fa
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

رفتن به کانال در Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

کانال Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 367 مشترک است و جایگاه 5 600 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 189 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 367 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 26 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 2 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 2 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 20.69% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 10.92% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 180 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 679 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 18 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 27 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

15 367
مشترکین
+224 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
+230 روز
آرشیو پست ها
ልዩ አዋጅ ዘወርኃ ጽጌ ꔰ ማኅሌተ ጽጌ ምን ማለት ነው? ------------ ( ወርኃ ጽጌ 40 ቀናት ነው፤ መስከረም 26 ተጀምሮ ኅዳር 5 ያልቃል፤ ጾመ ጽጌ የፈቃድ ጾም ነው፡፡ (የማኅሌተ ጽጌና የሰቈቃወ ድንግል ደራሲ አባ ጽጌ ድንግል ነው፡፡ ገዳሙም ፍልፍል ዋሻ ሲኾን ወሎ ወግዲ ወለቃ ወንዝ አጠገብ በረሃ ላይ (ከጋሥጫ ገዳም የ4 ሰዓት የእግር መንገድ) ይገኛል፡፡ ✤✤ በየዓመቱ ሳይመረገዱ ያመይታለፉ የማይቀሩ፤ ዚቃቸው የማይለወጥ፤ ( ከማኅሌተ ጽጌ፤ ጽጌ አስተርአየ(የመጀመሪያው ሳምንት)፣ በከመ ይቤ መጽሐፍ፣ ትመስል እምኪ ማርያም፣ ዘኒ ስብሐተ ወዘኒ ማኅሌተ፣ ኢየሐፍር ቀዊመ ቅድመ ሥዕልኪ እና ኅብር ሐመልሚል (የመጨረሻው ሳምንት)ናቸው፡፡ ( ከሰቈቃወ ድንግል፤ በስመ እግዚአብሔር ሥሉስ፣ ብክዩ ኅዙናን፣ እስከ ማዕዜኑ እግዝእትየ እና አብርሂ አብርሂ ናቸው፡፡ ( ከማኅሌተ ጽጌ ውስጥ እንዘ ተሐቅፊዮ ለሕፃንኪ እና ክበበ ጌራ ወርቅ በየሳምንቱ (በኹሉም ዓመታት) ይመረገዳሉ፤ ዚቁ ግን በዓሉን በተመለከተ ይኾናል፡፡ ( ከላይ ካየናቸው ውጪ የሚገኙት የማኅሌተ ጽጌና የሰቈቃወ ድንግል ክፍሎች ግን በየሰባት ዓመት አንዴ ነው የሚመረገዱት፡፡ ( የማኅሌቱ ሥርዐት የላይ ቤት (የጎንደር መካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ማርያም አብነት) እና የታች ቤት (የጎንደር ደብረ ኀይል በዓታ ለማርያምን አብነት) የሚያደርግ ሲኾን፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ የማኅሌት ቁመትም የላይ ቤትን አብነት የተከተለ ሲኾን የዚቁ ወረብ ግን የደብሩን የራሱን (የሸዋን) የተከተለ ነው፤ ( የላይ ቤት ቁመት የሚቆሙ አድባራት ዘግምጃ ቤት የሚለውን እንዲከተሉ፤ የታች ቤትን ቁመት የሚቆሙ አድባራት ዘበዓታ የሚለውን እንዲከተሉ፡፡ እንደ ደብራችሁ ይትበሃል መርጣችሁ እንድትጠቀሙበት ኹሉንም አስቀምጠነዋል፡፡ ꔰ ማኅሌተ ጽጌ ምን ማለት ነው? ማኅሌተ ጽጌ ከሁለት የግእዝ ቃላት ጥምረት የተገኘ ነው፡፡ ማኅሌት ማለት ምስጋና፣ ማወደስ ማለት ሲኾን፤ ጽጌ ማለት ደግሞ አበባ፣ የፍሬ ምልክት፤ ውበት፣ ደም ግባት ያለው ማለት ነው፡፡ ማኅሌተ ጽጌ ተብሎ በአንድነት ሲነገር እና ሲተረጎም ደግሞ የአበባ ምስጋና ማለት ነው፡፡ ይህም ድንግል ማርያም እና የማሕፀኗ ፍሬ ኢየሱስ ክርስቶስ በጎ በጎ መዓዛ በአላቸው አበባዎች እና ፍሬዎች እየተመሰሉ የሚመሰገኑበት ምስጋና ማለት ነው፡፡ የዘመን (የወራት) ስምም ይኾናል፤ ዘመነ (ወርኃ) ጽጌ 40 ቀን ነው፤ ከመስከረም 26 እስከ ኅዳር 5 ነው፡፡ በዚህ 40 ወራት የሚጾመው ጾም ጾመ ጽጌ ሲባል ጾሙም የፈቃድ ጾም ነው፤ በሀገራችን ዘመነ ክረምት አልፎ መስከረም 26 ቀን ዘመነ ጽጌ ይጀመራል፡፡ ዘመኑ አበቦች የሚያብቡበት እና ሜዳዎችን እና ተራሮችን የሚስጌጡበት ዘመን ነው፡፡ ፍሬ የተባለ ጌታን ያስገኘች እመቤታችን በአበባ ትመስላለችና ዘመኑ የጌታችንን እና የእመቤታችንን ነገር በአበባ እና በፍሬ ለመመስል የተመቸ ነው፡፡ የማህሌተ ጽጌ ደረሲ አባ ጽጌ ድንግል ይህንን የአበቦችን ነገር ከእመቤታችን ስደት ጋር እያደረገ፣ እጅግ አስደናቂ የሆኑ ታሪኮችን እያጣቀሰ ማኅሌተ ጽጌ (የአበባ ማኅሌት) የተባለውን ጸሎት ደርሷል፡፡ በዘመነ ጽጌ ወቅት ቅዳሜ ለእሑድ አጥቢያ ማኅሌት ይቆማል፤ የሚቆመው ቁመትም አባ ጽጌ ድንግል የደረሱት ማኅሌተ ጽጌና ሰቈቃወ ድንግል ነው፡፡ አባ ጽጌ ድንግል ጓደኛቸው አባ ገብረማርያም የጀመሩትን ማኅሌተ ጽጌ አብነት በማድረግ በተለይም በጎንደር ዘመነ መንግሥት በእቴጌ ምንትዋብ ዘመን በጎንደር ደብረ ፀሐይ ቊስቊም ማርያም የማኅሌተ ጽጌ ቁመት መቆም ተጀምሯል፤ ቆይቶ ግን ይህ ማኅሌት ወደ ዘንሥር ዮሐንስ ማእከላ ለጎንደር ተዛውሮ እስከ ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ድረስ ሲቆም ቆይቶ በመምህር ተክሌ ጊዜ ወደ መካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ማርያም ተዛውሮ በጎንደር አብያተ ክርስቲያናት በብቸኝነት በዚህችው ደብር የጎንደር አድባራት ሊቃውንት በመሰባሰብ ሲቆም ቆይቷል፤ ከ1999(2000)ዓ.ም. ጀምሮ በደብረ ፀሐይ ቊስቋምና የተወሰኑ ተወሰኑ የጎንደር አብያተ ክርስቲያናት የማኅሌተ ጽጌ ቁመትን ቢጀምሩም ቅሉ አሁንም ግን የጎንደር አድባራት በዋነኛነት በመካነ ነገሥት ግምጃቤት እየተሰባሰቡ የሚቆሙት የማኅሌተ ጽጌ ቁመት እጅግ በጣም ልብን የሚማርክና ኅሊናን የሚመስጥ ነው፡፡ በሌሎች የሃገራችን ክፍሎችና በመዲናችን በአዲስ አበባ ባሉ አብያተ ክርስቲያናት ደግሞ የአገልጋይ ካህናት እጥረት በሌለባቸው ኹሉ ይቆማል፡፡ በደብራችን በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ ከደብራችን ምሥረታ ጀምሮ የማኅሌተ ጽጌ ቁመት ልዩ በኾነና ደማቅ በኾኑ ሥርዐቶች ጭምር ይቆማል፤ ምንም እንኳን ደብራችን በሐምሌ 26 ቀን 1903 ዓ.ም. ቢመሠረትም በተለያዩ ቦታዎች ታቦተ ሕጉ ሲዘዋወር ከቆየ በኋላ አሁን ያለው ሕንፃ ቤ.ክን በ2ዓመት ከ6 ወር ሥራ ተጠናቅቆ ቅዳሴ ቤት ሁኖ የተመረቀው በወርኃ ጽጌ በጥቅምት 27 ቀን 1913 ዓ.ም. ነው፤ በቅዳሴ ቤት ማኅሌቱም ላይ ከተቆሙት መካከል ‹‹በወርቅ ወበዕንቊ ሥርጉት ደብረ ሰላም፤ ወነገሥት ይትቀነዩ ለኪ›› የሚለው ቀለም ሲገኝበት እስካሁንም ድረስ በማኅሌተ ጽጌ የሚወረብ ቀለምም ነው፡፡ ከዛን ዕለት ጀምሮም ማኅሌተ ጽጌ በልዩ ኹኔታ በደብራችን እየተቆመ ይገኛል፤ ይኸውም፤ ✤ ማኅሌተ ጽጌን በላይ ቤት አቋቋም፤ የማኅሌተ ጽጌን ወረቦች ደግሞ በጎንደር ወረብ ✤ የማኅሌተ ጽጌን ዚቅ በላይ ቤት አቋቋም፤ የዚቁን ወረቦች ደግሞ በራሱ በደብራችን ይትበሃል ✤ በወርኃ ጽጌ የሚዘመሙ የክብረ በዓላት ዝማሜን ደግሞ በተክሌ ዝማሜ እየተዘመሙ ይገኛል፡፡ ✤ ሌላው በቅድስትሰ ሃገር ኢየሩሳሌም በጸሓፌ ትዕዛዝ ኀይሌ ወልደ ሩፋኤል የተሳለችውና በደብራችንና በመናገሻ ገነተ ጽጌ ብቻ የምትገኘው ስዕለ እግዝዕትነ ማርያም (ኢትዮጵያን ይዛ እንባዋን ስታብስ ‹‹ኃዘና ስምዒ ወብካያ ለሃገሪትና ኢትዮጵያ›› የሚል ጽሑፍ ያለባት ስዕል) ወጥታ በዑደት ጊዜ የምትባርከው በዚሁ በዘመነ ጽጌ በመኾኑ፤ ✤ በሃገራችን ደረጃ ከ50 ዓመታት በፊት በወቅቱ በነበሩት በንቡረ ዕድ ዓሊ በማኅሌተ ጽጌ ላይ የተጀመረውና (ልዩ ኅብርና ውበት ባላቸው ጉንጉን አበቦች) ወርኃ ጽጌን ለማሰብ በማኅሌቱ ጊዜ ጉንጉን አበባ መታደሉ፤ (ይህ አበባ ዛሬ ለሌሎች አድባራት ምሳሌ ሁኖ በብዙ አብያተ ክርስቲያናት መሰጠት ተጀምሯል) ✤ ከተለያዩ ገዳማትና አድባራት ይህንን ማኅሌት ለመቆም የሚመጡ በርካታ ሊቃውንትና ምዕመናን መኖራቸው፤ ✤ ‹‹እንዘ ተሐቅፊዮና ክበበ ጌራ ወርቅ›› እየተባለ ወረብ እየተወረበ ዑደት በሚደረግበት ጊዜ ከጥንት ጀምሮ ጧፍ ቤተ ክርቲያኑ እያደለ በብርሃን ጎርፍ ቤተ ክርስቲያኑ አብርቶ መታየቱና፤ ……… በሌሎችም ኹኔታዎች ልዩ ያደርገዋል፡፡ በኹሉም አብያተ ክርስቲያናት ያሉ ካህናትና ምዕመናንም ድካም ሳይሰማቸው ወርኃ ጽጌ ደርሶልን ባገለገልን እያሉ በናፍቆት የሚጠበቁት ወራት ነው፡፡ ማኅሌተ ፡ ጽጌ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot