fa
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

رفتن به کانال در Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

کانال Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 383 مشترک است و جایگاه 5 582 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 194 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 383 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 09 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 38 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -1 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 21.91% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 9.42% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 370 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 449 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 25 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 10 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

15 383
مشترکین
-124 ساعت
-67 روز
+3830 روز
آرشیو پست ها
እንኳን አደረሳችሁ፥ አደረሰን፡፡ እናስተዋውቃችሁ ክፍል ፩፤ ጥምቀትን በጎንደር ለምታከብሩ፤ #ከ44ቱ_ #ታቦታተ_ጎንደር_መካከል_ወደ_ጥምቀተ_ባሕር_የሚወርዱት_የሚከተሉት_ናቸው፡፡ /ታቦታቱ የሚወጡት
+4
እንኳን አደረሳችሁ፥ አደረሰን፡፡ እናስተዋውቃችሁ ክፍል ፩፤ ጥምቀትን በጎንደር ለምታከብሩ፤ #ከ44ቱ_ #ታቦታተ_ጎንደር_መካከል_ወደ_ጥምቀተ_ባሕር_የሚወርዱት_የሚከተሉት_ናቸው፡፡ /ታቦታቱ የሚወጡት በጥር 10፣ 11፣ 12፣ 18 (ስባረ ዓፅሙ)፣ 21 (አስተርዕዮ)፣ 22 (ዑርኤል)፡፡) #፩ኛ) #በጥር_10፣ 11ና 12 #በጎንደር_ፋሲለደስ_መዋኛ_ገንዳ (#ቀድሞ_የሰማዕቱ_ቅዱስ_ፋሲለደስ_ቤተ_ክርስቲያን_በነበረበት ቦታ ላይ የሚወጡ ታቦታት) 1ኛ. ቀሃ ኢየሱስ 2ኛ. ደብረ ጽጌ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ 3ኛ. ዕልፍኝ ቅዱስ ጊዮርጊስ 4ኛ. ሰማዕቱ ቅዱስ ፋሲለደስ (አብሮ ከቀሃ ኢየሱስ ጋር ይወጣል) 5ኛ. መንበረ መንግሥት መድኀኔ ዓለም (መ.መ.መ) 6ኛ. አባ ጃሌ ተክለ ሃይማኖት 7ኛ. ፊት ሚካኤል 8ኛ. አጣጣሚ ሚካኤል፡፡ ናቸው #፪ኛ) #በጥር 10፣ 11 #በልደታ_ሜዳ_(ኮሌጅ አጠገብ) (ከአፄ ፋሲል መዋኛ ገንዳ በፊት በጥንቱ የታቦታት ማደርያ) ፠ መካነ ስብሐት ልደታ ለማርያም #፫ኛ) #በጥር_18 #ጎንደር_የመምህራን_ኮሌጅ_ወደ_መስጊድ_ጊዮርጊስ_መሄጃ_ጋር (የጥር 18 ስባረ ዓፅሙ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ዕለት) ፠ ርዕሰ አድባራት አበራ ጊዮርጊስ #፬ኛ) #በጥር_21 #በአዘዞ_ድማዛ_ወንዝ_አጠገብ_ (የጥር 21 የአስተርዕዮ ዕለት) አዘዞ ሎዛ ማርያም (ድፍን ጎንደር ተሰባስቦ የአስተርእዮ ዕልት የሚያከብርበት) #፭ኛ) #በጥር_22 #በበዓታ_ጠበል_ቤት (ጥር 22 የቅዱስ ዑርኤል ዕለት) ደብረ ኀይል ወደብረ ጥበብ ዑር(ራ)ኤልና በዐታ፡፡ #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/med

‹‹ ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ፤ ይህ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተ ክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡›› ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት በጥር ፫/፳፻፲፪ ዓ.ም. ጋብ
+2
‹‹ ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ፤ ይህ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተ ክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡›› ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት በጥር ፫/፳፻፲፪ ዓ.ም. ጋብቻሽን በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ቤ/ክ የፈጸምሽው የሰ/ት/ቤታችን አባል እኅታችን፤ #ስንታየሁ_መላኩ_ከቢልልኝ_ገረመው ጋር የፈጸማችሁትን ጋብቻ፤ የይስሐቅንና የርብቃን ጋብቻ የባረከ አምላክ፤ የትዳር ሕይወታችሁን ይባርክላችሁ፥ ያጣምራችሁ፥ ያዋሕዳችሁ፤ እመብርሃን በአማላጅነቷ አትለያችሁ፤ ቅዱስ ገብርኤል ከፊት ይምራችሁ ከኋላ ይከተላችሁ፡፡ ✤ ‹‹ጌታን እንዲወዱና በአካልም ይሁን በመንፈስ በባሎቻቸው ደስ እንዲሰኙ ለእህቶች ንገራቸው፡፡ ልክ እንደዚሁ ጌታ ቤተ ክርስቲያንን እንደወደደ ሚስቶቻቸውን እንዲወዱ ለወንድሞች በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ንገራቸው፡፡›› ቅዱስ አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ ለፖሊካርፐስ በላከው መልእክቱ ✤ ከተጋባችሁ በኋላ ባልና ሚስት አንድ አካል ናችሁ እንጂ ሁለት ስላይደላችሁ በፍጹም ልባችሁ እርስ በእርሳችሁ ተፋቀሩ፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ሌላ ወንድ ወይም ሌላ ሴት አትፈልጉ ይልቁንም በተቻላችሁ መጠን አንዳችሁ ሌላውን ደስ አሰኙ፤ በመረዳዳትና በፍጹም ፍቅር ኑሯችሁን ሁሉ አሳምሩ፡፡>> ኢትዮጵያዊው ፈላስፋ ዘርአያዕቆብ፡፡ /ከቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/

#ለ1512 #ዓመታት_ባለውለታዋን_ዘንግታ_የቆየችው_እንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳም_ጥር_3/2012 ዓ.ም. #ባለውለታዋን_አባ_ሊባኖስ_ዘመጣዕን_ፎቶ_ላይ_በምታዩት_ሁኔታ_ዘክራለች_፡፡ ፠ እንጦ
+6
#ለ1512 #ዓመታት_ባለውለታዋን_ዘንግታ_የቆየችው_እንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳም_ጥር_3/2012 ዓ.ም. #ባለውለታዋን_አባ_ሊባኖስ_ዘመጣዕን_ፎቶ_ላይ_በምታዩት_ሁኔታ_ዘክራለች_፡፡ ፠ እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት በ485 ዓ.ም. የሸዋ አባቶች የዐብዩ መድኀኔ ዓለምንና የበረከት ኪዳነ ምሕረት ታቦትን ይዘው ለ3 ወራት የተሰባሰቡባት ስትሆን፤ ታቦተ ኪዳነ ምሕረትን እንጦጦ ላይ አስቀምጠውና ገዳሟን መሥርተው፤ ታቦተ መድኀኔ ዓለምን ይዘው ወደ ዋልድባ በመሄድ ቀድሞ ጌታችን የገደመውን ገዳም ለ2ኛ ጊዜ አስፋፍተውታል፡፡ ፠ ከ16 ዓመታትት በኋላ በ500 ዓ.ም. ደግሞ አቡነ ሊባኖስ ዘመጣዕ ከአኵሱም ወደ ሸዋ ሲመጡ ሐመረ ኖኅን በገዳምነት ገድመው ጠበሏን አፍልቀው ሕሙማንን ፈውሰው ተመልሰዋል፡፡ ፠ በ197 ዓ.ም. አንድ ምዕመን ለአቡነ ተክለሃይማኖት አስፈቅደው፤ ገድላቸውን ከአኵሱም አጽፈው በማምጣት ማኅሌቱ እንዲቆም፣ ገድላቸው እንዲበብ፤ 50 ብር እየከፈሉ የጻድቁን ዝክር በዳቦና በለስላስ እንዲገለገል አስደርገዋል፡፡ ፠ ዘንድሮ በ2012 ዓ.ም. ደግሞ ታቦተ ሕጋቸው ወጥቶ ተከብሯል፤ በክብረ በዓሉም ላይ መናኙ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ስምዖን (የመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም የበላይ ኃላፊና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል) ተገኝተው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬን ሰጥተዋል፡፡ ፠ የአባቶቻችን አምላክ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ይመስገን፨ #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#ጥር 4 #የሐዋርያው የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ዓመታዊ ክብረ በዓል ነው፡፡ (የአባ ናርዶስ ዘደብረ ቢዘን እረፍቱ ነው፡፡ የጊዮርጊስ፤ የሊቀ ጳጳሳት ማርቴና፤ የሰማዕት ታኦድራ፤ የአባ ሊቃኖስ፤ የቀውስጦስ መታሰቢያቸውም ነው፡፡) ፨ሐዋርያው_ቅዱስ_ዮሐንስ፤ #በተለያዩ_ቅጽል_ስሞች_የሚጠራ፤ (100 አካባቢ ከሚጠጉ ስሞቹ ጥቂቶቹን /21ዱን ስሞች ከጽሑፍ በስተመጨረሻ ይመልከቱ) #ሰዓሊ_የኾነ፤ የጌታችንን ስነ ስቅለት የሳለ፡፡ #ከ81ዱ_የመጽሐፍ_ቅዱስ_ክፍሎች_5ቱንና_ሌሎች_መጻሕፍትንም_(ነገረ ማርያምን ..) የደረሰ፤ #ብዙ_ደቀ_መዛሙርትን_ያስተማረ፤ ✤ዮሐንስ ንጹሕ በአምሳለ ትጉሃን፤ (#ዮሐንስ_እንደ_መላእክት_ንጹሕ_ነው፤ ✤ዮሐንስ ድንግል ምክሐ ቅዱሳን፤ (#ዮሐንስ_ድንግል_የቅዱሳን_መመኪያ_ነው፤ ✤ዮሐንስ ስርግው በቀጸላ ሥን በሜላተ ብርሃን፤ (#ዮሐንስ_በብርሃን_መጐናጸፊያና_ሻሽ_የተጌጠ_ነው፤) ✤ዮሐንስ አርጋኖነ ዘቤተ ክርስቲያን፤ (#ዮሐንስ_የቤተ_ክርስቲያን_በገና_ነው፤ ✤ወበቃለ ቀርን ዘይኬልህ በኤፌሶን፥ ይስአል ለነ ስርየተ ለኀጥኣን፡፡ (#በኤፌሶን_ዐዋጅ_የሚናገር_ዮሐንስ_ኀጥኣን_ለምንሆን_ለኛ_ይቅርታን_ይለምንልን፡፡ /እመጽሐፈ ሰዐታት/ ፨ ‹‹ሰላም ለአፉከ ለዮሐንስ ዘሰዓሞ፤ ንጽሐ ኅሊናሁ ወልቡ ለዐይነ ፍትወትከ ሶበ አደሞ›› /መልክአ ኢየሱስ/ ፨ ሰላም ለሥዕልኪ ወለሥዕለ ወልድኪ ዘሰዓሞ፤ ዮሐንስ ርኄ ዮሐንስ ቀናንሞ፤ ለዝ ወልድኪ መሐሪ ኅሩመ በቀል ወተቀይሞ፤ ማርያም ሀብኒ በእዴኪ እንዘ ትጼውዒ ስሞ፤ ሥጋሁ ቅዱሰ ወክቡረ ደሞ፡፡ /መልክአ ሥዕል/ ፨#100_አካባቢ_ከሚጠጉ_ስሞቹ_ጥቂቶቹን_21ዱን_ስሞች_እነኾ፤ ዮሐንስፍቁረ እግዚእ፥ ወልደ ዘብድዮስ ፥ ዮሐንስ ነባቤ መለኮት ፥ ዮሐንስ ቦኦርኔጌስ ፥ ዮሐንስ አብቀለምሲስ ፥ ዮሐንስ ወንጌላዊ ፥ ዮሐንስ ድንግል 1. #ዮሐንስ_ብፁዕ (ብፁዕ ዮሐንስ) 2. ዮሐንስ ድንግል 3. #ዮሐንስ_ፍንው 4. #ዮሐንስ_ካህን 5. #ዮሐንስ_ኅሩይ 6. ዮሐንስ ሥርግው 7. #ዮሐንስ_ምዑዝ 8. ዮሐንስ ቅኑይ 9. #ዮሐንስ_ማኅቶት 10. ዮሐንስ ቤዛ ሰማይ 11. #ዮሐንስ_ክቡር 12. ዮሐንስ ጻድቅ 13. #ዮሐንስ_ረድእ 14. ዮሐንስ ማኅቶት 15. #ዮሐንስ_ድንግል 16. ዮሐንስ ንጹሕ 17. #ዮሐንስ_ለባዊ 18. ዮሐንስ መረግድ 19. #ዮሐንስ_ዕንቈ 20. ዮሐንስ መልአክ 21. #ዮሐንስ_ኪሩብ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#በሃገራችን_በኢትዮጵያ_ጥር_4_የቅዱስ_ዮሐንስ_ወልደ_ነጐድጓድ_ዓመታዊ_ክብረ_በዓል_የሚከበርባቸውን_ #13ቱ_ቦታዎች_እንጠቁማችሁ_፤ (ያልጠቀስነው ካለ ከነፎቱ ላኩልን) /ከዋይዜማው ጀምሮ በማኅሌቱ፥ በሰዐታቱ፥ በኪዳኑ፥ በቅዳሴው፥ በዑደተ ታቦተ ሕጉና በሠርክ ጕባኤ እንድንገናኝ ይሁን/፡፡ 1ኛ) #ደቡብ_ወሎ_ዮሐንስ_ወልደ_ነጐድጓድ /ጥንታዊው ደብር፤ ከመካነ ሥላሴ አጠገብ የሚገኝ/፤ (መላው ወሎ በዚሁ ደብር እንገናኝ/ 2ኛ) #ሐይቅ_ደብረ_ነጎድጓድ_ቅዱስ_ዮሐንስ_ (የሐይቅና የደሴ ነዋሪ በዚህ ታላቅ ደብር እንገናኝ) 3ኛ) #ዮሐንስ_ወልደ_ነጐድጓድ /#ከታላቁ_ደብር_ከደብረ_በንኰል_ገዳም_አጠገብ/ (ሰለኽላኻ ሽሬና አካባቢዋ ያላችሁ በዚሁ ደብር እንገናኝ) 4ኛ) #አደቁዋረክ_ዮሐንስ_ወልደ_ነጐድጓድ /ማኅበረ ዴጎ አጠገብ/፤ (አኵስምና በአካባቢው ያላችሁ በዚሁ ደብር እንገናኝ) 5ኛ) #ገደፈና_ዮሐንስ /ማይጨው አጠገብ/፤ (ማይጨው ራያና መቀለ ያላችሁ በዚሁ ደብር እንገናኝ) 6ኛ) #ዣት_ደብረ_ፀሐይ_ዮሐንስ_ወልደ_ነጐድጓድ /ሰሜን ሸዋ፥ ጅሩ/ (ሙሉ ሸዋ በዚሁ ደብር እንገናኝ) 7ኛ) #ዮሐንስ_ወልደ_ነጐድጓድ /ደምበጫ አጠገብ/፤ (ጎጃም በሙሉ በዚሁ ደብር እንገናኝ) 8ኛ) #ዘንስር_ደብረ_ተድላ_ዮሐንስ_ማዕከላ_ለጐንደር፤ /ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱና ዋነኛው፤ በጎንደር ከተማ የማኅሌተ ጽጌ ቁመት ወደ ግምጃ ቤት ማርያም ከመዛወሩ በፊት በብቸኝነት የጎንደርና የመላው ኢትዮጵያ ሊቃውንት የማኅሌተ ጽጌን ቁመት ለመቆም የሚተሙት ታላቅ ደብር/፤ (ጎንደርና አካባቢዋ ያላችሁ በዚሁ ደብር እንገናኝ) 9.1ኛ) #ደብረ_ነጐድጓድ_ቅዱስ_ዮሐንስና_መካነ_ጎልጎታ_ማርያም_ቤ_ክ_ማዕከላ_ለአዲስ_አበባ /መሐል አዲስ አበባ ከራስ ደስታ ዳምጠው ሆስፒታል አጠገብ የሚገኝ፤ ታቦተ ሕጉ ከኢየሩሳሌም የመጣና በአዲስ አበባ ብቸኛው የወልደ ነጐጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ.ክ./፤ (አዲስ አበባና በአካባቢዋ ያላችሁ በዚሁ ደብር እንድንገናኝ ይሁን) ፠፠ በአ.አ. በብቸኝነት ወደሚገኘው ደብረ ነጐድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ማዕከላ ለአዲስ አበባ ለማኅሌት ከመላው ዓለም ስትመጡ ጋቢና ምንጣፍ መያዛችሁን አትርሱ፤ ከሰዉ ብዛት የተነሣ ቤተ ክርስቲያኑ እጅጉን ስለሚሞላ፡፡ 9.2ኛ) #ምስካየ_ኅዙናን_መድኀኔ_ዓለም_ገዳም (ታቦተ ሕጉ ወጥቶ ባይከብርም ከጥንት ጀምሮ በውዳሴ በቅዳሴ ይከበራል፡፡) 10ኛ) #ቦኮሙራ_ወልደ_ነጐድጓድ_ቅዱስ_ዮሐንስ_ ቤ.ክን /ሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት ሚሻ ወረዳ ቦኮሙራ ቀበሌ/፤ (በሀድያ፣ በስልጤ፣ በጉራጌና በደቡብ የምትገኙ ሁሉ በዚሁ ደብር እንድንገናኝ ይሁን፡፡) 11) #ናዝሬት_ደብረ_ፍስሐ_ቅዱስ_ዮሐንስ_ወልደ_ነጎድጓድ_ቤ/ክ 12) #ደሴ_ዩኒቨርሲቲ_ደብረ_ነጎድጓድ_ቤ/ክ 13) #መቱ_ደብረ_ሳሌም_ሐይቅ_ደብረ_ነጎድጓድ_ #በሠረገላ_ተመሠለት_ቤተ_ክርስቲያን_ደብረ_ተድላ(#ደብረ_ነጐድጓድ_/#_ዮሐንስ_/)፤/፪/ #እንተ_፬ቱ #_ገበዋቲሃ_፬ቱ_ወንጌላውያን፡፡/፪/ ፨ #ሰላም ለከ ዮሐንስ አቡቀለምሲስ፤ ሰላም ለከ ዮሐንስ ታዎጎሎስ፡፡ ሰላም ለከ ዮሐንስ ፍቊረ እግዚእ፤ ሰላም ለከ ዮሐንስ ድንግል፤ ሰላም ለከ ዮሐንስ ዘረፈቀ ውስተ ሕፅኑ ለኢየሱስ፡፡ #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

ግነዩ ለእግዚአብሔር እስመ ኄር፤ እስመ ለዓለም ምሕረቱ፡፡ ፠ መደበኛ መዝሙር ጥናት አጥኚዎች፤ ፠ ለመደበኛ ክፍል አገልጋዮች፤ ፠ ለባለትዳር ጕባኤ አባላት ፠ ለወላጅ ኮሚቴ አባላት፤ ፠ ለቀደምት አባ
+1
ግነዩ ለእግዚአብሔር እስመ ኄር፤ እስመ ለዓለም ምሕረቱ፡፡ ፠ መደበኛ መዝሙር ጥናት አጥኚዎች፤ ፠ ለመደበኛ ክፍል አገልጋዮች፤ ፠ ለባለትዳር ጕባኤ አባላት ፠ ለወላጅ ኮሚቴ አባላት፤ ፠ ለቀደምት አባላት በሙሉ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱ ገብርኤል ቤ/ክ የፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት እንኳን ለ2012 ዓ.ም የጥምቀት በዓል በሰላም በጤና አደረሳችሁ እያልን፤ የጥምቀት በዓልን በድምቀት ለማክበር ዝግጅት እያደረገ ነው፤ በመሆኑም ከመደበኛ አባላት ጋር የባለትዳር ጕባኤ፣ የወላጅ ኮሚቴ አባላት፤ ቀደምት የሰ/ት/ቤታችን አባላት በሙሉ በአንድ ላይ የመዝሙር ጥናታችን የሚጀምረው #ከጥር 1 - 9 ፤ ማታ ማታ ከ12:00-2:00 በመሆኑ በሰዐቱ ተገኝታችሁ የመዝሙር ክለሳውን እንድታጠኑ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡ (ላልሰሙት ጥሪውን ያሰሙ)፡፡ #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#አዋጅ_አዋጅ_አዋጅ_፤ #በአ.አ. #እንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት ቀድሞ በቅዳሴና በውዳሴ ታቦተ ሕጋቸው ሲከበር የቆየው የአቡነ ሊባኖስ ዘመጣዕ ታቦተ ሕጋቸው #እሑድ_ጥር 3/2012 ዓ.ም. #ለመጀመሪያ_ጊዜ_ታቦተ_ሕጋቸው_ወጥቶ_ከብራል፡፡ (ሁላችሁም እንድትገኙ ገዳሟ ጥሪዋን አስተላልፋላች)፡፡ #ጥር_3 #አባ_ሊባኖስ_ዘመጣዕ_ዕረፍታቸው_ነው_፡፡ ፠ #የደብረ_ሊባኖስ_ገዳምን_የመሠረቱና_በስማቸው_የተሠየመላቸው፤ ፠ ቅዱስ ላሊበላ ከ11ዱ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት አንዱን በስማቸው ያነፀላቸው፡፡ ፠ #ከደረቅ_ዐለት_ላይ_ውኃ_እያፈለቁ_ድውያንን_የሚፈውሱ_ተአምረኛ_አባት ፠ በኤርትራ አካለ ጉዛይ ገዳመ መጣዕ፣ በአኵሱም ከተማ አጠገብ፣ በላስታ ላሊበላ፣ ደብረ ወርቅ አቡነ ሊባኖስ ገዳም፣ እንዲሁም ከ2012 ዓ.ም. ጀምሮ በአ.