ ስለ እመቤታችን ፍቅር ብሎ ሳመ፤ ከእመቤታችን ሥዕል አንደበትም ከዚህ በኋላ ስምህ ዮሐንስ ብቻ ሳይኾን ‹‹ዮሐንስ አፈወርቅ›› ይሁን ብላ ሰይመችው፤ አርሱም ‹‹እሰግድ ለኪ፥ እሰግድ ለኪ ወእዌድሰኪ … ›› ብሎ ዛሬ በተአምረ ማርያም የሚነበበውን ምስጋና ሰተት አድርጐ አደረሰላት፡፡ #፠ከላይ አንደተጠቀሰው በአብዛኛው ኪዳንና ተዓምር በየዕለቱ በሚደርሰባቸው ገዳማትና አብያተ ክርስቲያናት ‹‹እሰግድ ለኪ፥ እሰግድ ለኪ፥ እሰግድ ለኪ ወእዌድሰኪ … ›› የሚለውን የእመቤታችን ድርሳኑን በየቀኑ የምንሰማውን) የደረሰ፤ ፠እጅግ በጣም ብዙ የኾኑ ድንቅ የኾነ መጻሕፍትን እጁን እስኪያመውና እጁን በክር አሥሮ የጻፈ፤ ፠ኍልቈ መሳፍርት የሌላቸውን መልእክታት የከተበ ፠ ጳውሎስን የተካ ሰባኪ፤ ለአንዲት እናት ሳይቀር ጕኤ ዘርግቶ፥ አትሮኖስ አቁሞ የሚያስተምር ትጉህ አስተማሪ፤ ፠ በፓትርያርክነት ቤተ ክርስቲያንን የመራና ያስተዳደረ፤ ፠ ጠቢብ፣ መናኝ፣ ጳጳስ፣ ፈላስፋ፣ መምህር፣ ሰባኪ፣ ጸሐፊ፣ …. ነው ሰላም ለዮሐንስ እንተ አብደረ ስደተ። እምይሳተፍ በግፍዕ መፍቀሪተ ንዋይ ንግሥተ። እምነ አፉሁ ዘይወጽአ ሰሚዖ ግዘተ። እንበለ ይዕርግ ላዕለ ወንእንበለ ይረድ ታሕተ። መልአከ ሰማይ ቆመ ፲ተ ዓመተ"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) በረከቱ ይደርብን ! -------- ✤✤ #በአንበሳ ላይ የምትጫነው ኢትዮጵያዊቷ ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ ዕረፍቷ ነው፡፡ * በ16ኛው መቶ ክ/ዘመን በምሥራቅ ኢትዮዽያ ደዋሮና ፈጠጋር አካባቢ ሲኾን የተወለደችው፤ አባቷ ባሕር አሰግድና እናቷ ክርስቶስ ዕበያ ይባላሉ፡፡ * በወግ በማዕረግ ባል አገባች፤ ግን ወዲያው አፄ ያዕቆብ ገደሉባት፤ ወላጆቿም ግድ ብለው ስዕለ ክርስቶስ የተባለ የሱስንዮስን የጦር መሪ አጋቧት 24 ዓመት እስኪኾናት ድረስም 3ት ልጆችን ወለደች፡፡ አፄ ሱስንዮስ ካቶሊክ በኾነ ጊዜ ባሏ ወደ ንጉሡ እምነት ወደ ካቶሊክነት ገባ፡፡ ልጆቿም እግዚአብሔርን የማያስደስቱ ከኾነ በሞት ውሰዳቸው ብላ ለፈጣሪ በመንገሯ ሦስቱም ልጇቿ ሞቱ፤ ባሏም ክዶ ወደ ካቶሊክነት ስለገባ ተለይታው ወደ ጣና ገዳማትና ወደ ታላቁ ገዳም ዋልድባ ገብታ ብዙ ተጋደለች፡፡ * ንጉሡንም በካቶሊክ እምነቱ ከሌሎች ቅዱሳን ጋራ ኾና ስለተቃወመችው 2 ጊዜ ወደ በርሃ አግዟታል፤ ወደ ጉሙዝ ባጋዛት ወቅት ወደ እሳት ውስጥ ቢከታትም እሳቱ ሳያቃጥላት ወጥታለች፡፡ * ፋሲል ነግሶ ሃይማኖት ተመልሶ ሃገር ሲረጋጋ ወደ ምጽሌ ከዚያም ወደ መንዞ መጥታ 7ት ገዳማትን አቅንታለች፡፡ ከ700 በላይ ለሚኾኑ መነኰሳትና መነኰሳይያት እመ ምኔት ኾናም አስተዳድራለች፡፡ ምግቧም የመረረ ቅጠልና ኮሶ ነበረ፡፡ በስተመጨረሻም የሬማ መድኀኔ ዓለምን አቅንታ በተወለደች በ50 ዓመቷ ብዙ ቃል ኪዳንን ተቀብላ በ1630ዎቹ መጨረሻ አካባቢ ዐርፋ በዚሁ ገዳም በክብር አርፋለች፤ በበዓለ ዕረፈቷም የብርሃን ምሰሶ ከምድር እስከ ሰማይ ተተክሎ ታይቷል፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ፤ ትምሕርት ዋና ክፍል ፥ ንዑስ ክፍል /ሕትመት እና ሚዲያ/ የተዘጋጀ :: #share Contact: https://t.me/finotehiwot1927 .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot .YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w www.finotehiwotsundayschool.com ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ት.ቤት .

፨፨፨የዓለም ኹሉ መምህር የኾነው #ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ባረፈ በ35 ዓመቱ (በትንሹ ቴዎዶስዮስ ዘመን) በዛሬዋ ዕለት ያረፈበት ነው፤ የቅዱሱ ሥጋውም ፍልስት ኅዳር 17 በቊስጥንጢንያ ሆኗል ሥጋውም በዚያን ሰዓት ሕዝቡን ቀና ብሎ ባርኳል፡፡ #share ፨፨፨በአንበሳ ላይ የምትጫነው ኢትዮጵያዊቷ ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ ዕረፍቷ ነው፡፡ ---በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነው የሊቁ የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቤተ ክርስቲያን በደቡዊት ኢትዮጵያ ሌሾ ማዞሪያ ፤ ታኅሣሥ 12 ቀን 2012 ዓ.ም. የመሠረት ደንጊያ ተቀምጧል፡፡ሌሾ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቦታው፤ ከአ.አ. ወደ ወላይታ መንገድ፤ ወደ ዱራሜ መታጠፊያ፤ ከአደሮ ከተማ አጠገብ ሌሾ ማዞሪያ ጋር የሚገኝ፤ ሌሾ ማዞሪያ የሚገኘው፤ በደቡብ ክልል በከምባታ ጠንባሮና ሃላባ ሀገረ ስብከት፤ ከአ.አ 287 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ የሚገኝ ነው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ፨በ347 ዓ.ም. በሶርያ ዋና ከተማ በአንጾኪያ ሲኾን የተወለደው፤ አባቱ አስፋኒዶስ እናቱ አትናስያ ይባላሉ፡፡ ፨ገና የ15 ዓመት ሕፃን ሳለ በሕፃንነቱ ወደ ግሪክ ሔዶ የዘመኑን ሳይንስ (ፍልስፍና) በሙሉ ተምሮ ተመልሷል፤ በዚህም በመንፈሳዊውም ኾነ በዘመናዊው ይፍልስፍና ይህ ቀረህ የማይባል ሊቅ ኾነ፡፡ ፨ቅዱሱ በ16 ዓመቱ ኃብትና ንብረቱን ለነዳያን ሰጥቶ መጻሕፍትን ብቻ ሰብስቦ ከባልንጀራው ቅዱስ ባስልዮስ ጋር በርሃ ገባ፤ በበርሃ ሳለም ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስና ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ዼጥሮስ ወደ እርሱ መጥተው፤ ሊቀ ሐዋርያት የመንግስተ ሰማያትን መክፈቻ ስልጣን ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌሉን ሰጡት፡፡ የመጻሕፍት ድርሰት ተገለጹለት፤ በዚህም ቅዱስ በትጋትና በንቃት እጆቹ ታመው በክር አስሮ እስኪጽፍ ድረስ ዐሥር ሺህ የሚደርሱ ድርሳናትን መልዕክታትንና ትርጓሜያትን ጻፈ፡፡ ከዚህ በኋላ ቅስና ተሹሞ በስብከተ ወንጌል ብዙ ቦታዎችን አዳረሰ፤ በቅድስናው ወደውታልና የቊስጥንጥንያ ፓትርያርክ አድርገው ሾሙት፡፡ በሚያስተምርበት ጊዜም ከጣዕመ ትምህርቱ የተነሣ ሕዝቡ ተመስጠውና ተደመው ይሰሙት ነበር፤ ምድራዊው ሰው ይቅርና ልዑላኑ መላእክት ተሰብስበው ያደንቁት ነበር፡፡ በሠርጓ ቀን በሞት ሊወስዳት የመጣውን መልከአከ ሞት ቅዱሱ በሥልጣነ ቃሉ ገዝቶ 10 ዓመት አቁሞታል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ለሰው ፊት አያደላም:: በርሱ ዘንድ ንጉሥና ደሃ ነዳይ እኩል ነው:: ለሞት ያበቃውም ይሔው ነበር:: ምክንያቱም የወቅቱ ንግስት አውዶክስያ ያንዲት ድሃ መበለትን መሬት ቀምታ አልመልስም በማለቷ መክሮ አወገዛት:: እርሷ ግን ከኃጥአንና መናፍቃን ጋር መክራ 2 ጊዜ አጋዘችው:: በተሰደደበት ሃገር ፍሬ አፍርቶ: አስተምሮና አሳምኖ በ407 ዓ.ም. አርፏል:: ቤተ ክርስቲያንና ምእመናን ሳይጠግቡት እንደናፈቁት በ60 ዓመቱ አጡት:: በወቅቱ ታላቅ ሐዘንና ለቅሶ ተደረገ:: ገና የ15 ዓመት ሕፃን ሳለ በሕፃንነቱ ወደ ግሪክ ሔዶ የዘመኑን ሳይንስ (ፍልስፍና) በሙሉ ተምሮ ተመልሷል፤ በዚህም በመንፈሳዊውም ኾነ በዘመናዊው ይፍልስፍና ይህ ቀረህ የማይባል ሊቅ ኾነ፡፡ *ቅዱሱ በ16 ዓመቱ ኃብትና ንብረቱን ለነዳያን ሰጥቶ መጻሕፍትን ብቻ ሰብስቦ ከባልንጀራው ቅዱስ ባስልዮስ ጋር በርሃ ገባ፤ በበርሃ ሳለም ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስና ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ዼጥሮስ ወደ እርሱ መጥተው፤ ሊቀ ሐዋርያት የመንግስተ ሰማያትን መክፈቻ ስልጣን ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌሉን ሰጡት፡፡ የመጻሕፍት ድርሰት ተገለጹለት፤ በዚህም ቅዱስ በትጋትና በንቃት እጆቹ ታመው በክር አስሮ እስኪጽፍ ድረስ ዐሥር ሺህ የሚደርሱ ድርሳናትን መልዕክታትንና ትርጓሜያትን ጻፈ፡፡ ከዚህ በኋላ ቅስና ተሹሞ በስብከተ ወንጌል ብዙ ቦታዎችን አዳረሰ፤ በቅድስናው ወደውታልና የቊስጥንጥንያ ፓትርያርክ አድርገው ሾሙት፡፡ በሚያስተምርበት ጊዜም ከጣዕመ ትምህርቱ የተነሣ ሕዝቡ ተመስጠውና ተደመው ይሰሙት ነበር፤ ምድራዊው ሰው ይቅርና ልዑላኑ መላእክት ተሰብስበው ያደንቁት ነበር፡፡ በሠርጓ ቀን በሞት ሊወስዳት የመጣውን መልከአከ ሞት ቅዱሱ በሥልጣነ ቃሉ ገዝቶ 10 ዓመት አቁሞታል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ለሰው ፊት አያደላም:: በርሱ ዘንድ ንጉሥና ደሃ ነዳይ እኩል ነው:: ለሞት ያበቃውም ይሔው ነበር:: ምክንያቱም የወቅቱ ንግስት አውዶክስያ ያንዲት ድሃ መበለትን መሬት ቀምታ አልመልስም በማለቷ መክሮ አወገዛት:: እርሷ ግን ከኃጥአንና መናፍቃን ጋር መክራ 2 ጊዜ አጋዘችው:: በተሰደደበት ሃገር ፍሬ አፍርቶ: አስተምሮና አሳምኖ በ407 ዓ.ም. አርፏል:: ቤተ ክርስቲያንና ምእመናን ሳይጠግቡት እንደናፈቁት በ60 ዓመቱ አጡት:: በወቅቱ ታላቅ ሐዘንና ለቅሶ ተደረገ:: ✣✣✣ስለ ቀዳማዊው ሊቅ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ዳግማዊው ሊቅ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ (አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ) እንዲህ ብሎ ገልጾታል፡፡፣አፈ ዕንቊ ፣አፈ ጳዝዮን ፤(/ስለ እመቤታችን ፍቅር/ የወር አበባ ያላትን ሴት አንቀጸ ሥጋ ለመሳም ያላፈረ)፣አፈ ባሕርይ (በድርስቶቹ ቤተ ክርስቲያንን የሚያስጌጣት)፣አፈ መዐር ፣አፈ ሦከር (በቃሉ ጣፋጭነት ምእመናንን የሚያለመልማቸው)፣አፈ አፈው /ሽቱ/ (በትምህርቱ መዐዛ የምሥጢር በጎችን ደስ የሚያሰኛቸው) ፣አፈ ርኄ፣አፈ ሰይፍ (በውግዘቱ ሥልጣን ከሀዲዎችን የሚቆርጥ) ፣አፈ መጥባሕት፣የማይነዋወጥ ዐምድ፣የማይፈርስ መሠረት፣ከሞገዶች መነሣት የተነሣ የማይሰበር መርከብ፣በሃይማኖት ባሕር ውስጥ የሚዋኝ ዋናተኛ፣የማይፈርስ ግንብ፣በጠላት ፊት የሚፀና አዳራሽ /መጽሐፈ ምሥጢር፣ /

ግንቦት 12፤ የአባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖት ፍልሰተ አጽም ። ብድጋሚም ግንቦት 12 ፤ የእናታችን የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ዓመታዊ ክብረ በዓል ነወ፦። ✤ ብፅዕት ክርስቶስ ሠምራ ሰይጣንን ልታስታርቅ በሄደች ጊዜ ከሲኦል ቅዱስ ሚካኤል እየተራዳት ብዙ እልፍ ነፍሳትን ያወጣችበት ዕለት ነው።ራሷ ባነጸችው በጣና ገዳሟ ይከበራል። -------- ፠ ‹‹አባቴ ተክለ ሃይማኖት የሚለኝ ሁሉ፤ በፍልሰቴ ቀን በገዳሜ ይገኝ እኔም ልጄ እለዋለው ከቅዱስ ሚካኤልና ከልጄ ፊልጶስ ጋር እባርከዋለው።›› /ገድለ ተክለ ሃይማኖት/ ፠ አባታችን ባረፉ በ54ኛ ዓመታቸው በ1354 ዓ.ም በአፄ ሰይፈ አርዕድ ዘመን ለ4ኛው እጨጌ ሕዝቅያስ ተገልጸው አጽማቸው ከደብረ አስቦ ወደ ደብረ ሊባኖስ ግንቦት 12 ቀን እንዲፈልስ አድርገዋል፡፡ ፠ ግንቦት 12 በደብረ ሊባኖስ ትልቁ በዓል ነው፡፡ ጥንተ መሠረቱም፤ 12ቱ እጨጌዎች ከያሉበት ቦታ እየመጡ 1ድ 1ድ ወር ሙሉ በፈረቃ የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን ቅዱስ አጽም ተራ ገብተው ያጥኑ ነበር፡፡ ግንቦት 12 ግን ሁሉም ከያሉበት ተሰባስበው በአንድነት ያከብራሉ፡፡ #የጻድቁ_ዋና_ዋና_የታሪክ_ሂደቶች፤ ፠ከአባታቸው ከቅዱስ ጸጋ ዘአብና ከቅድስት እግዚዕ ኀረያ፤ መጋቢት 24 ቀን ተጸንሰው፤ በታኅሣሥ 24 ቀን በ1190 ዓ.ም. በእቲሣ ተወለዱ፡፡ ፠በተወለዱ በ3ኛው ቀን አሐዱ አብ ቅዱስ፣ አሐዱ ወልድ ቅዱስ፣ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ ብለው ፈጣሪያቸውን አመሠገኑ፡፡ ፠በተወለዱ በ40ኛው በደብረ አጋዓዚት ማርያም ፍስሐ ጽዮን “የጽዮን ደስታ” ተበለው ተጠሩ፡፡ ፠እስከ 7 ዓመታቸው ድረስ ከአባታቸው ከጸጋ ዘአብ ዘንድ እየተማሩ ፠በ15 ዓመታቸው ዲቁናን ከቄርሎስ ዘንድ ተቀበሉ፡፡ ፠በ22 ዓመታቸው ከአቡነ ቄርሎስ ዘንድ ቅስናን ተቀበሉ፡፡ ፠በከተታ አውራጃ 3 ዓመት ወንጌልን እያስተማሩ ብዙ ድንቅ ነገርን አደረጉ፡፡ ፠በኅዳር 24 ቀን ቅዱስ ሚካኤል ወደ ላይ ነጠቃቸው ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ ጋር 25ኛ ካህን ሆነው የሥላሴን መንበርን አጠኑ ፠በሐይቅ እስጢፋኖስ 10 ዓመት፥ በደብረዳሞ 12 ዓመት ኖረዋል፡፡ ፠በተለያዩ የሃገራችን ክፍሎች እየተዘዋወቱ አስተምረዋል፤ በአኵሱም ጽዮን፣ በዋልድባና በዙሪያቸው ባሉ ገዳማት እየዞሩ ተሳልመዋል፡፡ ወደ ኢየሩሳሌም በመውረድም ተሳልመው ተመልሰዋል፤ ሲመለሱም ብዙ ቅዱሳን አብረዋቸው ተመልሰዋል፡፡ /እነ እጨ ዮሐንስ ዘጎንድ (ዘጠገሮን) ልብ ይሏል፡፡ ፠በ1267 ዓ.ም ደብረ ሊባኖስን በአት አድርገው ኖሩ፡፡ ለ22 ዓመት ቆመው በመጸለይ የአንድ እግራቸው አገዳ ተሠበረ ደቀ መዝሙሮቻቸው በጨርቅ ጠቅልለው ቀበሩት፡፡ በአንድ እግራቸው ለ7 ዓመት በጸሎት ቆሙ በጠቅላላው ለ29 ዓመት በጸሎት ከቆሙ በኋላ በ99 ዓመት ከ10 ወር ከ10 ቀን ነሐሴ 24 ቀን 1290 ዓ.ም አረፉ፡፡ ፠፠፠አባታችን ባረፉ በ54ኛ ዓመታቸው በ1354 ዓ.ም በአፄ ሰይፈ አርዕድ ዘመን ለ4ኛው እጨጌ ሕዝቅያስ ተገልጸው አጽማቸው ከደብረ አስቦ ወደ ደብረ ሊባኖስ ግንቦት 12 ቀን እንዲፈልስ አድርገዋል፡፡ ፠የደብረ ሊባኖስንም ቦታ የሰጠው ሐኖ (ተክለ ሃይማኖት) /የግራርያ ሰው/፤ ሲሆን ዓፄ ልብነ ድንግል በነገሠ በ8ኛው ዓመት ‹መርሕ› ከምትባል ስፋራ ታቦቱ ከነዋየ ቅድሳቱ ጋር ‹ከምድኃሬ› ተዛውሯል፡፡ ይህንንም ያደረገው እጨጌው አባ ጴጥሮስ ነበር፡፡ #የጻድቁ_ክብረ_በዓላቶቻቸውም፤ #ኅዳር 24፤ ከካህናተ ሰማይ ጋር የሥላሴን መንበር ያጠኑበት #ታኅሣሥ 24፤ የአባታችን ልደት #ጥር 24፤ የአባታችን ስባረ አጽም #መጋቢት 24፤ የአባታችን ጽንሠት #ግንቦት 12፤ የአባታችን ፍልሰተ አጽም #ነሐሴ 24፤ የአባታችን በዓለ እረፍት ናቸው፡፡ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ .....share ፠ ትዌድሶ ደብረ ሊባኖስ ገዳሙ፤ እስመ በውስቴታ ተገብረ ፍልሰተ ሥጋሁ ወአጽሙ፡፡ Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem www.Finotehiwotsundayschool.com ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