fa
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

رفتن به کانال در Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

کانال Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 391 مشترک است و جایگاه 5 600 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 189 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 391 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 26 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 2 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 2 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 20.69% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 10.92% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 180 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 679 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 18 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 27 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

15 391
مشترکین
+224 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
+230 روز
آرشیو پست ها
https://youtu.be/VaMEkAllCCE አዲሱ የግብይይት ሥርዓት (Network Marketing ) እና ማንነት ግንባታ (Self-confidence-Building ) በቤተ-ክርስቲያን እይታ እና በክርስቲያናዊ ሕይወት ፡፡ ክፍል 1

እንኳን ለአባታችን #አቡነ_ሃብተማርያም በዓለ ጽንሰት በሰላም አደረሳቹ:: አቡነ ሀብተማርያም ፠፠በማዕጠንታቸው የታወቁ፤ ፠፠በጽድቅ ሥራቸው የተደነቁ፤ ፠፠5ት መቅሰፍቶችን የሚያርቁ ታለቅ አባታችን ናቸው፡፡፡፨ ፠ታላቁ ጻድቅ አባታችን #አቡነ_ሃብተማርያም የተወለዱት በመንዝ አውራጃ ልዩ ስሙ የራዊ በተባለ ቦታ ሲሆን የአባታቸው ስም ፍሬ ብሩክ የእናታቸው ስም ዮስቴና ይባላል፡፡ ሁለቱም በሕግ ጋብቻ ጸንተው ሕገ እግዚአብሔርን ጠብቀው ምግባር ቱሩፋት ሰርተው በንጽህና በቅድስና ይኖሩ ነበር፡፡ ሆኖም ልጅ አለነበራቸውም፡፡ በዚህ ሁኔታ ያዘኑ ቅድስት ዮስቴና ማለት እናታቸው መንነው በአከባቢያቸው ከሚገኝ ጫካ ውስጥ ዋሻ ፈልገው ገብተው ዘጉ፡፡ በዚያም አንድ መናኝ መነኩሴ አግኝተዋቸው እግዚአብሔር በቅድስቲቱ ያለው ድብቅ ነገር ስለገለጠላቸው አንቺ ለምንኩስና የተፈቀደልሽ አይደለሽም ወደ ቤትሽ ግቢ ጸሎቱ ለዓለም ሁሉ የሚጠቅም ሰው ሁሉ የሚማጸነው ስሙ፣ ገድሉ ትሩፋቱ በዓለም ሁሉ የሚነገርለት ወንድ ልጅ ትወልጃለሽ አሏቸው፡፡ የእግዚአብሔርን ድንቅ ተዓምር የሰሙ ቅድስት ዮስቴናም እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ወደ ቤቸው ተመለሱ፡፡ የተናገረውን የማያስቀር አምላክ በቸርነቱ ጎበኛቸውና ነሐሴ 26 ቀን ጸነሱ፡፡ ግንቦት 26 ቀንም ደም ግባታቸው እንደ ንጋት ኮከብ ያማሩ ሃብተማርያም ተወለዱ፡፡ እናታቸውም ጻድቁን ወልዳ በጽድቅ ኑሮ ኑራ #7_አክሊላትን ተቀብላ በክብር አርፋለች፡፡ ፠አቡነ ሀብተማርያም በሕፃንነታቸው ከእናታቸው ጋር ቆመው ሲያስቀድሱ ‹‹እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ›› ሲባል ይሰማሉ፤ በሕፃን አንደበታቸው ይዘው ሌሊት ሌሊት እየተነሱ ‹‹ማረን እባክህን›› እያሉ ይሰግዱ ነበር፡፡ ትንሽ ከፍ ብለው በእረኝነት ሳሉም ፍጹም ተሐራሚና ጸዋሚ ነበሩ፡፡ ጸጋው ስለ በዛላቸውም ልጅ ሆነው ብዙ ተአምራትን ሠርተዋል፤ ጓደኞቻቸው የሌላ ሰው እሸት እየነቀሉ ሲበሉ እርሳቸው ግን አይበሉም ነበር፡፡ የፈጣሪውን ስም ያቃለለውን አንድ እረኛም በአየር ላይ ሰቅለው አውለውታል፡፡ ፠ወደ ት/ቤት ገብተው ትምህርትን ከቀሰሙ በኋላ ለአካለ መጠን ሲደርሱ ቤተ ሰቦቻቸው ሚስት አጩለት፤ እርሱ ግን ወደ አፋር ከአባ ሳሙኤል ዘንድ ሂዶ ለ12 ዓመታት ረድዕ ሆኖ ተቀመጠ፡፡ ከአፋርም ወደ ምኔት ወደሚባል ቦታ መጥቶ በታላቁ አባት በአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሰ፤ ከአፋር ወደ ይነውፋ፥ ከይነውፋ ወደ ጉሐርብ ወደሚባል ሃገር ሂዶ ምናኔን፣ ትሩፋትንና ተጋድሎን ሠራ፡፡ ለአብነትም፤ ባሕር ውስጥ ሰጥሞ 500 ጊዜ ይሰግዳል፤ በየቀኑ 4ቱን ወንጌልንና 150 መዝሙረ ዳዊትን ይጸልያል፤ በ40 ቀናት ቀጥሎም በ80 ቀን አንዴ ብቻ ይመገባል፤ ምግቡ ደግሞ ሣርና ቅጠል ብቻ ነው፤ በየዕለቱ ያለ ማስታጐል ማዕጠንት ያሳርጋል፤ ዘወትር በንጽሕና ቅዱስ ሥጋውን ይበላል፥ ክቡር ደሙን ይጠጣል፤ በልቡ ውስጥ በፍጹም ቂምን፣ መከፋትን አያሳድርም፡፡ የብረት ሰንሰለት በወገቡ ታጥቆ ይሰግዳል ይጸልያልም፡፡ "ጽድቅና ትሩፋት እንደ ሀብተ ማርያም" የተባለላቸው ታላቅ አባታችን ናቸው ፡፡ ፠ዲቁናን ከጳጳሱ አቡነ ይስሐቅ ዘንድ ተቀበሎ ወደ በዓቱ ተመለሰ፡፡ ፠ኋላ ቆይቶም እንደገና ከአቡነ ይስሐቅ ዘንድ ቅስናን ተቀበለ፡፡ ወደ ጓና ወደ ምትባል ሀገርም ሂዶ ተቀመጠ፡፡ ቀጥሎም ጐላጐት ወደ ምትባል አገር ሂዶ ተቀመጠ፡፡ *የአፄ ናዖድ የንስሐ አባት ነበረና ንጉሡን ያስተምረውና ይገስጸውም ነበር፡፡ ፠ጌታችንም ለጻድቁ የእሳትና የብርሃን ሠረገላን ሰጥቶት በዚያ እየበረረ ወደ ኢየሩሳሌምና ወደ ተለያዩ ቦታዎች ይሔድ ነበር፡፡ ከብዙ የተጋድሎ ዘመናት በኋላም የክብር ባለቤት መድኀኒታችን ክርስቶስ አእላፍ መላእክትን አስከተትሎ መጥቶ እንዲህ አላቸው:: "*ስለ እኔ ረሃብና ጥምን ስለ ታገስክ: *ስለ ምናኔሕ: *ስለ ተባረከ ምንኩስናህ: *ስለ ንጹሕ ድንግልናህ: *ቂምና በቀልን ስላለመያዝህ: *ስለ ንጹሕ ክህነትህና ማዕጠንትህ: *ቅዱስ ወንጌልን በፍቅር ስለ ማንበብህ 7 አክሊላትን እሰጥሃለሁ::" "በሰማይም ከመጥምቁ ዮሐንስ ጐን: 500 የዕንቊ ምሰሶዎች ያሉበትን አዳራሽ ሰጥቼሃለሁ:: በስምህ የሚለምኑ: በቃል ኪዳንህ የሚማጸኑትንም ሁሉ እንድምርልህ 'አማንየ በርእስየ' ብዬሃለሁ" አላቸው:: +ቅዱሳን መላእክትም "ሀብተ ማርያም ወንድማችን" ሲሉ አቀፏቸው:: ጌታ ግን በዚያች ሰዓት አንድም ሦስትም ሆኖ ታያቸውና አቅፎ 3 ጊዜ ሳማቸው:: ከፍቅሩ ጽናትም የተነሳ ነፍሳቸው ከሥጋቸው ተለየች:: መላእክትም ዝማሬም ወሰዷት::  ከተሰጣቸው ቃል ኪዳኖች ውስጥ አምስት መቅሰፍቶች የማስወገድ ሥልጣን ተሰጧቸዋል፡፡ እነርሱም፤ ፩ኛ. #መብረቅ፣ ፪ኛ. #ቸነፈር፣ ፫ኛ. #ረሃብ፣ ፬ኛ. #ወረርሽኝ፣ ፭ኛ. #የእሳት ቃጠሎ ናቸው፡፡ ፨በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ትዕዛዝ ቦታውን ሲባርክ ሦስት አጋንንት በጸሎቱ ሥልጣን የታሠሩለት ታላቅ ጻድቅ ነው፡፡ በግንቦት 26 ተወልዶ፤ በ1490 ዓ.ም. በወርኀ ኅዳር 26 ባረፈ ጊዜም፤ ካህናት በመልካም ልብስ ገንዘው በዝማሬ በማኅሌት ከቅዱስ አባታችን ከአቡነ ተክለሃይማኖት አጽም ጋር በደብረ ሊባኖስ ቀበሩት፡፡ (ከወርቅ ንፁህ ከብርም የጠራ ከሁሉ የሚበልጥ የተመረጠ ሃብተማርያም መልአክ ዘበምድር ነው መልካሙ ዜናው እስከ አጽናፍ ተሰማ፡፡) ✞✞✞✞✞ #አቡነ #ተክለሃይማኖት አና #አቡነ #ሃብተማርያም ✞ #ያን ጊዜ ክቡር የሆነ #አቡነ_ተክለሃይማኖት ጠርቶኝ ልጄ #ሀብተ_ማርያም ሆይ ፈጣሪየ እግዚአብሔር ስለ ወደደህ ብዙ ምህርኮ እንደአገኝህ በአንተ ፈጽሞ ደስ ይለኛል አለኝ ፤ #ነገር ግን የሞለምንክ አንድ ነገር አለና እሽ በለኝ ቢለኝ አቤቱ ጌታዩ ምንድን ነው ነገሩ አልሁት ፣ #ክቡር አባታችን አባ ተክለሃይማኖትም ከተቀበርኩበት ቦታ እንድትቀብር ቃል ኪዳን ግባልኝ አለኝ፤ ይንን አደርግ ዘንድ ስለምን ትለምነኛለህ ብየ ብመልስለት፣ እነሆ በሀገሬ ላይ የታዘዙ አምስ መቅሰፍቶች አሉና ስለዚህ ነው ፤ እሊሁም አንዱ መብረቅ ነው ፣ ሁለተኛው ቸነፈር ነው ፤ ሦስተኛው የረኃብ ጦር ነው ፣ አራተኛ ወረርሽኝ ነው ፡፡ አምስተኛ የእሳት ቃጠሎ ነው ፤ የአንተ አጽም በውስጡ የተቀበረ እንደ ሆነ አጥንቴ የተቀበረባት ሀገር ከእንዚህ መቅስፍታት ትድናለች፣ #……ልጄ ሀብተማርያም ሆይ አንተ የማታውቀው ከፈጣሪያችን ከእግዚአብሄር የተሰጠህ እኔ የማውቀው ክብር አለህና ስለዚህ ነው አለኝ ፣ ይልቁንስ እንዳልኩክ በተቀበርኩበት ቦታ እንተቀበርልኝ ቃል ኪዳን ግባልኝ ብሎ መላልሶ ማለደኝ. ገድለ አቡነ ሃብተ ማርያም #አቡነ_ሀብተ_ማርያም በቃል ኪዳናቸው ሀገራችንን ከአምስቱ መቅሰፍታት ይጠብቁልን አሜን ! በአ.አ በዓሉ በድምቀት ከሚከበርባቸው አድባራት አንዱ በቃሌ ተራራ ደብር መድኃኒት አቡነ ሃብተማርያም ገዳም አንዱ ነው :: በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት የተዘጋጀ ::/ ፠፠፠ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like

#ቅዱስ_ቶማስ_ዘመርዓስ_ የመርዓስ ኤጵስ ቆጶስ የነበረው አባት አባ ቶማስ ክርስቶስን በማመን በጾም፣ በጸሎት፣ በሰጊድ፣ ቀንና ሌሊት በመትጋት ለድኆችና ለምስኪኖችም በመራራት ተጠምዶ የሚኖር ነበር። በዚህ ፅናቱ የክብር ባለቤት ጌታችን መርዓስ ለሚባል አገር ኤጲስ ቆጶስ ይሆን ዘንድ መንጋውንም ይጠብቅ ዘንድ መረጠው አባታችን ቶማስም ሐዋርያዊ ተልዕኮውን እየፈፀመ፣ ሕዝቡን እየመራ ሳለ ከሀዲ ዲዮቅልጥያኖስ በሱ ላይ፣ በአጠቃላይ ሕዝበ ክርስቲያኑ ላይም ተነሳባቸው፣ ክርስቲያኖችንም ያሰቃያቸው ጀመር በአንድ ወቅት ከመኳንንቶች አንዱ የነበረው፣ ቅዱስ ቶማስን ወደ እርሱ ያቀርቡት ዘንድ ጭፍሮቹን ላከ እነርሱም እየደበደቡ በምድር ላይ እየጎተቱ ወሰዱት ደሙም እንደ ውኃ ፈሰሰ ከዚህም በኋላ መኮንኑ ቅዱስ ቶማስን ለአማልክት ስገድ አለው ቅዱሱም እንዲህ ብሎ መለሰለት «እኔ ከሕያው እግዚአብሔር ልጅ ከጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ለረከሱ ጣኦታት አልሰግድም ለረከሱ ጣዖታት የሚሰግድ ሁሉ የተረገመ ነውና» በዚህም ጊዜ መኮንንኑ በጣም ተቆጥቶ እጅግ የበዛ ስቃይን አሰቃየው የነዳጅ ድፍድፍን አፍልተው በላዩ በአፉና በአፍንጫው እስከመጨመርም ደረሱ ልባቸው እንደ ድንጋያ የፀና ስለ ነበር ቅዱስ ቶማስን ገድለው ቶሎ ማሣረፍ አልፈለጉም ይልቁንም የስቃዩን ዘመን አስረዘሙ እንጂ እርሱም ስለ ስህተታቸው ይዘልፋቸው ነበር፣ እንደ ማይመልስም ሲገባቸው በጨለማ ቦታ ጣሉት በየዓመቱም ወደ እርሱ እየሄዱ ከሕዋሳቱ አንድ፣ አንዱን ይቆርጡ ነበር፡፡ በዚህም ለሃያ ሁለት(፳፪) ዓመት ቆየ ሲቆይ ግን አፍንጫውን፣ ከንፈሮቹን፣ ጆሮዎቹን፣ እጆቹንና እግሮቹን ቆርጠው ነበር፤ በዚህም ምክንያት የአገሬው ሰው ሞቷል ብለው አስበው በየዓመቱ መታሰቢያ ያደርጉለት ነበር ይህ ለምን ሳይሞት ቢሉ ጊዜው ሲረዝም ቢሞት ነው እንጂ እስካሁንማ ይመጣ ነበር ብለው ስላሰቡ ነበር፤ ነገር ግን ከሕዋሳቶቹ አብዛኛው ክፍል ቆርጠው ቢጥሉትም አካሉ ግን ተቆራርጦ ሲጣል አንዲት ሴት አየችው፣ ይህችም ሴት በሌሊት ወደርሱ ተሠውራ በመሔድ ትመግበው ነበር፡፡ ጻድቅ ቈስጠንጢኖስም እስከነገሠና የቀናች የክርስቶስን ሃይማኖት ክብር እስከገለጥ ድረስ እንዲህ ሲሰቃይ ኖረ፡፡ #ቈስጠንጢኖስም በነገሠ ጊዜ ስለክርስቶስ በመታመን የታሠሩ እስረኞች ሁሉ እንዲፈቱ በማዘዙ ሁሉም ተፈቱ፡፡ ቅዱስ ቶማስ ግን የተጣለበት ቦታ፤ በሕይወት ያለም ስላልመሠላቸው አላወጡትም ነበር፤ ነገር ግን ይህን አዋጅ ትመግበው የነበረችው ሴት ሰምታ ነበርና ወደ ካህናቱ ዘንድ ሄዳ ስለ ቅዱስ ቶማስ ሃያ ሁለት ዓመት በዚያ ስለመኖሩ ነገረቻቸው ቦታውንም አመለከተቻቸው እነርሱም ባገኙት ጊዜ አንስተው ተሸከሙት እየዘመሩና እያመሰገኑም ወደ ቤተ ክርስቲያን አደረሱት በቤተ መቅደስ ፊት ለፊት በወንበሩ ላይ አስቀመጡት ምእመናንም ሁሉ ወደርሱ እየመጡ ከርሱ ይባረኩና የተቆረጡ ሕዋሳቱንም ይሳለሙ ነበር፡፡ ከቦታ ቦታ ይዘዋወር የነበረውም በቅርጫት ኹኖ በዘህያ ላይ ተጭኖ ነው፡፡ ✤ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ የከበሩ ፫፻፲፰ ኤጲስ ቆጶሳትን (ሠለስቱ ምዕት) የአንድነት ጕባኤን በኒቂያ አገር በሰበሰበ ጊዜ ይህ አባት (ቅዱስ ቶማስ) ከሠለስቱ ምዕት አንዱ ነበር፤ ወደ ኒቅያ ጕባኤ በቅርጫት ሁኖ በአህያ ተጭኖ እየሄደ መሆኑን አርዮሳውያን ሲሰሙ፤ ቶማስማ በጕባኤው ከተገኘ ተከራክሮ ይረታናል አንችለውም በማለት መንገድ ላይ ባደረበት ይዘውት ይጓዙት የነበሩትን አህዮች በጨለማ በሰይፍ መተዋቸዋል፤ ነገር ግን ሌሊት ሊነጋጋ ሲል ለመንገድ ሲነሱ ቶማስ በተዓምራት አግልጋይ ረድኡን የተቆረጡትን የአህያዎቹን አንገታቸውን ከሰውነታቸው አጋጥመው ይነሳሉ ብሎ ሲያዘው የአንዱን አህያ ከሌላኛው አህያ ቢያጋጥመውም ቅሉ አህዮቹ ሕይወት አግኝተው ጕባኤ ኒቅያ አድርሰውታል፤ በዚያም አርዮስን መልስ እስኪያጣ ድረስ በጽናት ሲከራከረውና መልስ ሲያሳጠው የጕባኤው ሊቀ መንበር ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ እስኪደነቅ ድረስ በማየቱ ሃይመኖትስ የእነ ቶማስ ዘመርዓስ ነች ብሎ አጽንቶ ወስኗል፡፡ በጕባኤውም አርዮስን ተከራክረው ከረቱ በኋላ አውግዘው ለይተውታል፤ ከዚህ በኋላ መንፈስ ቅዱስ እንዳስተማራቸውና እንደመራቸው የሃይማኖትን ትምህርት በአንደበታቸው ተናገሩ፤ ሕግና ሥርዐትን ሥጋዊና፤ መንፈሳዊ ፍርድንም ሰሩ። ቅዱስ ቶማስ ወደ መንበረ ሢመቱ ከተመለሰ በኋላ ካህናቱና መንጋዎቹን ሁሉ ሰብስቦ አነበበላቸው እርሱንም እንዲያስተውሉት እንዲጠበቁትም በመጠበቅም እንዲጸኑ አዘዛቸው፡፡ ይህ አባት ለ፵ ዓመት ያህል በሢመቱ አገልግሎ በነሐሴ ፳፬ ቀን አርፋል፡ በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት የተዘጋጀ ::/ ፠፠፠ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like

ከዚህም ሌላ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅድስት ክርስቶስ ሠምራ እጅግ አስደናቂ ምሥጢራትን ፈጽሞላታል፡፡ ከእነዚህም ውስጥ ከጎኑ በፈሰሰው ደም ግንባሯ ላይ ቅዱስ ስሙን አትሞባታል፣ በዕለተ ዐርብ በጦር የተወጋ ጎኑንም እንድትጠባ ካደረጋት በኋላ ‹‹ቶማስ የተወጋውን ጎኔን ዳሰሰ፣ አንቺ ግን ጠባሽ›› ብሏታል፡፡ ራሱ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ሠራዒ ካህን ሆኖ ቀድሶ ሥጋ ወደሙን አቀብሏታል፡፡ በቸርነቱም የእናቱን ጡቶች እንድትጠባ ስለፈቀላት እመቤታችን ቅድስት የሆኑ ጡቷን አጥብታታለች፡፡ በመጨረሻም ጌታችን ለእናታችን ለቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ብዙ አስደናቂ የሆኑ ቃልኪዳኖችን ከገባላትና ዐሥር አክሊላትን ካቀዳጃት በኋላ ቅድስት ነፍሷ ከሥጋዋ ተለይታ ቅዱሳን መላእክት በዝማሬ አሳርገዋታል፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፡፡ እኛንም በአማላጅነታቸው የምንታመን ሁላችንን የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን፣ የአቡነ ቶማስ ዘመርዓስን እና የእናታችን የቅድስት ክርስቶስ ሠምራን ረድኤት በረከታቸውን ያሳድርብን፡፡ በጸሎታቸው ይማረን፡፡ ✤✣✤ ዳግመኛም መልአኩ ‹‹አሁንም እንደልማድሽ ሂጂና ጠይቂው ማን እንደሆነ ይነግርሻል›› አላት፡፡ በዚህን ጊዜ ወደ እርሱ ሄደችና ‹‹እሰግድልህ ዘንድ አንተ ማን ነህ?፣ ስምህስ ማን ይባላል?›› ስትል ጠየቀችው፡፡ ሰይጣንም ‹‹የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ነኝ›› አላት፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ከእርሷ ጋር እንዳለ አላወቀም ነበርና፡፡ እርሱ በእርሷ ላይ ተንኮል ለመሥራት እንደተራቀቀ ሁሉ እርሷም ነቃችበት ተራቀቀችበት፡፡ ቀጥሎም ‹‹እንግዲያውስ አንተ ሚካኤል ከሆንክ እስቲ ስለ ጽድቅ ነገር አስተምረኝ›› አለችው፡፡ በዚህም ጊዜ ሰይጣን ፈጽሞ ተደሰተ ከዓላማዋ አሳስቶ በእጁ የገባችለት መስሎታልና፡፡ እንዲህም አላት፡- ‹‹ለምን ሰውነትሽን ታደክሚዋለሽ? ከዛሬ ጀምሮ ከዚህ ኃላፊ ዓለም ድካም ማረፍ ያስፈልግሻል፣ መጾምና መጸለይስ ለምን ይጠቅምሻል? በባሕርስ ውስጥ ቆሞ መጸለይና ሰውነትን ማድከም ማን አስተማረሽ?›› አላት፡፡ በዚያን ጊዜ ‹‹አንተ የምትለውና መጻሕፍት የሚናገሩት የተለያየ ሆነሳ!?›› አለችው፡፡ እርሱም ‹‹ማነው የለያየን?›› አላት፡፡ እርሷም ‹‹ከአነጋገርህ የተነሣ እኔ ለየኋችሁ›› አለችው፡፡ እርሱም ‹‹እስኪ ልዩነታችንን ንገሪኝ?›› አላት፡፡ እርሷም ‹‹መጻሕፍት የጾመ፣ የጸለየ፣ የለመነም ሁሉ ፍጹም ዋጋውን ያገኛል ይላሉ፡፡ አንተ ግን አትጹሙ፣ አትጸልዩ ትላለህ›› አለችው፡፡ ይህንንም ባለችው ጊዜ በእርሷ ላይ ፈጽሞ ተቆጣ፣ እጅግም አድርጎ አስደነገጣት፡፡ ዳግመኛም መለሰችና ‹‹በምን ትሸነፋለህ?›› አለችው፡፡ አሁንም ቁጣውን አወረደባት፡፡ በሦስተኛው ጊዜ ከተቆጣ በኋላ ‹‹በእነዚህ በሦስቱ ነገሮች እሸነፋለሁ›› ሲል መለሰላት፡፡ ‹‹አንደኛ ማንኛውም ሰው በዚህ ዓለም በሚኖርበት ጊዜ ነፍሱ ከሥጋው ከመለየቷ በፊት እንግዳ ተቀብሎ የሚያስተናግድ፤ ሁለተኛው በራሱ ላይ ችግርና መከራ በመጣበት ጊዜ መከራውን ታግሦ የሚኖር፤ ሦስተኛው ቀድሞም ከመሬት የተገኘሁ ነኝ፣ ኋላም ተመልሼ ወደ መሬት እገባለሁ እሞታለሁ እፈርሳለሁ ብሎ በማሰብ ትሕትና የሚሠራና የመሳሰሉትን ሁሉ የሚያደርግ እርሱ ፈጽሞ ያሸንፈኛል›› አላት፡፡ ይህንንም ከተናገረ በኋላ ክንፉን እያማታ ወደ አየር በረረ፡፡ እርሷም ከግርማው የተነሣ ፈጽማ ደነገጠች፤ በመሬትም ላይ ወደቀች፡፡ በዚያን ጊዜ ለጌትነቱ ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መጥቶ ቅዱሳት በሚሆኑ እጆቹ ከወደቀችበት አነሣት፡፡ ከዚያም ‹‹ወዳጄ ክርስቶስ ሠምራ ሆይ! አይዞሽ አትፍሪው ነገር ግን ወደ ላይ ወደ ሰማይ አቅንተሽ ተመልከቺ›› አላት፡፡ ወደ ሰማይ አቅንታ በተመለከተች ጊዜ የዲያብሎስ ክንፉ በሰማይ ላይ ከጽንፍ እስከ አጽናፍ ተዘርግቶ (መላው ዓለምን ሞልቶ) አየች፡፡ ቀጥሎም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ‹‹በእኔ በባሕርይ አባቴ በአብ በባሕርይ ሕይወቴ በመንፈስ ቅዱስ ያላመነ ሊያሸንፈው አይችልም›› አላት፡፡ ዳግመኛም ‹‹ማንም ሰው ኃጢአት ቢኖርበት ወደ ቀደመ ኃጢአቱ ባለመመለስ ንስሐ ቢገባ ከወጥመዱ ያመልጣል›› አላት፡፡ ከዚህ በኋላ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ በቁመቷ ልክ ጉድጓድ አስቆፍራ በአራቱም አቅጣጫ ከፊትና ከኋላ፣ በግራና በቀኝ ሦስት ሦስት የተሳሉ ጦሮችን ተክላ የፊጥኝ ታስራ ስለ ዓለሙ ሁሉ ይልቁንም ስለ ኢትዮጵያ ልጆች ስትጸልይ ኖራለች፡፡ በምትሰግድበትም ጊዜ ጦሩ እየወጋት ከቁስሉ የተነሳ ጦሩ የወጋትና ገመዱ የከረከራት መላ ሰውነቷ እስኪሸትና እስኪተላ ድረስ ለ12 ዓመታት በጉድጓድ ውስጥ በተጋድሎ ኖራለች፡፡ ያረፈችውም በዚሁ ጉድጓድ ውስጥ ቆማ ስለ ዓለሙ ስትጸልይ ነው፡፡ ጌታችንም ክብሯ ከሙሴ፣ ከአሮን፣ ከጴጥሮስ፣ ከጳውሎስ፣ ከሕጻኑ ቂርቆስ፣ ከእንጦንስ፣ ከጊዮርጊስና ከእስጢፋኖስ ጋር የተካከለ መሆኑን በማይታበል ቃሉ ነግሯታል፡፡ በዚህች ምድር ላይም 375 ዓመት ኖራ አባታችን ቅዱስ ተክለሃይማኖት ባረፉበት ዕለት ነሐሴ 24 ቀን በታላቅ ክብር ዐርፋለች፡፡ በዚህችም ዕለት ከማረፏ በፊት መድኃኔዓለም ክርስቶስ ቅድስት እናቱን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምንና ሌሎች ቅዱሳንን ሁሉ አስከትሎ ወደ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ዘንድ መጥቶ ‹‹ወዳጄ ክርስቶስ ሠምራ ሆይ! ዛሬ ከዚህ ከሚያልፈው ዓለም ወደ ማያልፈው ዓለም አሳርፍሽ ዘንድ መጥቻለው›› አላት፡፡ ‹‹ድካምሽ ወደ ዕረፍት፣ ኀዘንሽም ወደ ደስታ ተለውጦልሻልና›› ሲላት እርሷም ‹‹አቤቱ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! እኔ ባሪያህ በፊትህ ባለሟልነትን አግኝቼ እንደሆን አንድ ነገር እንድናገር ፍቀድልኝ›› አለችው፡፡ እርሱም ‹‹ትናገሪ ዘንድ ፈቅጄልሻለው›› ሲላት ‹‹አቤቱ ሥጋዬ የሚቀበርበት ቦታ ወዴት እንዲሆን ታዛለህ?›› አለችው፡፡ ጌታችንም ‹‹መቃብርሽ በዚህች ደሴት ይሆናል›› ካላት በኋላ የሚከተለውን ቃልኪዳን ሰጣት፡- ‹‹… በስምሽ ለተራበ ያበላ እኔ ዕለተ ዓርብ ከተቆረሰው ሥጋዬ አበላዋለሁ፣ በስምሽ ለተጠማ እፍኝ ውኃ ያጠጣውን እኔ በዕለተ ዓርብ ከጎኔ በፈሰሰው ደሜ አረካዋለሁ፡፡ እውነት እውነት እልሻለሁ ሥጋሽ ከተቀበረበት ሄዶ መካነ መቃብርሽን የተሳለመ የእናቴን የማርያምን መካነ መቃብር እንደተሣለመ ይቆጠርለታል፡፡ ምሕረት ሊደረግለት የማይገባው ሁሉ ወደ አንቺ መጥቶ ዜና ገድልሽን ሊሰማ አይችልም፡፡ ስለሆነም ገድልሽን ለመስማት፣ ትሩፋትሽን ለማየት ወደ አንቺ የሚመጡትን ተስፋ መንግሥተ ሰማያትን እሰጣቸዋለሁ፣ አንቺን የሚያፈቅሩ ሁሉ የተመሰገኑ ናቸው፣ እውነት እውነት እልሻለሁ አንቺን የወደደሽን እኔ ደግሞ እወደዋለሁ፡፡ መኖሪያሽ ከእናቴ ከድንግል ማርያም ጋር ነው፣ እነሆ በትረ ማርያም ብዬ ሰየምኩሽ፣ ደረጃሽን ከእርሷ ቀጥሎ ሁለተኛ አደረግሁልሽ›› ብሏታል፡፡ ከዚያም በፊት የቅዱሳን ገድላቸው ሲነበብ ሐሰት ነው ብለው የሚያቃልሉ ሰዎች ዕጣ ክፍላቸው ከነአርዮስ ጋር መሆኑን ጌታችን ለክርስቶስ ሠምራ ነግሯታል፡፡ ይኸውም ከዕለታትም በአንደኛው ቀን ቅዱስ ሚካኤል በጌታችን ፊት አቁሟት ሳለ እናታችን ክርስቶስ ሠምራ ጌታችንን ‹‹አቤቱ ጌታዬ የቅዱሳን ገድላቸው ሲነበብ ሐሰት ነው በማለት የማያምኑ ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ እንግዲህ እንደነዚህ ያሉትን ትምራቸዋለህ? ወይስ አትምራቸውም?›› አለችው፡፡ ጌታችንም ‹‹በጥቡዕ ልብ ሆነው ያለመጠራጠር የሚያምኑት ወደ መንግሥቴ ይገባሉ፣ የማያምኑ ቢኖሩ ግን ክፍላቸው ከነ አርዮስና ሰባልዮስ ጋር ነው›› አላት፡፡ የእናታችን የቅድስትክርስቶስ ሠምራ ምልጃና ጸሎት አይለየን

በነገሯት ትንቢት መሠረትም ከብዙ ጊዜ በኋላ ቅዱስ ሚካኤል በስሙ የተቀረጸ ጽላት አምጥቶ ሰጣትና በዚያች በጓንጉት ደሴት ውስጥ በእርሱ ስም ቤተ ክርስቲያን እንድታሠራ ነገራት፡፡ ‹‹እንዴት ይሆንልኛል?›› ባለችውም ጊዜ ‹‹እኒያ ያጠመቁሽ ቅዱሳን ከጥቂት ዓመታት በኋላ እመ ምኔት ትሆኛለሽ ያሉሽን ረሳሽውን? ያ ጊዜ እነሆ ዛሬ ደረሰ›› ብሎ ነገራትና አባ ይስሐቅ የሚባል መነኩሴ ላከላትና የእሷ ልጆች ሊሆኑ ከመጡ 600 መነኮሳት ጋር በሦስት ወር ውስጥ የቅዱስ ሚካኤልን ቤተክርስቲያን ሠርታለች፡፡ ብዙ ተከታይ መነኮሳትንም አፍርታለች፡፡ በዚህችም ጓንጉት ደሴት ቆማ ስትጸልይ እንደሁልጊዜው ጌታችን ተገልጦላት ሳለ ‹‹አዳምን በአርአያህና በአምሳልህ ለምን ፈጠርከው? በእንጨት መስቀልስ ላይ ለምን ተሰቀልክ? ስለ አዳምና ስለ ልጆቹ አይደለምን?›› አለቸው፡፡ ጌታችንም ‹‹አዎ ስለ አዳምና ልጆቹ ስል ነው የተሰቀልሁት›› አላት፡፡ እርሷም ‹‹እንግዲያውስ መሰቀልህ ስለ እነርሱ ከሆነ ከአቤል ጀምሮ እስከዛሬ የሞቱትን ከዛሬም በኋላ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ የሚሞቱትን ማራቸው፣ ይቅርም በላቸው›› አለችው፡፡ ጌታችንም ‹‹ወዳጄ ክርስቶስ ሠምራ ሆይ! እስቲ አንቺ ራስሽ ፍረጂ›› በማለት በጲላጦስ ዘመን አይሁድ ያደረሱበትን እጅግ አሠቃቂ መከራዎችና የሞቱን ሁኔታ ሁሉ በዝርዝር ከነገራት በኋላ ‹‹እንግዲህ ይህን ውለታ ዘንግተው ከክፋት የማይመለሱትን፣ ለተንኮል የማያርፉትን ልምራቸው ወይስ ልኮንናቸው ይገባል? እስቲ ፍረጂ›› አላት፡፡ እንደልብ ጓደኛም ብዙ ከተወያዩ በኋላ መጨረሻ ላይ ቅድስት እናታችን ‹‹አቤቱ ፈጣሪዬ ፈቃድህስ ቢሆን የአዳም ልጆች ከሥቃይ ከኩነኔ ይድኑ ዘንድ ዲያብሎስን ይቅር ትለውና ትምረው ዘንድ እለምንሃለሁ፣ የኃጥእን መመለሱን እንጂ ጥፋቱን አትወድምና፡፡የምለምንህ ወድጄው አይደለም ነገር ግን እርሱ ከተማረ በአዳም ልጆች ላይ ሥቃይና ኩነኔ ሊኖር አይችልም ብዬ በመገመት ነው እንጂ›› አለችው፡፡ ይህንንም ባለችው ጊዜ ጌታችን በጥያቄዋ ተገርሞ ‹‹ሌሎች ካንቺ በፊት የነበሩ ካንቺም በኋላ የሚነሡ የማያስቡትን እጅግ የሚያስደንቅ ልመና ለመንሽኝ›› ብሎ ካደነቃት በኋላ ቅዱስ ሚካኤልን ጠርቶ ‹‹ሳጥናኤል እሺ ካላት ታወጣው ዘንድ ወደ ሲኦል ይዘሃት ሂድ›› ብሎ አዞታል፡፡ በእዚያም እንደደረሰች ለዲያቢሎስ ልታስታርቀው እንደመጣች ነገረችው፣ እርሱ ግን እንኳን ሊመለስላት ይቅርና እርሷንም እጇን ይዞ ወደ ሲኦል ወረወራት፡፡ በዚህ ጊዜ ይጠብቃት የነበረው መልአክ በእሳት ሰይፉ ዲያብሎስን በመቅጣት እርሷን መዞ ሲያወጣት በዚህ ጊዜ በቅዱስ ሚካኤልና በእርሷም ክንፍ ተጣብቀው ዐሥር ሺህ ነፍሳት ሊወጡ ችለዋል፡፡ እርሷም በዚህ እጅግ ተደስታ ወደ ፈጣሪዋ ሄዳ ‹‹አቤቱ ፍርድህ የቀና ምሕረትህ የበዛ ነው›› እያለች ለጌትነቱ ክብር ሰግዳለች፡፡ ✤✣✤ በሌላም ጊዜ ሰይጣን የሚሸነፍባቸውን ሦስት ዋና ዋና መንገዶች ለክርስቶስ ሠምራ ነገሯታል፡፡ ከዕለታት በአንደኛው ቀን እናታችን ክርስቶስ ሠምራ ዕለተ ሞቷን እያሰበች በጣና ባሕር ውስጥ ቆማ ስታለቅስና ስትጸልይ ዲያብሎስ በሊቀ ጳጳሳት ተመስሎ እጅግ አስደናቂና ግሩም በሆነ አርዓያ ወደ እርሷ መጣ፡፡ እርሷም ልትሰግድለት ወደደች፣ ከኃዘኗ ያረጋጋት ዘንድ ከቅዱሳን አንዱ የመጣ መስሏት ነበርና፡፡ ነገር ግን የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ፈጥኖ ደረሰና ‹‹ይህ ሰይጣን እንጂ ጳጳስ ወይም ከቅዱሳን አንዱ አይደለምና አትስገጂለት›› ብሎ ወደኋላዋ መለሳት፡፡ ✤✣✤ ዳግመኛም ጌታችን በቅድስት ቤተክርስቲያን የሚፈተተው ሥጋና ደሙ አማናዊ ሥጋና ደሙ መሆኑን በተግባር አሳይቷታል፡፡ ይኸውም በመጋቢት 27 ቀን የመድኃኔዓለም በዓል በሚከበርበት ዕለት ሥጋውና ደሙን ለመቀበል እናታችን ክርስቶስ ሠምራ ወደ ቤተ ክርስቲያን በገባች ጊዜ ድንቅና ረቂቅ ምሥጢርን እንድታይ አድርጓታል፡፡ በዚህች ዕለት እንደ ሕጉ እንደ ሥርዓቱ ካህናት ሥርዓተ ቍርባን ይፈጽሙ ዘንድ ወደ ቤተ መቅደስ ገቡ፡፡ በዚያው ወቅት ዲያቆኑ ሙቀት ያልተለየው ኅብስት በመሶበ ወርቅ ይዞ መጣ፡፡ ያች የወርቅ መሶብ ተለውጣ በድንግልና ያለች ብላቴና ሆነች፣ ኅብስቱም ሕፃን ልጅ ወደመሆን ተለወጠ፡፡ ቄሱ ከዲያቆኑ እጅ በተቀበለው ጊዜ ሕፃኑ ኅብስት ሆነ፣ ብላቴናይቱም መሶበ ወርቅ ሆነች፡፡ ከዚህ በኋላ ቄሱ ሥርዓተ ቅዳሴውን ጀምሮ ሲቀድስ ፈኑ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ (የመንፈስ ቅዱስ ጸጋህን ላክልን) ከሚለው ደረሰ፡፡ በዚያን ጊዜ ቍርባኑን (ኅብስቱን) ያከብረው ዘንድ መንፈስ ቅዱስ በነጭ ርግብ አምሳል ወረደ፡፡ ዳግመኛም ይህ ኅብስት ተለውጦ ሕፃን ሆነ፡፡ ከዚያም ሕፃኑን ይሠዋው ዘንድ መልአኩ ለቄሱ ሰይፍ ሰጠውና ቄሱም ሕፃኑን ሠዋው፡፡ ይህንንም መለኮታዊ ምሥጢር በተመለከተች ጊዜ እጅግ አደነቀች፣ ፈጽማም ደነገጠች፣ መሪር ዕንባንም አለቀሰች፡፡ ከዚያም ቅዱስ ሚካኤል መጥቶ ‹‹የእግዚአብሔር ባለሟል ክርስቶስ ሠምራ ሆይ! ምን ያስለቅስሻል ነገር ግን ይህን ድንቅ ምሥጢር ተመልከች እንጂ›› አላት፡፡ እርሷም ‹‹እሺ በጎ›› ብላ ትመለከት ጀመረች፡፡ ዳግመኛም ‹‹ይህ ቄሱ ሥርዓተ ቅዳሴውን በትክክል እንደሚያከናውንና ንጹሕ ካህንም ለመሆኑ ትመለከቺያለሽን?›› አላት፡፡ እርሷም ‹‹አዎን›› አለችው፡፡ ከዚያም ቄሱ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለሕዝቡ ያቀብል ዘንድ ወጣ፡፡ እርሷም ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀበለች፡፡ በምትቀበልበትም ጊዜ በአፍዋ ውስጥ ሥጋው ትኩስ ሥጋ፣ ደሙም ትኩስ ደም ሆኖ ተገኘ፡፡ እንዲሁም ከኅብስቱ አንዱ ከጻሕሉ ላይ ተነሥቶ በዲያቆኑ እጅ ተይዞ ባለው የደም ጽዋ ውስጥ ገብቶ በጽዋው ውስጥ ካለው ደም ጋር ተዋሕዶ ወደ መቅደስ ሲገባ አየች፡፡ ይህን ሁሉ አይታ ፈጽማ አደነቀች፡፡ ከእርሷም ጋር የነበረውን መልአክ ‹‹ይህ የምመለከተው ምሥጢር ምንድን ነው?›› ብላ ጠየቀችው፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ‹‹ቀድሞ ቄሱ እንደ በግ ሲሰዋው ተመልከተሻል፡፡ የእግዚአብሔር ባለሟል ክርስቶስ ሠምራ ሆይ! አሁንም እንደሰው ሞቶ የሚቀር እንዳይደለ በእውነት እነግርሻለሁ፣ በመለኮቱ ሕያው ነው እንጂ፡፡ መጽሐፍ ‹‹በሰውነትህ አንተ ከሙታን ጋር ትሞታለህ፣ በመለኮትህ ግን ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ሕያው ነህ፡፡ አንተ ሦስት መዓልት፣ ሦስት ሌሊት በከርሠ መቃብር አደርክ ዳሩ ግን በመለኮትህ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በዙፋንህ ላይ ትገኛለህ›› ብሎ እንደተናገረ ዳግመኛም በሥጋው ቢሞት በመለኮቱ ሕያው ነው›› አላት፡፡ እርሷም ይህን ባላት ጊዜ ፈጽማ ደስ ተደሰተች፡፡

#ቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ የትውልድ ሀገሯ ሸዋ ቡልጋ አውራጃ ልዩ ስሟ ቅዱስ ጌየ ሲሆን እግዚአብሔርን ከሚፈሩ ደጋግ ወላጆቿ ከአባተቷ ቅዱስ ደረሳኒ ከእናቷ ከቅድስት ዕሌኒ በግንቦት 12 ቀን ተወለደች፡፡ እነርሱም ቅድስት ክርስቶስ ሠምራን ከወለዱ በኋላ በደም ግባቷና በጠባይዋ እየተደሰቱ የእግዚአብሔርን ሕግጋትና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን በማስተማር ስላሳደጓት ከልጅነቷ ጀምራ በሥነ ምግባር፣ በሃይማኖት የታነጸች በመልኳም እጅግ ውብና ያማረች ሆነች፡፡ ባደገችም ጊዜ ለአቅመ ሔዋን ስትደርስ የንጉሥ ባለሟል ለሆነ ስሙ ሠምረ ጊዮርጊስ ለተባለ ደግ ሰው በሕግ አጋቧት፡፡ ከሕግ ባሏ ከሠምረ ጊዮርጊስም ዐሥራ ሁለት ልጆችን ወለደች፡፡ ከእነዚህም መካከል አስሩ ወንዶች ሁለቱ ሴቶች ነበሩ፡፡ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ በዐፄ #ገብረ መስቀል ዘመነ መንግሥት የነበረች ኢትዮጵያዊት ጻድቅ ስለነበረች ንጉሠ ነገሥቱ ዐፄ ገብረ መስቀል በትዳሯ፣ በሥነ ምግሯና በሃይማኖቷ በሁለመናዋ የተመሰገነች መሆኗን ዝናዋን ስለሰማ ‹‹#በጸሎትሽ አስቢኝ›› በማለት ከአገልጋዮቹ ውስጥ እርሷን እንዲያገለግሏት፣ 174 አገልጋዮቸን ላከላት፡፡ ብዙ ፈረስና በቅሎ እንዲሁም ለነገሥታት ሚስቶች የሚገባ ከሐርና ከወርቅ የተሠራ ልብስና የወርቅ ጫማም ላከላት፡፡ ነገር ግን እሷ ይህን ሁሉ ክብር አልፈለገችም ይልቁንም ‹‹ለዓላማዬ እንቅፋትና ውዳሴ ከንቱ ይሆንብኛል እንደዚሁም ወርቁ ጌጡ ተሸጦ ለነዳያን ይመጸወታል ነገር ግን እነዚህን አገልጋዮች ምን አደርጋቸዋለው?›› እያለች ወደ እግዚአብሔር አመለከተች፡፡ ከጥቂት ቀናት በኋላ የመላእክት አለቃ ቅዱስ #ሚካኤል ፊቱ እንደ ፀሐይ እያበራ ሦስት ኅብስት በእጁ ይዞ መጥቶ ‹‹የእግዚአብሔር ባለሟል ክርስቶስ ሠምራ ሆይ! እነሆ ይህን #ኅብስት ተመገቢ እግዚአብሔር በቸርነቱ ብዛት ሰጥቶሻል›› አላት፡፡ እርሷም ፈጣሪዋን አመስግና ኅብስቱን ከመልአኩ እጅ ተቀብላ ተመገበች፣ መዓዛ ጣዕሙም ሰውነቷን አለመለመው፡፡ በዚህም የተነሳ እስከ ሦስት ቀን እህል ሳትበላ ውኃ ሳትጠጣ ቆየች ኃይለ መንፈስ ቅዱስ በሰውነቷ አድሮባታልና፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን እንዲህ ሆነ፡- ከአገልጋዮቿ መካከል አንዷ ምግባሯ የከፋ ነበርና በጣም ስላበሳጨቻት በዚያች አገልጋይ አፍ ውስጥ የእሳት ትንታግ ጨመረችባት፡፡ ያም የእሳት ትንታግ እስከ ጉሮሮዋ ዘለቀና አገልጋይዋን ገደላት፡፡ በዚህ ጊዜ ብጽዕት ክርስቶስ ሠምራ ደንግጣ ወደ ሌላ ክፍል ገባችና ኃጢአቷን ለእግዚአብሔር እየተናዘዘች እጅግ በጣም አዝና ጥፋቷ እንደ ጸጸታትና እግዚአብሔር አምላክም በእጇ የሞተችውን አገልጋይዋን ከሥጋዋ አዋሕዶ ቢያሥነሳላት ያላትን ገንዘብና ሀብት ትታ ባላት ዘመኗ ሁሉ አገልጋዩ እንደምትሆን ብጽዓት (ስዕለት) አደረገች፡፡ እግዚአብሔርም ጸሎቷን ሰምቶ አገልጋይዋን ከሞት አሥነሳለት፡፡ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ‹‹ልመናዬን ቸል ያላለ ቸርነቱንም ከእኔ ከባሪያው ያላራቀ አምላክ ይክበር ይመስገን›› ብላ በታላቅ ምስጋና እግዚአብሔርን ካመሰገነች በኋላ አስቀድማ የገባችውን ቃል አስባ ልብሰ ምንኩስናዋን አዘጋጀች፡፡ ሕፃን ልጅዋንም ይዛ ወደ ደብረ ሊባኖስ ሄደች፡፡ ስትሄድም በልስላሴና በእንክብካቤ የኖረ እግሯ ከመንገዱ ብዛት ከእንቅፋቱም የተነሳ ፈለግ ሲያወጣ ሥጋውን እየቆረጠች ስትጥለው ደሟ መሬት ለመሬት እየፈሰሰ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ደረሰችና አስቀድማ ያዘጋጀችውን ልብሰ ምንኩስናዋን ለብሳ ከሴቶች ገዳም ገባች፡፡ ይዛው የተሰደደችውን ሕፃን ግን ወንድ ስለሆነ ከደጅ ላይ አስቀምጣው ስለገባች ሕፃኑ አምርሮ ሲያለቅስ ከመነኮሳቱ አንዲቷ ሕፃኑ ሲያለቅስ ከሚያድር ብላ ወደ በአዓቷ ልታስገባው ስትል የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ነጥቆ ወስዶ በገነት አስቀመጠው፡፡ ታኅሣሥ 29 ቀን ተወልዶ በ 3 ዓመቱ ታኅሣሥ 12 ቀን ብሔረ ብፁዓን ገባ፡፡ ከዕለታትም በአንደኛው ቀን ቅዱስ ሚካኤል ካለችበት በዓት አውጥቶ በክንፉ ተሸክሞ ከጣና ደሴት አደረሳት፡፡ ከዚያም ሰውነቷ ተበሳስቶ የባሕር ዓሣ መመላለሻ እስከሚሆን ድረስ እንደ ተተከለ ዓምድ ሆና ሳትወጣ ባሕሩ ውስጥ ዐሥራ ሁለት ዓመት ቆማ ስትጸልይ ኖረች፡፡ ከዐሥራ ሁለት ዓመት በኋላም ጌታችን ተገልጦላት #ቃልኪዳን ሰጥቷታል፡፡ ከዚህ በኋላ ሕይወቷን በሙሉ በታላቅ ተጋድሎ ስታሳልፍ ጌታችንም ከቅድስት እናቱ ጋር ሆኖ በየጊዜው ይጎበኛት ነበር፡፡ ቅዱስ ሚካኤልንም የሁልጊዜ ጠባቂዋ አድጎ ሰጥቷታል፡፡ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ብሔረ ብፁዓን እየሄደች ከዚያ ከሚኖሩ ቅዱሳን ጋር እስከ ሰባት ቀን ድረስ ስትነጋገር ትቆይ ነበር፡፡ #ሄኖክና #ኤልያስ ወዳሉበት ወደ ብሔረ ሕያዋንም እየሄደች ትመለስ ነበር፡፡ ✤✣✤ ከዕለታት አንድ ቀን በጣና ማዶ መዕቀበ እግዚእ የሚባል አንድ ሰው ነበረና መልአከ ጽልመት ወደ እርሱ ዘንድ መጥቶ ‹‹ፈጣሪውን ክደህ ይህን ዕፅ በሰውነትህ ብትቀብር ሞትና እርጅና አያገኝህም›› አለው፡፡ እርሱም ለዚህ ክፉ ሀሳቡ ፈቃደኝነቱን ስለገለጠለት መልአከ ጽልመት በሰውነቱ ውስጥ ዕፁን ቀብሮለት ሄደ፡፡ መዕቀበ እግዚእም ከዕለታት አንድ ቀን ወደ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ዘንድ መጥቶ ‹‹ሰላም እልሻለው በጸሎትሽም ተማጽኛለሁ፣ የፈጠረኝን እግዚአብሔርን እስከ መካድ ደርሼ ብዙ ኃጢአት ሰርቻለውና›› አላት፡፡ ቅድስት እናታችንም በዚያን ጊዜ ፈጥና ተነሥታ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሄደችና ስለዚህ ሰው በፍጹም ኀዘን በመሆን ወደ ፈጣሪዋ አመለከተች፡፡ በዚህ ጊዜ ጌታችን መጥቶ ‹‹ወዳጄ ክርስቶስ ሠምራ ሆይ! ለዚህ ሰው ምሕረት አይገባውም፣ የምገድል የማድን የምቀስፍ ይቅር የምል አምላክ እኔ እያለሁ ፈጣሪውን ክዶ በሰይጣን ምክር ተማምኖአልና›› አላት፡፡ በዚህ ጊዜ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ጌታችንን እግሩ ሥር ተደፍታ ‹‹አንተ መዓትህ የራቀ ምህረትህ የበዛ ፈጣሪ ሆይ! ማርልኝ ሁሉ ይቻልሃልና…›› ስትል አጥብቃ ለመነችው፡፡ ሁሉን የፈጠረ ጌታችንም ‹‹ስለ አንቺ ፍቅር ምሬልሻለው›› አላት፡፡ ከዚህ በኋላ ማዕቀበ እግዚእን ጠርታ ‹‹ኃጢአትህን ይቅር ብሎሃል›› አለችው፡፡ ከዚህ በኋላ ከራስ ጸጉሩ እስከ እግር ጥፍሩ የተቀበረውን ዕፅ ሰውነቱን ፍቃ ስታወጣለት ደሙ እንደ ቦይ ውኃ ወረደ፤ በዚያው ነፍሱ ከሥጋው ተለይታ ከማኅበረ ሰማዕታት ጋር አንድ ሆነች፡፡ እግዚአብሔር አምላካችን ለቅድስት ክርስቶስ ሠምራ #ስድስት ክንፎችን ሰጥቷታል፡፡ በበዓለ ጥምቀት ወቅት ሙሴ፣ ኤልያስና መጥመወቁ ዮሐንስ ጌታ የተጠመቀበትን የዮርዳኖስን ውኃ አምጥተው ሙሴ የቅድስት ክርስቶስ ሠምራን ቀኝ እጇን፣ ኤልያስ ግራ እጇን ይዘዋት ዮሐንስ ውኃውን በራሷዋ ላይ አፍስሶ አጥምቀዋታል፡፡ ከጌታችን ጥምቀት በኋላ እንደዚህ ዓይነት መንገድ የተጠመቀ ማንም የለም፡፡ እነርሱም ጓንጉት በምትባል ገዳም ውስጥ የገዳም አስተዳዳሪ እንደምትሆንና እጅግ ብዙ ተከታዮች እንደሚኖሯት ትንቢት ነግረዋት ወደ ሰማይ ዐርገዋል፡፡

#በደብራችን በቀጨኔ ደብረ ሰላም #መድኀኔዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ #ገብርኤል ቤተክርስቲያን ከሚነግሡት ዓመታዊ ክብረ በዓላት መካከል አንዱ ነሐሴ ፳፬ ቀን የሚከብሩት የጻድቁ አባታችን አቡነ #ተክለ_ሃይማኖት፣ የቅድስት እናታችን #ክርስቶስሠምራ እና የቅዱስ #ቶማስ ዘመርዓስ በዓለ ንግሥ ነው(ታሪኩን ከታች ይመልከቱ) ፡፡ በደብራችን ታቦታተ ሕጉን በማውጣት መከበር የተጀመረው #በ፲፱፻፹፪(1982) ዓ.ም እንደሆነ አባቶቻችን ይናገራሉ፡፡አሁንም የአባቶቻችንን ፈለግ የተከተልን እኛ ከቅዱሳኑ ረድኤት በረከት ለማግኘት በየዓመቱ በድምቀት እናከብረዋለን፡፡ ✤✣✤ ነሐሴ ፳፬(24) ቀን የሦስቱም ቅዱሳን በዓለ እረፍታቸው ነው ታሪከ አቡነ #ተክለሃይማኖት ወቅድስት #ክርስቶስ ሠምራ እንዲሁም አርዮስን መልስ ለመስጠት በቅርጫርት ውስጥ ተጉዞ ለሄደው እና ከ 318 ሊቃውንት አንዱ የሆንው የቅዱስ #ቶማስ ዘመርዓስ ታራክ:: #አቡነ_ተክለሃይማኖት አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቡልጋ ደብረ ጽላልሽ ወይም ዞረሬ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የሰበካ ክልል ከአባታቸው ከካህኑ ቅዱስ #ጸጋ ዘአብና ከእናታቸው ቅድስት #እግዚእ ኃረያ መጋቢት ፳፬ ቀን ተፀንሰው፤ በ፲፩፻፺፯ ዓ.ም ታኅሣሥ ፳፬ ቀን ተወለዱ፡፡ በተወለዱ በሦስት ቀናቸው ከእናታቸው እቅፍ ወርደው«አሐዱ አብ ቅዱስ፣አሐዱ ወልድ ቅዱስ፣ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ» ብለውሥላሴ ን አመስግነዋል፡፡ ወላጆቻቸውም ፍስሐ ጽዮን አሏቸው፡፡ ትርጓሜውም የጽዮን ተድላዋ ደስታዋ ማለት ነው፡፡ በወላጅ አባታቸው በካህኑ ቅዱስ ጸጋ ዘአብ ግብረ ዲቁናን ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን ሲያጠኑ ቆይተው በአሥራ አምስት ዓመታቸው ከ እስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቄርሎስ /ጌርሎስ/ ዲቁናን ተቀብለዋል፡፡ በዚህም ቅድስት ቤተክርስቲያንን በወጣትነት ዕድሜያቸው ሲያገለግሉ ቆይተዋል፡፡ ከዕለታት በአንዱ ቀን ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከጓደኞቻቸው ጋር ወደ ዱር አደን ሄደው ሳለ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጾ ለኢትዮጵያ ውያን ክርስቲያኖች ሐዲስ ሐዋርያ አድርጎ መረጣቸው። ስማቸውንም «ተክለ ኃሃይማኖት» አለው፡፡ ትርጓሜውም የኃይማኖት ፍሬ ማለት ነው፡፡ አባታችንም ሐዋርያዊ ጉዟቸውን ሲጀምሩ /ገድለ ተክለ ሃይማኖት ምዕ ፳፰ ቁ ፪ - ፫/ ትሕትና በተሞላበትና በተሰበረ ልብ ወደ ፈጣሪያቸው ከለመኑ በኋላ በልዩ ልዩ የኢትዮጵያ ክፍለ ሀገራት ከኃጢአት ወደ ገቢረ ጽድቅ፣ ከክህደት ወደ ሃይማኖት መልሰዋል፡፡ በዚህም የተነሣ ለኢትዮጵያውያን ብርሃን ፀሐይ ተብለዋል፡፡ አባታችን በዳዊት ፀሎት ከነቢያት ምስጋና ሌሊቱን ሙሉ ይተጉ ነበር በያንዳንዱ መዝሙርም 10፣ 10 ስግደትን ይሰግዱ ነበር፡፡ በሕዳር 24 ቀን ቅዱስ ሚካኤል ወደ ላይ ነጠቃቸው (አወጣቸው) ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ ጋር 25ኛ ካህን ሆነው የሥላሴን መንበረን “አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ” በማለት አጥነዋል ፡፡ በሐይቅ 10 ዓመት በደብረዳሞ 12 ዓመት ኖረዋል፡፡ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት በ1267 ዓ.ም ደብረ ሊባኖስን በአት አድርገው ኖሩ፡፡ ለ22 ዓመት ቆመው በመፀለይ የአንድ እግራቸው አገዳ ተሠበረ ደቀ መዝሙሮቻቸው በጨርቅ ጠቅልለው ቀበሩት፡፡ በአንድ እግራቸው #ለ7 ዓመት በፀሎት ቆሙ በጠቅላላው ለ29 ዓመት በፀሎት ከቆሙ በኋላ በ99 ዓመት ከ10 ወር ከ10 ቀን ነሐሴ 24 ቀን 1290 ዓ.ም አረፉ አባታችን ባረፉ 54 ዓመታቸው በ1354 ዓ.ም ለአባታችን ለአቡነ #ሕዝቅያስ ተገልጸው አጽማቸው ከደብረ አስቦ ወደ ደብረ# ሊባኖስ ግንቦት 12 ቀን እንዲፈልስ አድርገዋል ፡፡ በዚህም መሠረት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያናችን ለእኚህ ዕረፍታቸው በእግዚአብሔር ፊት ለከበረና ብዙ ክብር ለተሰጣቸው ለጻድቁ ተክለ ሃይማኖት በየዓመቱ በነሐሴ ፳፬ ቀን በዓለ ዕረፍታቸውን በታላቅ ድምቀት ታከብራለች፡፡ እኛንም ከጻድቁ ረድኤት በረከት ይክፈለን፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት የተዘጋጀ ::/ ፠፠፠ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like