አ. እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ገዳም ክብረ በዓል የሚከበርላቸው፡፡ (ሌሎቹን የምታውቋቸውን ከነፎቷቸው ላኩልን) (***** እኛም ለክብረ በዓሉ የሚሆነውን ከዋይዜማው ጀምሮ ሙሉውን ሥርዐተ ማኅሌት እነሆ ብለናል፡፡ ወረቦቹን በድምፅ ከፈለጉ በቴሌግራማችን https://t.me/medihanaelem ላይ ያገኛሉ፡፡) ፠ አባታቸው አብርሃም እናታቸው ንግሥት ሊድሯቸው ሲሉ መመነን በመፈለጋቸው መልአክ በሌሊት መጥቶ ወደ ታላቁ አባት አባ ጳኩሚስ ዘንድ አደረሳቸው፡፡ ፠ አባ ጳኩሚስም ሥርዐተ ገዳምን፥ አስኬማ መላእክትን፥ ቅናተ ዮሐንስን አስተማሯቸው፤ አመነኮሷቸውና ከ8ቱ ቅዱሳን ጋር እንዲገናኙ አደረጓቸው፡፡ ፠ ቀድሞ የመራቸው መልአክ ከአባ ጳኩሚስ ‹‹ወደ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ ሂድና ተጋድሎህን በዚያ ፈጽም ዝናህ በስፋት ይነገራል፣ ለብዙዎችም አባት ትሆናቸዋለህ›› አላቸው፡፡ ቀጥሎም ራሱ መልአኩ ወደ ኢትዮጵያ አመጣቸውና በአኵሱም ተቀመጡ፡፡ ፠ በዚያም ብዙ ከተጋደሉ በኋላ ወደ ሸዋ መጡና ወንጌልን ዞረው አስተምረው ብዙ ድውያንን ፈውሰው (ቀድሞ የዋልድባን ገዳም ባስፋፉ አባቶች የተመሠረተችውን #የእንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳምን እስፋፍተው፡፡) ተመልሰው ወደ አኵሱም ሄዱ፡፡ ፠ በአኵሱምም 7 የተለያዩ ጸበሎችን ከድንጋይ ላይ በተአምራት አፍልቀው ድውያንን ፈውሰው ፥ ዕውራንን አበሩ፡፡ በዓታቸውንም ከአኵሱም ጽዮን ፊት ለፊት አድርገው ሲኖሩ ከዕለታት በአንደኛው ቀን አባታችን በተአምራት ከጭንጫ ካፈለቁት ጸበል ‹‹ተራ ውሃ ነው›› ብላ አንዲት ሴት ልጇን አዝላ ልትቀዳ መጣች፡፡ ወዲውም ከቦታው ስትደርስ አድጧት ወደቀችና ልጇም አምልጥጧት ልቡን ድንጋይ መቶት ሞተ፡፡ ሴትዮዋም ስትጮህ አባ ሊባኖስ ፈጥነው ወጡና በልጁ ላይ ጸልየው በመስቀል ምልክት አማትበው ከሞት አስነሥተውታል፡፡ ሕፃኑ ልጅ ከሞት እንደተነሣ ‹‹አምላከ አባ ሊባኖስ›› ብሎ አመሰገነ፡፡ (ስዕላቸው የሚገልጸው ይህንን ተአምር ነው፡፡) ፠ ይህንንም ደግ ሥራቸውንና ተአምራታቸውን ያዩ አንዳንድ እኩይ ካህናት በቅናት ተመልተው ‹‹ምትሃት ነው የሚያሳየው›› ብለው በጻድቁ ላይ ሕዝቡን አሳደሙባቸው፡፡ አባታችንም ካህናቱን ለመምከር ቢሞክሩም አላስቀምጥ አሏቸው፡፡ ይልቁንም ጦር ጦራቸውን ይዘው አሳደዷቸው፡፡ ፠ አባታችንም በዚህ እጅግ አዝነው ከአኵሱም ተነሥተው ደርቃ ወደምትባል ቦታ ሄዱ፡፡ በዚያም በጾም በጸሎት እየተጋደሉ ሲኖሩ፤ በእነዚያ በጠሏቸውና በክፋት በተነሡባቸው ካህናት አገር ግን ለ3 ዓመት ምንም ዝናብ ሳይዘንብ ቀረ፡፡ አባታችን በተሰደዱባት በደርቃ አገር ግን ብዙ ዝናብ ይዘንብ ነበር፡፡ አባታችን በዚያችም አገር እንደልማዳቸው ከዐለት ላይ ውኃ አፍልቀው በውኃው ብዙ ድውያንን ፈውሰውበታል፡፡ በዚያም ትልቅ በዓት መሥርተው በተጋድሎ ሲኖሩ በክፉ የተነሡባቸው እኩይ የሆኑ ካህናት መጥተው ‹‹አባታችን በከንቱ አምተንሃል በድለንሃልና ይቅር በለን፣ በድርቅ ማለቃችን ነውና ዝናብም እንዲዘንብልን ጸልይን›› ብለው ከእግራቸው ሥር ወደቁ፡፡ አባታችንም ይቅር ብለው ከፈጣሪ አማለዷቸው፡፡ ዝናቡም ወዲያው ዘነበላቸውና በአገሪቱ ጥጋብ ሆነ፡፡ ፠ ከዚህም በኋላ አባታችን አስቀድመው ወዳዩአት ወደ ሸዋ ምድር ግራርያ (የአሁኗ ደብረ ሊባኖስ) መጡና በዓታቸውን በአሰቦት ጫካ አደረጉ፡፡ ነገር ግን መልአኩ ተገልጦላቸው ‹‹ሊባኖስ ሆይ! ከዚህ ቦታ የአንተ መኖሪያ አይደለም፣ በዚህ ቦታ ላይ እግዚአብሔርንና ሰውን የሚያገናኝ የሚያስታርቅ ታላቅ ጻድቅ (አቡነ ተክለ ሃይማኖት) ይወጣበታልና ይህ ቦታ የእርሱ ርስት ነው፣ የብዙ መነኮሳትም መንደር ይሆናል ነገር ግን የቦታው ስም በአንተ ስም ይጠራልሃል›› አላቸው፡፡ በኋላ አባታችን ተክለ ሃይማኖት ተወልደው በዓታቸውን በዚያ ቦታ ላይ ሲያጸኑ ቦታው ግን ‹‹ደብረ ሊባኖስ›› ተብሎ በመጀመሪያው አባት ስም ተሰየመ፡፡ ፠ መልአኩም በሌሊት እየመራ ወደ አኵሱም ወሰዳቸው፡፡ ከዚያም ‹‹ታሪክ ወደምትሠራበት ዕጣ ክፍልህ ወደሆነው ቦታ አደርስሃለሁ›› አላቸውና ወደ ኤርትራ አካለ ጉዛይ አውራጃ ልዩ ስሙ መጣዕ ወደተባለው ቦታ ወሰዳቸው፡፡ በዚያም አባታችን ድውያንን እየፈወሱ፣ ለምፃሞችን እያዳኑ፣ ሙታንን እያስነሡ ብዙ ተአምራትን እያደረጉ ወንጌልን እየሰበኩ ‹‹ሊባኖስ ዘመጣዕ›› የሚባለውን ትልቁን ገዳማቸውን መሠረቱ፡፡ በወቅቱ የነበረው አፄ ገብረ መስቀልም የመጀመሪያውን ቤተ ክርስቲያን አሠራላቸው፡፡ ፠ ቅዱስ ላሊበላ 23 ዓመት ሙሉ ካነጻቸው እጅግ ድንቅ 11 ቤተ መቅደሶች ውስጥ አንደኛውን በአባ ሊባኖስ ስም ሰይሞላቸዋል፡፡ አፄ ገብረ መስቀል ያሠራላቸው ሌላኛው ገዳማቸው ትግራይ ተንቤን ውስጥ ይገኛል፡፡ እጅግ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን በማድረግ የሚታወቁት አባታችን እንደ ተስዓቱ ቅዱሳን ከሮም በመምጣት በሀገራችን ላይ ብርሃንን አብርተዋል፡፡ ፠+፠ በመጨረሻም ጥቅምት 2 ቀን ተፀንሰው ፤ ፠+፠ ሐምሌ 3 ቀን ተወለደው፤ ፠+፠ በ140 ዓመታቸው ጥር 3 ቀን በክብር ዐርፈዋል፡፡ ፠+፠ ቅዳሴ ቤታቸው ደግሞ ሐምሌ 3 ነው፡፡ ይኸውም ለመጀመሪያ ጊዜ በዐፄ ገብረ መስቀል ጊዜ በስማቸው ቤተ ክርስቲያን ተሠርቶ የተመረቀበት ዕለት ነው፡፡ ***** እኛም ለክብረ በዓሉ የሚሆነውን ከዋይዜማው ጀምሮ ሙሉውን ሥርዐተ ማኅሌት እነሆ ብለናል፡፡ (ምንጭ፤ ሊቀ ብርሃናት መርቆሬዎስ አረጋ፣ 5ኛ መጽሐፍ የቅዱሳን ታሪክ) #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ #አጥቢያ_ለምትገኙ_የጽዋ_ማኅበራትና_ወጣቶች_በሙሉ፤ እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሰን ፥ አደረሳችሁ እያልን፤ የጥምቀት ክብረ
+9
በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ #አጥቢያ_ለምትገኙ_የጽዋ_ማኅበራትና_ወጣቶች_በሙሉ፤ እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሰን ፥ አደረሳችሁ እያልን፤ የጥምቀት ክብረ በዓልን እንደተለመደው በደማቅ ሥነ ሥርዐት እንድናከብር፤ በአጥቢያችን የምትገኙ፤ ፠ ቅጽረ ቤተ ክርስቲያንንና የታቦት መተላለፊያ መንገዶችን የምታጸዱ፤ ፠ ምንጣፍ በማንጠፍ፣ በመጥረግና ከቦታ ቦታ በማጓጓዝ የምታገለግሉ፤ ፠ ከሰ/ት/ቤቱ ጋር ለበዓለ ጥምቀት በዝማሬ የምታገለግሉ የጽዋ ማኅበራት፤ ፠ ባንዴራ በመስቀል የምታገለግሉ፤ ፠ ሠረገላውን የምታጓጕዙ፤ ፠ ድንኳን በመጣል፣ ቄጠማ በመጐዝጎዝ የምታገለግሉ፤ ….. ወንድሞቻችንና እኅቶቻችን በሙሉ በበዓሉ ዙሪያ ውይይት ስለሚኖረን #ሰኞ_ጥር_4፤ ከቀኑ #በ12_ሰዐት በሰ/ት/ቤቱ አዳራሽ እንድትገኙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡ (ጥሪውን ላልሰሙ በማሰማት ይተባበሩ) ‹‹ወንድሞች በኅብረት ቢቀመጡ እነሆ መልካም ነው ፥ እነሆም ያማረ ነው፡፡›› #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

የአዲስ ቤተ ክርስቲያን ምረቃ በአሜሪካንና ዲሲና አካባቢዋ ያላችሁ እዳትቀሩ ጥሪው ተላልፏል፡፡ #ቅዳሴ_ቤት_ወዘሕንፀተ_ቤት፤ #ዘጥር_፪ ና ፫ #ዘደብረ_ኃይል_ቅዱስ_ራጕኤል_፤ (#አሜሪካ_ዲሲ)፡፡ በ
+6
የአዲስ ቤተ ክርስቲያን ምረቃ በአሜሪካንና ዲሲና አካባቢዋ ያላችሁ እዳትቀሩ ጥሪው ተላልፏል፡፡ #ቅዳሴ_ቤት_ወዘሕንፀተ_ቤት፤ #ዘጥር_፪ ና ፫ #ዘደብረ_ኃይል_ቅዱስ_ራጕኤል_፤ (#አሜሪካ_ዲሲ)፡፡ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክን በዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው ሀገረ ስብከት የደብረ ኃይል ቅዱስ ራጕኤል ቤ/ክ በፍጥነት ተሠርቶ የተጠናቀቀውን አዲስ ሕንፃ ቤ/ን ጥር 2ና 3 በሃገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ተባርኮ አገልግሎት ይጀምራል፤ በበዓሉ ላይ እንዲገኙ ቤተ ክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች፡፡ ፠ JANUARY 11 2PM – 6PM ቅዳሴ ቤት ፠ JANUARY 12AM – 12PM ሥርዐተ ማኅሌት፣ ቅዳሴና የንግሥ ክብረ በዓል፡፡ (እኛም የቤተ ክርስቲያኑን መከፈት አስመልከተን ከዋይዜማው ጀምሮ ሌሊቱን ሙሉ የሚባለውን ሥርዐተ ማኅሌት አቅርበንላችኋል፡፡) ፠ እጼውዕ ስመከ ወእኤምሀከ በተድላ፤ ራጕኤል መልአክ ለዓለም መስተበቅላ፡፡ እለ ያንኰረኵሩ ዘልፈ ለጠፈረ ሰማይ በማእከላ፤ ድኅረ ኀለፈ መዓልት ለጽልመተ ሌሊት በክፍላ፤ ለሥልጣነ ቃልከ ይትኤዘዙ ከዋክብት ወእብላ፡፡ ፠ ሰላም ለፊደለ ስምከ ዘአዳም ዝክሩ፤ ዘተለክአ ቅድመ ለሄኖክ ውስተ ጦማሩ፡፡ ራጕኤል አንተ ለመሰንቆ ልብየ ቃለ መዝሙሩ፤ ዝክረ ገብርከ ጸላዒ እመ መከረ ይሠሩ፤ እግዚኦ እግዚኦ ዕልዋ ለምክሩ፡፡ መልካም ሥርዐተ ማኅሌት፡፡ #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

፠ ኦ እግዚኦ አእርፍ ለነፍሳቲሆሙ ሕዝባውያን እለ አእረፉ በሃገረ ኢራን፡፡ አቤቱ አምላካችን የዩክሬን አውሮፕላን በኢራን የአየር ክልል እየበረረ ወድቆ ያረፉትን የ166 ሰዎች ነፍስ ማር፡፡ * ታኅሣ
፠ ኦ እግዚኦ አእርፍ ለነፍሳቲሆሙ ሕዝባውያን እለ አእረፉ በሃገረ ኢራን፡፡ አቤቱ አምላካችን የዩክሬን አውሮፕላን በኢራን የአየር ክልል እየበረረ ወድቆ ያረፉትን የ166 ሰዎች ነፍስ ማር፡፡ * ታኅሣሥ 29/2012 ዓ.ም. ቦይንግ 737 የሆነው አውሮፕላን ከ166 ሰዎችን አሳፍሮ ከኢራን ኢማ ሆሜኒ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ወደ ዩክሬኗ ርዕሰ ከተማ ኬይቭ እየበረረ ሳለ በአጭር ጊዜ ውስጥ ነው የመከስከስ አደጋው የገጠመው፡፡ * አደጋው ከማሌዥያና የኢዮትጵያ ያለፈው ዓመት ተመሳሳይ ክስተት ቀጥሎ የተከሰት ከባዱ የመከስሰክ አደጋ ሲሆን በሞቱበት ሰዎች ብዛትም ከማሌዥያው በመቀጠል ሁለተኛው ሆኗል፡፡

ጕባኤ ደቂቀ አበው ፱፤ ‹‹#ነገረ_ማርያም_ዘቅዱስ_ኤፍሬም_ሶርያዊ_፡፡›› ጥር 3/2012 ዓ.ም. በመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ ሰ/ት/ቤት አዳራሽ ጥናት አቅራቢ፤ መምህር ግርማ ባቱ (የ
+2
ጕባኤ ደቂቀ አበው ፱፤ ‹‹#ነገረ_ማርያም_ዘቅዱስ_ኤፍሬም_ሶርያዊ_፡፡›› ጥር 3/2012 ዓ.ም. በመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ ሰ/ት/ቤት አዳራሽ ጥናት አቅራቢ፤ መምህር ግርማ ባቱ (የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ መምህር)፡፡

* 200 ቋድ (ኩብ መስሎ የተሠራና አንገት ላይ የሚነገት * 200 ሻሽ * 200 የውጭ ሀገር መሐረብ በድምሩ ለ1ድ ሰው ልብስ 60ብር የፈጀ አሠርተው፤ 100ውን ልብስ በአቶ አፈወርቅ ላንድሮቨር መኪና፤ 100ውን ደግሞ ሀብታሙ ዘውዴ በአውሮፕላን አስጭኖ በ19620ዓ.ም. ከልደት በዓል ከ3 ቀን በፊት ላልይበላ ደረሱ፡፡ የላልይበላ አለቃ፣ የ10ሩ መቅደስ ገበዝ (መሪጌቶች) በተሰባሰቡበት፤ እስከሚያደርስ ድረስ ብዙ ጊዜ አግልግሎት ለሚሰጡ፣ የተማሩና በአጋፋሪው እየተመረጡ ማሚ ጋራ ጋር ወጥተው ለሚያስረግጡ ደባትር ይሰጥ ላልደረሰው ለሚቀጥለው ዓመት እናመጣለን ብለው ተሰጠ፡፡ ‹‹#የተሰደደ_ዘመድ_ያለው_ለበሰ ፥ #የሌለው_ሳይለብስ_ቀረ›› 200 ሙሉ ልብስ ለ10ሩ መቅደስ መደበኛ አግልጋዮችና ማሚ ጋራ ለሚወጡ ሲታደል ከአ.አ. በኮሚቴት ለመጡ ለእነ መዘምር ሐኪም ማሞ. ለእነ አፈወርቅም ተሰጥቶ ነበር፡፡ ነገር ግን ከ40 የማያንሱ ደባትር ሳይደርሳቸው ቀረ፤ በተለይም 2ቱ ደባትር (አለቃ ባዬ አለሙና መጋቤ ቢሰጥ ዘአሸተንና የደብረ ሮሐ መጋቢ ሊቆችና ባለቅኔዎች ስለሆኑ) ልብሱ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰጠ በመሆኑ ከፍቷቸው ኖሮ፤ የልደት ክብረ በዓል ማሚ ጋራ ላይ ባለ ቀይ ጃኖ የለበሱ ከፊት ሲሰለፉ እነርሱ ግን የቀድሞ ሸማን በመልበሳቸው ከኋላ በመሰለፋቸው እንዲህ ብለው በቅኔ ተናገሩ፤ አለቃ ባየ አለሙ፤ ‹‹እንደ ፍየል ቆዳ ተፈየድን (ወደቅን፤ ልብሱ ሳሰጠን ቀረ፡፡ የተበላሸ ይወድቃልና)፡፡›› መጋቤ ቢሰጥ ‹‹የተሰደደ ዘመድ ያለው ለበሰ ፥ የተሰደደ ዘመድ የሌለን (አጥተን) ሳንለብስ ቀረን፤ ብለው ቅሬታቸውን አቀረቡ፡፡ በዓመቱ ግን ለ60 ሰዎች ሙሉ ልብሱ ከ2ቱ ባለቅኔ ምሁራን ጭምር ደረሰ፡፡ ልዩ ማስታወሻ፤ በቅዱስ ላሊበላ በ1962ና 63 ዓ.ም. የተሠራውና 50 ዓመታት ያስቈጠረው ጃኖ ሙሉ ልብስ ብዛቱ 260 ነው፡፡ #ማሚ_ጋራ፤ #ዮም_ተወልደ_ቤዛ_ኵሉ_ዓለም፡፡ ማሚ ጋራ ከ10ሩ ቤተ መቅደሶች በቤ ማርያም በስተምዕራብ በቅኔ ማኅሌቱ አቅጣጫ የሚገኝ ሲሆን፡፡ መላእክትና ኖሎት ተብሎ ይጠራል፡፡ ከላይ ከተራራው ላይ ጃኖ ለብሰው የሚያስረግጡበት፤ (ማሚ ጋራው) መላእክት ሲባል፤ ከታች መሬት ላይ እየሰገዱ የሚያስረግጡበት ደግሞ፤ ኖሎት ይባላል፡፡ ቤዛ ኵሉ ዓለም እየተባለ ከላይና ከታች በቅብብሎሽ ነው የሚባለው፡፡ ማሚ ጋራ ላይ ለልደት ወጥቶ የሚያስረግጥ፤ የከበሮ አመታቱና የማስረገጡ ሂደቱ ለየት ያለ ስለሆነ የላሊበላን ቀለም ከልጅነቱ ጀምሮ ያልተማረ ከሆነ ስለሚከብደው ከሌላ አካባቢ የመጣ ሊቅም ቢሆን በሥርዐተ ማኅሌቱ አገልግሎት ላይ ይሳተፋል እንጂ ከማሚ ጋራው ላይ አይወጣም፡፡ ይኸውም በጌታችን በመድኀኔ ዓለም መወለድ ሰውና (እረኞችና) መላእክት ‹‹ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ወሰለማ በምድር ስምረቱ ለሰብእ›› እያሉ የማመስገናቸው ምሳሌ ነው፡፡ (ወደ ቅዱሳ ላለበላ የሄዳችሁ እንደምታውቁት ቅዱስ ላሊበላ ውሃ መውረጃው ሳይቀር በምሳሌነት የተሠራ፤ ዕፁብ ዕፁንብ የሚያስበል ነው፡፡) ኮሚቴ በአዲስ አበባ ከተመረጠ በኋላ በግንባር ቀደምትንት ለማሚ ጋራ ተሰላፊ የሚዋደዱት ጓደኛማቾች መዘምር ሐኪም ማሞና … አፈወርቅ ተመርጠዋል፡፡ መዘምር ሐኪም ማሞ ሃገራቸውንና ቤተ ክርስቲያናቸውን በቅንነትና በታማኝነት ሲያገለግሉ ከርመው፤ በሰለምና በጤና ‹‹እንበለ ደዌ ወሕማም›› (ያለ በሽታና ያለ ሕማማ) በ106 ዓመታቸው ሰኔ 16/20111 ዓ.ም. አርፈዋል፤ ሥርዐተ ግብዐተ መሬቱም ከ72 ዓመታት በላይ ባገለገሉበትና በኖሩበታ በታላቁ ደብር በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም በቤተ ልሔም ቅጽር ግቢ ውስጥ ከአበው መቃብር አጠገብ አርፈዋል፡፡ የአባቶቻችን አምላክ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ነፍሳቸውን ከደጋጎቹ ከነቅዱስ ላሊበላ ካሉበት ጋር ይደምርልን፤፡፡ /ታሪኩን የነገሩን ከ1942 ዓ.ም. እስከ 2011 ዓ.ም. ለ70 ዓመታት ድረስ እንደ ወንድም ጭምር የቅርብ ጓደኛቸው የሆኑት ሊቀ ካህናት አፈወርቅ መኮንን፣ እና የኔታ ሙሴ ዘደብረ ሰላም ናቸው፡፡/ #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#መዘምር_ሐኪም_ማሞ_ገዛኸኝ፤ #የታላቁ_ደብር_ታላቁ_መዘምር፡፡ (ያረፉት ሰኔ 16 ነው፤ ነገር ግን በሰኔ 15ቱ የባሕር ዳር የባለሥልጣናት ሞት ምክንያት ወቅቱ በሀገራችን ኔትወርክ ስላልነበር ሳንዘግብ በመቅረታችን ይቅርታ እየጠየቅን፤ የ6ወር መታሰቢያ ላይ በወርኀ ታኅሣሥ ዘገብነው፡፡) ፠ #ከ72 #ዓመታት_በላይ_ታላቁን_ደብር_ቀጨኔ_ደብረ_ሰላም_መድኀኔ_ዓለምን_በመዘምርነት_በነጻ_ያገለገሉ፤ ፠ #የ101 #ዓመታት_የዕድሜ_ባለጸጋ፡፡ ፠ ከልጅነት እስከ ዕርግና በነጻ ቤተ ክርስቲያንን ያገለገሉ፤ በልጅነትና በወጣትነት ዘመናቸው በቅዱስ ላሊበላ በቤተ ጎልጎታ በዲቁና ፤ ከ1930ዎቹ እስከ 2011 ዓ.ም. በቀጨኔ ደብረ ሰላም በመዘመርነት በነጻ ያገለግሉ፡፡ ፠ ያገለገሉት አምላካችን መድኀኔ ዓለምም በዕድሜ (101 ዓመታትን)፤ በልጆች (13 ልጅ፤ 26 የልጅ ልጅ) ወልደው፤ በጤና (እስከ በዓለ ዕረፍታቸው አቅራቢያ ድረስ ማኅሌት በመቆም እያገለገሉ) በሰላምና በጤና ያረፉ፤ ፠ ደወል ተደውሎ ፥ ‹‹ስቡሕ..›› ተብሎ ማኅሌት ሲጀመር ከሌሎች በነጻ እንደርሳቸው በርካታ ዘመናትን እያገለገሉ ከሚገኙ ጓደኞቻቸው ጋር በሰዐቱ ተገኝተው ማኅሌቱን የሚያደምቁ ናቸው፡፡ (ከሌሎች አድባራት በተለየ ሁኔታ ቀጨኔ ላይ ገና ማኅሌቱ እንደተጀመረ በቀኝ ክንፍ ቆመው ደማቅ እንዲሆን የሚያደርጉ አበው ናቸው) ፤ እርሳቸው በማረፋቸውም በዘንድሮ የ2012 ዓመት የጽጌ ማኅሌት በቀኝ ክፍል ቀዝቅዞ ነበር ያለፈው፡፡ ፠ በሐኪምነት ሙያቸው ሕመም የሚያጋጥማቸውን ካህናት የካህናት ደመወዝ አነስተኛ በመሆኑ እቤታቸው ድረስ በመሄድ በነጻ ሕክምና የሚያደርጉ አባት፤ ፠ #በቅዱስ_ላሊበላ_ማማ_በልደት_ክብረ_በዓል_ላይ_የሚለበሰውን_ለ260_ደባትር_መዘምራን_ቀይ_ጃኖና_ተጓዳኝ_አልባሳት_ከሌሎች_ኮሚቴዎች_ጋር_በመሆን_ከ50_ዓመታት_በፊት_በ1962_ዓ.ም. አሠርተው ያበረከቱ፤ ፠ ከበሮ ሲመቱና በቅዱስ ላሊበላ ማሜ ጋራ ላይ ሲያስረግጡ ልብን የሚመስጡ አባት፤ ፠ ተወልድው ላደጉበት ለቅዱስ ላላበላና በላስታ ለሚገኙ የተለያዩ አድባራትን በልዩ ልዩ ነገሮች ሲያገለግሉ የነበሩ፤ #ልደት_ዕደገትና_ትምህርት፤ በ1910 ዓ.ም. በወሎ ፥ ላስታ ላሊበላ ደንጎባት ላይ ማዶ ቅፋፍ ላይ፤ ከአባታቸው ከአቶ ገዛኸኝ ገፊና ከእናታቸው ከእማሆይ እታገኘሁ ለየኸኝ ተወልደው፤ በቅዱስ ላልይበላ ከተማ በ7 ወይራ ሰፈር አደጉ፡፡ የቤተ ክርስቲያንን የዲቁና ትምህርት በአካባቢው ከነበረው ቅዱስ ላልይበላ ካነፃቸው አብያተ ክርስቲያናት አንዱ ከሆነው በቤተ ጎልጎታ በሚገባ ከቀሰሙ በኋላ ዲቁናን ተቀብለው በዚያው በተማሩበት ደብር በቤተ ጎግሎታ በዲቁና ሲያገለግሉ አድገዋል፡፡ ለትምህርት ካላቸው ፍቅርና ትጋት የተነሣም በጎንደርና በጎጃም እየተዘዋወሩ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት እንደ ንህብ ቀስመዋል፡፡ ከዚያም ወደ ትውልድ ሀገራቸው ወደ ላሊበላ በመመለስ ዘመናዊ ትምህርት ተምረዋል፡፡ #ሥራ፤ *ወደ አዲስ አበባ በመምጣት በቀድሞው ‹‹ክቡር ዘበኛ›› በመቀጠር በተለያዩ የሥራ ዘርፎች ላይ አገልግለዋል፡፡ *በመቀጠልም ወደ ጤና ጥበቃ ሚንስቴር በመዛወር የሕክምና ትምህርት በመማር በዲፕሎማ ተመርቀዋል፡፡ *በተማሩት የሐኪምነት ዘርፍም በራስ ደስታ ዳምጠው ሆስፒታልና በትምህርት ሚንስቴር ሥር ባሉ የተለያዩ የመንግሥት ትምህርት ቤቶች ውስጥ የሕክምና አገልግሎት ሰጥተዋል፡፡ በአገራችን በነበረው የሱማሌ ወረራ ወቅትም ከሠራዊቱ ጋር አብረው በመዝመት በሙያቸው በሐኪምነት ለሃገራችን ኢትዮጵያ ትልቅ አስተዋጽዖን አድርገዋል፡፡ *በታላቁ ደብር በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም አጥቢያ ችሎት በሚባል አካባቢ ትዳር መሥርተው፥ ቤት ሠርተው፥ 13ት ልጆችን (6ት ወንዶችንና 7ት ልጆችን) ወልደው፥ 26ት የልጅ ልጆችን ስመው፤ በክርስትና ሕይወታቸው ታማኝና ቅን ሆነው ያስተማረቻቸውን እናት ቤተ ክርስቲያን ባለመርትና ባለመዘንጋት ከ1930ዎቹ እስከ 2011 ዓ.ም. ድረስ ‹‹ዘነሣዕክሙ በጸጋ ፥ ሀቡ በጸጋ›› የሚለውን የጌታ ቃል ቀድሞም በልጅነታቸው በቤተ ጎልግታ በነጻ ሲያገልግሉ እንዳደጉት ሁሉ ከ72 ዓመታት በላይ በነጻ በመዘምርነት በቅኔ ማኅሌቱ በቀኝ ክንፍ አገልግለዋል፡፡ *በ1942 ዓ.ም. በላላበላ የልደት በዓል ላይ በሥርዐተ ማኅሌት ቁመት ላይ የተዋወቋቸውና የቅርብ ጓደኛ (እንደ ወንድም የሚዋደዱት) ሊቀ ካህናት አፈወርቅ መኮንን ከመንግሥት ተሹመው በአውርፕላን አብራሪ እጅ ደብዳቤ ተልኮላቸው የአ.አ.አ የመናገሻ አራዳ ገነተ ጽጌ ፀሐፊና መዝገብ ሹም ሆነው ሚያዝያ 29/1959 ዓ.ም. መጡ፤ ነገር ግን ደብሩ በ40 ዓመታት ውስጥ በባንክ ያስቀመጠው ገንዘብ 44 ሺህ ብር ብቻ ነበር የተረከቡት፤ አዲስ የመጡትም ፀሐፊ ከግንቦት 1 እስከ ጳጕሜን 3 (በ4 ወር ከ3 ቀናት ውስጥ) ለደብሩ 105 ሺህ ብር ገቢ አደረጉ፤ ይህም ዜና በታዋቂው ጋዜጣ በመርስዔ ኀዝ አበባ ዘገቢነት ሲዘገብ አብዛኛውን ሕዝብ ጉድ አሰኘ፤ በአዲስ አበባ ያሉ የላስታ ላሊበላ ተወላጆችም ከፓርላማ ተመራጮች ከእነ ቀኛ አዝማች አበራ ጀምሮ መጥተው ደስታቸውን ገለጹ፡፡ መዘምር ሐኪም ማሞም ጓደኛቸውን በቅርብ ማግኘት ቻሉ፡፡ ታዲያ ይህ ወዳጅነታቸው ጠንክሮ ከ3ት ዓመታት በኋላ በ1962 ዓ.ም. በአዲስ አበባ በተለያዩ ቦታዎች የሚኖሩ የቅዱስ ላሊበላ ተወላጆች ተሰባስበው ‹‹ለቤዛ ኵሉ ዓለም›› ክብረ በዓል ምን እናድርግ የሚል ኅብረትን ፈጠረ፤ ይህም ኅበርት በርካት ተግባራትን አከናውኗል፡፡ ለአብነትም ዋነኞቹ፤ 1ኛ) በየዓመቱ ከአ.አ. ወደ ቅዱስ ላሊበላ የሚወርዱ ተወላጆች የቤዛ ኵሉ ዓለም ይትበሃልን፤ ከታላቁ ምሁርና የታላቁ ደብር የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም የድጓ መምህር ከሆኑት ከመሪጌታ ይኄይስ ለ5 ወራት ጥናት አካሂዶ በላሊበላ የልደት ቀን አብሮ የሚሠለፍ ሁኗል፡፡ 2ኛ) ከቅዱሱ ላሊበላ ጀምሮ ለቤዛ ኵሉ ዓለም ክብረ በዓል የሚለበሰው የሸማ ልብስ በማርጀቱ ሙሉ ልብስ ለማሠራት ተስማሙ፤ ይህንንም ኅብረት የሚያስተባበሩ ሰዎች ተመርጠው ወደ ሥራ ተገባ፡፡ እነርሱም፤ *መሪጌታ ይኄይስ ያለው፤ የኮሚቴ ሊቀ መንበር፤ የታላቁ ደብር የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም የድጓ መምህር *ሀብተ ወልድ መኰንን፤ ካህንና በተለያዩ ቦታዎች (በመርሐ ቤቴ፣ በደሴ፣ በአዲስ አበባ) የአውራጃ ፍርድ ቤት ዳኛ፤ *ሀብታሙ ዘውዴ፤ ካህንና በተለያዩ ቦታዎች የአውራጃ ፍርድ ቤት ዳኛ፤ *ወዳጅ ክብረት፤ የብርሃንና ሰላማ ማተሚያ ቤት መዘገብ ሹም፤ *ወረደ ቃል፤ መምሬ ይትባረክ፤ መኳንንት አበራ፤ ክህነት ሲሳይ፤ ... እንዲሁም በዋነኛነት ሥራውን በቅርብ እንዲያስተባብሩና እንዲመሩ እንደ ወንድም የሚዋደዱትን *ሊቀ ካህናት አፈወርቅ መኰንን *መዘምር ሐኪም ማሞ ገዛኸኝ በመሆን ነበር፡፡ #ዮም_ተወልደ_ቤዛ_ኵሉ_ዓለም_ላይ_የሚለበሰው_ልብስ_ጥንተ_ታሪክ_፤ ቅዱስ ላሊበላ ሕንፃውን አንፆ 9ኙን ደብተራ በቤተ ክርስቲያኑ ትክለኛ አድርጎ ሲሾም የ9ኙን ደባትር ቤተሰብና ቦታዋን ለቅዱስ ላሊበላ ሕንፃ መሥሪያ የሰጠችውን የቀ… ቤተስብ ሸማውን እንዲለብስ ሥርዐተ ሠርቶ ስለነበር ከትውልድ ወደ ትውልድ በዚሁ መልክ ሲተላለፍ ቆይቷል፡፡ በ1962 ዓ.ም. ከላይ የጠቀስናቸው ኮሚቴዎች ለ200 ማኅሌታውያን (መዘምራን) ለ10ሩ ቤተ መቅደስ አገልጋዮች፤ ጃኖ (ጥንግ ድርብ የሆነና በቀይ ክር በልዩ አሠራር፥ ቀለሙ የማይለቅ፥ በጠንካራ ማግና ክር አ.አ. ዶርዜ ሰፈር የተሠራ)፤ በወቅቱ ከ20-30ብር የተሠራ፡፡ * 200 እጀ ጠባብ * 200 ሱሪ * 200 ነጭ ሐር ሱሪ

#አቡነ_አብሳዲ_ዘደብረ_መጒና_፤ #ታኅሣሥ 29 ልደታቸው ከጌታችን ልደት ጋር ከተባበረላቸው ቅዱሳን መካከል አንዱ ናቸው፡፡ ፠ #የበረሃው_ዕንቊ_ገዳም_መንበረ_ልዑል_ጽርሐ_አርያም_ደብረ_መጕናን_የመሠረቱ፡፡ ፠ አብርሃም ቅድስት ሥላሴን እንዳስተናገደ፤ #አቡነ_አብሳዲ_ደግሞ_ጌታችንን_ተቀብለው_እግሩን_ያጠቡ_ናቸው፡፡ (ፎቶውን ይመልከቱ) ፠ #ደቀ_መዛሙርቶቻቸው_በተሰየፉበት_አንገረብ_ወንዝ_ላይ_ #44ት #የፍል_ውኃ_ፈዋሽ_ጠበል_አንገረብ_የሚባል_ያላቸው፤ በሃገራችን ብዙሃን ሕዝብ ከሚጠመቅባቸው ጠበሎች ዋነኛው ከተጠማቂው ሕዝብ ብዛት የተነሣ #ቀንና_ሌሊት_ጥምቀት_የሚካሄድበት፡፡ (ፎቶውን ይመልከቱ) ፠ ከብቃታቸው የተነሣ ወደ ላይ ጽርሐ አርያምን ወደ ታች በርባሮስ ድረስ የሚደረገውን የሚመለከቱ፤ ፠ #ወላዴ_አእላፍ ፥ #ወላዴ_ቅዱሳን_ሊቃውንት፥ #አበ_ብዙኃን፥ #ወላዴ_ሰማዕታት የሆኑ፤ ፠ በፀሐይ ሰረገላ፥ በብርሃን መንኰራኵር እየተጫኑ እንደ ሐዋርያት የሚያስተምሩት፤ ፠ 470 ዓመታትን የኖሩት፡፡ ፠ ታኅሣሥ 29 የጌታችንና,ን የጻድቁን የልደት በዓል፤ ሙሉ አርማጭሆ እንዲሁም የትክል ድንጋይ፣ የዳንሻና አካባቢው ምዕመናን በ10ሺዎች የሚቈጠር ሕዝብ የሚያከብርላቸው፡፡ * ምንኵስናን የተቀበሉት ከአቡነ ዮሐንስ ከማ ነው፡፡ * በማንዳባ ገዳም ከ7ቱ ከዋክብትና ከ7ቱ ከዋክብተ ጣና አንዱ ከኾኑትና ደንጊያን እንደ ጀልባ ከሚጠቀሙት ከአቡነ ያሳይ ጋር ብዙ የጽድቅ ሥራና የትሩፋት ተጋድሎን ፈጽመዋል፡፡ * ቀድሞ በኤርታ ደብረ ማርያም ነበር የሚኖሩት፤ ኋላ ታቦተ ማኅበረ በኵርንና ታቦተ ኪዳነ ምሕረትን ይዘው ብዙ ቅዱሳንን ወዳፈለቁበት መሥዋዕተ ኦሪት ይሠዋበት ወደነበረው ገዳመ መጕና መጡ፤ ገዳሙ የሚገኘውም በጎንደር ታች አርማጭሆ ነው፡፡ ‹‹በሬ ሜዳ›› የሚባለው ቦታ ላይ የጌታችን ልደትና የጻድቁ ልደት ዝክር የሚዘከርበት ምርፋቅ ነው፡፡ ጻድቁ የተጓዙባቸው ምዕራፋት ከቁርባኔ ወንዝ እስከ መታጠቂያ በር 13ት ሲሆኑ የ13ቱ ሕማማት ምሳሌ ሲሆኑ፤ የመታጠቂያ በር ደግሞ የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው፡፡ በ1407 ዓ.ም. በአፄ ይስሐቅ ዘመን ‹‹ዳሩ እሳት ፥ መሐሉ ገነት፡፡›› ተብሎ ተገድሟል፡፡ ወላዴ አእላፍ አበ ብዙኃን ዐምዳ ወብርሃና ለደብረ መጒና በቆብ የወለዷቸው በርካታ ቅዱሳን ቢኖርም፤ #ገዳማትን_የመሠረቱ_ለአብነት_ዋናዎቹ_፤ ፠ #አቡነ_ስነ_ኢየሱስ_ (ቅዱስ ያዕቆብ ዘግሙድ ገዳምን የመሠረቱ) ፠ አቡነ ሥልጣነ ክርስቶስ (አመራ ቊስቋም ገዳምን የመሠረቱ) ፠ #አቡነ_ልብሰ_ክርስቶስ_ (ዳውጨና አማኑኤል ገዳምን የመሠረቱ) ፠ አቡነ ማቴዎስ (ያይራ ተክለ ሃይማኖት ገዳምን የመሠቱ) ፠ #አቡነ_ዮሐንስ_ዘመረባ (ጊዮርጊስ ገዳምን የመሠረቱ) ፠ ሰማዕቱ አቡነ ጽጌ ድንግል (እንኮ ድብ ገዳምን የመሠረቱ) ፠ #አቡነ_ዘወልደ_ዳዊት (ጐረፍ ተክለ ሃይማኖትን የመሠረቱ) ፠ አቡነ መቅደሰ ክርስቶስ (ሳይኮ ኪዳነ ምሕረትን የመሠረቱ) ፠ #አቡነ_ህላዌ_ክርስቶስ (አምስትያ ገዳምን የመሠረቱ) ፠ አቡነ ተላዌ ክርስቶስ ( ገዳምን የመሠረቱ) ፠ #አቡነ_ከናፍረ_ክርስቶስ (ገዳምን የመሠረቱ) ፠ አቡነ የማነ ክርስቶስ (ገው ጊዮርጊስን የመሠረቱ) ፠ #አቡነ_ዕደ_ክርሰቶስ (የኢትዮጵያና የግብፅ ሐዋርያ ፥ የደብረ መጕና 3ኛ መምህር /አበምኔት/) ፠ አቡነ መዝራዕተ ክርስቶስ (በትግራይ ገዳምን የመሠረቱ፤ ልደታቸው ከአባታቸው ጋር በታኅሣሥ 29 የተባበረላቸው) ፠ #ሰማዕቱና_በአባታቸው_ወንበር_የተተኩት_አቡነ_አምኀ_ጊዮርጊስ፡፡ (የደብረ መጕና 2ኛው መምህረ /አበምኔት/) ሲሆኑ፤ #ቅዱሳን_ደራስያን_ሊቃውንት_ከሆኑት_መካከል_ለአብነት_፤ ፠ #አባ_ገብረ_ኢየሱስ_ (የሰቈቃወ ድንግል ደራሲ) ፠ #እጨጌ_በትረ_ጊዮርጊስ_ (በአፄ ፋሲል ዘመን የኢትዮጵያ ሊቃውንት አፈ ጕባኤ የነበሩና የቅባት ሃይማኖት መሪዎች እነ አልፎንሱ ሜንዴዝን የረቱ …. በዚህም ሊቃነታቸው በዐይኑ ያየ ባለቅኔ፤ ‹‹ወረከብናሁ ለበትር ዘያደክማ ለሮሜ፤ ቅሩጸ በንባብ ወጽሩበ በትርጓሜ፡፡›› ብሎ የተቀኘላቸው የሊቃውንት ዋልታ፡፡ ፠ #አባ_ስብሐት_ለአብ_ (የመልክ ሥላሴ፣ ሰይፈ ሥላሴ፣ ዘይነግሥን የደረሱና 14ቱን ቅዳሴ ያመሠጠሩና በአንድምታ የተረጐሙ፣ በጎንደር ደብረ ብርሃን ሥላሴ ከብዙ ሊቃወንት ጋር በመሆን የቅኔና የመጻሕፍትን ምሥጢር ከነሙሉ አገባቡና እርባ ቅምሩን እንዲሁም የአቡሻኽርን ሁሉ የቀመሩ፤ የንጉሡ የአድያም ሰገድ ኢያሱ መምህረ ንስሐ የነበሩ) ፠ #አባ_ዳንኤል_፤ (ብዙ መጻሕፍትን ያሰባሰቡና የጻፉ፤ ንዋያተ ቅድሳትን የሚሠርቅ ‹‹ቢዘራ ለበረድ ፥ ቢወልድ ልጁን ለጕጓድ፡፡›› ብለው ከ8000 በላይ ሊቃውንትን በማሰባሰብ እንዲወሰን ያደረጉ፡፡ #ከላይ_ያሉትን_ለአብነት_የጠቀስናቸውን_ቅሳንና_ሊቃውንት_አስተምረውና_ወልደው_፤ ለ90 ዓመታት ፍሬና ቅጠላ ቅጠል ተመግበው፤ ራቁታቸውን በጋ ከክረምት በበረሃው መንነው፤ ሳማ (አበርባራን) ለትሩፋትና ለተጋድሎ ለብሰው፤ በፀሐይ ሰረገላ፥ በብርሃን መንኰራኵር እየተጫኑ እንደ ሐዋርያት በማስተማራቸው፤ የጸጋና የቅብዐት ተካተዮችን እያስተማሩ ወደ እናት ቤ/ክ በመመለሳቸው፤ ** የሚያምረውን ሥጋዊ ደም ግባታቸውንና ሰውነታቸው እንደ ጻድቁ ቅዱስ ኢዮብና እንደ ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ወደ ቁስል በመቀየራቸውና ሥስቃዩንና መከራውን በመቻላቸው፤ ቁስላቸው ተልቶ ትሎቹን የገዳሙ አእዋፋት እስኪመገቡት ድረስ በመታገሣቸው፡፡ *** በርካታ ቃል ኪዳን አምላካችን ሰጥቷቸው በተወለዱ በ470 ዓመታቸው ዐርፈዋል፡፡ #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#ታኅሣሥ_29_ልደታቸው_ከጌታችን_ልደት_ጋር_የተባበረላቸው_ቅዱሳን፤ #አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ፤ #ቅዱስ ላሊበላ፤ #ቅዱስ ነዓኵቶ ለአብ፤ #አቡነ አብሳዲ ዘደብረ መጕናና የቆብ ልጃቸው #አቡነ መዝራዕ
+5
#ታኅሣሥ_29_ልደታቸው_ከጌታችን_ልደት_ጋር_የተባበረላቸው_ቅዱሳን፤ #አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ፤ #ቅዱስ ላሊበላ፤ #ቅዱስ ነዓኵቶ ለአብ፤ #አቡነ አብሳዲ ዘደብረ መጕናና የቆብ ልጃቸው #አቡነ መዝራዕተ ክርስቶስ፤ #ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ፤ #ቅዱሳን ነገሥታት አብርሃ ወአጽብሃ፤ #አቡነ አካለ ክርስቶስ፤ #መስፍኑ ኢያሱ፤ #አቡነ ዳንኤል ዘገርዓልታ፤ #ዳግማዊ ቂርቆስ ዘቡልጋና ሌሎችም ቅዱሳን አሉ፤ ነገር ግን ከቅዱሳን በዓል በላይ የጌታ በዓል መከበር ስለሚገባው የቅዱሳኑ ዋና በዓላቸው በሌላ ቀናት /በዕረፍታቸው…../ ቀን ይታሳባል፡፡ #የቅዱስ_ላላበላ_ክብረ_በዓል_የሚከበርባቸው_ቦታዎች_፤ ፠ በደብረ ሮሐ ላስታ ቅዱስ ላሊበላ ፠ በመዲናችን በአዲስ አበባ አንቀጸ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ፤ በድርብነት ይከብራል፡፡ ፠ በአሸዋ ሜዳ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ላሊበላ ወቅዱስ መርቆሬዎስ ወኪዳነ ምሕረት ወቅድስት ሥላሴ፡፡ ..(ሌሎችም ካሉ ከነፎቷቸው ጨምሩበት) #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem