fa
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

رفتن به کانال در Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

کانال Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 335 مشترک است و جایگاه 5 641 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 191 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 335 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 15 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -80 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -1 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 22.23% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 10.47% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 409 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 605 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 22 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 16 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

15 335
مشترکین
-124 ساعت
-117 روز
-8030 روز
آرشیو پست ها
፬. ሸኖ ጎልባ ደብረ ሣሕል ቅዱስ ሚካኤል ደብር፤ (በአብርሃ ወአጽብሃ ዘመን የተመሠረተ) ፨አድራሻው፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ሰኖ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ሸኖ፡፡ ፭. መላሃይዘንጊ ቅዱስ ሚካኤል፤ (በ8ኛው ክፍለ ዘመን የታነጸ) ፨አድራሻው፤ ሰሜን ሸዋ ሰላሌ ፍቼ ሀገረ ስብከት፥ ጎሐ ጽዮን፥ ዐባይ በረሃ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎሃ ጽዮን ወይም ደብረ ማርቆስ በሚለው መኪና ዐባይ በረሃ ላይ መውረድ፤ ፮. ላስታ ላሊበላ ቤተ ሚካኤል፤ (በ11ኛው ክፍለ ዘመን በቅዱስ ላሊበላ የታነፀ፥ ከ11ዱ የላስታ ላሊበላ ፍልፍል ሕንጻዎች አንዱ) ፨አድራሻው፤ ላስታ ሀገረ ስብከት፥ ላሊበላ ከተማ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ላሊበላ፡፡ ፯. ገርዓልታ ዋሻ ቅዱስ ሚካኤል፤ ፨አድራሻው፤ ትግራይ ሀገረ ስብከት፥ ገርዓልታ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → መቀለ → ገርዓልታ፡፡ ፰. ሚካኤል ዓምባ፤ (በ11ኛው ክፍለ ዘመን የታነጸ) ፨አድራሻው፤ ትግራይ ሀገረ ስብከት፥ ውቅሮ፥ (በመቀለና በአዲግራት መሃል)፥ አጽቢ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ውቅሮ → አጽቢ፤ ፱. ባሕር ዳር ሽምብጥ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ (በ13ኛው ክፍለ ዘመን የተመሠረተ) ፨አድራሻው፤ ምዕራብ ጎጃም ባሕር ዳር ሀገረ ስብከት፥ ባሕር ዳር ከተማ፥ ቀበሌ 13 ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ባሕር ዳር ከተማ → ሆስፒታል በሚል ታክሲ (ዲፖ ጋር)፡፡ ፲. እስቴ አበርጉት ቅዱስ ሚካኤል ፤ (በአፄ ዓምደ ጽዮን ዘመነ መንግስት በልጃቸው በአቡነ ፊልሞና የተሠራ ታሪካዊ ጠበል ያለበት) ፨አድራሻው፤ ደቡብ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ እስቴ ወረዳ፥ ደስኳ አጋማች ቀበሌ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → እስቴ፡፡ ፲፩. በሮ ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል፤ በ16ኛው መ/ክ/ዘመን መጨረሻ የተመሠረተ ፨አድራሻው፤ ደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት፥ ሳይንት ወረዳ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ → አማራ ሳይንት፡፡ ወይም፤ ከጎጃም በመርጠሉ ማርያም → አማራ ሳይንት ፲፪. ጎንደር ፊት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ በአፄ ፋሲለደስ ዘመነ መንግሥት ተመሠረተ፤ ፨አድራሻው፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር፡፡ ፲፫. ጎንደር አጣጣሚ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ ፨አድራሻው፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር፡፡ ፲፬. ተንታ ደብረ ብርሃን ቅዱስ ሚካኤል፤ (ንጉሥ ሚካኤል በሚያስደንቅ ሁኔታ ያሠሩት) ፨አድራሻው፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ አምባሰል፥ ተንታ ወረዳ፥ ጠዓት ቀበሌ፥ እሜገኝ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ጻድቃኔ፡፡ ፲፭. አጃና ቅዱስ ሚካኤል፤ (በቀስተ ደመና ጠበል አጥማቂው) ፨አድራሻው፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ተጉለት፥ አጃና፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ጻድቃኔ → አጃና፡፡ ፲፮. ቦንብ አርግፍ ቅዱስ ሚካኤል (ሰሜን ወሎ ሀ/ስብከት፤ የጁ ወልዲያ) ፲፯. ቦረዳ ቅዱስ ሚካኤል ፲፰. ዋሻ ቅዱስ ሚካኤል (ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፣ ኢቲሳ) ፲፱. አንኮበር ቅዱስ ሚካኤል (ሰሜን ሸዋ ሀ/ስብከት) ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #በኢትዮጵያና በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚከበርባቸው ገዳማትና_አድባራት፡፡ 1. ግሸን ደብረ ከርቤ ቅዱስ ሚካኤል 2. ጎሚስታው ሚካኤል (ትግራይ) 3.  እንዳ ቅዱስ ሚካኤል (ትግራይ) 4.  መቀለ ቅዱስ ሚካኤል 5.  ጾረና ቅዱስ ሚካኤል (ኤርትራ) 6.  ዓለም ገና ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል 7.  ደብረ ዘይት /ቢሾፍቱ/ ደብረ አሚን ቅዱስ ሚካኤል 8.  ዱከም ቅዱስ ሚካኤል 9.  ናዝሬት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል 10. ድሬዳዋ ቅዱስ ሚካኤል 11. ጭሮ አሰበ ተፈሪ ቅዱስ ሚካኤል (ድሬዳዋ፥ አሰበ ተፈሪ) 12. ሻሸመኔ ቅዱስ ሚካኤል 13. አርባ ምንጭ ላከ ኢየሱስና ሚካኤል 14.ዲላ ቅዱስ ሚካኤል 15. አሰላ ደብረ ሰላም ቅድስ ሚካኤል 16. ጂጂጋ ቅዱስ ሚካኤል 17. ሚዛን ቴፒ ደብረ ኀይል ቅዱስ ሚካኤል 18. ቦንጋ ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል 19. ኢሉባቦር ሌንቃ ቅዱስ ሚካኤል 20. እነሞርና ኤነር ወረዳ ቅዱስ ሚካኤል (ጉራጌ ሀ/ስብከት) 21. አሰቦት ደብረ ወገግ ቅዱስ ሚካኤል (ምሥ. ሀረርጌ ሀ/ስብከት) 22. ሽንቁሩ ቅዱስ ሚካኤል 23. ኩክ የለሽ ዛሪያ ቅዱስ ሚካኤል 24. ጅሩ ሞቶሎኒ ቅዱስ ሚካኤል (ጅሩ አርሴማ ውስጥ) 25. መንዝ ይገም ቅዱስ ሚካኤል 26. መሐል ሜዳ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል 27. የሲጠር ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል (መንዝ ቀያ ገብርኤል ወረዳ) 28. ወንጪት ቅዱስ ሚካኤል (በነብር የሚጠበቅ) 29. ሸዋሮቢት ጫሬ ቅዱስ ሚካኤል 30. ወልዲያ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል 31. ኮምቦልቻ ቅዱስ ሚካኤል 32. ደሴ ጢጣ ደብረ ሲና ቅዱስ ሚካኤል 33. ራያ ቆቦ ቅዱስ ሚካኤል 34. ደብረ ማርቆስ ዋሻው ቅዱስ ሚካኤል 35. ደብረ ማርቆስ አጠገብ ብዕርና ቅዱስ ሚካኤል 36. ደምበጫ ቅዱስ ሚካኤል 37. መርዓዊ ደብረ ኀይል ቅዱስ ሚካኤል 38. ባሕር ዳር ድባንቄ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል 39. አዘዞ አይራ ቅዱስ ሚካኤል 40. ዛራ ቅዱስ ሚካኤል (ባሕር ዳር አጠገብ ሐሙሲት) 41.ጉመር ደብረ ኅሩያን ቅዱስ ሚካኤል 42. ካምባ ቅዱስ ሚካኤል 43. ሳንቃ ወይራ ቅዱስ ሚካኤል 44. ዳስ ዓምባ ቅዱስ ሚካኤል 45. ላሐ ቅዱስ ሚካኤል 46. ጊራራ ቅዱስ ሚካኤል 47. መለኮዛ ቅዱስ ሚካኤል 48. ዋይሎ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል

፲፮. ወረገኑ ቅዱስ ሚካኤልና አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ሩዋንዳ አጠገብ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ (ቦሌ) → ወረገኑ፡፡ ፲፯. ቃሊቲ ሰፈረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ሰፈረ ገነት፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ቃሊቲ → ሰፈረ ገነት፡፡ ፲፰. ንቡ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ሃራብሳ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ቱሉ ዲምቱ → ንቡ ሚካኤል፡፡ ፲፱. ጀሞ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ጀሞ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (ሜክሲኮ) → ጀሞ፡፡ #እንዲሁም_በአንድነት_በተሠሩ_በሚከተሉት_አብያተ_ክርስቲያናት_ይከበራል፤ ፳. ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ ልደታ ክፍለ ከተማ፥ ጎላ (ኢምግሬሽን ጀርባ)፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል (ኢምግሬሽን)፡፡ ፳፩. ደብረ ናዝሬት ቅዱስ ዮሴፍና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ዮሴፍ፥ ደጃዝማች መርዕድ መንገድ፥ ቀለበት መንገድ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ከላጋር (ከፒያሣ) (ከ4 ኪሎ) (ከቦሌ)(ከመገናኛ) → ቃሊቲ መናኸሪያ /በቀለበት መንገድ/ ወይም፤ ከሳሪስ አቦ → ቦሌ /በቀለበት መንገድ/ ፳፪. ጀሞ ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ጀሞ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (ሜክሲኮ) → ጀሞ፡፡ ፳፫. ቃሊቲ ደብረ ቊስቋም ማርያምና ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ሰፈረ ገነት፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ቃሊቲ → ሰፈረ ገነት፡፡ ፳፬. ኮተቤ ማኅደረ ቅዱሳን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ሎቄ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ሎቄ፡፡ ፳፭. ፉሪ መካነ ቅዱሳን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ እና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ለቡ፥ ፉሪ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ለቡ፡፡ ፳፮. ቂሊንጦ መካነ ፍስሐ ቅዱስ ሚካኤልና በዓታ ለማርያም ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ቂሊንጦ አደባባይ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ቱሉዲምቱ፡፡ ወይም፤ ከፒያሳ → ቃሊቲ → ቂሊንጦ፡፡ ፳፯. ቱሉ ዲምቱ ደብረ ሰላም ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ አቃቂ ኬላ አጠገብ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ቱሉዲምቱ፡፡ ወይም፤ ከፒያሳ → ቃሊቲ → ቱሉዲምቱ፡፡ #እንዲሁም በድርብነት በሚከተሉት አብያተ ክርስቲያናት ይከበራል፤ ፳፰. መንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ 6 ኪሎ ዐደባባይ፤ ታክሲ፤ ከጊዮርጊስ → 6 ኪሎ (ማርቆስ)፡፡ ፳፱. ደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ገርጂ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ቦሌ በሚል ታክሲ → መስቀል ዐደባባይ፡፡ ፴. ማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያምና ደብረ መድኃኒት መድኃኔ ዓለም ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ ልደታ ክፍለ ከተማ፥ ልደታ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ጦር ኃይሎች በሚለው ታክሲ → ልደታ፡፡ ፴፩. ደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስና መካነ ጎልጎታ ማርያም ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ አረዳ ክፍለ ከተማ፥ ሰባራ ባቡር፥ ራስ ደስታ ዳምጠው ሆስፒታል አጠገብ (አርበኞች መንገድ)፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ አራዳ → በዊንጌት አስኮ /ሩፋኤል ፊንሐስ/ ታክሲ →  ዮሐንስ፡፡ ፴፪. ኮልፌ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ዊንጌት፥ ጠሮ፥ አራት መንታ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ አራዳ → ዊንጌት፡፡ ፴፫. ሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገዳም፤ ፨አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ልኳንዳ፥ ፈጥኖ ደራሽ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → መርካቶ → ኮልፌ አጣና ተራ → ልኳንዳ → (በስተግራ ባለው አስፓልት በእግር 5 ደቂቃ ፈጥኖ ደራሽ ማሰልጠኛ)፡፡ ፴፬. ቃሌ ተራራ ደብረ መድኀኒት አቡነ ሀብተ ማርያም ወቅድስት ልደታ ወቅድስት አርሴማ ገዳም፤ ፨አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ አስኮ፥ ካኦ ጄጄ ዱቄት ፋብሪካ፥ ቃሌ ተራራ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መርካቶ) → አስኮ፤ ፴፭. ማኅደረ መለኮት ወይብላ ቅድስት ማርያም ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ የሺ ደበሌ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → መርካቶ → የሺ ደበሌ፡፡ ፴፮. ቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ገርጂ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ገርጂ፡፡ ፴፯. ኮተቤ ደብረ ልዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቅድስት ኪዳነ ምሕረትና አቡነ ሀብተ ማርያም ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ኮተቤ፥ ካራ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ኮተቤ (ካራ) ፴፰. ረቢ መካነ ጎልጎታ መድኃኔ ዓለም ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ካራ ቆሬ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ አራዳ → አለም ባንክ → ካራቆሬ (ረጲ)፡፡ ፴፱. ፉሪ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ጋራ ኦዳ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ጋራ ኦዳ፡፡ ፵. ሐመረ ወርቅ ማርያምና አርሴማ ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ወርቁ ሰፈር፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ቃሊቲ → ወርቁ ሰፈር፡፡ ፵፩. ቶታል ደብረ ገነት ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ሰፈረ ገነት፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መርካቶ) → ሰፈረ ገነት፡፡ ፵፪. ቦሌ ቡልቡላ ምስካበ ቅዱሳን አባ ሳሙኤል ዘዋልድባና ቅዱስ አማኑኤል ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ቡልቡላ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ሳሪስ አቦ → ቡልቡላ መድኀኔ ዓለም (ኮንዶሚኒየም)→ ወደ ላይ በአስፓልቱ የ5 ደቂቃ የእግር መንግድ፡፡ ወይም፤ ከቦሌ መድኃኔ ዓለም → ቡልቡላ (በአዲሱ መንገድ) ፵፫. አቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔ ዓለም ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ አቃቂ፥ ጋራው መድኃኔዓለም፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ቃሊቲ → አቃቂ፡፡ ፵፬. ሣሎ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ሣሎ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ቃሊቲ → ሣሎ፡፡ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #በኢትዮጵያና በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚከበርባቸው ጥንታውያን #፲፱ ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. #እየላ_ቅዱስ_ሚካኤል፤ (#የ3 ሺህ_ዓመታት_ባለታሪክ፤ ከታቦተ ጽዮን ጋራ በ980 ከክ.ል.በ. ታቦቱ የመጣ፤ መሥዋዕተ ኦሪት ይቀርብበት የነበረ፤ አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን መጥቶ የባረከው) ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ላሊበላ → ግዳን (እየላ)፡፡ ፪. ሰሜን ትግራይ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል፤ (መሥዋዕተ ኦሪት ይቀርብበት የነበረ) ፨አድራሻ፤ ሰሜን ትግራይ ሀገረ ስብከት፥ ሰሜን ትግራይ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎሃ ጽዮን ወይም ደብረ ማርቆስ በሚለው መኪና ዐባይ በረሃ ላይ መውረድ፤ ፫. ጎሐ ጽዮን ቅዱስ ሚካኤል፤ (በ4ኛው ክፍለ ዘመን በአብርሃ ወአጽብሃ ዘመን የተሠራ) ፨አድራሻው፤ ሰሜን ሸዋ ሰላሌ ፍቼ ሀገረ ስብከት፥ ጎሐ ጽዮን፥ ዐባይ በረሃ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎሃ ጽዮን ወይም ደብረ ማርቆስ በሚለው መኪና ዐባይ በረሃ ላይ መውረድ፤

#ኅዳር 12 #እንኳን አደረሳችሁ ለሰው ወገን የሚያዝንና የሚራራ፥ በእግዚአብሔር የጌትነት ዙፋን ፊት ሁልጊዜ ለምስጋና የሚቆም፥ ለፍጥረት ሁሉ የሚማልድ፥ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በዓለ ሢመቱና እስራኤላውያንን በባሕረ ኤርትራ ያሸገረበት በዓል ነው፡፡ በዓለ ሢመቱ፤ ሚካኤል ማለት ማን እንደ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡ በእለተ እሁድ ካለመኖር ወደ መኖር የመጣ ሲሆን እርሱም የነገደ ኃይላት አለቃቸው ነው በተጨማሪም ከሳጥናኤል ውድቀት በኋላ የአጋእዝትን ነገድም በአለቅነት ደርቦ የያዘ ሲኾን፤ ለ100ውም(99ኙም) ነገደ መላእክት አለቃቸውም ነው፡፡ ቅዱስ ሚካኤል ለሰው ልጆች ምሕረትን ከኅዳር 12 (በዓለ ሢመቱ) ጀምሮ እስከ 13 (የአእላፍ መላእክት) በዓል ድረስ ከአምላኩ ምሕረትን የሚለምንበት ነው፡፡ በዚህ ቀን የሚከበረው እስራኤልን ከግብጽ ባርነት እየመራቸው ማውጣቱን ለማዘከር ነው፡፡ ይህም የሆነው ያዕቆብ በረሃብ 70 ኹኖ ወደ ግብፅ ከወረደ በኋላ በ215 ዓመታት (አብርሃም ወደ ግብፅ በተሰደደ በ430 ዓመታት) በኋላ፤ የዮሴፍን ዝና ያልሰማ ፈርኦን በግብፅ ነገሠ፡፡  እስራኤል ከእኛ ይልቅ በዝተዋል ጠላቶቻችን ቢነሱብን ተደርበው ያጠፉናል በማለት አገዛዝ አጸናባቸው ፍርድ አጓደለባቸው፡፡ የእስራኤል ሴቶች ልጅ ሲወልዱ ወንድ ከሆነ እንዲገደል በማድረግ መከራ አጸናባቸው፡፡ 430 ዘመን በባርነት ከቆዩ በኋላ ከእብራውያን ወገን የሆነችው ራሔል ጭቃ እያቦካች ምጥ በያዛት ጊዜ እንዲያሳርፏት ጠየቀች ግብጻውያን ግን የሕፃናቱ ደም ጡቡን ያጠነክራል እርገጭ  አሏት፡፡ ከመሐጸኗ የወጡ ሁለት መንትያ ልጆቿን እያየች ከጭቃ ጋር ረገጠች፡፡ ራሔልም አለቀሰች ስለ ልጆቿም መጽናናትን እንቢ አለች፡፡ የእስራኤል ንጉሥ ሆይ የሆነብንን እይ ስትል ራሷን ይዛ ታለቅስ ጀመር እንባዋንም ወደ ሰማይ ንጉሥ ወደ እግዚአብሔር ረጨች፡፡ የራሔል እንባ የሕዝበ እስራኤል ሁሉ ጩኸት እሮሮ ይዛ ቅድመ እግዚአብሔር ደረሰች፡፡ “. . . ራሔል ስለ ልጆቿ አለቀሰች የሉምና ስለ ልጆቿ መጽናናት እንቢ አለች” /ኤር 31፥5፤ ማቴ 2፥17/ እንዲል፡፡ ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር ሙሴን አስነሳና፤ በሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል መሪነት፤ 10 ተዓምራትን በምድረ ግብፅ በ11ኛ ተዓምር ደግሞ በኅዳር 12 (ፈርዖንን ከነሠራዊቱ በኤርትራ ባሕር አስጥሞ) ድል በማድርግ ወደ ተስፋይቱ ምድረ መራቸው፡፡  ባሕረ ኤርትራን እስራኤላውያን እንደተሻገሩም የእስራኤል ልጆች የሙሴ የአሮን እኅት ማርያም ከበሮ እየመታች ንሴብሆ ለእግዚአብሔር ስቡሐ ዘተሰብሐ እግዚአብሔር ተዋጊ ነው ስሙም እግዚአብሔር ነው እያሉ ጠላታቸውን የመታላቸውን እነሱንም በተአምራቱ ያሻገራቸውን ከጠላታቸው እጅ ያዳናቸውን እግዚአብሔርን አመሰገኑ፡፡ ከዚህ በኋላ መጋቢ ብሉይ ቅዱስ ሚካኤል እየመራቸው መና ከሰማይ እያወረደላቸው ውሃ ከጭንጫ እያፈለቀላቸው ቀኑን በደመና ሌቱን በብርሃን መርቷቸው አርባ ዘመን ተጉዘው የቃል ኪዳን አገራቸው ምድረ ርስት ከነዓን ገብተዋል፡፡ /ዘጸ 15/ ከሙሴ በኋላ እስራኤልን የመራው ነቢዩ ኢያሱም እስራኤልን በሚመራበት ጊዜ ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል እስራኤልን ይረዳቸው ነበር፡፡ ከጠላቶቻቸው ጋር ሲዋጉም ሰልፉን ይመራ የነበረው ቅዱስ ሚካኤል ነበር፡፡ ለምሳሌ እስራኤላውያን ከኢያሪኮ አጠገብ በነበሩበት ጊዜ ቅዱስ ሚካኤል ተገልጦ ኢያሱን አነጋግሮታል፡፡ ኢያሱ በኢያሪኮ አጠገብ ሳለ ቀና ብሎ ሲመለከት የተመዘዘ ሰይፍ በእጁ የያዘ አንድ ሰው ከፊቱ ቆሞ አየ፤ ኢያሱም ወደ እርሱ ቀርቦ “ከእኛ ወገን ነህ ወይስ ከጠላቶቻችን?” ሲል ጠየቀው፡፡ እርሱም “አይደለሁም ነገር ግን የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ በመሆኔ መጥቻለሁ” ብሎታል /ኢያሱ 5፥13-15/፡፡ ይህ የተመዘዘ ሰይፍ ይዞ ከኢያሱ ፊት ለፊት የቆመው መልአክ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡ ይህን ለአብነት አነሣን እጅ እስራኤል በሚበድሉበት ጊዜ ሁሉ ወደ እግዚአብሔር የሚማልድላቸው ይህ ታላቅ መልአክ መጋቢ ብሉይ ቅዱስ ሚካኤል ነበር፡፡ እግዚአብሔር አምላክ በእደ መልአኩ ይጠብቀን፤ ከበዓሉ በረከት ይክፈለን፡፡                               #በአዲስ_አበባ_የሚከብርባቸው  #፵፬ ገዳማትና_አድባራት እነሆ፡፡ ፩. የካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (በኦሪት ዘመን መሥዋዕተ ኦሪት ይሰዋበት የነበረ፥ ዋሻ ቤተ ክርስቲያኑ በ4ኛው ክ/ዘመን በአብሃ ወአጽብሃ ዘመን የተመሠረተ) ፨አድራሻው፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ሾላ መገናኛ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(4 ኪሎ) → ሾላ መገናኛ፤ ፪. አንቀጸ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (ራስ ካሳ ሚካኤል) (ጭቁኑ)፤ ፨አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ራስ ካሳ ታክሲ፤ ከ4ኪሎ(ከ6 ኪሎ) → ፈረንሳይ፡፡ ፫. ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (አዲሱ ሚካኤል) ፨አድራሻ፤ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ፥ አውቶቡስ ተራ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(4ኪሎ) → አውቶቡስ ተራ፡፡ ፬. አፍሪካ ኅብረት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (ወህኒ ቤት) (ከርቸሌ) ፨አድራሻ፤ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ፥ ቡልጋርያ (ከርቸሌ) (አፍሪካ ኅብረት)፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ቄራ፡፡ ፭. ኮተቤ (ሲኤምሲ) ደብረ ጽባሕ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ /ሳጠራው/ (ቀድሞ ኮተቤ አሁን ሲኤምሲ) ፨አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ካራ አሎ ፥ አባዶ አጠገብ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ሲኤምሲ፡፡ ፮. መካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ መካኒሳ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → መካኒሳ፡፡ ፯. ላፍቶ ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ላፍቶ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ላፍቶ፡፡ ፰. ቤተል ደብረ ኢዮር ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ቤተል፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ጦር ኃሎች → አየር ጤና፡፡ ወይም፤ ከፒያሳ ሸዋ ዳቦ ቤት → አለም ባንክ/ኤር ጤና/፡፡ ፱. ኤረር በር መካነ ሰላም ቅዱስ ሚካኤልና ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ጎሮ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ (ፒያሳ) → ጎሮ፡፡ ፲. መንበረ ክብር ቅዱስ ሚካኤል ወአቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅድስት አርሴማ ገዳም፤ ፨አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ ቀጨኔ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(ከመርካቶ)(ከአዲሱ ገበያ) → ቀጨኔ፡፡ ፲፩. አያት ጨፌ ኢያሪኮ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ (በ1980ዓ.ም ጽላቱ ከነ ድርሳናቱ ተቀብሮ የተገኘበት) ፨አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ወረዳ 9፥ ጎሮ ሰፈር፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ጎሮ፡፡ ፲፪. ካራ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ሚካኤል፥ 24ቱ ካህናተ ሰማይና ማርያም ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አባዶ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → አባዶ ፲፫. ቦሌ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ቦሌ ሚካኤል፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ቦሌ ሚካኤል፡፡ ፲፬. የካ አባዶ ገ/አ/ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አባዶ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → አባዶ ፲፭. ምሥራቀ ፀሐይ ዳንሴ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ ፨አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ወረዳ 10 ከጉራራ ከፍ ብሎ፤ ታክሲ፤ ከጊዮርጊስ (4 ኪሎ) (6 ኪሎ) → ፈረንሳይ → ጉራራ፡፡

ኅዳር 11 #የክርስቶስ_አያት #ቅድስት_ሐና በዚህችም ቀን ፀሐይን እና ጨረቃን ለሚገዛ፣ ሰውን በአርያውና በመልኩ ለፈጠረ ፈጣሪያችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ #አያት የሆነች፤ ለእመቤታችን ለቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያምም #እናቷ የሆነች የተመሰገነች እና የከበረች #ቅድስት_ሐና ዕረፍቷ ነው፡፡ #ቅድስት_ሐና በኢየሩሳሌም ከሌዊ ነገድ ከካህኑ አሮን ትውልድ የሌዊ የሚልኪ ልጅ ለሆነው ማጣት ለተባለ ሰው ልጁ ናት፡፡ #ማጣትም 3 ልጆች አሉት፤ እነርሱም፦ 1) የመጀመሪያይቱ ስሟ ማርያም ነው፤ አዋላጅ የነበረች ስትሆን ቅድስት ሰሎሜን ወልዳለች፤ ሰሎሜም እመቤታችን መድኃኒታችንን ከወለደችው ጀምሮ በስደቷም ወራት ከአረጋዊ ዮሴፍ ጋር እመቤታችንን ያገለገለቻት ናት፡፡ 2) ሁለተኛይቱ ስሟ ሶፍያ ነዉ ፤ ይህቺ ቅድስት ለመጥመቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እናት የሆነችውን ቅድስት ኤልሳቤጥን ወለደች፡፡ 3) ሦስተኛይቱም ስሟ ሐና ነው፤ ይህች ቅድስት ሐናም የአምላክን እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ወለደቻት፡፡ ቅድስት ሰሎሜ፣ ቅድስት ኤልሳቤጥ እና እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የእኀትማማች ልጆች ናቸው፡፡  የሐና ወላጆች ልጃቸውን በሥርዓት አሳደጓት፡ለአካለ መጠን ስትደርስም ከይሁዳ ነገድ ለሆነ ጻድቅ ስሙም ኢያቄም የተባለውን ጻድቅ ሰው አጋቧት፡፡ ሐና ግን ልጅ መውለድ አልቻለችም ነበር፡፡ ከዕለታት አንድ ቀንም ቅድስት ሐና ርግቦች ከልጆቻቸው ጋር ሲጫወቱ ተመልክታ «ፈጣሪዬ ሆይ! የእንስሳትን ማኅፀን የምትከፍት ዕፅዋትንም ከባሕርያቸው እንዲያፈሩ የምታደርግ እውነትም ሐናን ድንጋይ አድርገህ ፈጥረሃታልን?» ስትል አለቀሰች። ቅዱስ ኢያቄምም ወደ ተራራ ወጥቶ ለዐርባ ቀናት አለቀሰ። ይህ ሲሆን ሁለቱም አርጅተው ነበር። ፈጣሪ ልጅ ከሰጣቸው ለቤተ እግዚአብሔር አገልጋይ እንዲሆን ለመስጠት ስእለት ተሳሉ፡፡ በሐምሌ ፴ ቀን ኢያቄም ለሐና ራእይ አየ፤ ነጭ ርግብ ፯ቱን ሰማያት ሰንጥቃ ወርዳ በራሷ ስታርፍ በቀኝ ጆሮዋ ገብታ በማኅፀኗ ስታድር አየ፤ ሐናም ለኢያቄም <<ፀምር ሲያስታጥቁህ መቋሚያህ አብባ አፍርታ ፍጥረት ሁሉ ሲመገባት አየሁ>>  ብላ ነገረችው፡፡ ከዚህም በኋላ በነሐሴ ፯ በዕለተ እሑድ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ፀነሰቻት፤ ይህም ለእነርሱም ለወገኖቻቸውም ታላቅ ተድላ ሆነ። ብፅዕት ሐና ግን ፈጣሪዋን ታከብረው ዘንድ በጐነትንና ንጽሕናን አበዛች። ፀንሳ ሳለም ዕውራንን አበራች፤ ድውያንን ፈወሰች። የጦሊቅ ልጅ በሞተ ጊዜም እያለቀሰች ስትዞረው ጥላዋ ቢያርፍበት አፈፍ ብሎ ተነሥቶ፦ «ሰላም ለኪ እሙ ለፀሐየ ጽድቅ» ብሎ ድንግል ማርያምን «ወሰላም ለኪ እምሔውቱ ለዘገብረ ሰማየ ወምድረ» ብሎ ቅድስት ሐናን አመስግኗል። ትርጉሙም ድንግልን «የፀሐየ ጽድቅ እናቱ» ሐናን «ሰማይና ምድርን ለፈጠረ አያቱ» ማለት ነው። ይህንን ያዩ አይሁድ ቅድስት ሐናን ሊገድሉ ብዙ ጊዜ ሞክረዋል። ነገር ግን መልአከ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል አልፈቀደላቸውም። ቅድስት ሐናም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን በፀነሰች በ፱ኛው ወር ግንቦት ፩ ቀን ነቢያት የተናገሩት ትንቢት ይፈጸም ዘንድ በአምስት ሺህ አራት መቶ ሰማንያ አምስት ዓመተ ዓለም በፈቃደ እግዚአብሔር ወለደቻት። ይህችም ቅድስት ሰማይና ምድርን ለፈጠረ ማደሪያ ትሆን ዘንድ እግዚአብሔር አምላክ ለመረጣት ከፍጥረት ሁሉ የተለየችና የከበረች ቅድስት ድንግል ማርያምን ለመውለድ የተገባች ሆናለች፡፡ ቅድስት ሐና ልጇ ሦስት ዓመት እስኪሆናት ከክንዷ አውርዳት አታውቅም ነበር። አንድ ጊዜም መላእክት ወስደውባት ፍጹም አልቅሳለች። ከዚህም ግን መልሰውላታል። ነገር ግን ስእለታቸውን የሚሰጡበት ጊዜ በደረሰ ጊዜ ሳይሰስቱ ለእግዚአብሔር ቤት እንድታገለግል ሰጧት፤ ቅድስት ሐናም ድንግል ማርያም ወደ ቤተ መቅደስ ከገባች በኋላ የእናትነት ፍቅሯ እያገበራት ለአምስት ዓመታት እየተመላለሰች ትጐበኛት ትስማትም ነበር። እመቤታችን ስምንት ዓመት በሞላት ጊዜ ግን የእግዚአብሔር ጥሪ ወደ ቅድስት ሐና ደረሰ። ከክርስቶስ ልደት ስምንት ዓመታት አስቀድማ ብፅዕት እናት ቅድስት ሐና በኅዳር ፲፩ ቀን ዐረፈች። በጌታ የዘር ሐረግ ውስጥ የተቆጠሩ ሁሉ ክቡራን ናቸው የመጨረሻዎቹ አያቶቹ ደግሞ የመጨረሻው ክብር ይገባቸዋል እነርሱም ሐና እና ኢያቄብ ናቸው፤ አምላካችንን የልጅ ልጃችን ነው ለማለት ተገብተዋልና። ቅድስት ሐና ከሴቶች ሁሉ የምትከብርና የምትበልጥ መሆኗን አምላክን ለወለደችልን ለቅድስት እናታችን ድንግል ማርያም እናት ሆና አይተናል፤ ከሴቶች ሁሉ የሚበልጥ ትሩፋትና ተጋድሎ ባይኖራት ይህ ጸጋ ባልተገባት ነበር፡፡ አባቶችም ታጋድሎዋ እጅግ ብዙ እንድሆነ ነግረውናል፡፡ ምልጃዋ አይለየን፤ ከበዓሉ በረከት ያሳትፈን፤ አሜን! ሃገራችንን ቅድስት ኢትዮጵያን እና ቅድስት ቤተክርስቲያናችንን ትጠብቅልን አሜን!      አርኬ ሰላም ለኪ ለጸሎተ ኵሉ ምዕራጋ፡፡ ከመ አስካለ ወይን ዲበ ሐረጋ፡፡ ሐና ብፅዕት ተፈሥሒ እንበለ ንትጋ፡፡ እስመ ረከብኪ ሞገሰ ወአድማዕኪ ጸጋ፡፡ እምሔውተ አምላክ ትኵኒ በሥጋ፡፡ በቦታው ሄዳቹ በዓሉን ማክበር ለምትፈልጉ (ፎቶዎቹ፤ በአዲስ አበባ እና በሌሎች የሚገኙ የቅድስት ሐና አብያተ ክርስቲያናት እነሆ ...) 👉 ኮተቤ መካነ ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና ቤ/ክ 👉 ፉሪ መንበረ ንግስት ቅድስት ሐና ቤ/ክ 👉 ደብረ ንግስት መንዝ ቅድስት ሐና 👉 በድሬዳዋ ሀገረ ስብከት በደብረ መንክራት ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን በድርብነት ትገኛለች ሌሎች በዓሉ የሚከብሩባቸውን ቦታዎች  ኮሜንት ላይ ያጋሩን /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚዲያ እና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ክፍል የተዘጋጀ/ #share ፨Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchoolYouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2wTelegram https://t.me/FinotehiwottTiktok http://tiktok.com/@finotehiwotWebsite www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like

የ2018 ዓ.ም የጥቀት በዓል በጃንሜዳ ተረኛ አዘጋጅ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም እና ደብረ ትጉኀን ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ን
የ2018 ዓ.ም የጥቀት በዓል በጃንሜዳ ተረኛ አዘጋጅ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም እና ደብረ ትጉኀን ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ን

፪. #ገዳመ_አባ_ጽጌ_ድንግል_ገዳም_፤ አድራሻው፤ ደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ → ወግዲ → ገዳመ ጽጌ፤ ወይም፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎጃም (በመርጡለ ማርያም) → መካነ ሰላም ወግዲ → ገዳመ ጽጌ፤ ወይም፤ ከአ.አ. ቦሌ መርካቶ አውቶቡስ ተራ → መርሐ ቤቴ ወግዲ → ገዳመ ጽጌ፡፡ ፫. #አምባ_ጽጌ_ድንግል_ገዳም፤ አድራሻው፤ ዋግኽምራ ሀገረ ስብከት፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ላሊበላ → ሰቆጣ (ዋግኽምራ)፡፡ ፬. #ጎንደር_ደብረ_ፀሐይ_ቊስቋም_ማርያም_ቤ/ክ፤ አድራሻው፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፥ ቸቸላ (ሆስፒታል አጠገብ)፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር ከተማ → ሆስፒታል → ቊስቋም፤ ፭. #ደሴ_ቊስቋም_ማርያም_ቤ/ክ፤ አድራሻው፤ ደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት፥ ደሴ ከተማ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ ከተማ፡፡ #ከኢትዮጵያ_ውጭ_የሚከብርባቸው_ #፩ #ጥንታውያን_ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. #ግብፅ_ቊስቋም _ማርያም_ገዳም_፤ (#እስከ_ቅርብ_ዘመናት_በግብፅ_የኢትዮጵያ_ርስት_የነበረ_) አድራሻው፤ ግብፅ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ → ግብፅ → ገዳመ ቊስቋም፤ • Facebook 👉 https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 https://t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 http://tiktok.com/@finotehiwot • YouTube 👉 https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#ኅዳር_6፤ ደብረ ቊስቋም፤ #እመቤታችን_ከልጇ_ጋር_ስደትን_የጀመረችበት_ዕለት_ነው፡፡ **ድንግል ማርያም ከልጇና ከአረጋዊ ቅዱስ ዮሴፍ ጋርለ3 ዓመታት ከ6 ወራት (ወይም ለ42 ወራት) (1275 ቀናት) ከተሰደደች በኋላ #ግንቦት_24_ደግሞ_በዓተ_ግብጽ_ (ወደ ግብጽ ወደ ደብረ ቊስቊም ገብታ ያረፈችበት ቀን ነው)። ዖፍኒ ረከበት ላቲ ቤተ፤ ወፍም ቤቷን ሰራች፡፡ መዝ. ፹፫፥፫ ንጉሥ ተወልዷል መባሉን የሰማው ሔሮድስ 144,000 ሕጻናትን ሲፈጅ በቅዱስ ገብርኤል ትዕዛዝ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አንድ አምላክ ልጇን አዝላ፤ በአንዲት አህያ ላይ ተቀምጣ፤ ጥቂት ስንቅ ቋጥራ፤ ከዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር ስደት ወጣች፡፡ ከገሊላ ተነሥታ በጭንቅ፣ በመከራ፣ በረሃብና በጥም፣ በሐዘንና በድካም፣ በእንባ ተጕዛ በዚህች ቀን ምድረ ግብፅ ገብታ በሥደት እጅግ ብዙ መከራ ተቀብላለች:: † የአምላክ እናቱ እሳትን አዝላ በብርድ ተንገላታለች:: † ለእኛ የሕይወት እንጀራን ተሸክማ እርሷ ተራበች:: † የሕይወትን ውሃ ተሸክማ ተጠማች:: † የሕይወት ልብስን ተሸክማ ተራቆተች:: † የሕይወት ፍስሐን ተሸክማ አዘነች:: † እመ አምላክ ተራበች፣ ተጠማች፣ ታረዘች፣ ደከመች፣አዘነች፣ አለቀሰች፣ እግሯ ደማ፣ ተንገላታች::      ለሚገባው ይሕ ሁሉ የተደረገው ለእኛ ድኅነት ነው:: በእውነት ይህንን እያወቀ ለድንግል ማርያም ክብር የማይሰጥ ሰይጣን ብቻ ነው:: አራዊት: ዕፀዋትና ድንጋዮች እንኳን ለአመላክ እናት ክብር ይሰጣሉ:: አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍና ቅድስት ሰሎሜ ደግሞ የክብር ክብር ይገባቸዋል:: ከአምላክ እናት ከድንግል ማርያምና ከቸር ልጇ ጋር መከራ መቀበልን መርጠዋልና:: #መድኃኔ_ዓለም_ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ_ለምን_ተሰደደ? #ለምን_ስደቱን_ወደ_ግብፅና_ኢትዮዽያ_አደረገ? 1. ፠ትንቢቱን ይፈጽም ዘንድ:: በፈጣን ደመና ወደ ግብፅ እንደሚወርድ ተነግሯልና(ኢሳ 19፥1፣ ዕን. 3፥7) 2. ፠ምሳሌውን ለመፈጸም፤ የሥጋ አባቶቹ እነ አብርሃም፥ ያዕቆብ (እሥራኤል):፥ ኤርምያስ ወደዚያው ተሰደዋልና:: 3. ከግብፅ ጣዖት አምልኮን ያጠፋ ዘንድ:: (ኢሳ. 19፥1) 4. የግብፅና የኢትዮዽያ ገዳማትን ይቀድስ ዘንድ:: 5. ሰው መሆኑ በአማን (በእውነት) እንጂ ምትሐት እንዳልሆነ ለማጠየቅ:: (ሰው ባይሆን ኑሮ አይሰደድም ነበር:: ሔሮድስ ቢያገኘው ደግሞ ሊገድለው አይችልም:: ያለ ፈቃዱና ያለ ዕለተ ዐርብ ደሙ አይፈስምና:: 6. ስደትን ለሰማዕታት ባርኮ ለመስጠት:: እና 7. የአዳምን ስደት በስደቱ ለመካስ ነው::      እመ ብርሃን ድንግል ማርያም ለ3 ዓመታት ከ6 ወራት (ወይም ለ42 ወራት) (1275 ቀናት) በስደት የቆየችባቸው ቦታዎች አሉ:: ፠ በመጀመርያ ድንግል ማርያም ከርጕም ሔሮድስ ስትሸሽ መጀመሪያ የሔደችው ከገሊላ ወደ ሶርያ ደንበር (ደብረ ሊባኖስ) ነበር:: በዚያም የሸሸጋት ቅዱስ ጊጋር መስፍኑ በሔሮድስ ሲገደል ወደ ምድረ ግብጽ ወረደች፡፡ ፠ በግብጽም ለብዙ ጊዜ ከአንዱ ወደ ሌላው ስትሸሽ ቆየች:: ‹‹እንዘ ከመ በግዕት ግድፍት አመ ሳኮይኪ ውስተ ምድረ በዳ፡፡›› እንዲል:: (እሴብሕ ጸጋኪ) ፠ ቀጥላም በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ገብታ ደብረ ቢዘን ላይ (አሁን ኤርትራ ውስጥ ነው) ዐረፈች፤ ፠ ከደብረ ቢዘን ደብረ ሐዊ፣ በደብረ ዳሞ፣ አኵሱም፣ ደብር ዐባይ፣ ዋልድባ አድርጋ እየባረከች ቆይታለች፤ ፠ በዋልባም ቆይታቸው ልጇ ገዳሙን በኢትዮጵያ በብጨኝነት ራሱ የገደመውን ገዳም መሥርቶ እየባረከ ወደ ጣና ሄደዋል፡፡ ፠ በጣና ገዳማትም፤ በተለይ በጣና ቂርቆስ ለ100 ቀናት ቆይታ ቀጥታ በጐጃም ወደ ሸዋ ሔዳ ደብረ ሊባኖስን ቀድሳለች:: ፠ ቀጥላም እስከ ደብረ ወገግና ደብረ ሐዘሎ ደርሳለች፤ በእግሯ ያልደረሰችባቸውን የሀገራችን ክፍሎች በደመና ተጭና ዐይታ ባርካቸዋለች፡፡ ፠ በደብረ ኤረር ተራራ ላይም ከልጇ ኢትዮጵያን በዐሥራትነት ተቀብላለች፡፡ ሔሮድስ መሞቱን መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል የነገራትም እዚሁ ኢትደዮዽያ ውስጥ መሆኑን ትውፊት ያሳያል::      እመቤታችን የሄሮድስን ሞት ከሰማች በኋላ ቊስቋም ከሚባል ተራራ ላይ ሆና ደስታዋን አብረዋት መከራን ከተቀበሉት ከዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር አከበረች፡፡ ከሃገራችን ሰዎች (ከሰብአ ኦፌር) የተቀበለችውን ስንቅና ስጦታ በ5 ግመሎች ጭና ከቅዱሳኑ ዮሴፍና ሰሎሜ ጋር ኅዳር 6 ቀን ቊስቋም ውስጥ ገብተው ከድካም ዐርፈዋል፤ ሐሴትንም አድርገዋል:: ***ኅዳር 5 ለኅዳር 6 ከዋይዜማው ጀምሮ የሚባለውን ሙሉ ሥርዐተ ማኅሌትም እነሆ ብለናል፤ መልካም የማኅሌት ሌሊት ይሁንልን፡፡ #የቊስቋም_ክብረ_በዓልን_በየት_ሊየከብሩ_ዐስበዋል??? #በመላው_ዓለም_የቊስቋም_ክብረ_በዓል_የሚከበርባቸው_ #፲፬ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ (ሌሎች ያልጠቀስናቸው አብያተ ክርስቲያናት ካሉ አሳውቁን) #በአዲስ_አበባ_የቊስቋም_ክብረ_በዓል_የሚከበርባቸው_ #፰ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. #መንበረ_ንግሥት_ቊስቋም_ማርያም_ቤ/ክ_፤ (#፫፻፷፭ት #ቀናት_ሙሉ_ዝክር_በማኅበረ_ሰላም_መድኀኔዓለም_የሚዘከርባት_ቤ/ክ) አድራሻው፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ እንጦጦ፥ ቊስቋም፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ/ጊዮርጊስ  (መርካቶ) (4 ኪሎ) → ሽሮሜዳ (መነን) → ቊስቋም፤ ፪. #ደብረ_ናዝሬት_ቅዱስ_ዮሴፍ_ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክለ ከተማ፥ ደጃዝማች መርዕድ መንገድ፥ ቀለበት መንገድ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) (ከላጋር) (ከ4 ኪሎ) → ቦሌ → ሳሪስ /ቃሊቲ ቀለበት መንገዱ ላይ/ ወይም፤ ከሳሪስ አቦ → ቦሌ /በቀለበት መንገድ/ ፫. #ቃሊቲ_ደብረ_ገነት_ቅዱስ_ሚካኤልና_ደብረ_ቊስቋም_ማርያም_ቤ/ክ፤ (ቃሊቲ ቊስቋም) አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክለ ከተማ፥ ሰፈረ ገነት፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) (ከላጋር) (ከ4 ኪሎ) → ቃሊቲ መናኸሪያ → ሰፈረ ገነት ወይም፤ ከሳሪስ አቦ → ቦሌ /በቀለበት መንገድ/ ፠፨፠ #እንዲሁም_በድርብነት_የሚከበርባቸው_፤ ፬. #ኮልፌ_ደብረ_ብርሃን_ቅድስት_ሥላሴ_ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ዊንጌት፥ ጠሮ፥ አራት መንታ፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ/አቡነ ጴጥሮስ ዐደባባይ/ → ዊንጌት → ጠሮ፡፡ ወይም፤ ከመርካቶ ኮልፌ አጣና ተራ → ጠሮ ፭. #ማኅደረ_መለኮት_ወይብላ_ቅድስት_ማርያም_ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ የሺ ደበሌ፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መርካቶ) → የሺ ደበሌ፡፡ ፮. #ላፍቶ_ደብረ _ኢያሪኮ_መድኀኔ_ዓለምና_መጥምቀ_መለኮት_ቅዱስ_ዮሐንስ_ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ላፍቶ ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ሜክሲኮ → ላፍቶ፡፡ ፯. #መዝገበ_ምሕረት_ፋኑኤልና_ቊስቋም_ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ካራ ፥ አጀንባ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ ሸዋ ዳቦ ቤት (ከሜክሲኮ) → አየር ጤና → ካራ፡፡ ፰. #ጉለሌ_ሸጎሌ_ኪዳነ_ምሕረት_ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ አዲሱ ገበያ ፥ ቶታል፥ ጉለሌ ዕፅዋት ማዕከል (ወደ ዊንጌት በቀለበት መንገገዱ ትንሽ ሄደው)፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (አስኮ) → አዲስ ገበያ /ጸዮን ሆቴል/፤ #በኢትዮጵያ_ደረጃ_የሚከብርባቸው_ #፭ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. #ደብረ_ፀሐይ_ፋርጣ_ቊስቋም _ቤ/ክ፤ (በ1254 ዓ.ም. የተመሠረተች) አድራሻው፤ ደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ/ወልድያ → ፋርጣ፡፡ ወይም፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ባሕር ዳር → ወረታ → ፋርጣ፤

በምሥራቅ አርሲ የኦርቶዶክሳውያን ግድያ እና የወጣቶች አፈና አሁንም ተባብሶ እንደቀጠለ የአካባቢው ምእመናን ገለጹ። ዛሬ ኅዳር 01 ቀን 2018 ዓ.ም ልዩ ቦታው ጠለታ ቅዱስ ገብርኤል በተባለ አካባቢ
በምሥራቅ አርሲ የኦርቶዶክሳውያን ግድያ እና የወጣቶች አፈና አሁንም ተባብሶ እንደቀጠለ የአካባቢው ምእመናን ገለጹ። ዛሬ ኅዳር 01 ቀን 2018 ዓ.ም ልዩ ቦታው ጠለታ ቅዱስ ገብርኤል በተባለ አካባቢ ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ገደማ ሦስት ኦርቶዶክሳውያን በአውድማ ላይ እህል እየወቁ ባሉበት በጥይት ተደብድበው በግፍ መገደላቸው ከአካባቢው የደረሰን መረጃ ያመላክታል ። ከተገደሉት ምእመናን መካከል ዲ/ን ኢዮብ እጅጉ፣ ጥላሁን ቦጌ እና ሕፃን ጻድቃኔ ሠራዊቱ የተባሉ ኦርቶዶክሳውያን ይገኙበታል ። ሥርአተ ቀብራቸው በጠለታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ዛሬ ኅዳር 01 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ላይ ተፈጽሟል። በተጨማሪም ከዚህ ቀደም በነበሩ የኦርቶዶክሳውያኑ አፈናና ግድያን በተመለከተ መረጃ አቀብላችኋል በሚል ምክንያት የአካባቢው ወጣት ምእመናን ወዳልታወቀ ሥፍራ ታስረው እየተወሰዱ እንደሚገኝ ምእመናኑ ለማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ተናግረዋል። በሥፍራው ላይ የጸጥታ ኃይል ቢኖርም ኢ-ሰብአዊ ድርጊቱ ፣ አፈናና ግድያውም ተባብሶ መቀጠሉን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል ። ስለጉዳዩ ተጨማሪ መረጃ ለመጠየቅ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን መዋቅር ወደ ሆነው የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ እና የዞኑ የጸጥታ ዘርፍ ኃላፊ የእጅ ስልክ ላይ በተደጋጋሚ ብንደውልም ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ ሳይሳካ ቀርቷል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በአሁኑ ሰዓት ሴቶች እና ሕጻናት አካባቢውን ለቀው እሬቻ ወደሚባል ቦታም እየሸሹ እንደሆነ የደረሰን መረጃ ያመላክታል። ©️ የማኅበረ ቅዱሳን ፍኖተ ሕይወት ሚዲያ • Facebook 👉 https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 https://t.me/finotehiwott

#ፎቶዎቹ ፤ እመቤታችን ከልጇ ጋር ያረፈችበት ገዳመ ቊስቋም ማርያም ገጽታ የሚያሳዩ ___ ደብረ ቁስቋም በደቡብ ግብፅ የሚገኝ ተራራ ነው፡፡ ደብረ ቁስቋም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን እንዲሁም ቅዱስ ዮሴፍንና ቅድስት ሰሎሜን ይዛ ከስደት ሲመለሱ ያረፉበት ቦታ ነው፡፡ ይህም ‹‹ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ግብፅ ሽሽ›› ባለው መሠረት የተፈጸመ ነው፡፡ (ማቴ. ፪፥፲፫-፲፭) የክርስቶስ ስደቱ ቀድሞ በነቢዩ ኢሳይያስ ‹‹. . . እነሆ፥ እግዚአብሔር በፈጣን ደመና ተቀምጦ ወደ ግብፅ ይመጣል፡፡ የግብፅም ጣዖታት በፊቱ ይዋረዳሉ›› ተብሎ በተነገረው መሠረት የተፈጸመ ነው፡፡ ነቢዩ ፈጣን ደመና ያለው ጌታችን በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ጀርባ ላይ ሆኖ ወደ ግብፅ መውረዱን ለመግለጽ ነው፡፡ ፈጣን ደመና የተባለችውም እመቤታችን ነች፡፡ (ኢሳ. ፲፱፥፩) በስደቱም ጣዖታተ ግብፅ እየተሰባበሩ ሲወድቁ፤ በእነርሱም አድረው ሰውን ሲያስቱ የነበሩ አጋንንትም ሲሸሹ ታይተዋል፡፡ ደግሞም ጌታችን ዳግማዊ አዳም ነውና በምክረ ከይሲ (ዲያብሎስ) ምክንያት ተሰዶ የነበረው ቀዳማዊ አዳምን ለመካስ ተሰደደ፤ በዚህም አጋንንትን ከሰው ልቦና አውጥቶ አሳደደ፡፡ እመቤታችንም ልጇን ይዛ ከስደት ስትመለስ ያረፈችበትን ተራራ ደብረ ቁስቋምን ባረከችው ቀደሰችውም፤ ይህ ተራራ የተቀደሰ ተራራ ስለመሆኑ የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ታኦፊሎጎስ በድርሳነ ማርያም እንዲህ አለ፤ ‹‹ይህም ከሀገሮቹ ሁሉ ተራሮች የሚበልጥ (የተለየ) ከፍ ያለ ተራራ ነው፡፡ በውስጡ ቅዱስ አግዚአብሔር ያድራል፡፡ ይህንን ተራራ የእግዚአብሔር ልጅ ወዶታል፤ አክብሮታልምና፤ ከዓለም ሀገሮች ሁሉ ከተቀደሰች እናቱ ጋር አድሮባታልና። ከመላእክት ቤት ያድር ዘንድ አልወደደም፤ ቢታንያንም አልመረጠም፡፡ ከተራራው ላይ ባለች ገዳም ቤት ውስጥ አደረ እንጂ፤ ነቢዩ ዳዊት፤ የጽዮንን ተራራ ወደደ፤ በአርያምም መቅደሱን ሠራ እንዳለ፡፡›› ‹‹አንተ ተራራ ሆይ የእግዚአብሔር ማደሪያ በሆንህ ጊዜ በኪሩቤልና በሱራፌል መካከል ፍጹም ደስታ ተደረገ፡፡ የመላእክት ሠራዊት ቅዱስ የሆነ ፈጣሪያቸውንና ጌታቸውን ይታዘዙ (ያገለግሉ) ነበር፡፡ አንተ ተራራ ሆይ ያደረብህ ጌታችን ስለሆነ ከተራሮች ሁሉ ከደብረ ሲናም ይልቅ ከፍ ከፍ አልህ፤ ጌታችን በደብረ ሲና ባረፈ ጊዜ ፍጹም ደስታ፣ ታላቅ ብርሃንም በሆነ ጊዜ መቅረብና መመልከት ከሙሴ በቀር የቻለ የለም፡፡ እርሱም ቢሆን ፊቱን ማየት አልቻለም፡፡ ሥጋ ለባሽ ሁሉ እርሱን ዐይቶ በሕይወት መኖር የሚቻለው የለምና፡፡ እኛ ግን አየን፤ ከዚህ ማደሩንም ተረዳን፤ ዳግመኛም ንጽሕት በሆነች በማርያም ዘንድ አየነው፡፡ ቅድስት ከሆነች ከእመቤታችን ማርያም ዘንድ በቤተልሔም ስለ እኛ በተዋሐደው ሥጋ በጨለማና በሞት ጥላ ሥር ያለን እኛን ከቸርነቱና ሰውን ከመውደዱ የተነሣ መጥቶ አዳነን፤ ከዓለም ሁሉ ይልቅ ጣዖትን በማምለክ ሲበድሉም ወደ ግብፅ ሀገር ወርዶ በእነርሱ ላይ የመለኮትነት ብርሃኑን በማብራት ታላቅ የሆነ ክብሩን ገለጠ››፡፡ (ድርሳነ ማርያም) ኅዳር ፮ ቀን የሚነበበው የመጽሐፈ ስንክሳር ክፍል ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግመኛም በኋላ ዘመን ሐዋርያትን በደብረ ቁስቋም ሰብስቦ፤ ታቦትንና ቤተ ክርስቲያኑን አክብሮ የቊርባን መሥዋዕትንም ሠርቶ ቅዱስ ሥጋው ክቡር ደሙን እንደ ሰጣቸው፤ እኛንም ለዚህ ክብር የበቃን እንሆን ዘንድ የእግዚአብሔር አምላክ ቅዱስ ፈቃድ ይሁንልን፤ አሜን። • Facebook 👉 https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 https://t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 http://tiktok.com/@finotehiwot • YouTube 👉 https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w