fa
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

رفتن به کانال در Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

کانال Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 333 مشترک است و جایگاه 5 639 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 190 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 333 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 15 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -80 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -1 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 22.23% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 10.47% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 409 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 605 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 22 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 16 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

15 333
مشترکین
-124 ساعت
-117 روز
-8030 روز
آرشیو پست ها
የጥቀምት 2 የማኅሌተ ጽጌ ዚቅ፤ በደብራችን ርዕሰ ደብር ጥሩነህ፡፡ 1) 1) መሥ- ለአፉክሙ… አሰርጎካ ለምድር-1 2) 2) ማኅ - ጽጌ አስተ… ናሁ አስተርአየ ጽጌ-1 3) 3) ማኅ- እንዘ ተሐቅ… ንዒ ርግብየ-1 4) 4) ማኅ - ክበበ ጌራ ወርቅ… ውድስት አንቲ-1 5) 5) ማኅ - ቅዳሴኪ ማርያም… አስተምሕር ለነ-1 6) 6) ሰቆ. በስመ እግዚ… እወ አማን-1

ሥርዐተ ማኅሌት ዘወርኀ ጽጌ (‹ዘላይ ወዘታች› ቤት) (፪ኛ ዙር ዓመት፤ ፩ኛ ሳምንት፥ጥቅምት ፪) በዓለ አባ ሕርያቆስ፡፡ የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/
+4
ሥርዐተ ማኅሌት ዘወርኀ ጽጌ (‹ዘላይ ወዘታች› ቤት) (፪ኛ ዙር ዓመት፤ ፩ኛ ሳምንት፥ጥቅምት ፪) በዓለ አባ ሕርያቆስ፡፡ የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት http://t.me/finotehiwott

✤✤ እንኳን ለማኅሌተ ጽጌ አደረሳችሁ፤ ምንም እንኳን በመጽሐፈ ገጽ (Facebook) ጽሑፎችን ማቅረብ ከጀመርን በርካታ ዓመታት ብናስቈጥርም፤  ለመጀመሪያ ጊዜ በመጽሐፈ ገጽ(Facebook) ፋና ወጊ ኾነን ሥርዐተ ማኅሌትን ይዘን መቅረብ ከጀመርን ግን 12ኛ ዓመታችን ኾነ፤ እንደ መድኀኔዓለም ፈቃድም ዘንድሮም 12ኛ ዓመታችን (የ2ኛ ዙር ዓመት ሙሉ የማኅሌተ ጽጌ ሥርዐተ ማኅሌትና በዓመት ውስጥ የሚገኙ የክብረ በዓላት ሥርዐተ ማኅሌትን ይዘንላችሁ እንቀርባለን፡፡) ✤ የማኅሌት ቁመት የላይ ቤትና የታች ቤት ኾኖ እንደየአድባራቱ ይትበሃል የሚቆም እንደመኾኑና ማኅሌተ ጽጌ በኹሉም አድባራት በደመቀ ኹኔታ ስለሚቆም የላይ ቤቱንም ኾነ የታች ቤቱን በአንድነት አቅርበንላችኋል፤ የላይ ቤት የምትቆሙ አድባራት ‹‹ዘግምጃ ቤት›› የሚለውን፤ የታች ቤት የምትቆሙ ‹‹ዘጎንደር በዓታ›› በሚል አስቀምጠንላችኋል፡፡ ደብራችን ቀጨኔ ደብረ ሰላም የላይ ቤት የሚቆምበት ደብር እንደመኾኑ ላይ ቤቱን እያስቀደምን ታች ቤቱን አስከትለን አስቀምጠናል፡፡ የላይ ቤት የሚቆምባቸው አድባራት የታች ቤቱን እየዘለሉ፤ የታች ቤት የሚቆሙ አድባራት የላይ ቤቱን እየዘለሉ እንዲጠቀመቡት ኹሉንም አዘጋጅተነዋል፡፡ የላይ ቤትና የታች ቤት በአንድነት የሚቆሙት ቀለም ሲኾን ግን ‹‹ዘግምጃ ቤት ወዘበዓታ›› ብለን አስቀምጠነዋል፡፡ /በማኅሌት በምትቆሙ ጊዜ በጸሎታችሁ ደብራችንን ደብረ ሰላምንና ሰ/ት/ቤታችንን ፍኖተ ሕይወትን እና በውስጧ ያሉ አገልጋዮቿን አስቡልን፡፡ ✤ ልዩ አዋጅ ዘወርኃ ጽጌ ✤ ✤ ወርኃ ጽጌ 40 ቀናት ነው፤ መስከረም 26 ተጀምሮ ኅዳር 5 ያልቃል፤ ጾመ ጽጌ የፈቃድ ጾም ነው፡፡ ✤ የማኅሌተ ጽጌና የሰቈቃወ ድንግል ደራሲ አባ ጽጌ ድንግል ነው፡፡ ገዳሙም ትልቅና ሰፊ የኾነ የፍልፍል ዋሻ ሲኾን ወሎ ወግዲ ወለቃ ወንዝ አጠገብ በረሃ ላይ (ከጋሥጫ ገዳም የ4 ሰዓት የእግር መንገድ) ይገኛል፡፡ ✤✤ በየዓመቱ ሳይመረገዱ ያመይታለፉ የማይቀሩ፤ ዚቃቸው የማይለወጥ፤ 1) ከማኅሌተ ጽጌ፦ ጽጌ አስተርአየ (የመጀመሪያው ሳምንት)፣ በከመ ይቤ መጽሐፍ፣ ትመስል እምኪ ማርያም፣ ዘኒ ስብሐተ ወዘኒ ማኅሌተ፣ ኢየሐፍር ቀዊመ ቅድመ ሥዕልኪ እና ኅብረ ሐመልሚል (የመጨረሻው ሳምንት)ናቸው፡፡ 2) ከሰቈቃወ ድንግል፦ በስመ እግዚአብሔር ሥሉስ፣ ብክዩ ኅዙናን፣ እስከ ማዕዜኑ እግዝእትየ እና አብርሂ አብርሂ ናቸው፡፡ ✤ ከማኅሌተ ጽጌ ውስጥ እንዘ ተሐቅፊዮ ለሕፃንኪ እና ክበበ ጌራ ወርቅ በየሳምንቱ (በኹሉም ዓመታት) ይመረገዳሉ፤ ዚቁ ግን በዓሉን በተመለከተ ይኾናል፡፡ ✤ ከላይ ካየናቸው ውጪ የሚገኙት የማኅሌተ ጽጌና የሰቈቃወ ድንግል ክፍሎች ግን በየሰባት ዓመት አንዴ ነው የሚመረገዱት፡፡ ✤ የማኅሌቱ ሥርዐት የላይ ቤት (የጎንደር መካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ማርያም አብነት) እና የታች ቤት (የጎንደር ደብረ ኀይል በዓታ ለማርያምን አብነት) የሚያደርግ ሲኾን፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ የማኅሌት ቁመትም የላይ ቤትን አብነት የተከተለ ሲኾን የዚቁ ወረብ ግን የደብሩን የራሱን (የሸዋን) የተከተለ ነው፤ ✤ የላይ ቤት ቁመት የሚቆሙ አድባራት ዘግምጃ ቤት የሚለውን እንዲከተሉ፤ የታች ቤትን ቁመት የሚቆሙ አድባራት ዘበዓታ የሚለውን እንዲከተሉ፡፡ የዚቁ ወረብን ግን የቀጨኔ ደብረ ሰላም የቤቱን ቀለም አስቀድመን ቀጥሎ ደግሞ ዓዲ (ወይም) በማለት የጎንደርን ስላስቀመጥነው እንደ ደብራችሁ ይትበሃል መርጣችሁ እንድትጠቀሙበት ኹሉንም አስቀምጠነዋል፡፡ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

#ነግሥ_ነግሥ_ነግሥ እንኳን ለመድኀኔ ዓለም ጥንተ ስቅለት ክብረ በዓል አደረሳችሁ፡፡ የመድኀኔ ዓለምን ክብረ በዓል በማስመልከት፤ በማንኛውም ወርኀዊና ዓመታዊ ክብረ በዓላት ላይ ማኅሌት ሲቆም፤ መጀመ
+5
#ነግሥ_ነግሥ_ነግሥ እንኳን ለመድኀኔ ዓለም ጥንተ ስቅለት ክብረ በዓል አደረሳችሁ፡፡ የመድኀኔ ዓለምን ክብረ በዓል በማስመልከት፤ በማንኛውም ወርኀዊና ዓመታዊ ክብረ በዓላት ላይ ማኅሌት ሲቆም፤ መጀመሪያ የሚባለውን ነግሥንና የነግሥ መቅድምን ለመጀመሪያ ጊዜ አዘጋጅተንላችኋል፡፡ *ነግሥ ምን ማለት ነው *ዚቅ ምን ማለት ነው *የነግሥ መቅድምና ነግሥ ቀመረ መረግድ፤ (ማንኛውም ማኅሌት ሲቆም ባለ 5 መስመር ግጥም ሲሆን እያንዳንዱ መስመር 28ት ጊዜ በከበሮና በጸናጽል ይመረገዳል ፤ የአመረጋገዱን ቅደም ተከተል እንዲቀላችሁ በማሰብ በቀመር (በቊጥር አስቀምጠንላችኋል፡፡) ከጽሑፉ ያገኟቸዋል፡፡ ይህን ነግሥ በሁሉም ማኅሌት መጀመሪያ የሚባል እንደመሆኑ መጠን በቃላችሁ አጥኑት፡፡ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/

እንኳን ለቅድስት አርሴማ ዓመታዊ ክብረ በዓል (በዓለ ዕረፈት) አደረሰን፥ አደረሳችሁ፡፡  በዚህች በመስከረም 29 ቀን አርሴማ ቅድስት ወሰማዕት እና የእርሷ ማኅበርተኞች ድል አድራጊዎች 27 ሰማዕታት በሰማዕትነት ያረፉባት ዕለት ነች፡፡ እግዚአብሔር ከእነዚህ ቅዱሳን ሰማዕታት ረድኤት በረከታቸውን ይክፈለን፡፡ እነዚህም ቅዱሳን፤ 1ኛ. #አርሴማ፤ #ቅድስት_ወሰማዕት_ኃያል_ተጋዳሊት_ 2ኛ. ኢያሚኖስ፤ ጸሎትን የሚያሳርግ ካህን 3ኛ. አፍጢኖስ፤ ከብዙዎች የተመረጠ 4ኛ. በርቲኖስ፤ ጻድቅና ቸር 5ኛ. ጢሞና፤ በመላላክ ሥራ አገልጋይ የኾነ 6ኛ. ጢሞዓና፤ ተአጋሽና ጸዋሚ 7ኛ. ዘኬዎስ፤ ከከበሩ የከበረ 8ኛ. እስጢፋኑ፤ ተጋዳይና የበደሉትን ይቅር ባይ 9ኛ. አርሞና፤ ከጎልማሶች ይልቅ ደም ግባቱና መልኩ ያማረ 10ኛ. ኪርያኮስ፤ ሥጋውን ያላረከሰ ንጹሕ 11ኛ. አንጥያኮስ፤ ቡሩክ የኾነ የአቡሪ ልጅ 12ኛ. ያዕቆብ፤ የእግዚአብሔር ታማኝ የኾነ 13ኛ. ቡራኬሌስ፤ በሰው ዘንድ ተወዳጅ የኾነ 14ኛ. አስቂርያቆስ፤ ክርስቶስን የሚወደው 15ኛ. አስኪርያኖስ፤ ባለሟል የኾነና ግርማው የሚያስፈራ 16ኛ. ሚርያኖስ፤ ፊቱና መልኩ ደስተኛ የኾነ 17ኛ. ትትግርጦስ፤ ወደ ንስሐ የተመለሰ 18ኛ. ያስቲኖስ፤ የሚፈርድና የሚበይን 19ኛ. ጥልያኖስ፤ ያላመኑ ሰዎችን የሚገስጽ 20ኛ. ዑልያኖስ፤ የዚህ ዓለም ጥበብ መምህር የኾነ 21ኛ. ጴርቅላስ፤ በስም አጠራርና በሽምግልና መልካም የኾነ 22ኛ. ኬብያኖስ፤ ተጋዳይ የኾነ 23ኛ. ጴጥሮስ፤ የጠራ የባሕርይ ዕንቊ 24ኛ. ጰኵንዮስ፤ የሮምያ ሹም 25ኛ. ሐናንያ፤ የዋህና ሽንገላ የሌለው 26ኛ. ሐሊባኖስ፤ ጾምና ጸሎትን የሚወድ 27ኛ. ኤስያኖስ፤ በመንፈስ ቅዱስ ጎልማሳ የኾነ 28ኛ. ኤልያብ፤ በረኛና የሰማዕት መጀመሪያ፡፡ ሰላም ለፀዐተ ነፍስኪ በጊዜ ኃለፈ ሰይፍ፤ መንገለ ክሣድኪ ድኑን ለአምሳለ መሥዋዕት ውኩፍ፡፡ እስእለኪ አርሴማ በከናፍር ወአፍ፤ ረድኤትኪ ትሩፍ በላዕሌየ ያንጸፈጽፍ፤ እስመ አርአየኒ ዘንተ ሞትኪ ትሩፍ፡፡ ሰላም ለዘአዕረፉ ምስሌኪ ፳ወ፯ቱ ሰማዕታት፤ ረድኤቶሙ ትረድ ላዕሌየ ዘምስለ ብዙኅ ምሕረት፡፡ ወኀበ ሀለወ ስሞሙ ምስለ ስምኪ ቅድስት፤ ዓዲ ኢይቅረብ አርሴማ ሕማመ ብድብድ ወሞት፤ በኵሉ አዝማን ወበኵሉ ዓመታት፡፡ /የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/

#እንኳን #ለፆመ_ጽጌ በሳላም አደረሳቹህ ✤ወርኃ ጽጌ 40 ቀናት ነው፤ መስከረም 26 ተጀምሮ ኅዳር 5 ያልቃል፤ ጾመ ጽጌ የፈቃድ ጾም ነው (ከሰዓትም ቅዳሴ የሚቀደሰስባቸው አካባቢዎች አሉ (ጎንደር )፡፡ በግዕዝ ጸገየ ማለት አበበ ፤ አፈራ ፣ በውበት ተንቆጠቆጠ ማለት ነው፡፡ በማኀሌቱም ወቅትን እመቤታቸንን 3 ዓመት ከ6 ወር እስከ ግብፅ ከዚያም የአሥራት ሀገሯ በሆነችው በኢትዮጵያ የተሰደደችበትን ወቅት በማሰብ በጽጌና በአበባ እመቤታቸንን እና ጌታቸንን በመመሰል ሲያመሰግኗት ፣ ከልጇ ጋር ያየችውን መከራ እያሰቡ እና ምልጃዋን ሲለምኑ ያድራሉ ፡፡ ✤እምግብጽ ጸዋዕክዎ ለወልድየ ለክብረ ቅዱሳን፤ ለቅዱሳን ክብር ልጄን ከግብጽ ጠራሁት›› በማለት ነቢዩ ሆሴዕ በምዕራፍ ፲፩ ቍጥር ፩ እና ፪ ላይ አስቀድሞ እንደ ተናገረው ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በልጅነቱ ወደ ምድረ #ግብጽ (ምስር) የተሰደደው የነቢያት ትንቢት ይፈጽም ዘንድ ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ሕፃናትን በመፍጀት ከሚታወቀው ከአረመኔው ንጉሥ ከሄሮድስ ለማምለጥ ነው፡፡ አምላካችን ክርስቶስ ያለጊዜው (ዕለተ ዓርብ) #ደሙ #አይፈስምና፡፡ ስለዚህም ‹‹ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ምድረ ግብጽ ሽሽ፤ ሄሮድስ ሕፃኑን ለመግደል ይፈልጋልና›› ብሎ መልአኩ ቅዱስ #ገብርኤል ለዮሴፍ በነገረው ቃል መሠረት ሕፃኑንና እናቱን ይዞ በሌሊት ወደ ግብጽ ምድር ተሰደደ፡፡ ይህንን ስደት አስመልክቶ #ሰቆቃወ ድንግል የሚባለውን ቃለ እግዚአብሔር ካህናቱ በሚያሳዝን ዜማ ያደርሳሉ፤ ያቀርባሉ፡፡ #በመቶ ሺሕ የሚቆጠሩ ሕፃናትን ሄሮድስ አስፈጅቷል፡፡ ‹‹ድምፅ በራማ ተሰማ፤ ለቅሶና ብዙ ዋይታ፡፡ ራሔል ስለ ልጆቿ አለቀሰች፡፡ መጽናናትም አልወደደችም፤ የሉምና›› የሚለው ትንቢትም ተፈጸሟል፡፡ #ከሦስት ዓመት ከመንፈቅ የግብጽ ስደት በኋላ ሊቃውንቱ፡- ‹‹ተመየጢ ማርያም ሀገረኪ ናዝሬተ፣ በላዕሌኪ አልቦ ዘያበጽሕ ሁከተ፣ ወኢትጎንድዪ በግብጽ ከመ ዘአልብኪ ቤተ፣ ዘየኀሥሦ ለወልድኪ ይእዜሰ ሞተ፣ በከመ ነገሮ መልአክ ለዮሴፍ ብሥራተ›› እያሉ ከስደት መመለሷን ያበሥራሉ፡፡ ትርጉሙም፡- ‹‹ማርያም ሆይ! ወደ ሀገርሽ ወደ ናዝሬት ተመለሺ፡፡ በአንቺ ላይ ሁከት የሚያመጣ ማንም የለም፡፡ ቤት እንደሌለሽ ሁሉ በግብጽ አትቆይ፡፡ ለዮሴፍ በሕልሙ መልአክ እንደ ነገረው የሕፃኑን ነፍስ የፈለገው (ጠላት ሄሮድስ) ሞቷልና›› ማለት ነው፡፡ የኢትዮጵያ #ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን በዐርባው ቀን (በዘመነ ጽጌ) ወቅት የማርያምን የሽሽትና የመመለስ (የሚጠት) ታሪክ እያነሡ ውዳሴ የሚያቀርቡትና ማኅሌት የሚቆሙት በዚሁ ምክንያት ነው፡፡ በዚህ ወቅት ለእመቤታችን ክብር ሲባል የፈቃድ ጾም የሚጾሙ ምዕመናንና ምዕመናትም ብዙዎች ናቸው በመሃል ኢትዮጵያ በፈቃድ ጾምነት ሲጾም ; በሰሜኑ አካባቢ ተጹሞ ከሰዓት ይቀደሳል ሌሎች ጋር ግን ጠዋት ያበቃል፡፡ የእመቤታችን ምልጃ ና ጸሎት አይለየን #ማኅሌተ_ጽጌ ✤የማኅሌተ ጽጌ የሰቈቃወ ድንግል ደራሲ አባ ጽጌ ድንግል ነው ፡፡ ገዳሙም ትልቅና ሰፊ የኾነ የፍልፍል ዋሻ ሲኾን ወሎ ወግዲ ወለቃ ወንዝ አጠገብ በረሃ ላይ (ከጋሥጫ ገዳም የ4 ሰዓት የእግር መንገድ) ይገኛል፡፡ ✤✤ በየዓመቱ ሳይመረገዱ ያመይታለፉ የማይቀሩ፤ ዚቃቸው የማይለወጥ፤ እጅጉን በምንወደው የማኅሌተ ጽጌ ቁመት ላይ በየዓመቱ ሳይመረገዱ የማይታለፉ የማይቀሩ፤ ዚቃቸው የማይለወጥ ( ከማኅሌተ ጽጌ፤ ጽጌ አስተርአየ(የመጀመሪያው ሳምንት)፣ በከመ ይቤ መጽሐፍ፣ ትመስል እምኪ ማርያም፣ ዘኒ ስብሐተ ወዘኒ ማኅሌተ፣ ኢየሐፍር ቀዊመ ቅድመ ሥዕልኪ እና ኅብር ሐመልሚል (የመጨረሻው ሳምንት)ናቸው፡፡ ✤ ከሰቈቃወ ድንግል፤ በስመ እግዚአብሔር ሥሉስ፣ ብክዩ ኅዙናን፣ እስከ ማዕዜኑ እግዝእትየ እና አብርሂ አብርሂ ናቸው፡፡ ✤ከማኅሌተ ጽጌ ውስጥ እንዘ ተሐቅፊዮ ለሕፃንኪ እና ክበበ ጌራ ወርቅ በየሳምንቱ (በኹሉም ዓመታት) ይመረገዳሉ፤ ዚቁ ግን በዓሉን በተመለከተ ይኾናል፡፡ ✤ ከላይ ካየናቸው ውጪ የሚገኙት #የማኅሌተ ጽጌና የሰቈቃወ ድንግል ክፍሎች ግን #በየሰባት ዓመት አንዴ ነው የሚመረገዱት፡፡ ( የማኅሌቱ ሥርዐት የላይ ቤት (የጎንደር መካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ማርያም አብነት) እና የታች ቤት (የጎንደር ደብረ ኀይል በዓታ ለማርያምን አብነት) የሚያደርግ ሲኾን፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ የማኅሌት ቁመትም የላይ ቤትን አብነት የተከተለ ሲኾን የዚቁ ወረብ ግን የደብሩን የራሱን (የሸዋን) የተከተለ ነው፤ ( የላይ ቤት ቁመት የሚቆሙ አድባራት #ዘግምጃ ቤት የሚለውን እንዲከተሉ፤ የታች ቤትን #ቁመት የሚቆሙ አድባራት ዘበዓታ የሚለውን እንዲከተሉ፡፡ የዚቁ ወረብን ግን የቀጨኔ ደብረ ሰላም የቤቱን ቀለም አስቀድመን ቀጥሎ ደግሞ ዓዲ (ወይም) በማለት የጎንደርን ስላስቀመጥነው እንደ ደብራችሁ ይትበሃል መርጣችሁ ተጠቀሙ፡፡ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958 የ2013 ዓ.ም እና የቀደሙት ዓመታት የፎቶ ማስታወሻዎች

ለ64 ዓመታት ታላቁን ደብር ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምን በጸሎት ያገለገሉት ጸሎተኛው አባት አባ ወልደ አረጋዊ ዐረፉ፡፡ ፨ ‹‹ወኢትጸመም ሞቶ ለዘተልአከከ (ያገለገለህን ሰው ሞት ቸል አትበል)፡፡›› ሲራ. 38÷16 ሁልጊዜም ጠዋት ጠዋት ከደወል ቤት ፊት ለፊት ቁጭ ብለው ጸሎት ማድረስ የዘወትር ተግባራቸው በመሆኑ በሁሉም ዘንድ ይታወቃሉ! አባ ወልደ አረጋዊ፡፡ አባ ወልደ አረጋዊ አብርሃ ጎሹ መካነ ትውልዳቸው ትግራይ ገርዓልታ ማይ ደዓሮ ሲሆን፡፡ በተወለዱበት አካባቢ በሚገኘው፤ በቦታው አቀማመጥ በሀገራችን እና በዓለማችን ዕፁብ ድንቅ በተባለለት በታላቁ ገዳም በገርዓልታ ማይቁዲ ዮሐንስ (በገመድ የሚወጣ ገዳም ነው) የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ተምረዋል፡፡ በዚሁ ገዳምም በወጣትነት ዘመናቸው በዲቁና እያገለገሉ ቤተሰቦቻቸውንም ደግሞ በግብርና ሥራ እያገለገሉ አድገዋል፡፡ በዚሁ አገልግሎት እያሉ ሕመም ስላጋጠማቸው ለሕክምና ወደ ራያ ወደሚገኝ ሐኪም ቤት፤ ከዚያም ወደ አዲስ አበባ አቅንተዋል፡፡ ወደ አዲስ አበባ እንደመጡም መጀመሪያ ወደ ዘነበ ወርቅ ገብረ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን በማቅናት ለጥቂት ጊዜ ቆይተዋል፤ ነገር ግን ሕመማቸው የአንድ እግራቸውን አሳጥቷቸዋል፡፡ ከዚህም በኋላ ወደ ታላቁ ደብር ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም በደጅ ጸኚነት መጡ፡፡ ደብራችንም ከመላው ኢትዮጵያ የሚመጡ አገልጋዮች ማረፊያ (ወደ አዲስ አበባ የመጣ ካህንን ቀጨኔ ፈልጉት) እስከሚባል ድረስ የደረሰ የእንግዳ ተቀባይነት ታሪክ ስላለው፤ በዚሁ መሠረት በወቅቱ የነበሩት የደብራችን አባቶችም ለአባ ወልደ አረጋዊ መኖሪያ ቤት ሰጥተው፣ የሚያስፈልገውን ነገርም አሟልተው በጸሎት እያገለገሉ እንዲቀመጡ አደረጓቸው፡፡ እርሳቸውም በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም የ64 ዓመታት የአገልግሎት ቆይታቸውም፤ 1ኛ) ለ64 ዓመታት ሁልጊዜም በጸሎት ይተጉ ነበረ፤ የጾም ሰዐታቸውም ሁልጊዜም ዘነፍ አትልም ነበረ፡፡ 2ኛ) በጸሎት አስቡኝ የሚላቸውንም ማንኛውንም ምዕመን ያለምንም ክፍያ በጸሎት ያስቡ ነበረ፡፡ 3ኛ) ጥንታዊ የሆነውን የገርዓልታ ድጉም አቡነ ስምዖን ገዳም ሕንፃ ቤ/ክ ለብቻቸው አሣንጸዋል፡፡ 4ኛ) ለ131 አብያተ ክርስቲያናት መቀደሻ አልባሳት፣ ንዋያተ ቅድሳት፣ ለመሥዋዕት መገበሪያ፣ …… አበርክተዋል፡፡ 5ኛ) በተለያዩ ቦታዎች ላሉ ረጂ ለሌላቸው፤ እናት አባት ለሞተባቸውም ሕፃናት ከ3መቶ ሺሕ ብር በላይ እየላኩ ረድተዋል፡፡ ፨ ዕድሜ ዘመናቸውን በዚህ ዓይነት አገልግሎት ሲያገለግሉ ከቆዩ በኋላ የዕረፍት ጊዜያቸውን ቀድመው በማወቃቸው ይረዷቸው እና ይላላኳቸው ወደነበረው ወደ አቶ ተክሌ ቤት ሄደው ለ10 ቀናት ከቆዩ በኋላ እመቤቴ እየመጣች ነው ጸሎት ላድርስ ብለው ጸሎታቸውን እንደጨረሱ ለአቶ ተክሌ አንድ ቃል ብቻ ነግረዋቸው በብዙኃን ማርያም ቀን መስከረም 21 ቀን በ92 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ዐረፈዋል፡፡ ሥርዐተ ግብዓተ መሬታቸውም በኑዛዜያቸው መሠረት መስከረም 22/2018 ዓ.ም. ባሣነጹት ትግራይ ገርዓልታ ድጉም አቡነ ስምዖን ገዳም ተፈጽሟል፡፡ ‹‹…በጺሐኪ ድንግል ጊዜ ዕረፍትየ፤ ጽጌ ዕፀ ገነት ገሪ ላዕሌየ፤ በመዐዛሁ ትትመሠጥ ነፍስየ፡፡ (ድንግል በዕረፍቴ ጊዜ ደርሰሽ የገነት የዛፍ አበባን በእኔ ላይ ጣዪ፥ ዕጠኚ፤ በመዐዛው ነፍሴ ከሥጋዬ ትለይ ዘንድ፡፡) /ማኅሌተ ጽጌ ቊ.፻፲፮/

በቀጨኔ መድኀኔዓለም ቤተክርስቲያን ለሰባት ዓመታት አስተዳዳሪ የነበሩት መልአከ ገነት ምናሴ ዘለቀ የሕይወት ታሪካቸው በመጽሐፍ ተዘጋጅቶ የቀረበ ሲሆን መስከረም 25, 2018 ዓ.ም ከቀኑ 7:00 ሰዓ
በቀጨኔ መድኀኔዓለም ቤተክርስቲያን ለሰባት ዓመታት አስተዳዳሪ የነበሩት መልአከ ገነት ምናሴ ዘለቀ የሕይወት ታሪካቸው በመጽሐፍ ተዘጋጅቶ የቀረበ ሲሆን መስከረም 25, 2018 ዓ.ም ከቀኑ 7:00 ሰዓት ጀምሮ በቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ አዳራሽ ይመረቃል።