fa
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

رفتن به کانال در Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

کانال Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 406 مشترک است و جایگاه 5 570 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 189 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 406 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 12 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 76 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 7 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 25.12% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 9.38% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 871 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 446 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 23 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 13 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

15 406
مشترکین
+724 ساعت
+347 روز
+7630 روز
آرشیو پست ها
ዐርብ የካቲት 8 ፻፲፰ኛ ሳምንት ልዩ የዐርብ ጕባኤ የካቲት ፰ ፳፻፲፩ዓ.ም. ከ፲፪-፪ ሰዓት በሰዐቱ ይገኙ!!!!!!!! እንዳያመልጥዎ! ላልሰሙት ያሰሙ፤ <> በማድረግ ይተባበሩ የቀ.ደ.ሰ መድኀኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት

የነነዌ ሰዎችም ኃጢአታቸውን አምነው (ከኃጢአቱ የሌሉበትም ቢሆን መከራው ስለማይቀርላቸው) ከመሪ እስከ ተመሪ፤ እንደ አንድ ልብ መካሪ፥ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ሁነው፤ ንጉሡም በከተማዋ የጾም አዋጅ አስነግሮ፥ ከዙፋኑ ወርዶ፤ ሕዝቡም ማቅ ለብሰው፥ አመድ ነስንሰው፥ በፍጹም ልባቸው አዝነው አልቅሰው፥ ሕፃናት ከጡት፥ ከብቶችም ከሣር መሠማራት ተከልክለው፥ ያለምግብ በበረት ተዘግተው፤ ጾሙንም በልባዊ ጸጸት፥ ራስን ዝቅ በማድረግና በማዋረድ ንስሓ ገቡ /“የነነዌ ሰዎችም እግዚአብሔርን አመኑ” ዮናስ 3፡5 ‹‹... ለጾም ዐዋጅ ነገሩ፤ ከታላቁም ጀምሮ እስከ ታናሹ ድረስ ማቅ ለበሱ፡፡ ወሬውም ወደ ነነዌ ንጉሥ ደረሰ፡፡ እርሱም ከዙፋኑ ተነሥቶ መጎናጸፊያውን አወለቀ፤ ማቅም ለበሰ፤ በአመድም ላይ ተቀመጠ...” ዮናስ 3፥5-9፡፡/ እንዳለ ከአምላካችን ምሕረትን አገኙ፡፡ ነቢዩ ዮናስም ይህን አይቶ በየዋሕነቱ ‹‹እንግዲህማ ሊምራቸው ነው፣ እኔም ሐሰተኛ ነቢይ ልባል ነው›› ብሎ እያዘነና ከሕይወት ሞት ይሻላል ነፍሴን ከእኔ ውሰድ እያለ ከከተማ ወጥቶ ዳስ ሠርቶ ተቀመጠ፡፡ እግዚአብሔርም በውኑ ትቆጣ ዘንድ ይገባሃልን አለው፡፡ /ዮናስ. 4፥3-11/ አምላካችን መሐሪ በመሆኑ /አባት ለልጆቹ እንደሚራራ እንዲሁ እግዚአብሔር ለሚፈሩት ይራራል ፍጥረታቸውን እሱ ያውቃልና መዝ. 102፥8-14፡፡ ጥበብ 3፡፡/ ብለዋል፤ አምላካችንም /እናንተ ክፉዎች ስትሆኑ ለልጆቻችሁ መልካም ስጦታ መስጠትን ካወቃችሁ በሰማይ ያለው አባታችሁ ለሚለምኑት እንዴት አብልጦ መልካም ነገርን አይሰጣቸው ብሏል ማቴ. 7፥12/ ቀጥሎም ነቢዩ ዮናስ እንቅልፍ እንቅልፍ ብሎት ተኝቶ ቢነቃ ከራስጌው ቅል በቅላ ፀሐይ ስትከለክልለት አየና እጅግ ደስ አለው፡፡ ሁለተኛም ተኝቶ ቢነሣ ቅሏ ጠውልጋ፥ ደርቃ አገኘና አዘነ፡፡ እግዚአብሔርም ‹‹አንተ ላልተከልካትና ውኃ ላላጠጣሃት ቅል እንዲህ ስታዝን እኔስ በዝናም አብቅዬ፥ በፀሐይ አብስዬ ለምመግባቸው ሕዝቤ አላዝንምን?›› አለው፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር የዮናስን ፈቃዱን ይፈጽምለት (ሐሳዊ ነቢይ እንዳይሉት) ለምልክት እንዲሆን በሦስተኛው ቀን እሳት ከሰማይ ወርዶ ከፍ ከፍ ያሉትን ዕፅዋት ጫፍ ጫፋቸውን በልቶ ተመልሷል፡፡ ነቢዩ ቅዱስ ዮናስ በቀሪ ዘመኑ ፈጣሪውን እያገለገለ ኑሮ፤ በመልካም ሽምግልና በ170 ዓመት እድሜም መስከረም 25 አርፏል፡፡ ዮናስ በሕይወት ሥጋ ሣለ ሰማርያንና ነነዌን ብቻ ነበር ያስተማረው፤ ከሞተ በኋላ ግን ዛሬ ዓለምን የሚያስተምር ነቢይ ነው፡፡ /ከጾሙ ረድኤት በረከት ይክፈለን፤ የቀ.ደ.ሰ. መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት፡፡/

#ነነዌ **በጤግሮስ ወንዝ ምሥራቃዊ ቆሬ፥ ከዛሬዋ የሞሱል ከተማ በተቃራኒ ከባግዳድ በሰሜን ምዕራብ አቅጣጫ 350 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የነበረች ታላቅ ከተማ ነች፡፡ **ነነዌን በመጀመሪያ የቆረቆራት ናምሩድ ነው፡፡ /ዘፍ. 10፥11/ **በጣም ሰፊ ነበረች “የቅጥሯም ዙሪያ በእግር የሦስት ቀን መንገድ ያህል ነበረ” /ዮና. 3፥3/ **እግዚአብሔር አምላካችን ነነዌን “ታላቂቱ ከተማ” በሚል ቅጽል ጠርቷል፤ /ዮናስ 3፥2፤ 4፥11/ **ስለ መጥፋቷ ነቢዩ ሶፎንያስ “...ነነዌንም ባድማ እንደ በረሃም ደረቅ ያደርጋታል” በማለት ትንቢት ተናግሮባታል፡፡ /ትን. ሶፎ 2፥13/፡፡ እንደ ነቢያቱ ትንቢት ታላቋ ነነዌ ከ300 ዓመታት በኋላ ጠፍታለች፡፡ **የነነዌ ሰዎች በስብከተ ዮናስ አምነው፥ ንስሐ ገብተው ድነዋል፤ በዚህም ጌታችን በወንጌል ላይ ስለ ንስሓቸውና ስለ እምነታቸው /‹‹...የነነዌ ሰዎች በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥተው ይፈርዱበታል፤ በዮናስ ስብከት ንስሐ ገብተዋልና፡፡›› በማለት አመስግኗቸዋል፡፡ ማቴ 12፥41/ #ዮናስ_ነቢየ_አሕዛብ_ወሕዝብ **ዮናስ ማለት ርግብ፥ የዋኅ ማለት ነው፡፡ **በዳግማዊ ኢዮርብአም ዘመነ መንግሥት /825-784 ቅ.ል.ክ./ በሰማርያ የነበረ ነው፡፡ /2ነገሥ. 14፥25/፡፡ **ቊጥሩ ከ12ቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ ነው፡፡ **ነገዱ ከነገደ ይሳኮር ወገን ሲሆን፤ #አባቱ_አማቴ_እናቱም_ሶና(የሰራፕታዋ ደግ ሴት የሆነችውና ቅዱስ ኤልያስን በዚያ በረሃብ ዘመን የመገበችው ናት)፡፡ **ኤልያስ በረሃቡ ዘመን ወደ ሰራፕታዋ መበለት ቤት በመሄድ "ውኃ አጠጪኝ ጥቂት ቁራሽም አምጪልኝ" አላት፡፡ ‹‹ሕያው እግዚአብሔርን እፍኝ ዱቄት አለችኝ ጋግሬያት አንተም እኔም ልጄም (ዮናስ) በልተናት እንሞታለን›› አለችው፡፡ ኤልያስም "የረሀቡ ዘመን እስኪያልፍ ይበርክት" አላት፤ ከቤቷ ብትገባ ዱቄቱ በማድጋው፣ ዘይቱ በማሰሮው መልቶ አገኘች፡፡ ከጥቂት ጊዜም በኋላ ልጇ ዮናስ ታሞ ሞተ፡፡ እናቱም ሄዳ ነቢየ እግዚአብሔር ኤልያስን "ሳይገባኝ ከቤቴ ገብተህ ኀጢአቴን ተመራምረህ ልጄን ትገድልብኝ?" አለችው፡፡ ነቢዩ ኤልያስም ወደ አምላኩ ሰባት ጊዜ ጸሎት አድርሶ ዮናስን ከሞተ በኋላ አስነሥቶታል፡፡ **ዮናስ ትንሽ ከፍ ባለ ጊዜም ከነቢያት ጓደኞቹ አብድዩና ኤልሳዕ ጋር ሆነው የታላቁ ነቢይ የኤልያስ ደቀ መዛሙርት ሆኑ፡፡ /1ነገ.17፥1-24፤ 18፥10-24/ ነቢዩ ኤልያስ ካረገ በኋላ ደግሞ ሁሉም በተሰጣቸው አገልግሎት ተሠማርተው እግዚአቤሔርን አገለገሉ፡፡ ነቢዩ ዮናስ አርባ ዓመት ሲሞላው ሀብተ ትንቢት ተሰጥቶት ማስተማር ጀመረ፡፡ **የሰማርያውን ንጉሥ ኢዮርብአምን ጠቃሚ ምክር በመለገስ የእሥራኤልን ድንበር ከሔማት እስከ ዐረብ ባሕር ድረስ እንዲይዝ አድርጎታል፡፡ /2ነገሥ. 14፥25/፡፡ **ነቢዩ ዮናስ ምንም እንኳን የእስራኤል ነቢይ ቢኾንም ከምድረ እስራኤል ውጪ በነነዌ ስላስተማረ #ነቢየ አሕዛብ ወሕዝብ ይባላል፡፡ የትንቢት መጽሐፉም ዋና መልእክት እግዚአብሔር የእስራኤል ብቻ ሳይሆን የአሕዛብም አምላክ እንደሆነና በንስሐ ወደ እርሱ የተመለሱትን ሁሉ በምሕረት እንደሚጐበኝ ማሳየት ነው፡፡ #ዮናስና_ነነዌ_ **የነነዌ ሰዎች ኀጢአት ከመሥፈርቱ በማለፉ፤ የእግዚአብሔር ቃል ወደ አማቴ ልጅ ወደ ዮናስ መጣ “ተነሥተህ ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሂድ፤ የክፋታቸውም ጩኸት ወደ ፊቴ ወጥቷልና ለእነርሱ ስበክ” አለው፤ ዮናስ ግን የፈጣሪው መሐሪነት፥ ቸርነት መስፈርት እንደሌለው ያውቃልና፤ እርሱ ቢምራቸው ማን ለቃሉና ለትንቢቱ ይገዛል፤ እኔም ሐሰተኛ ነቢይ ልባል አይደለምን? ብሎ አልሔድም አለ፤ እግዚአብሔር እየደጋገመ ሲናገረው ግን ዮናስ የዋሕ ነበረና እንዲህ የሚዘበዝበኝ ከፊቱ ብቀመጥ አይደል ብሎ ከፊቱ ለመሰወር ወደ ተርሴስ በመርከብ ኮበለለ፡፡ **ዮናስ ወደ መርከብ ገብቶ ጕዞ ከተጀመረ በኋላ በእርሱ ምክንያት ታላቅ ማዕበል ተነሳ፤ በመርከቡ ውስጥ የተሣፈሩትም ሊያልቁ ሆነ፤ ሌሎች እንዲያ እየተናወጡ እርሱ ግን የእምነት ሰው፥ የዋሕና ቅን ስለሆነ ተረጋግቶ በመርከቡ ውስጥ ተኝቶ ነበር፡፡ መርከበኞቹም እጅግ ሲጨንቃቸው እያንዳንዳቸው ወደ አምላካቸው ጮሁ፤ መርከቢቱም እንድትቀልላቸው በውስጧ የነበረውን ዕቃ ሁሉ እያወጡ ወደ ባሕር ጣሉ፡፡ ባሕሩ ጸጥ ሊል ስላልቻለ ዮናስንም ቀስቅሰው “ይህ ክፉ ነገር በማን ምክንያት እንዳገኘን እናውቅ ዘንድ፤ ኑ ዕጣ እንጣጣል ተባባሉ፡፡” /ዮናስ 1፥7/፡፡ እጣ ቢጥሉ በዮናስ ላይ ወጣ፤ ዮናስም በራሱ ተጠያቂነት፤ ‹‹የእኔ ጥፋት ስለ ሆነ ወደ ማዕበሉ ጣሉኝ›› አላቸው፡፡ መርከበኞች ግን ዮናስን ለመታደግ የሚችሉትን ሁሉ አደረጉ፡፡ መርከቢቱ ወደ ምድር ትጠጋላቸው ዘንድ አብዝተው ቀዘፉ፤ የእርሱ ወደ ባሕር መጣል ፈቃደ እግዚአብሔር ስለሆነ ልፋታቸው ሁሉ ከንቱ ሆነ፡፡ ሁሉም አንድ ሆነው ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፡፡ “አቤቱ! አንተ እንደ ወደድህ አድርገሃልና ስለዚህ ሰው ነፍስ አታጥፋን፤ ንጹሕ ደምንም አታድርግብን፡፡” በማለት እያዘኑ በሐምሌ 15 ቀን ወደ ባሕሩ ጣሉት፤ ባሕሩም ከመናወጥ ጸጥ አለ፡፡ **ነቢዩ ወደ ባሕር ቢጣልም የእግዚአብሔር ጥበቃ አልተለየውምና ዮናስን ይውጠው ዘንድ ታላቅ ዓሣ አንበሪን አዘዘለት፡፡ ነቢዩ ዳዊት ‹‹እግዚአብሔር የቀባውን እንዳዳነው ዛሬ ዐወቅሁ›› እንዳለ /መዝ. 19፥6/ የመረጠውን ነቢይ ለማዳን ዓሣ አንበሪን አዘጋጀለት፡፡ *ዮናስም በአሣ አንበሪ ሆድና በማዕበል ውስጥ ሆኖ ለ3 ቀናት ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፤ በመጽሐፍ ቅዱስም በዓሣ ሆድ ተጕዞ ያስተማረ፥ ትንቢትም የተናገረ የመጀመሪያ ነቢይ ሆነ፡፡ ዓሣ አንበሪው ዮናስን በሆዱ ቋጥሮ የሦስት ቀን ጎዳና በባሕር ውስጥ ገስግሶ በ3ኛው ቀን ነነዌ ዳር ደረቅ መሬት ላይ አራግፎ ተፋው፡፡ /ዮናስ 1፥4-16፤ 2፥1-11፣ መዝ. 138፥7-10/፡፡ **ዮናስ በግዙፉ አሣ አነበሪ ውስጥም ያለ እንቅልፍ በጾም፥ በጸሎትና በምስጋና ለ3 ቀናት መቆየቱ ለክርስቶስ ትንሣኤ ምሳሌ ነው፤ ዮናስ በአሣ አንበሪ ሆድ 3 ቀን 3 ሌሊት ኑሮ፥ ሙስና (ጥፋት) ሳያገኘው መውጣቱ አዳምና ልጆቹን ለማዳን የመጣው ጌታችንም 3 መዓልትና 3 ሌሊት በከርሠ መቃብር አድሮ ከሙታን ተለይቶ የመነሣቱ ምሳሌ ነው፡፡ ለዚህም ራሱ ጌታችን በወንጌል ‹‹ክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክት ይሻል፡፡ ከነቢዩም ከዮናስ ምልክት በቀር ምልክት አይሰጠውም፡፡ ዮናስ በአሣ አንበሪ ሆድ 3 ቀንና 3 ሌሊት እንደ ነበረ፤ እንዲሁ የሰው ልጅ በምድር ልብ 3 ቀንና 3 ሌሊት ይኖራል፡፡ የነነዌ ሰዎች በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥተው ይፈርዱበታል፡፡ በዮናስ ስብከት ንስሐ ገብተዋልና፡፡ እነሆም ከዮናስ የሚበልጥ ከዚህ አለ፡፡›› /ማቴ. 12፥39/ **እግዚአብሔር አምላክም ለሁለተኛ ጊዜ ዮናስን ወደ ነነዌ እንዲሄድ አዘዘው፤ “ተነሥተህ ወደዚያች ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሂድ፤ የነገርሁህንም የመጀመሪያውን ስብከት ስበክላት” አለው፡፡ ዮናስም እንቀድሞው ሳያንገራግር ወደዚህች ከተማ ገብቶ እንዲህ እያለ ‹‹እስከ ሠሉስ ዕለት ትትገፈታእ ነነዌ ዐባይ ሃገር›› (እስከ ሦስት ቀን ድረስ ነነዌ ትገለበጣለች) ንስሐን ሰበከ፥ አስተማረ፡፡

#በአዲስ_አበባ_በብቸኝነት_እንደ_ደብረ_ሊባኖስ_ገዳም_በየቀኑ_ውዳሴ_ማርያም_በዜማ፥#ክስተተ_አርያም_በዜማ፤#መስተጋብዕ_በዜማ_የሚያደርሰው_ደብራችን_ደብረ_ሰላም_የዜማ_ትምህርት_የተጀመረበትን_፳፮ኛ #ዓመት_ጥር_18 (22) 2011 ዓ.ም. አክብሯል፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን የምታስምራቸውን ትምህርቶች በዘርፍ በዘርፍ ከፍላ ነው የምታስተምረው፤ እነዚህም የፊደል ቤት፣ የንባብ ቤት፣ የዜማ ቤት (ከሰላም ለኪ ዜማ ጀምሮ ውዳሴ ማርያም፣ ሰዐታት፣ ቅዳሴያት፣ ምዕራፍ፣ ድጓ፣ ዝማሬ፣ መዋስዕት፣ አቋቋም፣….)፣ የቅኔ ቤት፣ የትርጓሜ ቤት፣ የቊጥር (የአቡሻኽር) ቤት ብላ በመክፈል ነው፤ ከእነዚህ ትምህርቶችም አብዛኞቹ በደብራችን የሚሰጡ ቢኾንም፤ የዓለማዊ (የአስኳላ) ትምህርት በእጅጉ እየተስፋፋ በመጣባቸው ዘመናት (ከ1960-1980 ተማሪዎች በቀኑ መርሐ ግብር የዓለማዊ (የአስኳላ) ትምህርት ስለሚማሩ የቤተክርስቲያንን ትምህርት የሚማሩበት ጊዜ አጥተው፤ ደብራችንም በአዲስ አበባ ከሚገኙ አድባራትና ገዳማት ሰፊ አጥቢያን የሚያቅፍና የብዙ ሊቃውንት መኖሪያ እንደመኾኑ መጠን ከአጥቢያው የሚወለዱ ተተኪ እንደሚፈለገው መጠን ሳይኾን እስከ 1985ዓ.ም. ዘልቆ ነበር፡፡ ይህንን ችግር በውል የተረዱት ቄሰ ገበዝ መርሐ ጽድቅ ኃ/ጊዮርጊስ በቀኑ መርሐ ግብር የአስኳላ ትምህርታቸውን ለሚማሩ ተማሪዎች በማታው መርሐ ግብር የንባብና የዜማ ትምህርትን በራሳቸው ተነሳሽነት ‹‹ዘነሳእክሙ በጸጋ፥ ሀቡ በጸጋ›› የሚለውን ሲማሩ ያደጉትን የወንጌል ቃልና፤ ቀደሞውንም የተማሩት ከታላቁ ሊቅ አለቃ መርዓዊ ሣህለ ሚካኤል በመኾኑ፤ የወንጌልን ቃልና የመመህራቸውን አሠረ ፍኖት ተከትለው ያለምንም ደመወዝ በመቃብር ቤት ማስተማር ጀመሩ፤ እነኾ ዘንድሮም ማስተማር ከጀመሩ 26 ዓመታትን አስቈጠሩ፤ በእነዚህ ዓመታትም ከ850 በላይ ተማሪዎችን ሲያስተምሩ አብዛኞችንም እስከ ዲቁናና ቅስና ማዕርግ ያበቁ ትጉህና ታታሪ መምህር ናቸው፤ ማታ ማታ ከ12፡30-3፡00 ለ26ዓመታትም ተማሪዎቼን ማስተማር ይበልጥብኛል ብለው ብዙ ነገሮችን (ማኅበራዊ ጉዳዮችን ሳይቀር) ትተው እያስተማሩ ያሉ ታላቅ መምህራችንም አባታችንም ናቸው፡፡ ሰንበት ትምህርት ቤታችንም ላፈራቻቸው ዲያቆናትና ቀሳውስት ትልቁን አስተዋጽዖ ያደረጉት እኒሁ መምህር ናቸው፡፡ ስለ መምህራችንም የቱን ተናግረን እንዘልቀዋለን!! ወደፊት የእርሳቸውን የሕይወት ልምድ፣ ምክር ይዘን የምንቀርብ መኾኑን እንገለጽን፤ የዜማ ትምህርቱ ከዛሬ ከ26 ዓመታት በፊት በ1985ዓ.ም. በመቃብር ቤት በመመህራችን በቄሰ ገበዝ መርሐጽድቅ ኃ/ጊዮርጊስ (ከ10-15 በሚጠጉ ተማሪዎች /ለአብነትም ሸዋረጋ አዳነ፣ ሚሊዮን ከበደ፣ አዲስ ወርቅ ደበበ፣ ደረጀ ተክሌ፣ በላይ አዳነ፣ መሳፍንት አለማየሁ፣ …./ ተነሳሽነት የተጀመረ ነው፡፡ በመቀጠልም ተማሪው እየበዛ በመምጣቱ የዜማ መማሪያ ቦታው (መቃብር ቤቱ) ባለመቻሉ ወደ ደወል ቤት መጣ በቅቱም ይማሩ የነበሩ ተማሪዎች በግምት 120-125 ይጠጉ ነበር (በወቅቱ ይማሩ ከነበሩት ውስጥም ለአብነት ያህል ቴዎድሮስ አዳነ፣ ዮሐንስ ደምሴ፣ ወንድይፍራው ጌታቸው፣ ፍስሐ አዱኛ፣ ተፈሪ ተስፋዬ፣ ሰብስቤ ተክለማርያም፣ ዘለዓለም ተረፈ፣ ዘካርያስ አለማየሁ፣ መልአኩ ገብረሥላሴ፣ (አቡሽ) ገብረሥላሴ፣ ቃልአብ አለማየሁ፣ ሔኖክ አለማየሁ፣ ሚሊዮን እሸቱ፣ ዐሥራት ለይኩን፣ ሚሊዮን ለይኩን፣ ተክሉ ተዋበ፣ ፣ ተስፋዬ ገብረሥላሴ፣ ደሳለኝ ገብረ ሥላሴ፣ ምሕረቱ አዳነ፣ በልሁ ሰሎሞን፣ ጥበቡ መኮንን፣ ከተማ ወርቅአለማሁ፣ ቡሩክ አድማሱ፣ ደርብ ወርቁ፣ ዐሥራት ማሙዬ፣ ዐቢይ አለማየሁ፣ ግሩም መልአኩ፣ አበባየሁ ዕንቈ፣ ጌትዬ ዕንቈ፣ ዳንኤል ገብረ ሥላሴ፣ ካሣ ፍቅሩ፣ አፈወርቅ ማሞ፣ ጸጋ ዘአብ ማሞ፣ ስንሻው ውብአየሁ፣ ይስሐቅ ውብአየሁ፣ ስዩም አስቻለው፣ ናርዶስ ንጉሤ፣ አቡሽ ጌታቸው፣ ………… ይገኙበታል፤ አብዛኛው ተማሪዎችም የማርገጃ አካባቢ ልጆች ነበሩ፤ በአብዛኛው የአካባቢ ተወላጆች ዲያቆናትን ደብሩ ያፈራበት ዘመን ነበር፤ ለዚህም የዜማ ትምህርቱ ከፍተኛውን ሚና ተጫውቷል፡፡ ከደወል ቤት ቀጥሎ የመማሪያ ቦታው ወደ ወንዶች መጠለያ (ገረገራ)ና በመሃል ላይ ወደ ደብሩ የአብነት ትምህርት ቤት እየተዘዋወረ ትምህርቱ ሲሰጥ ቆይቷል፤ በዚህ ወቅትም ከ105-110 የሚጠጉ ተማሪዎች ሲኾኑ፤ በወቅቱ ከተማሩ ተማሪዎች መካከልም መስፍን ለገሠ፣ ስመኘው ጌትዬ፣ ዮሐንስ ጌትዬ፣ ዘካርያስ ጌትዬ፣ ሱራፌል አውግቸው፣ ወንድወሰን ሺፈራው፣ ኢሳያስ ቦጋለ፣ ያሬድ እንደሻው፣ ….. ይገኙበታል፤ በዚህ ወቅትም ከማርገጃ አካባቢ በተጨማሪ ከሌሎች የደብሩ አጥቢያዎች (ከቀጨኔ፣ ከሰሜን፣ ከችሎት፣ ከ20ቀበሌና ከመነን) መጥተው ተማሪዎች መማር የጀምሩበት ነበር፡፡ አሁን ባለንበት ጊዜ ደግሞ በቋሚነት በወንዶች መጠለያ (ገረገራ) ትምህርቱ እየተሰጠ ይገኛል፤ እየተማሩ ያሉትም ተማሪዎች ከ100-120 ሲኾኑ፤ እየተማሩና እያስተማሩ ካሉት ተማሪዎች (ዲያቆናት ጭምር) መካከልም ለአብነት ቡሩክ መርሐ ጽድቅ፣ አበበ ብርሃኑ፣ ዳንኤል እስጢፋኖስ፣ አዳም ተሾመ፣ ሰሎሞን ብርሃኑ፣ ዳግም ተሾመ፣ ተመስገን ማሞ፣ አርከቦም አርአያ፣ አሮን አርአያ፣ ዮናስ ባየልኝ፣ አውግቸው ተጫን፣ ያሬድ ብርዙ፣ ተክለማርያም ሰብስቤ፣ አሸናፊ ጌቱ፣ …… ይገኙበታል፤ በአሁኑ ወቅትም በፊት ወንድሞች ይማሩ የነበረው ይህ የማታ የዜማ ትምህርት እኅቶችንም ያካተተ ሁኗል፡፡ አሁን ባለበት የዜማ ትምህርት ሒደት ከምሽቱ 12፡30 ላይ ውዳሴ ማርያም በዜማ፥ ክስተተ አርያም በዜማ፤ እንዲሁም መስተጋብዕ በዜማ ከደረሰ በኋላ የትምህርቱ መርሐ ግብር እስከ ምሽቱ 2፡30 ድረስ ይካሔዳል፤ ከ26 ዓመታት በፊት የዜማ ትምህርቱ በተጀመረበት ወቅት ግን መርሐ ግብሩ ላይ ይደርሱ የነበሩት የዜማ ይዘቶች አሁን የሚደርሱት እንዳሉ ሁኖ ሌሎች የቅዱስ ያሬድ የዜማ ድርሰቶችም የሚጨምር ነበር፡፡ ይህ የዜማ ትምህርት ከቀድሞ የወረሰውን የፍልሰታ ልዩ የሱባኤ የጸሎት መርሐ ግብር እና የደብረ ታቦር ዝክርን፤ አሁንም ሳይቋረጥ አሁን በመማር ላይ ያሉ፣ ከዚህ በፊት የተማሩና የደብሩ ማኅበረ ካህናትና ዲያቆናት በአንድነት በመኾን ሱባኤውንና የደብረ ታቦር ዝክሩን አጠናክረው የቀጠሉበት ኹኔታ ነው ያለው፡፡ የዘንድሮ የዜማ 26ኛ አመት ሲከበርም ለበርካታ ሊቃውንት ዋልታ የኾኑትና በደብራችንም የሚገኙትን /የዜማ መመህራችንን ቄሰ ገበዝ መርሐ ጽድቅ ኃ/ጊዮርጊስና፣ የደብራችን የመጻሕፍት መምህር መምህር ላዕከ ሰላም እንዲሁም የቀድሞ ተማሪዎች ጨምረው ተገኝተዋል፡፡

#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤#ክፍል፫_ #ሰይጣን_ሰዎችን_እንዴት_እንደሚፈትንና_ኃይል_እንዴት_እንደሚያገኝ_የሐሰት_አባት_ሁኖ_ሳለ_ሰዎች_እንዴት_እንደሚያምኑትና_ባይፈልጉም_አምላካቸውን_እንደሚያመሰግኑና_እንደሚታዘዙ፡፡ በሳምር ሃገር ሰሉቅያ (አስቀሎና) በምትባል ቦታ ከሄሮድስ ወገን የሚሆኑ ጣዖት የሚያመልኩ ክፉዎችና ኀጢአተኞች ነበሩ፤ ሴቶችም ወንዶችም ከሚስቶቻቸውና ከባሎቻቸው ከልጆቻቸው ጭምር ተሰብስበው በየወሩ ወደ ጭፈራ ቤት የመግባት ክፉ ልማድ ነበራቸው፡፡ ቅዱስና ንጹሕ፥ ጻድቅና መስተጋድል፥ መነኰስና ካህን አባ ጳውሊ ከዚህች አገር ደርሶ፤ የዚያችን ሃገር ሰዎች ወደ ጭፈራ ቤት ሲሄዱ ባደረበት ጸጋ እግዚአብሔር የሰዎቹን የኀጢአት ሥራ አውቆ ፈጽሞ አዘነ፤ ወደ ዳንስ ቤቱ ተጠግቶም ከበር ቆመ ሰዎቹም መብራት አጥፍተው፥ ራቁታቸውን ሆነው በዱር እንዳሉና እንደጠገቡ ፈረሶች ሲጮሁ ሰማቸው፡፡ አባ ጳውሊም ወደ እግዚአብሔር እነዚህ ሰዎች ለሌሎች የኀጢአት አብነት እንዳይሆኑ ቅጣቸው፤ አጥፊ የሆነውንም ሰይጣን በኀይልህ አጥፋው እያለ በፍጹም ልቡ ጸለየ፡፡ እግዚአብሔርም ጸሎቱን ሰማውና አጥፊ የሆነው ሰይጣን የሚንቦገቦግና የተመዘዘ ሰይፍ ይዞ እንዲገለጽለት አደረገ፡፡ +አባ ጳውሊ፤ ሰይጣንን አንተ ማነህ? ማንንስ ትፈልጋለህ? ሰይፍህ በእጅህ የተመዘዘው ለምንድን ነው? አለው፡፡ ሰይጣን፤ የምትሻውን ንገረኝ እንጂ አንተ ማነህ አትበለኝ፤ ከፈጣሪህ የለመንከውን አንተ ታውቃለህና አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ የአንተን ሥራ የሚሠሩትን ወዳጆችህን (ጭፈራ ቤት ያሉትን) እንዴት ታጠፋለህ አለው፡፡ ሰይጣን፤ እኔ ከፈጣሪ ታዝዣለሁ፤ የአዛዤን ትእዛዝ እተላለፍ ዘንድ አይቻለኝም አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ ብዙ ጥያቄ እጠይቅሃለሁና እንዳትዋሸኝ በሕያው በእግዚአብሔር ስም አምዬሐለሁ፥ አውግዤሃለሁ፥ በቅዱስ መስቀሉ አስሬያለሁ አለው፡፡ ሰይጣን፤ በሰዎች ላይ የማደርገውን ክፉ ሥራዬን ልትገልጽብኝ ነውን? የምትሻውን ጠይቀኝ፤ ትእዛዛህን አልተላለፈም ኀይሌ በጸሎህ ደክሟልና አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ ከሰዎች በአንዱ አድረህ በኀጢአት ትጥለው ዘንድ አጋዥ የሚሆንህ ምንድን ነው? /ሔዋንን በእባብ አዳምን በሔዋን ማሳቱን ልብ ይሏል/ ሰይጣን፤ ሰው #በእግዚአብሔር_ሕግ_ጸንቶ ሳለ በማንም ላይ ማደር አይቻለንም፤ ከእግዚአብሔር ሕግ ትንሽ ፈቀቅ ቢል፤ እንዲሁም #በየጊዜው_ስሙን_ከልቡ_ባይጠራ (በፍጹም ሃይማኖት ሁኖ የማያማትብ፤ ሕፃን ቢሆንም ከመጠመቁ በፊትም እናቱ የማታማትብና የእግዚአብሔርን ስም የማትጠራ ከሆነ፤ ባለትዳሮችም ከመጋባታቸው በፊት በካህናት ጸሎት በሚጋቡ ጊዜ በሥጋ ወደሙ በመኝታቸው አንድ በሚሆኑ ጊዜም የአምላክን ስም የማይጠሩ ከሆነ) ያንጊዜ በሰው ላይ ለማደር ኀይል እናገኛለን፤ በእነርሱና በልጆቻቸውም ላይ እናድራባቸዋለን፤ እንሰለጥንባቸዋልን፤ ሰላምንና ፍቅርን እናሳጣቸዋለን፤ ኑሯቸው ጠብና ክርክር እንሞላበታለን፤ መጨረሻቸውም መለያየት ይሆናል አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ መላውን የዓለምን ሰዎች የምትፈትናቸው በምንድን ነው? አለው፡፡ ሰይጣን፤ እንደምኞታቸው እንፈትናቸዋለን፤ ሥጋዊ ሐሳብን አሣምረን እናቀርብላቸዋለን፤ በከራት በትምክት እናቃጥላቸዋልን፤ እንቅልፍንና ዝሙት መመኘትን እናመጣባቸዋለን፤ ጾም እንዳይጾሙ፥ ጸሎት እንዳይጸልዩ እናደርጋቸዋለን፤ ከሥጋ ወደሙና ከመልካም ሥራ ሁሉ እናርቃቸዋለን፡፡ ዘወትር ይህን ዓለም በማሰብ (በስካር፥ በውሸት፥ በቂምና በቅናት፥ ሐሰት በመመስከር፥ ወርቅና ብርን በመውደድ፥ በስንፍና፥ ሰውን በመስደብ አእምሯቸው እንዲጠፋ እናደርጋለን፡፡ ቅዱሳንን ሳይቀር ልባቸው ከእግዚአብሔር ፍቅር እንዲርቅ፥ ቃልኪዳናቸውን እንዲተዉ በተለያዩ ምክንያት ባለን ኀይል እንዋጋቸዋለን አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ ሰውን ታጠፋ ዘንድ ኀይልና ሥልጣን የምታገኘው እንዴት ነው? አለው፡፡ ሰይጣን፤ #የእኛን ሐሳብ ተከትለው ኀጢአትን አዘውትረው በሚሠሩ ክፉዎችና አመንዝራዎች እንዲሁም ፈጽመው ንስሐ በማይገቡ ላይ ነው፡፡ የሚጠብቋቸው ቅዱሳን መላአክት ስለበደላቸውና ስለ ኀጢአታቸው ሲርቋቸው ያንጊዜ እኛ በእነርሱ ላይ እንበረታለን፡፡ #ክፉ ሥራንም ሁሉ ወደው እንዲሠሩ እናደርጋቸዋለን፡፡ መልካም በማስመሰል በሐሰተኛ ሕልም እናስታቸዋለን፡፡ እኛ እግዚአብሔርን መሳደብና መንቀፍ ባይቻለን ሰዎች ፈጣሪያቸውን ና ድንግል ማርያምን እንዲሁም ቅዱሳን መላእክትንና ቅዱሳን ሰዎችን ለመስደብና ለመንቀፍ እንዲነሳሡ እናደርጋቸዋለን፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ አንተ ሐሰተኛና የሐሰት አባቷ ሆነህ ሳለ /ዮሐ. ፰፥፵፬/ ሰዎች ቃልህን እንደት ያምኑሃል? አለው፡፡ ሰይጣን፤ አንተና እንዳንተ ያሉ ባታምኑኝም በኋላ ዘመን ብዙ ሰዎች በእኔ ቃል ያምናሉ፥ ምክሬን ይቀበላሉ፥ ጥበቤን ይፈልጋሉ፡፡ ያለ ጊዜዬ አኔን ማጥፋት የማይሻ ጌታ ክርስቶስን እንኳን ፈትኜዋለሁ አለው፡፡ እግዚአብሔርን የምናመሰግንበት ሰዐት ደርሷልና የታዘዝኩትን ፈጥኜ አደርግዘንድ ልቀቀኝና ልሂድ አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ እግዚአብሔርን በምታመሰግኑበት ጊዜ ጥቅማችሁ ምንድን ነው? አለው፡፡ ሰይጣን፤ በተፈጠርን ጊዜ ምስጋናው በአንደበታችን ተፈጥሯልና፤ ስሙ ኅቡዕ ለሚሆን ብርሃናትና ለፈጠረ ለእርሱ የምንሰግድበትና የምናመሰግንበት ሰዐት አለን እንጂ የምንጠቀመው ጥቅምና ክብር የለንም አለው፡፡ #ሰዐቱን ጠብቀን ካላመሰገንን መኖር አንችልም አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ የምትሰግዱትና የምታመሰግኑት በፈቃዳችሁ ነውን? ወይስ ያለፈቃዳችሁ? አለው ሰይጣን፤ በግድ ነው እንጂ ደስ ብሎን አናመሰግንም አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ ደስ የማይላችሁ ለምንድነ ነው? አለው ሰይጣን፤ ከክብራችን ተዋርደን ጨለማ ከለበስን በኋላ ደስታ የለንም፤ ደስ ብሎንም አናመሰግንም፡፡ ስለዚህ እስከዛሬ ምስጋናውን አቋርጠን አናውቅም አለው፡፡ #ክፍል ፬.… ሰይጣን የቅዱሳን መላእክትን ቃል(ምሥጢር) እንደሚሰማና ከመደረጉ በፊት ለሰዎች በመናገር እንደሚያስት፤ ሰይጣን ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ በዘመን ብዛት ሰውን ያሚያስትበት ብዙ ጥበብ እንዳለው፤ የክርስቶስ ሰው መሆን ከሰይጣን የተሰወረ እንደነበር፤ ሰይጣናት አለቃና ታዛዥ እንዳላቸው፤ ገሃነነም ስለመኖሩና ዲያብሎስ ለምን ንስሐ እንደማይገባ፤ ክፍል ፬.… ይቀጥላል ነገ ይጠብቁን/ /#ዋልድባ_ዋሊ_ገጽ/

#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤ #ክፍል፪_መቅድም #ሰይጣን_ምንጊዜም_ቢሆን_እንደየሰው_ምኞትና_ፍላጎት፥ #እንደ_ጊዜውና_እንደ_ሰዐቱ፥ #እንደ_ዘመኑና_እንደ_ወቅቱ_ተጨባጭ_ሁኔታ_የማሳት_ጥበቡን_እየለዋወጠ_ይጠቀማል፡፡ (ሳኦል የአማሌቃውያንን ምርኮ ባገኘበት ወቅት፣ ሐናንያ ገንዘብ በእጁ በገባበት ወቅት ሰይጣን እንደፈተናቸው ልብ ይሏል /ሐናንያ ሆይ መንፈስ ቅዱስን ታታልል ዘንድ ከመሬቱ ሽያጭ ታስቀር ዘንድ ሰይጣን በልብህ ስለምን ሞላ?፡፡›› ሐዋ. ፭፥፫/ እኛንም እንዲሁ እንደ ዘመናችን ሁኔታ መልኩን እየለዋወጠ ይፈትነናል፡፡ እርሱ የ7511 ዓመታት የመፈተን የሥራ ልምድ ያለው ነውና!!፡፡ ##መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም የመጣውና መጽሐፍ ቅዱስም የተጻፈበት ዐቢይ ጉዳይ ሰይጣን በሰው ልጆች ላይ እያደረሰ ካለው ጉዳትና ጥፋት ለመታደግና ችግሩንም በዝርዝር ለማሳወቅና ሰዎችም የሰይጣንን ክፉ ሥራ ዐውቀው እንዲርቁ ለማድረግ ነው፡፡ /‹‹የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ፡፡›› ፩ዮሐ. ፫፥፰/ ‹‹በእኔም የሚያምን ሁሉ በጨለማ እንዳይኖር እኔ ብርሃን ሆኜ ወደ ዓለም መጥቻለሁ፡፡›› ዮሐ. ፲፪፥፵፮ ***ነገር ግን ጌታችን ወደዚህ ዓለም በመምጣቱ፤ ሰው በመሆኑ ይህ የሕይወት ብርሃን ለዓለም ቢበራም፤ ሁሉም #ሰው ነፃ ፈቃዱን ተጠቅሞ ከዲያብሎስ ሽንገላ ለመላቀቅ ፈቃደኛ አለመሆኑን ተመልክቶ /‹‹ወደ ሕይወት የሚወስደው በር የጠበበ መንገዱም የቀጠነ ነውና የሚገቡትም ጥቂቶች ናቸው፡፡›› ብሏል ማቴ. ፯፥፲፬/ ጌታችን እንዲህ ያለው ሰዎች ነፃ ፈቃዳቸውን ተጠቅመው የሰይጣንን ፈቃድ በመፈጸም በፈቃደ ሥጋቸው ስለሚመሩና የእርሱን ትዕዛዝ ለመፈጸም ደስተኛና ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ለመግለጽ እንጂ ወደ ሕይወት የሚወስደው መንገድ የሚጠብ ሁኖ አይደለም፡፡ ይህ የሕይወት መንገድ የሚሰፋው የራስ ፈቃደኝነት ሲታከልበት ነው፡፡ #ለሰው ልጅ ወደ ሕይወት ለመግባት ወሳኙ ነገር ፈቃደኝነት ነው፡፡ እግዚአብሔር ሁሉን አዋቂ ቢሆንም የሰውን ልጅ ሲፈጥረው ነጻ ፈቃድ ያለው አድርጎ ስለፈጠረው መልካሙን ነገር ሊያደርግ በሚፈልግበት ጊዜ ፈቃደኝነታቸው ይጠይቃል፡፡ /ድውያንን ሲፈውስ ልትድን ትወዳለህን እያለ የሚጠይቃቸውን ልብ ይሏል፡፡ ዮሐ. ፭፥፮/ #የራስ ፈቃደኝነት ካለ ትእዛዛትን መጠበቅ ቀላል ይሆናል፡፡ /የዘለዓለምን ሕይወት እወርስ ዘንድ ምን ላድርግ ብሎ ለጠየቀው ሀብታም ጎልማሳ ‹‹ወደ ሕይወት መግባት ብትወድ ትእዛዛትን ጠብቅ … ፍጹም ልትሆን ብትወድ ሂደህ ያለህን ሸጠህ ለድሆች ስጥ፤ መዝገብም በሰማያት ታገኛለህ፡፡›› ነገር ግን ሀብታሙ ጎልማሳ ፈቃደኛ ባለመሆኑ ታላቅ ሐዘን ተሰምቶታል፡፡ ማቴ. ፲፱፥፳፩/ #ጽድቅ፣ ቅድስናና ሰይጣንን ማሸነፍ የሚመጣው በራስ ፈቃደኝነት ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ #አንድ_ሰው_በፍጹም_ትሕትና_ትእዛዛትን_ለመጠበቅ_የራስ_ፈቃደኝነት_ካለውና_ንስሐ_ከገባ__በቀላሉ_ሰይጣንን_የሚያሸንፍበት_ኀይል_ከእግዚአብሔር_ያገኛል፡፡ ሰይጣንም የብዙ ዘመን ልምድ ስላለው ይህን ሁኔታ ጠንቅቆ ስለሚያውቅ ሰዎች፤ ++ሰዎች ትእዛዛትን ለመጠበቅ የራስ ፈቃደኝነት እንዳይኖራቸው የተለያየ ምክንያት በመፍጠር አጥብቆ ይዋጋቸዋል፡፡ ++ሰዎች ትእዛዛትን ሊጠብቁና ንስሐ ሊገቡ ሲያስቡ በታላቅ ፍርሃትና ስጋት እንዲያዙ ያደርጋቸዋል፡፡ ++ሰዎችን ሕግና ትእዛዛትን መፈጸም ከባድና ጭንቅ፥ በሩም የጠበበ፥ ፈጽሞም የማያሳልፍ አድርጎ ያሳያቸዋል፡፡ ++ሰዎች ትእዛዛትን የሚጠብቁና በቁርጠኝነት ንስሐ የሚገቡ ከሆነ በዚህ ምድር ላይ መኖር እንደማይችሉና ታላቅ ጉዳት እንደሚደርስባቸው ደጋግሞ በማሳሰብና በማስፈራራት ያሳምናቸዋል፡፡ … ነገር ግን በፍጹም ትሕትናና በራስ ፈቃደኝነት ትእዛዙን በመጠበቅና ንስሐ በመግባት ከዚህ ሰይጣናዊ ውጊያ ነጻ ይወጣሉ፤ ነጻ ሲወጡም በሰይጣን አሳሳቢነትና ማስፈራርት ከባድ መስሎ ይታያቸው የነበረው ትእዛዛት ለእነርሱ የደስታና የሰላም ምንጭ ይሆንላቸዋል፡፡ /ይህንንም በሐዋርያትና በቅዱሳንና ቅዱሳት ሕይወት ታውቋል ማቴ. ፲፩፥፳፰/ ከእውነተኛ (መንፈሳዊ) ሕይወት ርቀው የሚኖሩ ሰዎች በጥቂት የፈተና ሰዐት ስንኳ መታገሥና መረጋጋትን፥ ሰላማዊነትንና አስተዋንትን አጥተውና ተስፋ ቆርጠው ለከፋ ችግር የሚጋለጡት አስቀድሞ የጠጠጋቸው ሰይጣናዊ መንፈስ ስለሚያስጨንቃቸውና ስለሚያስፈራራቸው ነው፡፡ #የሰው ልጅ በምድር ላይ እስካለ ድረስ በጥንተ ጠላቱ ሰይጣን በየጊዜው መፈተኑ አይቀሬ በመሆኑ /ዘፍ. ፫፥፲፭/ ውጊያውም ከደምና ከሥጋ ጋር ሳይሆን ከጨለማ ዓለም ገዦች፣ ከአለቆችና ከሥልጣናት እንዲሁም ከረቂቃን ሰይጣናት ከዲያብሎስ ሠራዊት ጋር በመሆኑ፤ ፈተናውን ለማለፍ የሰይጣን መግቢያ የሆኑ ቀዳዳዎችን ለመድፈን እንዲያስችለው መንፈሳዊ ዝግጅት ማድረግ አለበት፡፡ ከኃጢአት ንጹሕ ሁኖ ሀብተ መንፈስ ቅዱስን ገንዘብ ያደርግ ዘንድ ስለሰይጣን አስከፊነት በእጅጉ መማርና ማወቅ፥ መረዳትና ማስተዋል ይገባዋል፡፡ +‹‹ከሚመጣው ሁሉ መዳን ትችሉ ዘንድና በሰው ልጅ ፊትም ለመቆም እንድትችሉ ሁል ጊዜ በጸሎት ትጉ፡፡›› ሉቃ. ፳፩፥፮ +‹‹ለጸሎት ትተጉ ዘንድ … ሰይጣን እንዳይፈታተናችሁ ደግሞ አብራችሁ ሁኑ፡፡›› ፩ቆሮ. ፯፥፭ +‹‹የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ፡፡›› ኤፌ. ፮፥፲፩ +‹‹በመጠን ኑሩ፥ ንቁም ባላጋራችሁ ዲያብሎስ የሚውጠውን ፈልጎ እንደሚያገሣ አንበሳ ይዞራልና፡፡›› ፩ጴጥ. ፭፥፰ +‹‹በቁጣችሁ ላይ ፀሐይ አይግባ፤ ለዲያብሎስም ፈንታ አትስጡት፡፡›› ኤፌ. ፬፥፳፯ #አንድ ሰው ካመነና ከተጠመቀ በኋላ ስለሰይጣን ክፋትና ተንኮል ጥልቅ እውቀት ከሌለውና በመንፈሳዊ ትሩፋት የማይተጋ ከሆነ በቀላሉ ተመልሶ በሰይጣን አገዛዝ ሥር ይወድቃል፡፡ ከዚያ በኋላም ሕይወቱ በእጅጉ የከፋ ይሆንበታል፡፡ /‹‹ርኩስ መንፈስ ከሰው ከወጣ በኋላ ዕረፍት ለማድረግ ፈልጎ ውኃ ወደሌለበት ምድረ በዳ ይዞራል፤ አያገኝም፡፡ ከዚህም በኋላ እንግዲህስ ወደ ወጣሁበት ቤቴ እመለሳለሁ ይላል፡፡ በመጣም ጊዜ ባዶ ሁኖ ተጠርጎና ተጊጦ ያገኘዋል፤ ከዚህም በኋላ ይሄዳል፤ ከእርሱም የሚከፉ ሌሎች ሰባት አጋንንትን ያመጣል፤ ገብተውም በዚያ ይኖራሉ፤ ለዚያም ሰው የኋላ ኑሮው ከፊተኛው የከፋ ይሆናል፡፡›› ማቴ. ፲፪፥፵፫ ‹‹በጌታችን በመድኀኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እውቀት ከዓለም ርኵሰት ካመለጡ በኋላ ዳግመኛ በእርሷ ተጠልፈው ከተሸነፉ ከፊተኛው ኑሯቸው ይልቅ የኋለኛው ኑሯቸው የባሰና የከፋ ይሆንባዋቸዋል፡፡›› ፪ጴጥ. ፪፥፳/፡፡ ሰዎች ዳግመኛ በሰይጣን ሽንገላ ተታለው በዓለም ርኵሰት እንዳይወድቁ የሚረዳ እውቀት ማግኛ የሚሆኑ ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብና ማወቅ እንዲረዳ መምህረ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ በሮሜ ፲፭፥፬ ላይ .. መጻሕፍት በሚሰጡት መጽናናት ተስፋ ይሆንልን ዘንድ አስቀድሞ የተጻፈው ሁሉ ለትምህርታችን ተጽፏልና ብሎ እንደተናገረው፤ ርዕሰ ባሕታውያውን ቀሲስ ቅዱስ አባ ጳውሊ ከሰይጣን ጋር ያደረገውን ምልልስ ከብራና ገልብጠው ከግእዝ ወደ አማርኛ የሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም አሳተመው፡፡ /#የዋልድባ_ዋሊ_ገጽ/ ደግሞ ኃይለ ቃል ያላቸውን በመጭመቅ አዘጋጅተን አቀረብንላችሁ፡፡ #ቀሲስ ጳውሊ ወደ ጭፈራ ቤት የሚሄዱትን ሰዎች የሚያስተውን ሰይጣን በዙ ጥያቄዎችን ሊጠይቀው እንደገዘተው፤ ሰይጣን ሰዎችን እንዴት እንደሚፈትንና ኃይል እንዴት እንደሚያገኝ፤ ክፍል ፫.… ይቀጥላል ነገ ይጠብቁን/ /#ዋልድባ_ዋሊ_ገጽ/

‹‹ያለ ሥርዓት የሚሄዱትን ገስጿቸው፡፡›› 1ተሰ. 5፥14 ‹‹ነገር ግን ሁሉ በአገባብና በሥርዐት ይሁን፡፡›› 1ቆሮ. 14፥40 /#ዋዜማ_ቅኔ_ዘሊቁ_ክፍለ_ዮሐንስ/ #ለመልአክ ኢናከብሮ፣ ለእመ አስረጸ ቈጽለ በመጠነ ነዊኀ ቆሙ፤ ለዖፍ ወለትንንያ እስመ ክንፍ ቦሙ፡፡ ወበሲበቱ ለሰብእ ኢናከብሮ ቀዲሙ፤ ፀዐዳ ሲበት እስመ ሀለወሙ፤ ለዕፀው ወአዕባን ኵሎሙ፡፡ #ትርጕም፤ በረጅም ቁመቱ ክንፍን ቢያበቅል በክንፍ ቢሸፈን መልአኩን አናከብረውም፤ ለወፍና ለትንኝ ክንፍ አላቸውና፤ መልአኩን በክንፍ አናከብረውም፡፡ #ሰውንም በሽበት አናከብረውም፤ ለድንጋይና ለእንጨቶች ሁሉ ነጭ ሽበት አላቸውና፤ ሰውን በእውቀቱ እንጂ በሽበቱ አናከብረውም፡፡ #ፍቅር ያጌብረኒ ነጊረ ነጊረ ዜናሆሙ ለቅዱሳን፤ የቅዱሳንን ዜናቸውን ለመናገር ፍቅር ግድ ይለኛል ወቅንዐት ያጌብረኒ ከመ እዝልፎሙ ለዕልዋን፤ #ቅናትም_ዝንጉዎችን_እንድሸሻቸው_ግድ_ይለኛል፤ #ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እትልዎሙ ለሐዋርያተ ክርስቶስ፤ ፍቅር የክርስቶስን ሐዋርያት እንድከተላቸው ያስገድደኛል፤ ወቅንዐት ያጌብረኒ ከመ አጕይዮሙ ለረሲዓን፤ #ቅንዐትም_ከሀዲዎችን_እነቅፋቸው_ዘንድ_ያስገድደኛል፤ /አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ/ #አድኅነኒ እግዚኦ እስመ ሀልቀ ሔር፤ ወውኅደ ሃይማኖት እም እጓለ እመሕያው #እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ፡፡ #አምላክ ሆይ ማረን፤ ማረን ይቀር በለን፡፡ #ኢሀሎኑ በዝ ሰማይ፤ አምላከ ኢትዮጵያ አዶናይ!፡፡ በሃገረ አሜሪካ ዲያቆን ሲያገባ በሙሉ ልብስና ጠጉር ሰይሸፈን፤ ሌሎች ምዕመናን ደግሞ ከንፈር ለከንፈር በመሳሳም ጭምር …… በሀገራችንና በውጭ ለምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምዕመናን በሙሉ፤ #ወደ ቤተ ክርስቲያን ነጠላ ሳትለብሱ ዘው ማለትን አቁሙ፤ መድኀኔ ዓለም ቤቱን ያከበረውን ያከብራልና፡፡ #ሴት እኅቶቻችን በጋብቻችሁና በተለያዩ ቀረጸዎች ላይ ለካሜራ በሚል ሽፋን ማኅተብ አትበጥሱ፤ ምልክቱን የበጠሰና ያፈረበትን እርሱም ያፍርበታልና፡፡ #በሥርዐተ ቊርባንና ተክሊል ስም የቤተ ክርስቲያንን ሥርዐት መጣስ ይቁም፤ በመጨረሻ ቤተ መቅደሱን ደፍረው ላስደፈሩ አገልጋዮችና የደፈሩ ምዕመናንን ዝም ብለን ብናልፍ አምላካችንስ ምን ይለናል!!፡፡ …. ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያንን በመተላለፍ ቤተ መቅደሱን ለናቃችሁ፥ ላስናቃችሁና የናቃችሁ ሁሉ፤ **ላላስተዋላችሁ፣ ላላወቃችሁና ለፈዘዛችሁ አምላከ አበው መድኀኔ ዓለም ልቡናና ማስተዋል ይስጣችሁ! **አስተውላችሁና አውቃችሁ ላደረጋችሁ፤ አምላከ አበው መድኀኔ ዓለም ይናቃችሁ እንደ ምናምንቴም ይቊጠራችሁ፤ ሰላምና ጤና ያሳጣችሁ፨

#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤ #ክፍል_፩_መቅድም ‹‹እነሆ በትዕግስት የጸኑትን ብፁዓን እንላቸዋለን፤ ኢዮብ እንደታገሠ ሰምታችኋል፥ ጌታም እንደፈጸመለት አይታችኋል፡፡›› ያዕ. ፭፥፲፩ ሰይጣንን በዘመናቸው ታግሰው ያሸነፉ ሰዎች ልቡናቸው አስተሳሰባቸው አጠቃላይ አኗኗራቸው ንጹሕና ቅዱስ ስለሚሆን ፍጹም ይቅር ባይና ቸሮች ርኅሩኆችና አዛኞች ናቸው፤ ሐዘኔታቸውም ለወዳጆቻቸውም ብቻ ሳይሆን ለጠላቶቻቸው ጭምር ነው (ቅዱስ ዳዊት /፩ኛ ሳሙ. ፳፬፥፲፰/ ና ቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስን /ሐዋ. ፯፥፰/ ልብ ይሏል) ቅዱሳን ከሰው ልጆች አልፈው ለአራዊት፣ ለአዕዋፍና ለእንስሳ እንዲሁም ለታላቁ ጠላት ለሰይጣን ሳይቀር የሚያዝኑ ናቸው፡፡ (ነቢዩ ሳሙኤል /፩ኛ ሳሙ. ፲፮፥፩/፣ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራን /ገድለ ክርስቶስ ሰምራ/ ልብ ይሏል/ #ቅዱሳን ሰዎች እንዲህ ዓይነቱን ጸጋ ሊያገኙ የሚችሉት የሰይጣንን ክፋት ለይተው ተረድተው ሰይጣንን በፍጹም ትዕግስትና ትሕትና ማሸነፍ በመቻላቸውና ከሰይጣን ባርነት ነጻ ወጥተው የእግዚአብሔርን መንፈስ ገንዘብ በማድረጋቸው ነው፡፡ #በተቃራኒ ደግሞ በዓለም ላይ ለተፈጠሩትና እየተፈጠሩም ላሉት ችግሮች መንስኤያቸውና ምንጫቸው የሰይጣን ሰለባና ማደሪያ በሆኑ ሰዎች አማካይነት የሚከሠት ነው፡፡ (ቃዔልን /ዘፍ.፬፥፰፣ ሄሮድስን /ማቴ. ፪፥፲፮/፣ አምኖንን /፪ኛ ሳሙ. ፲፫፥፩/፣ ሰዶማውያንን /ዘፍ. ፲፱፥፩፣ ሮሜ. ፳፮፥፳፱፣ ፪ጴጥ. ፪፥፮/) …. ልብ ይሏል፡፡ ምክንያቱም፤ *ሰይጣን ተዘክሮተ እግዚአብሔርንና መንፈሳዊ ተግባራትን ካስተወ በኋላ በኃጢአት ላይ ኃጢአት እንዲጨምሩ እንጂ *ሰይጣን ኃጢአትን በቃኝ እንዳይሉ ስለሚያደርጋቸው ነው /ዘዳ. ፮፥፲፫/፡፡ *ሰይጣን ኃጢአትንም ተዉ ብሎ በሚመክራቸው ሰው ላይ በጠላትነት እንዲነሳሡ ያደርጋቸዋል፡፡ *ሰይጣን ቀና የሆኑ ነገሮችን ሁሉ ክፉ አስመስሎ ስለሚያሳያቸው ቅን አሳቢዎችንና ለመልካም ሥራ የተሰለፉትን እንዲጠሉ ያደርጋቸዋል፡፡ *ሰይጣን ቅን አስተሳሰብን መንፈሳዊ ሥራን ሰላምን ፍቅርን ርኅራኄን ከውስጣቸው አሟጦ አውጥቶ የራሱን መንፈስ ስለሚሞላባቸው ማንኛውንም ዓይነት ወንጀል ቢሠሩ ወንጀል የሠሩና ጥፋት ያጠፉ አይመስላቸውም፡፡ እውነተኛ ሕይወት እንደሚኖሩ ያስመስላቸዋልም፡፡ *ሰይጣን ዲያብሎስ የጥፋተኝነት ስሜት እንዳይሰማቸው ስለሚያደርጋቸው ለጥፋታቸው ገደብ የለውም፡፡ ##መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ከሰማያት ወርዶ ከድንግል ማርያም የተወለደው ሰው ሁሉ የሰይጣንን የክፋት ሥራ ተረድቶ ከሰይጣን እንዲሸሽና የእግዚአብሔርን ልጅነት አግኝቶ የዘለዓለም ሕይወት መንግሥተ ሰማያትን እንዲወርስ ለማድረግ ነው፡፡ /‹‹ኃጢአትን የሚያደርግ ከዲያብሎስ ነው፡፡ ዲያብሎስ ከመጀመሪያ ኃጢአትን ያደርጋልና፤ ስለዚህ የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ፡፡ ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ኃጢአትን አያደርግም ዘሩ በእርሱ ይኖራልና፤ ከእግዚአብሔር ተወልዷልና ኃጢአትን ሊያደርግ አይችልም፡፡ የእግዚአብሔር ልጆችና የዲያብሎስ ልጆች በዚህ የተገለጡ ናቸው፡፡›› ፩ዮሐ.፫፥፰/ /‹‹ክፉ ፍሬ የሚያፈራ መልካም ዛፍ የለምና እንዲሁም መልካም ፍሬ የሚያፈራ ክፉ ዛፍ የለም፡፡ ዛፍ ሁሉ ከፍሬው ይታወቃልና፤ …. መልካም ሰው ከመልካም ልቡ መልካሙን ያወጣል፡፡›› ሉቃስ ፮፥፵፫/ #ማንኛውም ሰው በሚሠራው ሥራ የማን ወገንና የማን ማደሪያ እንደሆነ ለመረዳትና ራሱንም ለመፈተሸ ይችላል፡፡ ##ጠላት ዲያብሎስ ንስሐ ገብተን መንግሥተ ሰማይትን እንዳንወርስ ማድረግ ብቻ ሳይሆን በሥጋዊ ኑሯችንም ቢሆን በተገቢው ሰዐትና ጊዜ ተምረን ተገቢውን እውቀት ይዘን ሥራችንን በተገቢው ሰዐትና ጊዜ እንዳንሠራ በማድረግ፤ ሠርተንም እንዳንጠቀም ዕንቅፋት በመፍጠር (በስንፍናና በውሸት፤ በዝሙትና በስካር፤ በቃሚነትና በአጫሽነት፤ በጨፋሪነትና በዳንሰኛነት፤ በስርቆትና በአጭበርባሪነት፤ …. በተለያዩ የኃጢአት አሸክላዎች ተብትቦ ይይዘናል፤ እንዲህ ካደረገን በኋላም ሰይጣን በሚያመነጭልን አእምሯዊ ስሜትና ጭፍን አስተሳሰብ እየነዳን መልካም ሥራን ለሚሠሩ ለእውነተኛ ሰዎች እንቅፋት እንድንሆን በመሣሪያነት ይጠቀምብናል፡፡ /‹‹ወደ እናንተ ልንመጣ ወደን ነበር … አንድና ሁለት ጊዜ ሰይጣን አዘገየን፡፡›› ፩ተሰ. ፪፥፲፰/ /አንተ (ኤልማስ የተባለ አስማተኛን/ ተንኮልንና ክፋትንም ሁሉ የሞላብህ የዲያብሎስ ልጅ የጽድቅም ሁሉ ጠላት የቀናውን የጌታን መንገድ ከማጣመም አታርፍምን?›› ሐዋ. ፲፫፥፮/ /እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ የአባታችሁን ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ፡፡ እርሱ ከመጀመሪያ ነፍሰ ገዳይ ነበረ፤ እውነትም በእርሱ ስለሌለ በእውነት አልቆመም፡፡ ሐሰትን ሲናገር ከራሱ ይናገራል፡፡ ሐሰተኛ የሐሰትም አባት ነውና፡፡›› ዮሐ. ፰፥፵፬/ #ከላይ ባየነው ዓይነት ሕይወት ሰይጣን በእጁ ያደረጋቸውን ሰዎች፤ **ለሕይወታቸው ጠቃሚ ምክርና ትምህርት በሚሰጣቸው ሰዐት ወዲያው እንዲዘነጉትና እንዳይቀበሉት ያደርጋል፡፡ /‹‹ወዲያው እንደሰሙ ሰይጣን መጥቶ በልባቸው የተዘራውን ቃል ይወስዳል፡፡›› ማር. ፬፥፲፭/ **ቢመከሩም ምክርን አይሰሙም አይቀበሉምም፤ /ይሁዳ ሕይወት የሚሆን የጌታን ትምህርት አልሰማ ብሎ ነው ጌታን አሳልፎ የሰጠው፡፡ ማቴ. ፳፮፥፵፱/ /አምኖንም የእኅቱን የትዕማርን ምክር አልሰማ ብሎ ነው አስነዋሪ ጥፋት በእኅቱ ላይ የፈጸመው፡፡ ፪ሳሙ. ፲፭፥፲፱/ /እንዲሁም ደግሞ ሳዖልም የነቢዩ ሳሙኤልን ምክር አልሰማ ብሎ ነው ከአማሌቃውያን ለማረከው ምርኮ በመሣሣት ነው ክፉ መንፈስ ሊጠድርበትና በጠላት እጅ ሊወድቅ የቻለው፡፡ ፩ሳሙ. ፲፭፥፲፱/ #ሰይጣን_ምንጊዜም_ቢሆን_እንደየሰው_ምኞትና_ፍላጎት፥ #እንደ_ጊዜውና_እንደ_ሰዐቱ፥ #እንደ_ዘመኑና_እንደ_ወቅቱ_ተጨባጭ_ሁኔታ_የማሳት_ጥበቡን_እየለዋወጠ_ይጠቀማል፡፡ /#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤ ክፍል ፪ መቅድም.… ይቀጥላል ነገ ይጠብቁን/ /#ዋልድባ_ዋሊ_ገጽ/

ለ10 ተከታታይ ቀናት ማታ ማታ ከዛሬ 04/06/2011ዓ.ም. ጀምሮ ይጠብቁ፤ ቅዱሱ ቀሲስ አባ ጳውሊ ከጻፋቸው መጻሕፍት አንዱና ዋነኛ ከሆነው ‹‹ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን (#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ)›› ላይ ጨምቀን እናቀርባለን /ዋልድባ ዋሊ ገጽ/ ሰላም ለአባ ጳውሊ፤ ዘንጉሥ ወዓሊ፤ ገዳማዊ ዘበአማን ኅሩይ፤ ርዕሶሙ ለፈላስያን እለ በገዳም፡፡ ትርጉም፦ በበረሃ ላሉ ባሕታውያን(መናንያን) አለቃቸው፤ በእውነት የተመረጠ ገዳማዊ፤ የንጉሥ ሎሌ ለኾነ ለአባ ጳውሊ ሰላምታ ይገባል:: /ከዋልድባ ዋሊ ገጽ የተወሰደ/

#መሠረት_ደንጊያ_የሚጣልበት_ቀን_እሑድ_የካቲት_3_2011ዓ.ም. ሁላችንም ቀጠሯችን #በመንበረ_ክብር_ደብረ_ታቦር_ቅዱስ_ሚካኤል_ወአቡነ_ተክለሃይማኖት_ገዳም_ይሁን፡፡ #የሕንፃ_ቤተ_ክርስቲያኑ_መሠረት_ደንጊያ_የሚጣልበት_ቀን_ነው፡፡ .. ለፍጻሜ ደርሶ ለዛቲ ቤት ሳረራ አቤቶ ኢያሱ ቀዲሙ ወፈጸሞሙ ሕዝበ ክርስቲያን ለማለት ያብቃን፡፡ ይህ ገዳም ከ108 ዓመታት በፊት የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም ታቦተ ሕግ ለ6ወራት (ከጥቅምት 27/1903ዓ.ም. እስከ ጥር 27/1904ዓ.ም.) በመቃኞ ቤተ ክርስቲያን የቆየበት፤ የቀድሞ የመቃኞና የአጥሩ ፍርስራሽ የሚገኝበት አጽመ ርስት ቦታ ነው፡፡ የቀድሞ ርስትነቱ የልዑል ራስ መኰንን (የአፄ ኃይለ ሥላሴ አባት) ነው፤ በዚህም የቦታው ዋነኛ መጠሪያ ስሙ #የራስ_መኰንን_ደን፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ጽድ በመባል ይጠራል፡፡ #መንበረ_ክብር_ደብረ_ታቦር_ቅዱስ_ሚካኤል_ወአቡነ_ተክለ_ሃይማኖት_ገዳም፤ #ቀድሞ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም በነበረበት ቦታ ላይ #በግንቦት_11_1992ዓ.ም. #ታቦተ_ቅዱስ_ሚካኤል_ወደ_መቃኞው_ገባ፤ በማግስት ግንቦት 12/1992ዓ.ም. ቅዳሴ ቤቱ ተከበረ #በሰኔ 8/1992ዓ.ም. ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ከበርካታ ሊቃነ ጳጳሳትና የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሠራተኞችን ይዘው በመምጣት ስሙን ‹‹መንበረ ክብር ደብረ ታቦር ቅዱስ ሚካኤል ወአቡነ ተክለ ሃይማኖት›› ብለው ሰየመው የመሠረት ድንጋይ አስቀመጡ #ነሐሴ 24/1992ዓ.ም. ታቦተ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገባ #ኅዳር 20/1995ዓ.ም. ታቦተ እግዝእትነ ማርያም ገባች #ኋላ ታቦተ ቅደስስት አርሴማ ገባች፡፡ #የካቲት 14/1994ዓ.ም. ፈዋሽ ጠበል ፈልቋል፡፡ #በቤተ ክርስቲያኑ በስተሰሜን በር ዐፄ ምኒልክ ከተከሏቸው 100 የባሕር ዛፎች መካከል 2ቱ ይገኙበታል፤ ምንም እንኳን በቅርብ በተወሰነ መልኩ በአውሎ ነፋስ እየወደቀ ቢሆንም፡፡ #ቀጨኔ_ደብረ_ሰላም_መድኀኔ_ዓለም_ከራስ_መኰንን_ደን_እልፍኝ_ቤት_አሁን_እስካለበት_ቀጨኔ *ሐምሌ 26 ቀን 1903 ዓ.ም. አቤቶ ኢያሱ ታቦተ መድኀኔ ዓለምን አስመጥተው በልዑል ራስ መኰንን ቦታ ላይ አባ አየለ የተባሉ መነኩሴ የሚኖሩበት ክብ የሣር ክዳን ቤት ላይ ዙሪያውን በረንዳ ተጨምሮለት መቃኞ ሆኖ ቅዳሴ ቤቱ ተቀደሰበት፡፡የቅዳሴ ቤት ክብረ በዓሉ የማኅሌቱ ምራትም ለደብረ ኀይል ራጕኤሎች፤ ቅዳሴው ለእንጦጦ ማርያም ካህናት ተሰጥቶ ቃለ እግዚአብሔሩ ከዋይዜማው ጀምሮ በማኅሌቱ ደምቆና አሸብርቆ አደረ፡፡ *በማግስቱ ሐምሌ 27 1903ዓ.ም. ጠዋት አቡነ ማቴዎስና እጨጌ ወልደጊዮርጊስ መጥተው አዲሱን ቤተክርስቲያን ባረኩ፡፡ ቀጥሎም ልጅ ኢያሱና ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ መጥተው ታቦት አንግሠውና በዓሉን አክብረው ተመለሱ፡፡ በዚህ ቀን ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ልጅ ኢያሱ ባሉበት በአዳራሻቸው ለካህናት ግብር አድርገው ዋሉ፤ ግብዣውም በዛ ቀን ለእርሳቸው ተሰጠ፡፡ *ከ1 ወር በኋላ በነሐሴ ወር የደብረ ዳሞ መነኰሳት ለአቤቱታ አዲስ አበባ መጥተው ስለነበር፤ ለጊዜው በዚሁ ቦታ ታቦተ መድኀኔዓለምን እየሠለሱ እየቀደሱና እያገለገሉ ደጅ ጥናታቸውን እንዲቀጥሉ ከመንግሥት ትእዛዝ ስለተሰጠ የደብረ ዳሞ መነኰሳት መንፈሳዊውን አገልግሎት በንቃትና በትጋት እየሰጡ ቆዩ፡፡ *በቀጣዩ ዓመት በጥቅምት 27 ቀን 1904 ዓ.ም. የመድኀኔ ዓለም በዓል በዛው ቦታ በታላቅ ክብር እንዲከበር ስለተወሰነ፤ ከእንጦጦ ማርያም፤ ከእንጦጦ ራጕኤልና ከአዲስ አበባ መካነ ሥላሴ በዓለ ወልድ አብያተ ክርስቲያናት በተውጣጡ መዘምራን ከበዓሉ ዋዜማ ጥቅምት 26 ጀምሮ በዋይዜማና መላ ሌሊቱን በሥርዐተ ማኅሌት ሲያከናውኑ ካደሩ በኋላ ጥቅምት 27 ቀን 1904ዓ.ም. ኪዳን ተደርሶ፥ ቅዳሴው ተቀድሶ እንዳበቃ አቤቶ ኢያሱ በተገኙበት ሥርዐተ ዑደት ተደርጎ፥ ነጋሪት ተጎስሞ፥ ሰባት ጊዜ መድፍ ተተኩሶ ሥርዐተ ንግሡ ተፈጸመ፡፡ ***#ይህ ቦታ ከአዲስ አበባ ጥግ ላይ ያለ በመኾኑና በጫካ ውስጥ የሚገኝ በመኾኑ፤ ለሕዝበ ክርስቲያኑ የማያመችና ከቤተ መንግሥቱም ኾነ በወቅቱ ከነበረው ከመሐል ከተማ የራቀ በመኾኑ በዚሁ በጥቅምት 27 ቀን 1904ዓ.ም. ታቦተ ሕጉ ከእንጦጦ ጥግ ወደ መሐል አዲስ አበባ የማርቆስ ሰፍር ወደሚባለው ሥፍራ እንዲወርድ ተደርጎ ከዋግ ሥዩም ጓንጉል ቤት ገባ በዚህም ቤት ከጥር 27 1904ዓ.ም. እስከ ጥር 26 1905ዓ.ም. ለአንድ ዓመት ቆየ፡፡ ቋሚ ቤተ ክርስቲያን ለማሠራት አመቺ ቦታ በመፈለግ፤ ሀ. ጃንሜዳ ላይ የአዛዥ ወንድም ተገኝና የደጃዝማች ወልዴ ቦታ ላይ በጎጃም ደብረ ማርቆስ ከተማ በሚገኘው በቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ዓይነት ሊሠራ ታቅዶና ተቀይሶ ቁፋሮውም ተጀምሮ ባልታወቀ ምክንየት ጅምሩ ሳይሳካ ሊቀር ቻለ፡፡ ለ. በጃንሜዳ ያለው ሥራ ከተቋረጠ በኋላ እንደገና በዚያው በመቃኞ ባለበት በዋግ ሥዩም ጓንጉል ቦታ ላይ መጠነኛ ቤተ ክርስቲያን ተጀምሮ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ 1 ሜትር ከፍ ካለ በኋላ ‹‹አባ ኃይለ ጊዮርጊስ የተባሉ ሰው ቤተ ክርስቲያኑን አቃጠሉት ታቦተ መድኀኔ ዓለም ግን በተአምራት ሳይቃጠል ተረፈ፡፡ በዚህም ምክንያት በዋግ ሥዩም ጓንጉል ቦታ ላይ በተሠራው መቃኞ ቤት ሲወደስና ሲቀደስ ለአንድ ዓመት ከአራት ወር ከቆየ በኋላ በ1906 ዓ.ም መጋቢት 27 በልጅ ኢያሱ ትእዛዝ ካለበት ቦታ ተነስቶ አሁን ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ሕንፃ ቤተክርስቲያን ከታነጸበት በስተምሥራቅ ከሚገኘው ከአዛዥ መሸሻ ቦታ ላይ በድንኳን ተቀመጠ፤ በፍጥነትም መቃኞው ስለተሠራ በዚሁ መቃኞ መቃረቢያነት ለ 7 ዓመታት ተቀመጠ፡፡ ሐ. አሁን ታለቁ ደብር ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም የሚገኝበት ቦታን ልጅ ኢያሱ ወደ ቀጨኔ ጫካ ቦታውን ለማየት ሄዱ፤ መንገድ ላይ ጫካ ውስጥ አንድ ትልቅ ዋርካ አገኙ እዚያ ቆመው ከአሽከራቸው ጦር በመቀበል ወረወሩ፤ ጦሩ የተተከለበት ቦታ መቅደሱ ሲሆን ዋርካው የነበረበት ደግሞ ደወል ቤት እንዲኾን በመወሰናቸውና፤ ሕንፃው በአስቸኳይ ተሠርቶ ፍጻሜ እንዲያገኝ ጠበቅ ያለ ትእዛዝ አስተላልፉ፡፡ ተገቢው ሥርዐተ ጸሎት ደርሶ በመምህር ወልደ ጊዮርጊስ ሥፍራውን በመስቀል ተባርኮ፤ መሬቱ በመስቀል አምሳል በዶማ ተቆፍሮ መሠረት ተጣለ፤ የሕንፃ ሥራውንም በመሐንዲስነት ኢጣሊያዊው ሙሴ ከስተኛና በሥራ ተቋራጭነት ግሪካዊው ሙሴ አንጀሎስ በተፋጠነ ኹኔታ እንዲሠሩ ትእዛዝ ተሰጣቸውና የመሠረት ድንጋይ ማስቀመጥ ሥነ ሥርዐቱ ተፈጸመ፡፡ ቀጥሎም የሕንፃውን ሥራ በፍጥነት እንዲሠራና አጠቃላይ የቁጥጥር ሥራውን እየተቈጣጠረ የሚያሠራ ኢትዮጵያዊው መርሻ እንዲኾን የሥራ ሚኒስትሩ ቀኛዝማች ወልደ ሐና (ኋላ መልአከ ገነት) አዘዙና በተፋጠና ኹኔታ ለ10 ወራት የሕንፃው ሥራ ቀጠለ፡፡ ሆኖም እስከ 1910ዓ.ም ስራው ተቋረጠ፡፡ ንግሥት ዘውዲቱ በሰኔ ወር 1910 ዓ.ም. ቀኝ አዝማች ወልደሐናንና ከመሐንዲሶቹ ጋር ወደ አካባቢው መጥተው ሥራው በአስቸኳይ እንዲያልቅ፣ የቤተ ክርስቲያኑ ዓቅድም (ፕላንም) በአንድ ጣሪያ ብቻ መኾኑ ቀርቶ በባለ 3ት ክፍል መቅደሱ ቅድስቱና ቅኔ ማኅሌቱ ለየብቻው እንዲሠራ አዘዙ፤ ቀኝአዝማች ወልደ ሐናም ተከታትለው እንዲያስፈጽሙ ኃላፊነት ተሰጣቸው፤ አሁን ያለው የመጨረሻው ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ሥራ ለ2 ዓመት ከ4 ወር ከ1911 እስከ 1913 ዓ.ም. ታንጾ በወርኃ ጽጌ በእለተ እሑድ ጥቅምት 27 ቀን 1913 ዓ.ም. ታቦተ ሕጉ ለ7ዓመታት ከቆየበት ከመቃኞው ተዛውሮ ወደታነጸለት ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ገባ፡፡

የካቲት ፩/፳፻፲፩ዓ.ም. ከ፲፪-፪ ሰዓት ልዩ የዐርብ ጕባኤ ፻፲፯ኛ ሳምንት በሰዐቱ ይገኙ!!!!!!!! እንዳያመልጥዎ! ላልሰሙት ያሰሙ፤ <> በማድረግ ይተባበሩ የቀ.ደ.ሰ መድኀኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት