fa
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

رفتن به کانال در Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

کانال Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 377 مشترک است و جایگاه 5 568 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 195 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 377 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 04 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 23 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -1 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 22.11% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 9.42% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 401 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 449 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 20 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 05 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

15 377
مشترکین
-124 ساعت
-107 روز
+2330 روز
آرشیو پست ها
———— ወረብ | #ትምስል እምኪ | በ ዲ/ን ፍቅረሥላሴ እና ፀጋዬ | ከማኀሌተ ጽጌ በየቲዩብ ገጻችን ላይ ያምልከቱ https://youtu.be/_COmSOCC9hY ከማኀሌተ ጽጌ 2013 በቀጨኔ ደብረሰላም መድኀኔዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ -------------

ታላቁ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ #ገብርኤል #ቤተክርስቲያን፤
ታላቁ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ #ገብርኤል #ቤተክርስቲያን፤

ማኀደረ ሰላምነ ቅድስት #ደብረሰላም ✤ታላቁ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም ቤተ ክርስቲያን፤ (ስብስብ 3)፤ # የ116 ዓመታት ዕድሜ ያለው ጥንታዊ የኢያሱ ደብር፡፡ ‹‹በወርቅ ወበዕንቊ ሥርጉት ደ
ማኀደረ ሰላምነ ቅድስት #ደብረሰላም ✤ታላቁ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም ቤተ ክርስቲያን፤ (ስብስብ 3)፤ # የ116 ዓመታት ዕድሜ ያለው ጥንታዊ የኢያሱ ደብር፡፡ ‹‹በወርቅ ወበዕንቊ ሥርጉት ደብረ ሰላም፤ ወነገሥት ይትቀነዩ ለኪ›› ለዛቲ ቤት ሣረራ ኢያሱ ቀዲሙ ለዛቲ ቤት፤ ወፈጸመታ ንግሥት ዘውዲቱ፡፡ (ይህችን ደብረ ሰላምን በመጀመሪያ አቤቶ ኢያሱ /አልጋ ወራሽ ልጅ ኢያሱ/ (ክፍለ ያዕቆብ) በሐምሌ 26 ቀን 1903 ዓ.ም. መሠረታት፤ ንግሥት ዘውዲቱ አሁን ያለውን ሕንፃው ቤ.ክ ጥቅምት 27 ቀን 1913 ዓ.ም አስፈጸመች፡፡) ስለ ታላቁ ደብር ብዙ ነገር ባወራን ደስ ባለን ነበር ….. የሰላም አምላክ የፍቅር ጌታ ያደረባት ደብረ ሰላም ብዙ ነገሮች አሏት፤ የብዙ ሊቃውንት መፍለቂያ፤ የላይ ቤት አቋቋም፣ የተክሌ ዝማሜና የሸዋና የራሱ የደብሩ ቀለም እንደ ወንዝ የሚፈስባት፤ ታሪካዊ ቅርሶችን የያዘ ቤተ መዘክር (Museum)ና ቤተ መጻሕፍት የሚገኙበት፤ ደብሩን አገልግለው ወደ ሌላ ደብር የሚዛወሩ ካህናት ኹሌም በዓይናቸው የደብሩ ፍቅር ውልብ የሚልባቸው፤ ምዕመናኑ በአጸዱና በግርማ ሞገሱ ኹሌም የሚደነቁበት፤ ስዕለት ሰሚ ታቦታት ያሉበት፤ 4ት የሚጠጉ ፈዋሽ ጠበሎች የሚገኙበት፡፡ ጽዶቹ ሳይቀሩ #በ72 አርድዕት ቅዱሳን አምሳያ የተተከሉበት፤ በቀድሞ ዘመን መዐዛ ቅዳሴ የተሰኘው የአባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ቅዳሴ በወርኃ ጽጌ የሚቀድስበት፤ 3 ጳጳሳትን ያፈራ፣ ……. ደብር ነው፡፡ ✣ ለደብረ ሰላም ይደልዋ ስብሐት፤ እስመ በውስቴታ ኀደረ መድኀኔዓለም (በደብረ ሰላም በውስጧ መድኀኔዓለም ስላደረ ምስጋና ይገባታል፡፡) በዓሉ በዚሁ ደብር በታላቅ ድምቀት ይከብራል፡፡ https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool

#በምዕራብ ወለጋ እና በጉራፈርዳ እንዲሁም በቤንሻንጉል በግፍ #የተገደሉ ዜጐች አስመልክቶ ከቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ በከፊል ---------- ፟አላስፈላጊ በሆነ ምክንያት በግፍ ለተገደሉትና ሕይ
#በምዕራብ ወለጋ እና በጉራፈርዳ እንዲሁም በቤንሻንጉል በግፍ #የተገደሉ ዜጐች አስመልክቶ ከቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ በከፊል ---------- ፟አላስፈላጊ በሆነ ምክንያት በግፍ ለተገደሉትና ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖቻችን በቤተ ክርስቲያናችን ስም ልባዊ ሐዘናችንን እየገለጽን ዳግሞ እንዲህ ዓይነት ኢ-ሰብአዊ ድርጊት እንዳይፈጸም መንግሥት ለዜጐች አስፈላጊውን ጥበቃ እንዲያደርግ ወንጀለኞችንም ለፍርድ እንዲያቀርብ እያሳሰብን መላው ኢትዮጵያውያን ልጆቻችንም በቀጣይ ለጋራ ሰላምና አንድነት እንድትቆሙ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡ የሞቱ ወገኖቻችንን ነፍስ ይማርልን፡፡፟ እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ፤ ይቀድስ፤ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!! አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም. ---------- በሞት የተለዩንን ወገኖቻችንን እግዚአብሄር በእቅፉ ያኑርልን አሜን! https://t.me/medihanaelem

ወረብ (ቅኝት) —>ጌራ ወርቅ— (የቀጨኔ ደብረሰላም የቤቱ ቀለም ) ፤ በመሪጌታ ሙሉጌታ ተክለ ያሬድ ከማኀሌተ ጽጌ ዩቲዩብ ገጻችን ላይ ይመልከቱ https://youtu.be/EAOmo0vR8wU

በሃገራችን ከሚገኙ #በመድኀኔዓለም ስም የተሰየሙ #አብያተ_ክርስቲያናት፤ #ስብስብ 2፤ ጨነቅ ዋሻ መድኀኔዓለም፤ በቅዱስ ላሊበላ በዋሻ ውስጥ እንደገና ፎቅ ተደርጎ የተፈለፈለ፤ በሰሜን ተራሮች (በራስ
+3
በሃገራችን ከሚገኙ #በመድኀኔዓለም ስም የተሰየሙ #አብያተ_ክርስቲያናት፤ #ስብስብ 2፤ ጨነቅ ዋሻ መድኀኔዓለም፤ በቅዱስ ላሊበላ በዋሻ ውስጥ እንደገና ፎቅ ተደርጎ የተፈለፈለ፤ በሰሜን ተራሮች (በራስ ደጀን) እግር ሥር የሚገኝ፤ በፓርክ ክልል ውስጥ በመኾኑ በብዙ ኢትዮጵያውያን የማይታወቅ፤ ነገር ግን ብዙ ተዓምራትን እጅጉን ፈዋሽ የኾነ ጠበል የሚገኝበት፡፡ 1. ✤መናገሻ ጋራ መድኀኔዓለም፤ ግማደ መስቀሉ ያረፈበት፤ ቀድሞ የቅዳሴ ቤቱን ታላቁ አባት አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ (ቀድሞ የልደታ ቤ.ክ) በአካል በመገኘት በመስቀሉ የባረከው፤ በድርሳነ ራጕኤል ላይ የተገለጸና ቅዱስ ራጕኤል የማይለየው፤ በአረማዊው ግራኝ ወረራ ጊዜ ቤተ ክርስቲያኑ ካህናቱን መነኮሳቱንና ምዕመናኑን እንደያዘ በምድር ውስጥ ገብቶ የተሰወረበት በሥጋ ዕረፍተ ሞት ያልተገቱ ሥውራን ግሩማን አበው የሚኖሩበት "ዛቲ ይእቲ አምባ ማርያም መካነ ክብሮሙ ወጸሎቶሙ ለቅዱሳን ወለነገሥታተ ኢትዮጵያ በሐ በልዋ ተሳለምዋ ጊሱ ሐቤሃ ኢትርሐቁ እምኔሐ" ብለው አበው ያወደሷት የጸሎት የአርምሞና የትኅርምት ቦታ፡፡ 2. ✤ገዳመ አባ ጽጌ ድንግል (መድኀኔዓለም ቤ.ክ)፤ ማኅሌተ ጽጌ የተደረሰበት ወሎ፤ ወግዲ፤ ወለቃ ወንዝ አጠገብ፤ የበረሃው ዕንቊ ገዳም፤ አባ ጽጌ ድንግል የፈለፈሉት ባለ 3 መቅደስ እጅግ ሰፊ ዋሻ ቤ.ክ፡፡ 3. ✤ደብረ ቀራንዮ መድኀኔዓለም ቤ.ክ፥ አዲስ አበባ፤ በአዲስ አበባ ከተመሠረተ ከ1826 ዓ.ም ጀምሮ ፍልሰት ሳያጋጥመው በመቆየቱ፤ የመጀመሪያው የአዲስ አበባ ቤ.ክ፡፡ (ነገር ግን በመሃል ፍልሰት እያጋጠማቸው እንጂ በአዲስ አበባ ከ1600 ዓመታት በፊት ደብረ ኤረር፣ የካ ዋሻ ተክለሃይማኖትና /ኋላ የካ ሚካኤል/ በአብርሃ ወአጽብሃ ዘመን፤ እንዲሁም እንጦጦ ኪዳነ ምሕረት በአልአሜዳ ዘመነ መንግሥት መመሥረታቸውን ልብ ይሏል)

#እንኳን ለመድኀኔዓለም ክብረ በዓል (ለመጋቢት 27 #ጥንተ_ስቅለት ልዋጭ በዓል)ና ለአቡነ #መብዓ_ጽዮን ክብረ በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡ ✤፨✤ #አቡነ መብዓ ጽዮን አቡነ መብዓ ጽዮን ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በዓል (ጥቅምት 27 ቀን) ጋር አብረው የሚታሰቡ ታላቅ የተጋድሎ አባት ናቸው፡፡ የጻድቁ አቡነ መብዓ ጽዮን መታሰቢያቸው ከመድኃኔዓለም በዓል ጋር ስለሆነ በዚህ ጽሁፍ ሥር ታሪካቸውን ይዘን ቀርበናል፡፡ መልካም ንባብ! አቡነ መብዓ ጽዮን የተገኙት እግዚአብሔርን እያስደሰቱ ያለነቀፋ ከሚኖሩ ቅዱሳን ነው፡፡ በክህነታቱ፣ በየዋህነቱ ከሰዎች የተስማማው አባታቸው ሀብተጽዮን፣ በደግነቷና በቸርነቷ የምትታወቀው እናታቸው ጽዮንትኩና በሕግ በንፅህና በጋብቻ ተወስነው ሲኖሩ የተባረከ ልጅ ይሰጣቸው ዘንድ ወደ ጌታ ይለምኑ ነበር፡፡ የለመኑትን የማይነሳ መድኃኔዓለም ክርስቶስም መብዓ ጽዮን የተባለ ደግ ልጅ ሰጣቸው፡፡ መብዓ ጽዮን ከልጅነቱ ጀምሮ ማስተዋል እና የእግዚአብሔር ፍቅር ያደረበት ሰው እንደነበር ገድሉ ይናገራል፡፡ ይኸውም በአንዲት ቀን ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ተቀብሎ ከቤተክርስቲያን ወጥቶ ይሄድ የነበረ ሰው እግሩን እንቅፋት ተመቶ ደሙ ከመሬት ሲፈስስ በአየ ጊዜ እውቀት በልጅነቱ የሞላ መብዓ ጽዮን የደማው ጣቱ እስኪደርቅ ድረስ ጠባው፡፡ በመሬት የፈሰሰ ደሙን ከአፈሩ ጋር በላ፡፡ ይህ ሥራው ከልጅነቱ የመስቀሉ ፍቅር በልቡ የቸነከረ መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡ #ያገባ ሰው ሚስቱን ደስ የሚያሰኝበትን ሥራ ያስባል፡፡ ያላገባ ግን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘውን ሥራ ያስባል$ የሚለው የመጽሀፍ ቃል ያፀናው ወጣቱ መብዓ ጽዮን ከቤተሰቡ የመጣለትን የጋብቻ ጥያቄ አልተቀበለውም፡፡ ኃጢአትን ከመጨመር ውጭ ምን እጠቀማለሁ እያለ የዚህችን ዓለም ጣዕም ናቃት፡፡ በዚህም ቤተሰቦቹ ተውት፣ እርሱም ራሱን ይበልጥ ለእግዚአብሔር አስገዛ፡፡ የምንኩስና እና ተጋድሎ ሕይወቱ የምንኩስ እና የተጋድሎ ሕይወት የጣመ የላመ የሌለበት ፍፁም ራስን ለእግዚአብሔር ማሳለፍ ነው፡፡ ይህንን የማይወድ ጠላት ዲያብሎስ ደግሞ ፍፁም ፈተናን ያበዛል፡፡ ቅድሳንም በረድኤተ እግዚአብሔር እና በተጋድሏቸው ያልፉታል፡፡ ሠይጣንን ድል ይነሡታል፡፡ አቡነ መብዓ ጽዮንም የምንኩስና ቀንበር ከተሸከመ ጊዜ ጀምሮ ከፈረስ፣ ከበቅሎ፣ ከአልጋ፣ ከምንጣፍ ላይ ሳይቀመጥና ሳይተኛ መኖሩን ገድሉ ይነግረናል፡፡ ለዚህም ተጋድሎ ሕይወቱ ያግዘው እና ይረዳው ዘንድ ክህነትን አባ ገብርኤል ከተባለ ጳጳስ ተቀብሏል፡፡ ቄስም ሆኖ የመድኃኔዓለምን ሥጋው እና ደሙን እያቀበለ ብዙ ዘመን ኖሯል፡፡ የምንኩስና ሕይወቱና ትጋቱም ታላቅ አባት እንደሆነ ያስረዳል፡፡ ትልቅ ድንጋይ በደረቱ ተሸክሞ ከምድር ከአመድ በተቀመጠም ጊዜ በራሱ ተሸክሞ፣ በሚሰግድም ጊዜ በጀርባው አዝሎ ስለ ክርስቶስ መከራ ያስባል፡፡ ራሱን ይበድላል፣ ስጋውን ያደክማል፡፡ ይኸውም ያለሰንበት እና ያለበዓላት በቀር በዚህ ተጋድሎ የምንኩስና ሕይወቱን ቀጠለ፡፡ ከዛም ወደ ደብረ ሊባኖስ በመሄድ ከአቡነ ተክለሃይማኖት መቃብር በረከትን እንደተቀበለ ገድለ መብዓ ጽዮን ይነግረናል፡፡ አቡነ መብዓ ጽዮን ራሱን ለእግዚአብሔር በሰጠ ቁጥር መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ በስጋወደሙ እየተገለፀ፤ እመቤታችንም እየታየች ትመክረው ታስተምረው ነበር፡፡ ቅዱሳንን ማክበር በዓላቸውን መዘከር እንዲገባ ከምንማርባቸው ታሪኮች አንድ የአቡነ መብዓ ጽዮን ታሪክ ነው፡፡ የመድኃኔዓለምን እና የእናቱን የቅድስት ድንግል ማርያምን በዓል አብዝቶ ያከብር ነበር፡፡ በዚህም መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ እና ከቅድሳን ጋር መጥቶ ባርኮታል፡፡ የመለኮት ምሥጢርም ሥርዓትም በአካባቢው ላሉ ሠዎችም ተሠጥቷቸዋል፡፡ መናፍቃን በዓል ማክበር አይገባም ቢሉ የበዓል ማክበር ውጤቱ እዚህ ድረስ መሆኑን እናያለን፡፡ በፀሎቱም #ኦ እግዚኦ አንተ ትብለኒ ሰአል ኩሎ ዘፈቀድከ ወአነ እሁበከ፣ ጌታ ሆይ አንተ የወደድከውን ሁሉ ለምን እኔ እሠጥሃለሁ አልከኝ፡፡ አሁንም የለመንኩን ግለጽልኝ$ በማለት የቀራንዮን መስቀል መከራውን ያሳየው ዘንድ ሁልጊዜ ይለምን ነበር፡፡ የለመኑትን የማይነሳ መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስም ቅዱሳን የሆኑ እጆቹን በመስቀሉ እንዲዘረጋ፣ እግሮቹም እንዲቸነከሩ፣ የሾህ አክሊልም በራሱ ተሸክሞ የጥቅምት 27 ቀን ታየው፡፡ ለሙሴ ሊታያቸው እንዳልቻለ አባ መብዓ ጽዮን ከመሬት ወደቀ፡፡ እንደ ሞተም ሆነ፡፡ ማንም የመስቀሉን መከራ ሕማሙን ማየት እንደማይችል ነገረው፣ በቸርነቱም አነሳው፡፡ የሞቱ ገናንነት የሚያስፈራ እና የሚያስደነግጥ መሆኑን አሳውቀው፡፡ መከራው ታላቅ በሰው አእምሮ አይታሰብምና ነው፡፡ ኃጢአትን ያልሠራ ሐሰትም በአፉ ያልተገኘበት ስለሠው ኃጢአት ስለሞተው ስለመድኃኔዓለም ክርስቶስ የሞቱ መታሰቢያ በምትሆን በዕለተዓርብ ታላቅ ተጋድሎን በማድረጉ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የስቅለት በዓል በሚታሰብበት በ27 በመድኃኔዓለም ዕለት የአቡነ መብዓ ጽዮን መታሰቢያ ተደረገ፡፡ ይኸውም ጥቅምት 27 ነው፡፡ /ከቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ሰሌዳ መጽሔት የተወሰደ/ የጻድቁ የአባታችን የአቡነ መብዓ ጽዮን በረከት ከእኛ ጋር ትሁን!!! የመስቀሉ ፍቅር በልባችን ይኑር አሜን!!!

#ጥቅምት 20 የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ መተዳደሪያ ደንብ በቅዱስ ሲኖዶስ ጸደቀ ፤ በኮሮና ቫይረስ ሳቢያ የተሸኙት ደቀ መዛሙርቱ ከሰኞ ጀምሮ ይመለሳሉ !!! የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ዓርብ ጥቅምት 20 ቀን የቀትር በኋላ ውሎው ወደ ዩኒቨርሲቲ ደረጃ ያደገውን የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የመተዳደሪያ ደንብ አጽድቋል፡፡ ምልአተ ጉባኤው አስቀድሞ የሰየመው የብፁዓን አባቶች ፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሓላፊዎች እና ልዩ ልዩ ምሁራን ኮሚቴ ከዩኒቨርሲቲው ሠራተኞች ጋራ በመኾን በአማርኛ እና በእንግሊዘኛ ቋንቋዎች ያዘጋጁት የመተዳደሪያ ደንቡ የመንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲውን ተጠሪነት ፣ አደረጃጀት እና የዐዲስ ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ በማስፋፋት እና በማጠናከር የሚመራበት መኾኑ ታውቋል፡፡ የመንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲው የበላይ ሓላፊ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ ለምልአተ ጉባኤው አቅርበውት በቅዱስ ሲኖዶሱ የጸደቀው የአንጋፋው ተቋም መተዳደሪያ ደንብ በዐዲስ መልክ የተዘጋጀውን ሥርዐተ ትምህርት ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚያስችል ታምኖበታል፡፡ በይዘቱም የሚከተሉትን ዐበይት ለውጦች ማካተቱ ተጠቁሟል፦ • ለጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የነበረው ተጠሪነቱ ለቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ኾኗል ፤ • በዋና ፕሬዝዳንት እና በኹለት ማለትም በአካዳሚክ እና በአስተዳደር ምክትል ፕሬዝዳንቶች ይመራል ፤ የበላይ ሓላፊው ሊቀ ጳጳስ የዩኒቨርሲቲው ብፁዕ ፕሬዝዳንት ናቸው ፤ • የሀገርን ታሪክ እና የውጭ የነገረ መለኰት ኮሌጆች ልምዶችን ያገናዘበ የሥርዓተ ትምህርት ክለሳ ተደርጓል ፤ ከቅድመ ምረቃ እስከ ዶክትሬት ዲግሪ ለሚጠናባቸው የትምህርት መርሐ ግብሮች ሦስት ዋና ዋና የትምህርት ዘርፎች(Faculties) ተደራጅተዋል ፤ • የመሠረተ እምነት(Faculty of Fundamental Theology – FFT)፣ የተግባረ እምነት(Faculty of Practical Theology – FPT) እና የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጥናት(Faculty of Ethiopian Church Studies – FECS)ተደራጅተው በየራሳቸው የዘርፍ ሓላፊዎች ይመራሉ፤ • የትምህርት ዘርፎቹ በሥራቸው ልዩ ልዩ የትምህርት ዓይነቶችን ያቀፉ 10 የትምህርት ክፍሎችን (Departments) እና በየትምህርት ክፍሎቹ የተካተቱ 311 የትምህርት ዓይነቶችን (ኮርሶችን) አካተዋል ፤ *** • በዐዲሱ ሥርዓተ ትምህርት፣ ደቀ መዛሙርቱ በአራቱ ዓመት ቆይታቸው የአብነት ትምህርቶችን በተጓዳኝ ቀስመው ለመውጣት እንዲችሉ መጽሐፍ ቤት ፣ ቅኔ ቤት ፣ ዜማ ቤት እና አቋቋም ቤት ጊዜውን በዋጀ ዘመናዊ የማስተማሪያ ሥርዓት ተዘጋጅተዋል ፤ • በተጨማሪም የማኅበራዊ ሳይንስ ጥናት ፣ ባሕላዊ የሕክምና ምርምር ፣ የፍልስፍና ዕይታ ፣ የቋንቋ ትምህርት ፣ የሕግ ትምህርት እና የፍትሕ መርሕ ፣ የመልካም አስተዳደር አመለካከት ፣ የንግድ ሥራ አደረጃጀትና አስተዳደር ወዘተ አጉልቶ በማውጣት ያስታውቃል ፤ • በዩኒቨርሲቲው የሚሰጡ ትምህርቶችን በሀገር ውስጥና በውጪ ኾነው በርቀት መማር ለሚፈልጉ ተማሪዎች በተደራጀ መንገድ ለማስተማር የE-Learning ማስተማሪያ ዘዴው ተሠርቶ አገልግሎት ላይ እንዲውል ተደርጎ አድማሱ ሰፍቷል ፤ • በሦስት ዓመት ለካህናት በአማርኛ እየተተረጎመ ሲሰጥ የቆየው የልዩ ፕሮግራም ቴዎሎጂ ዲፕሎማ ከተያዘው ዓመት ጀምሮ በአንድ ዓመት አጥሮ በሥልጠና ሰርቲፊኬት ይተካል ፤ • የአስተዳደር እና ልማት ዘርፎች በሰው ኃይል እና ቴክኖሎጂ ይጠናከራሉ ፤ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲውን በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሥርዓት ለማበልጸግ የሚያስችል ውል ተፈርሞ፣ ሥራው እየተፋጠነ ይገኛል ፤ *** በሌላ በኩል፣ በኮሮና ቫይረስ ወረርሺኝ ምክንያት የተቋረጠውን የመማር ማስተማር ሒደት ለማስጀመር በጤና ጥበቃ እና በትምህርት ሚኒስቴር መመሪያዎች መሠረት የቅድመ ጥንቃቄ ርምጃዎቹ እንደተጠናቀቁ በዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ተገልጿል፡፡ የመኝታ ክፍሎች ፣ የመመገቢያ ካፊቴሪያዎች ፣ የመማሪያ ክፍሎች እና ቢሮዎች ፣ ለቅድመ ጥንቃቄው መራራቅ እና ምጣኔ ምቹ ተደርገዋል ፤ ዓርብ ዕለትም የፀረ ተዋሕስያን ርጭት ሲካሔድ ውሏል፡፡ ከመጪው ሰኞ አንሥቶ ነባር መደበኛ ደቀ መዛሙርቱ እንዲገቡ ጥሪ ማስተላለፉ ታውቋል፡፡ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲው በቀኑ መርሐ ግብር በዐዲስ ገቢ ከሚቀበላቸው የመጀመሪያ ዓመት እና የድኅረ ምረቃ ተመዝጋቢዎች ጋራ እስከ 250 መደበኛ ደቀ መዛሙርት ይኖሩታል፡፡ ጥቅምት 20 በተጠናቀቀው የማታው መርሐ ግብር ምዝገባም ከ1ሺሕ058 በላይ ተማሪዎች አሉት፡፡ የ2013 ዓ.ም. የትምህርትን ዘመን የሚጀምረው በታኅሣሥ ወር ሲኾን ከዚያ ቀደም ብሎ ባለው የአንድ ወር ጊዜ ውስጥ የዝጉን ወቅት የሚያካክስ ትምህርት በመስጠት ፣ የመፈተንና የማጥራት ብሎም ደቀ መዛሙርቱን ለቀጣዩ ደረጃ የማመቻቸት ሥራ ይከናወናል፡፡ በቅድመ ጥንቃቄ መመሪያው መሠረት ተማሪዎችን አራርቆ እና አመጣጥኖ የመማር ማስተማር ሥራውን ለማስቀጠል ዝግጅታቸው ከተጠናቀቁት ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎች እና ዶርሚተሪዎች ባሻገር ፣ የመምህራንንና የአስተዳደር ሠራተኞችን አበል መሸፈን ይጠበቅበታል፡፡ ይኸውም የመንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲውን ወጪ በማናሩ ለጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ባቀረበው የ2013 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን ዕቅድ 30 ሚሊዮን ብር የወጪ በጀት መጠየቁ ተመልክቷል፡፡ የቤተ ክርስቲያንን መንፈሳዊ እና ዘመናዊ የትምህርት ተቋማት የመጠበቅ ፣ የማስፋፋት እና የማጠናከር እንዲሁም ተጠሪነታቸውንና ደረጃቸውን የመወሰን ሥልጣን ያለው ቅዱስ ሲኖዶስ ከኅዳር ወር 2011 ዓ.ም. ጀምሮ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ እየተባለ ለቆየው አንጋፋ የትምህርት ተቋም የመተዳደሪያ ደንቡን በማጽድቅ በሕግ ወደ ዩኒቨርሲቲ አሳድጎታል፡፡ በተጨማሪም ከዚሁ በማስከተል የቀረበውን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፖሊሲ መርምሮ እንዲሠራት አጽድቋል፡፡ በተያያዘ ዜና ... ምልአተ ጉባኤው የበጀት እና ሒሳብ መምሪያ አዘጋጅቶ ባቀረበው የ2013 ዓ.ም. የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በጀት ረቂቅ ላይ በመወያየት በሰጠው አስተያየት መሠረት ተስተካክሎ እንዲቀርብ አዟል ፤ በዛሬው ዕለት እንደሚያጸድቀውም ይጠበቃል፡፡

#ቅዱስ_ሲኖዶስ: በምሥራቅ ጎጃም ቆጋ ምስካበ ቅዱሳን ኪዳነ ምሕረት ገዳም የተፈጸመውን #ኢቀኖናዊ እና ኢሕጋዊ የጵጵስና እና የፕትርክና ሹመት #ሻረ፤ እጃቸውን ያስገቡ ባዕዳን እንዲቆጠቡ አሳሰበ!!! • የቤተ ክርስቲያንን ቀኖና በመጣስ እና ሕግን በመተላለፍ ፣ ራሳቸውን በራሳቸው የሾሙ መነኰሳት ፣ በቀኖና እንዲቀጡ ወሰነ ፤ የቅስና ሥልጣናቸው እና ማዕርገ ምንኵስናቸው ተጠብቆላቸዋል ፤ • “ኮሚቴ ነን” እያሉ የተወገዘውን የቅብዐት እምነት በቤተ ክርስቲያናችን ይዞታ እና ንብረት ለማደራጀት የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦች ፣ ከሕገ ወጥ ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳሰበ ፤ • ፕሮቴስታንታውያንና የተሐድሶ መናፍቃን ፣ በገንዘብም ጭምር እንደሚደግፉት በማስረጃ በመረጋገጡ፣ ከጣልቃ ገብነት እጃቸውን እንዲሰበስቡ አስጠነቀቀ ፤ • በአንዲት ቤተ ክርስቲያን በአንድ ሃይማኖት እና በአንድ ካህን የምትፈጸመው ጥምቀት አንዲት በመኾኗ ፣ “ዳግም ጥምቀት” በሚል የሚደረገው እንቅስቃሴ እንዲቆም አዘዘ ፤ • ሀገረ ስብከቱ ፣ ኦርቶዶክሳዊውን የነገረ ክርስቶስ (ነገረ ሥጋዌ) አስተምህሮ ፣ በልዩ እና ተከታታይ የስብከተ ወንጌል ጉባኤያት እንዲሁም የትምህርተ ወንጌል እና የሥልጠና መርሐ ግብሮች እንዲያጠናክር እና እንዲያጸና መመሪያ ሰጠ ፤ • ሕገ ወጦቹን ተሿሚዎች እና ግብረ አበሮቻቸውን በማጋለጥ እና በመቆጣጠር ትብብር ያደረጉ ፣ የሀገረ ስብከቱን አድባራት እና ገዳማት ፣ ምእመናንና የመንግሥት አካላት አመሰገነ፡፡

የሰሞኑን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዕተ ጉባኤ #ጥቅምት ፳፪/፳፻፲፫ ዓ/ም #ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በምልዓተ ጉባኤ ውሳኔ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበበ ሀገረ ስብከት ገቡ፡ #አባቶች "እኛና መንፈስ ቅዱስ ወሰንን" ብለው ያገለገሉባት ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን በመሆኗ የአባቶቼን አደራ ለመቀበል ችያለሁ " ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ ጥቅምት ፳፪/፳፻፲፫ ዓ/ም የዚህ ዓመት የጥቅምት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ከወሰናቸው ውሳኔዎች መካከል አንዱ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ራሱን ችሎ በሊቀ ጳጳስ ይመራ የሚለው እንደሆነ ከጽ/ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ ይህንን ተከትሎ ቅዱስ ሲኖዶስ ሦስት ሊቃነ ጳጳሳትን ለቦታው አጭቶ በውጤቱም ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሀገረ ስብከታቸውን እንደያዙ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከትን እንዲመሩ ምልዓተ ጉባኤው መርጧቸዋል ተብሏል፡፡ ስለሆነም ጥቅምት ፳፩ /፳፻፲፫ ዓ/ም ከሰዓት በኋላ የተመደቡት ብፁዕ ሊቀ ጳጳስ አቡነ መልከ ጼዴቅ ከቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍና ከሌሎች ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ጋር በመሆን ወደ ሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት ያቀኑ ሲሆን በሀገረ ስብከቱ የስብከተ ወንጌል አዳራሽ እንደቤተ ክርስቲያኗ ሥርዓት አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡ በመርሐ ግብሩ ላይ በቅድሜያ የሓላፊነት ደብዳቤው በብፁዕ አቡነ ናትናኤል የተነበበ ሲሆን አያይዘውም ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት መልእክት አስተላልፈዋል፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና በአዲሱ ምድባቸው የሲዳማና የጌዲኦ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጉዳይ በሰፊው ቅዱስ ሲኖዶስ የተወያየበትና የሄደበትን ሂደት ያነሱት በተለይም ሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ ፶ ማሻሸያ የተደረገበት እንደሆነበትም የጠቅሱ ሲሆን የብፁዕነታቸው የሓላፊነት ደብዳቤ አወጣጥ በተመለከተም በቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ይውጣ ብሎ ያዘዘው ምልዓተ ጉባኤው በቃለ ጉባኤ አስደግፎ እንደሆነም ገልጸዋል፡፡ አክለውም ብፁዕነታቸው ሀገረ ስብከቱን በመልካም ስም ለሌላው አርአያ ሊሆን በሚችል መልኩ በመልካም አስተዳደር መመራት እንዳለበትም በአጽንዖት ተናግረዋል፡፡ ብፁዑ አቡነ ሳዊሮስ በበኩላቸው የቅዱስ ሲኖዱስ ውሳኔ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ነባራዊ ሁኔታ በማጥናት የተሰጠ መፍትሔ ሲሆን ለሌሎች አህጉረ ስብከትም ደረጃ በደረጃ ችግሮችን ለመቅረፍ በመንፈሳዊ ጥብዓት እየሰራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ብፁዕነታቸው አክለውም ሁላችንንም የጠራችን የሰበበሰችን ይህችው ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ናት እናም በአሁኑ ጊዜ እየደረሰባት ያለውን መጠነ ሰፊ መከራ ለመቅረፍ በውስጥ ያለው የአስተዳደር ችግር በመቅረፍ ለዘለዓለማዊ ቅዱስ ወንጌል ዓላማና ሕይወት ተገግቶ መሥራት የሚገባን ሰዓት ነውም ብለዋል ፡፡ የተመደቡት ብፁዕ ሊቀ ጳጳስ አቡነ መልከ ጼዴቅ በበኩላቸው ሀገረ ስብከቱን የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተ/ሃይማኖት ረዳት ሊቀ ጳጳስ ሆነው ሀገረ ስብከቱን የመሩ መሆናቸውን አውስተው የአሁኑ የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ድንገተኛ እንደሆነባቸውና አልሆንም ፣አይገባኝም ብለው እንደነበር በኋላ ግን አባቶች "እኛና መንፈስ ቅዱስ ወሰንን" ብለው ያገለገሉባት ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን በመሆኗ የአባቶቼን አደራ ለመቀበል ችያለሁ ብለዋል፡፡ ብፁዕውነታቸውም አያይዘውም ሁሉን በሁሉ የሚያደርግ እግዚአብሔር ነውና ፈቃዱን በሠመረ አገልግሎት እንድንገልጥ ከሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት ጀምሮ እስከ አጥቢያ ያለው አገልጋዩ እና ምዕመናን ተግባራዊ ተሳትፏቸው እጅጉን አስፈላጊ ነውም ብለዋል፡፡ በመጨረሻም ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ለብፁዕነታቸው መልካም የአገልግሎት ዘመን እንዲሆንላቸውም ተመኝተው መርሐ ግበሩን በጸሎት ዘግተዋል፡፡ #ጥቅምት 21 ቅዱስ ሲኖዶስ የብፁዓን አባቶች ዝውውር እና ምደባ አደረገ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ ከኒውዮርክ ቀድመው ወደነበሩበት ምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት መመለሳቸው ምልዓተ ጉባኤውን እያነጋገረ ነው!!! የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዛሬ ቅዳሜ ጥቅምት 21 ቀን ውሎው የአራት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ዝውውር አድርጓል፡፡ በዚኽም መሠረት፡- 1) የምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ በፈቃዳቸው ለመዛወር ባቀረቡት ጥያቄ መሠረት፣ ወደ ሲዳማ ጌዲዮ እና ቡርጂ ዞኖች አህጉረ ስብከት(ሓዋሳ) ተዛውረዋል፤ በእርግና ያሉት ብፁዕ አቡነ ገብርኤል በመንበረ ፓትርያርክ ማረፊያቸው በጸሎት ተወስነው ረዳት እንዲመድብላቸው ወስኗል፡፡ 2) የኒውዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ ቀድሞ ወደነበሩበት ምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ተዛውረው እንዲሠሩ እና የምሥራቅ አውስትራልያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ወደ ኒውዮርክ እንዲዛወሩ ወስኗል፡፡ *** የምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት፥ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ፣ ከአስተዳደራዊ ችግር ጋራ በተያያዘ በከፍተኛ እና ተደጋጋሚ የሕዝብ ተቃውሞ የተነሡበት እንደነበር እየታወቀ በዝውውር ተመልሰው እንዲመደቡ መደረጉ፣ “ሁከቱን ዳግም ይቀሰቅሰዋል፤” በሚል የምልአተ ጉባኤውን አባላት እያነጋገረ ነው፤ ቅዱስ ፓትርያርኩም ጭምር፣ “ይኼ ነገር ችግር ያመጣል፤” ብለው ስጋታቸውን ቢገልጹም፣ የብፁዕ አባ ማርቆስን መመለስ የሚደግፉ ብፁዓን አባቶች ቡድን፣ “ሀገረ ስብከቱን ቀድሞም ያውቁታል፤ ሰላም ያደርጉታል፤ ያለሙታል፤” በማለት ግፊት በማድረጋቸው፣ ማሳሰቢያው ሰሚ አጥቶ ዝውውሩ መወሰኑ ተጠቁሟል፡፡ **** 3) የምዕራብ አውስትራልያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሙሴ ሀገረ ስብከታቸውን እንደያዙ የምሥራቅ አውስትራልያ ሀገረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ መድቧቸዋል፡፡ 4) ባለፈው ዓመት ባረፉት የዩናይትድ ኪንግደም እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጎርጎሬዎስ ምትክ የሩቅ ምሥራቅ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ ያዕቆብ ሀገረ ስብከታቸውን እንደያዙ ደርበው እንዲሠሩ መድቧቸዋል፡፡

#እንኳን ለጥቅምት መድኀኔዓለም ክብረ በዓል (ለመጋቢት 27 ጥንተ ስቅለት ልዋጭ በዓል)ና ለአቡነ መብዓ ጽዮን ክብረ በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡ በሃገራችን ከሚገኙ የመድኀኔዓለም ገዳማትና አ
+1
#እንኳን ለጥቅምት መድኀኔዓለም ክብረ በዓል (ለመጋቢት 27 ጥንተ ስቅለት ልዋጭ በዓል)ና ለአቡነ መብዓ ጽዮን ክብረ በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡ በሃገራችን ከሚገኙ የመድኀኔዓለም ገዳማትና አድባራት ጥቂቶቹ፤ ፤ ስብስብ 1፤ ፠ ለየብቻቸው ያሉት፤ ዋልድባ አበረንታት መድኀኔዓለም ገዳምና ኤልሻማ ደብረ ማኅቶት መድኀኔዓለም ቤ.ክ. ፠ አንድ ላይ ያሉት፤ ✤1. ዋልድባ አበረንታት መድኀኔዓለም ገዳም፤ ✤2.ላሊበላ መድኀኔዓለም ✤3. ጎንደር መንበረ መንግሥት መድኀኔዓለም ✤4. መንዳባ አቡነ ያሳይ መድኀኔዓለም፤ ጣና ✤5. ሽረ እንዳሥላሴ መድኀኔዓለም ወመስቀል ክብራ ✤6. ቆላድባ መድኀኔዓለም፤ ጎንደር ከተማ አጠገብ ✤7.ቦሌ ደብረ ሳሌም መጥምቁ ዮሐንስ፤ (የመድኀኔዓለም ታቦት በድርብ አለ) ✤ 8.ድሬዳዋ መድኀኔዓለም ✤9.ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም

ሥርዓተ ማኀሌት ዘወርኀ ጽጌ ‹‹ዘላይ ወዘታች››ቤት ፫ኛ ዙር ዓመተ ፤፬ኛ ሳምንት፣ ጥቅምት ፳፪ በዓለ ሉቃስ ወንጌላዊ
+3
ሥርዓተ ማኀሌት ዘወርኀ ጽጌ ‹‹ዘላይ ወዘታች››ቤት ፫ኛ ዙር ዓመተ ፤፬ኛ ሳምንት፣ ጥቅምት ፳፪ በዓለ ሉቃስ ወንጌላዊ

#የአራዳና ጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰንበት ት/ት ቤቶች አንድነት አዲስ የስራ አመራር ምርጫ አደረገ፡፡ በዚሁም መሰረት  #_ኤልያስ_አበበ ከመንበረ ንግስት ቁስቋም ማርያም ቤተክርስቲያን ዋና_ሰብሳቢ 
#የአራዳና ጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰንበት ት/ት ቤቶች አንድነት አዲስ የስራ አመራር ምርጫ አደረገ፡፡ በዚሁም መሰረት  #_ኤልያስ_አበበ ከመንበረ ንግስት ቁስቋም ማርያም ቤተክርስቲያን ዋና_ሰብሳቢ  #_ይስሐቅ_ወርቅዬ ከቀ/ደ/መድኃኔዓለም ወደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ #_ዋና_ጸሐፊ ሆነው ተሹመዋል በመቀጠልም የአ.አ ሐገረ ስብከት የሰንበት ት/ት ቤቶች አንድነት በዋና ሰብሳቢነት እንዲመራ ከቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤተክርስቲያን ወጣት መንክር ግርማ በዋና ሰብሳቢነት ተሹሟል ሰንበት ት/ት ቤታችን አዲስ ለተመረጣችሁት አመራሮች መልካም የአገልግሎት ዘመን እንዲሆንላችሁ ተመኝተናል፡፡

ሥርዓተ ማኀሌት ዘወርኀ ጽጌ ‹‹ዘላይ ወዘታች››ቤት ፫ኛ ዙር ዓመተ ፤፬ኛ ሳምንት፣ ጥቅምት ፳፪ በዓለ ሉቃስ ወንጌላዊ ሙሉውን ሥርዓተ ማኀሌት ለማግኝት ወደ facebook ገጻችን (like page)
+1
ሥርዓተ ማኀሌት ዘወርኀ ጽጌ ‹‹ዘላይ ወዘታች››ቤት ፫ኛ ዙር ዓመተ ፤፬ኛ ሳምንት፣ ጥቅምት ፳፪ በዓለ ሉቃስ ወንጌላዊ ሙሉውን ሥርዓተ ማኀሌት ለማግኝት ወደ facebook ገጻችን (like page) 👇 ይሂዱ https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool