fa
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

رفتن به کانال در Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

کانال Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 382 مشترک است و جایگاه 5 582 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 195 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 382 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 07 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 40 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 9 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 22.55% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 9.50% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 469 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 461 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 20 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 08 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

15 382
مشترکین
+924 ساعت
-177 روز
+4030 روز
آرشیو پست ها
፠፠ ወረቦቹን፣ አንገርጋሪንና እስመ ለዓለምን በድምፅ ማግኘት ከፈለጉ በቴሌግራም ገጻችን https://t.me/medihanaelem ያገኛሉ፡፡

እንኳን ለኪዳነ ምሕረት ክብረ በዓል (ቃል ኪዳን ለተቀበለችበት) በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡ (ድንግል ሆይ ቃል ኪዳንሽ ባይኖር ኖሮ የሲኦል እሳት ባሰጠመን ነበር፡፡) ፠ የካቲት ፲፮ ቀንም በጎልጎ
+6
እንኳን ለኪዳነ ምሕረት ክብረ በዓል (ቃል ኪዳን ለተቀበለችበት) በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡ (ድንግል ሆይ ቃል ኪዳንሽ ባይኖር ኖሮ የሲኦል እሳት ባሰጠመን ነበር፡፡) ፠ የካቲት ፲፮ ቀንም በጎልጎታ ቦታ ቆማ ወደ ልጇ እንዲህ ብላ ለመነች፡፡ ፠ጸሎትና ልመናዬን ስማኝ ቃሌንም አድምጥ እኔ እናትህ አገልጋይህ የምለምንህን ይህ ነው፡፡ ፨ መታሰቢያዬን ለሚያደርጉ፣ ፨ አብያተ ክርስቲያኔን ለሚሠሩ፣ ወይም ፨ ለታረዙ ለሚያለብሱ፣ ለተራቡ ለሚያጠግቡ፣ የተጠማውንም ለሚያጠጡ (በስሜ ለድሆችና ለችግረኞች ቀዝቃዛ ውኃ ለሚሰጡ)፣ ፨ የታመመውንም የሚጎበኝ፣ ያዘነውንም የሚያረጋጉ፣ የተከዘውንም ደስ የሚያሰኙ ወይም ፨ ምስጋናዬን ለሚጽፉ፣ ልጆቹንም በስሜ ለሚሰይም፣ ፨ በበዓሌም ቀን በማኅሌት ለሚያመሰግን አቤቱ በዓይን ያልታየውን በጆሮ ያልተሰማውን በጎ ዋጋ ስጣቸው፡፡ ፨ በአማላጅነቴም የሚተማመኑትን ሁሉ ከሲዖል ነፃ አድርጋቸው ከአንተ ጋር የደረሰብኝን ረሃብና ጥማቱን መከራውን ሁሉ አስብ አለችው፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም እንዳልሽው ይሁንልሽ የሰጠሁሽን ቃልኪዳን እንዳይታበይ በራሴ በባሕርይ አባቴ በአብ በባሕርይ ሕይወቴ በመንፈስ ቅዱስ ማልኩልሽ ብሎ ቃል ኪዳን ሰጣት፡፡ #ሥርዐተ_ማኅሌት_ዘየካቲት_16፤ #በዓለ_ኪዳነ_ምሕረት፡፡ የሚቆመው ቁመት፤ የ3ት ዐበይት አድባራት አብነት ነው፡፡ እነዚህም፤ 1ኛ) የደ/መድኀኒት ዐቢየ እግዚእ ኪዳነ ምሕረት አብነት 2ኛ) የደ/ኀይል ወደብረ ጥበብ በዓታ አብነት 3ኛ) የደፈጫ ኪዳነ ምሕረት አብነት ናቸው፡፡ ስለዚህ ደብራችሁ የላይ ቤት ከኾነ ‹‹ዘዐቢየ እግዚእ›› የሚለውን፤ የታች ቤት ከኾነ ‹‹ዘበዓታ›› የሚለውን እንድትጠቀሙ እናሳስባልን፡፡ ፠፠ ወረቦቹን፣ አንገርጋሪንና እስመ ለዓለምን በድምፅ ከፈለጉ በቴሌግራም ገጻችን https://t.me/medihanaelem ያገኛሉ፡፡

እንኳን ለኪዳነ ምሕረት ክብረ በዓል አደረሳችሁ፤ በአዲስ አበባ የኪዳነ ምሕረት ክብረ በዓል የሚከበርባቸው ገዳማትና አድባራት፤ (፠ …….. በአዲስ አበባ ያልዘገብናቸው ሌሎችም ካሉ ከተቻለ ከነፎቷቸው አሳውቁን፡፡) ፠ እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪደነ ምሕረት ፠ ደብረ …. ሥዕል ቤት ኪዳነ ምሕረት (በዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ግቢ ውስጥ የምትገኝ ጥንታዊት ቤተ ክርስቲያን) ፠ ጉራራ ምሥራቀ ፀሐይ ኪዳነ ምሕረት ቤ/ክ (ከፈረንሳይ ሌጋሲዮን አልፎ) ፠ አየር ጤና አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት፤ ፈለገ ሕይወት ኪዳነ ምሕረት (ኮልፌ ቀራንዮ፥ ወረዳ 5) ፠ ጉለሌ(ሸጎሌ) ቅድስት ኪዳነ ምሕረት፤ ፠ ቀበና ቤዛዊተ ዓለም ቅድስት ኪዳነ ምሕረት፤ ፠ ኮተቤ ደብረ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ፠ ደብረ ወርቅ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት (ነፋስ ስልክ ላፍቶ) ፠ ቤዛ ብዙኃን ኪዳነ ምሕረት (ጎፋ ሠፈር) ፠ አዲስ አምባ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት (ነፋስ ስልክ ላፍቶ ፥ ቅዱስ ዮሴፍ አካባቢ) ፠ ጃቲ ደብረ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት (አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ) ፠ ቦሌ ሰሚት ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ፠ አያት ጌቴ ሴማኒ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ፠ ቀራንዮ መድኀኔ ዓለም (በድርብነት ይከበራል) ፠ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ (በድርብነት ይከበራል) ፠ ደብረ ሲና ቅዱስ እግዚአብሔር አብ (በድርብነት ይከበራል) ፠ ቦሌ (ገርጂ) ደብረ ገነት ቅዱ ጊዮርጊስና ቅዱስ ገብርኤል (በድርብነት ይከበራል) ፠ ኤረር ጎሮ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል (በድርብነት ይከበራል) ፠ ጽርሐ አርያም ቅዱስ ሩፋኤል (በድርብነት ይከበራል) ፠ መርካቶ ደብረ ኀይል ቅዱስ ራጕኤል (በድርብነት ይከበራል) በፎቶ ላይ የምትመለከታቸው አብያተ ክርስቲያን፤ 1ኛ) #አዲስ አበባ እንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳም፡፡ ይህች ገዳም ታሪኳ ከታላቁ ገዳማችን ዋልድባ (ገዳመ ዋሊ) ለ2ኛ ጊዜ መሥፋፋት (መመሥረት ጋር) የተያያዘ ታሪክ ያላት ናት፡፡ ይኸውም የሸዋ አባቶች ወደ ዋልድባ በ485 ዓ.ም. በንጉሥ አልአሜዳ ዘመነ መንግሥት ባቀኑ ጊዜ የተሰባሰቡባት ቦታ ናት፡፡ እነዚህም አበው ከመኖሪያ ቀዬቸው (ቡልጋ/ምንጃር/) ሲሆንሁለት ታቦታትን (ታቦተ ኪዳነ ምሕረት ዘምሕረት አምባና ታቦተ መድኀኔ ዓለምን ዘዐብየ ገዳምን) ይዘው ነበር፤ በዚህች በተቀደች ቦታ ይዘዋት በመጡት ታቦተ ኪዳነ ምሕረት ገዳመ ሐመረ ኖኅን መሥረተዋል፡፡ የመድኀኔዓለም ታቦትን ደግሞ በታላቁ ገዳም በዋልድባ አኑረዋል፡፡ ይህች ሐመረ ኖኅ፤ *በ500 ዓ.ም በአባ ሊባኖስ ዘመጣዕ የአንድነት ገዳም ሆና ተስፋፍታ ተቋቋመች፡፡ *በ9ኛ መቶ ክ/ዘመን ዮዲት ጉዲት የአክሱም ጽዮንን ቤተ መቅደስ ለማቃጠል ስትነሳ ንጉሡ አንበሣ ውድም ታቦተ ጽዮንን በምሥጢር በማስያዝ ወደ ሸዋ መጥተው በእንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነምሕረት ገዳም ታቦተ ጽዮንን አሳድረው ወደ ዝዋይ ደሴት ሲሄዱ ለገዳሟ ንዋየ ቅድሰት ስጦታ አበርክተዋል ጸበሏን ተጠምቀው ቦታውን መርቀው ሄደዋል፡፡ *በ12ኛው መቶ ክ/ዘመን ጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ከንጉሥ ላሊበላ ጋር ወደ ዝቋላ አምባ ሲመጡ በዚህች ገዳም በእንግድነት አድረው በጸበሏ ተጠምቀው ቦታውን ባርከዋል፡፡ * አፄ ዘርዐ ያዕቆብም ወደዚህች ገዳም መጥተው አቀማመጧንና የጸበሏን ፈዋሽነት ተመልክተዋል ‹‹ዳሯ እሳት መሐሏ ገነት ይሁን›› ብለው ብዙ ስጦታ አበርክተዋል፡፡ * አፄ ልብነ ድንግልም ወደ ገዳሟ መጥተው ተማኅጽኖ አድርገው በጸበሏ ተጠምቀው ታቦተ ልደታንና ብዙ ንዋየ ቅድሳት ሰጥተው ሄደዋል፡፡ * በንግሥት ዘውዲቱ ዘመነ መንግሥት ይህች ገዳም ሐመረ ኖኅ ኪዳነምሕረት ገዳም ተብላ ተሰይማለች፡፡ **ይህች ቦታ ከታላቁ ገዳም ከዋልድባ ጋር አሁንም ግንኙነቷ እንደጠነከረ ነው፤ ከዋልድባ ያሉ አባቶች በተለያየ ምክንያት ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ በዋነኛነት የሚያርፉባት ጥንተ ርስታቸውም ናት፡፡ **ይህች ቦታ በርካት ቅዱሳን በኪደተ እግር የረገጧት እንደመኾኗ፤ ጸበሏ የአጋንንት ድል መንሻ፤ የብዙ መነኰሳት መጠጊያ፤ የሕሙማን መፈወሻ፤ … በመሆኗ በአዲስ አበባ የእመቤታችንን ቃል ኪዳን ለማግኘት ብዙውን ጊዜ ለሱባኤ ከሚመረጡ ቦታዎችም አንዷ ናት፡፡ 2ኛ) #ደብረ_መድኀኒት_ዐቢየ_እግዚእ_ኪዳነ ምሕረት፤ * በሃገራችን ኢትዮጵያ የመጻሕፍተ ብሉያት አንድምታ ትርጓሜ ዋና ማስመስከሪያ መካነ አእምሮ (University) የኾነች፤ * ታላቁ ጻድቅ አቡነ ዐቢየ እግዚእ በኪደተ እግር የረገጧት፤ * በአቋቋም በኩልም የላይ ቤት አብነት የኾነች፤ * የታላላቅ ሊቃውንት መፍለቂያና ታላላቅ ሊቃውንት ወንበር ዘርግተው፥ ጕባኤ አስፋፍተው ያስተማሩባትና በማስተማር ላይ ያሉባት ቦታ ናት፡፡ የምትገኘውም ጎንደር ከተማ ነው፡፡ 3ኛ) #ኢየሩሳሌም_ደብረ_ገነት_ኪዳነ_ምሕረት፡፡ ሕንፃ ግንባታዋ፤ በዐፄ ዮሐንስ 4ኛ ተጀምራ በዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ የተጠናቀቀች፡፡ 4ኛ) አዲስ አበባ #ስዕል_ቤት_ኪዳነ_ምሕረት፤ በታዕካ ነገሥት በኣታ ለማርያም ግቢ ውስጥ የምትገኝ፡፡ በዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ የተሠራች፡፡ 5ኛ) #ራማ_ኪዳነ_ምሕረት፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#ዐርብ_የካቲት_13፤ #ከ፲፪-፪ ሰዓት #የሕይወት_ፈተና_ምንጮች_ክፍል_፲፩፡፡ #የማጠቃለያ_ትምህርት Shareee, Like … እንዳያመልጥዎ በጕባኤው ላይ ይገኙ፡፡ ፠ ለምን እንፈተናለን፤ ፠ ፈተናዎ
+1
#ዐርብ_የካቲት_13፤ #ከ፲፪-፪ ሰዓት #የሕይወት_ፈተና_ምንጮች_ክፍል_፲፩፡፡ #የማጠቃለያ_ትምህርት Shareee, Like … እንዳያመልጥዎ በጕባኤው ላይ ይገኙ፡፡ ፠ ለምን እንፈተናለን፤ ፠ ፈተናዎች ለምንና እንዴት ይመጣሉ፤ ፠ ፈተናዎችን እንዴት አድርገን ድል እናድርጋቸው፤ …. ፠ ……እንዳያመልጣችሁ፤ በሌሎችም ርዕሶች ዙሪያ በብዙ ጕባኤያት ላይ ያልተዳሰሱ ርዕሶች የሚዳሰሱበት ጕባኤ ስለሆነ እንዳያመልጣችሁ፤ #ደግመን_እንላለን_ይህ_ትምህርት_በፍጹም_እንዳያመልጣችሁ!!!!! ለተከታታይ ሳምንታት፤ ትምህርቱ ተከታታይነት ስላለው መቅረትና ማርፈድ አይመከርም!!፡፡ (፻፷፩ኛ ሳምንት የዐርብ ጕባኤ) #ዐርብ_የካቲት_፲፫፤ #ከ፲፪-፪ ሰዓት አሁንም በድጋሚ እንላለን ለሕይወታችን ወሳኝና በብዙ የትምህርት ጕባኤያት ላይ የማይዳሰሱ ትምህርቶች ስለሆኑ እንዳያመልጣችሁ!!!! የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#የዐቢይ_ጾም_ሳምንታት_ስያሜዎች ከፍኖተ ሕይወት ሰሌዳ መጽሔት የተወሰደ ፩ኛ)የመጀመሪያው እሑድ(ሳምንት)፥ #ዘወረደ (#ሙሴኒ፣ #ጾመ_ሕርቃል) ይባላል፡፡ በመጽሐፉ መጀመሪያ አምላክ ከሰማይ መውረዱን
+1
#የዐቢይ_ጾም_ሳምንታት_ስያሜዎች ከፍኖተ ሕይወት ሰሌዳ መጽሔት የተወሰደ ፩ኛ)የመጀመሪያው እሑድ(ሳምንት)፥ #ዘወረደ (#ሙሴኒ፣ #ጾመ_ሕርቃል) ይባላል፡፡ በመጽሐፉ መጀመሪያ አምላክ ከሰማይ መውረዱን፣ ሰው መሆኑንና መስቀሉን ስለሚያወሳ ነው፡፡ ፪ኛ. የሁለተኛው እሑድ፥ #ቅድስት ይባላል፤ ስለ ዕለተ ሰንበት ቅድስና ስለሚያወሳ ነው ፫ኛ. የሦስተኛው እሑድ፥ #ምኲራብ ይባላል፤ በዚህ ሰንበት ጌታ በመዋዕለ ትምህርቱ በምኲራብ ገብቶ ማስተማሩ ይነገራል፡፡ ፬ኛ. ዐራተኛው እሑድ፥ #መፃጉዕ ይባላል፤ ድውያንን መፈወሱን፣ ዕውራንን ማብራቱን፣ የሚያነሣ መዝሙር ይዘመርበታል፡፡ ፭. አምስተኛው እሑድ፥ #ደብረ ዘይት ይባላል፡፡ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ሁኖ ያስተማረው ትምህርት፥ የዳግም ምጽአትን ነገር የሚያስታውስ መዝሙር ይዘመርበታል፡፡ ፮. ስድስተኛው እሑድ፥ #ገብርኄር ይባላል፡፡ የጌታውን ብር ተቀብሎ ያተረፈበት፣ በጌታውም ፊት ምስጋናን ያገኘው ሰው ታሪክ ይዘመርበታል፡፡ ፯. ሰባተኛው እሑድ፥ #ኒቆዲሞስ ይባላል፡፡ በሌሊት ወደ ጌታ እየመጣ ይማር የነበረውን የኒቆዲሞስን ታሪክ የሚያስታውስ መዝሙር ይዘመርበታል፡፡ ፰. ስምንተኛው እሑድ፥ #ሆሣዕና ነው፡፡ ጌታ በአሕያ ውርንጭላ ሆኖ ሆሣዕና በአርያም እየተባለ ወደ ቤተ መቅደስ የገባበት ዕለት መታሰቢያ ነው፡፡  ከሠርክ ሆሣዕና እስከ ትንሣኤ ያለው ሰባት ቀን #ሕማማት ይባላል፡፡- የጌታን መከራና ስቃይ እንዲሁም ሞት የምናስታውስበት ሳምንት ነው ፡፡ #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#የዐቢይ_ጾም_ሌሎች_መጠሪ_ስያሜዎች ፩. #ዐቢይ_ጾም ይባላል፤ ፪. ጾመ ሁዳዴ ይባላል፤ ፫. #የካሣ_ጾም ይባላል፤ ፬. የድል ጾም ይባላል፤ ፭. #የመሸጋገሪያ_ጾም ይባላል፤ ፮. ጾመ አስተምህሮ ይባ
#የዐቢይ_ጾም_ሌሎች_መጠሪ_ስያሜዎች ፩. #ዐቢይ_ጾም ይባላል፤ ፪. ጾመ ሁዳዴ ይባላል፤ ፫. #የካሣ_ጾም ይባላል፤ ፬. የድል ጾም ይባላል፤ ፭. #የመሸጋገሪያ_ጾም ይባላል፤ ፮. ጾመ አስተምህሮ ይባላል፤ ፯. #የቀድሶተ_ገዳም ጾም፤ ፰. የመዘጋጃ ጾም ይባላል፤ ፱. #የሥራ_መጀመሪያ ጾም፤ ፲. ጾመ አርብዓ ይባላል፡፡ #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

እንኳን ለዐቢይ ጾም አደረሳችሁሁ፡ የ2012ዓ.ም. (አበቅቴ 6፤ መጥቅዕ 24 ነው) *ጾመ ነነዌ፤ የካቲት 2 (February 10) ሰኞ ውሏል፡፡ #ዐቢይ ጾም = 14 ተውሳክ + 2ቀናት(የጾመ ነነዌ) = 16፤ #የካቲት_16_ (February 24)ሰኞ_ይገባል፡፡ *ደብረ ዘይት = 11 ተውሳክ + 2ቀናት(የጾመ ነነዌ) = 13፤ መጋቢት 13 (March 22) እሑድ ይከበራል፡፡ #ሆሳዕና = 2 ተውሳክ + 2ቀናት(የጾመ ነነዌ) = 4፤ ሚያዝያ 4 (April 12) እሑድ ይከበራል፡፡ *ስቅለት = 7 ተውሳክ + 2ቀናት(የጾመ ነነዌ) = 9፤ ሚያዝያ 9 (April 17) ዐርብ ይውላል፡፡ #ትንሣኤ = 9 ተውሳክ + 2ቀናት(የጾመ ነነዌ) = 11፤ ሚያዝያ 11 (April 19) እሑድ ይከበራል፡፡ *ርክበ ካሕናት = 3 ተውሳክ + 2ቀናት(የጾመ ነነዌ) = 5፤ ግንቦት 5 (ረቡዕ ይውላል፡፡ #ዕርገት = 18 ተውሳክ + 2ቀናት(የጾመ ነነዌ) = 20፤ ግንቦት 20 (May 13) ኀሙስ ይውላል፡፡ *ጰራቅሊጦስ = 28 ተውሳክ + 2ቀናት(የጾመ ነነዌ) = 30፤ ግንቦት 30 (June 7) እሑድ ይከበራል፡፡ #ጾመ ሐዋርያት = 29 ተውሳክ + 2ቀናት(የጾመ ነነዌ) = 1(በ30 ተገድፎ)፤ ሰኔ 1 (june 8) ሰኞ ይገባል፡፡ *ጾመ ድኅነት = 1 ተውሳክ + 2ቀናት(የጾመ ነነዌ) = 3፤ ሰኔ 3 (June 10) ረቡዕ ይገባል፡፡ #ለቡ_!!፥ (N.B)፥ ልዩ ዓዋጅ፥ ልዩ መስታወሻ፤ ፠ ሁልጊዜም፤ ጾመ ነነዌ፥ ዐቢይ ጾምና ጾመ ሐዋርያት የሚጀምሩት በሰኞ ነው፡፡ ፠ ሁልጊዜም፤ በዓለ ደብረ ዘይት፥ ሆሳዕና፥ ትንሣኤና ጰራቅሊጦስ የሚከበሩት በእሑድ ቀን ነው፡፡ ፠ ሁልጊዜም፤ በዓለ ዕርገት የሚከበረው ኀሙስ ነው፡፡ ፠ ሁልጊዜም፤ ስቅለት የሚውለው ዐርብ ነው፡፡ ፠ ሁልጊዜም፤ ርክበ ካሕናት የሚውለውና ጾመ ድኅነት የሚጀመረው ረቡዕ ነው፡፡ ፠ እንደ አምናው የዐቢይ ጾም የየሳምንታቱን ማብራሪያና የየሰንበታቱን መዝሙርና ምንባባት የምናቀርብ መሆኑን እንዲሁም ‹‹ከሰይጣን ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ /ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን/፡፡›› የሚለውን ደግሞ ከክፍል 1 ጀምሮ ሰኞና ዐርብ የምናቀርብ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem