cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

ንፅፅር🕌እስልምና ወይስ ⛪ክርስትና

እሥልምና የሰዎች ሁሉ ተፈጥሮአዊ እምነት ሲሆን ነቢያቶች ደግሞ ከኢሥላም ላፈነገጡ አስጠንቃቂዎች እና ወደ ቀጥተኛው መንገድ መሪና ተውሒድን አስተማሪ ይሆኑ ዘንድ ወደ ሰዎች ከአምላካችን ዘንድ የተላኩ ናቸው ። የመጨረሻውና መደምደሚያው አስንጠቃቂ ለአለማት የተላኩት ነቢይ ሙሐመድ ﷺ ናቸው...! ኑ ሳይመሽ ወደ ኢሥላም ። t.me/islamistruereligion

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استزبان مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
پست‌های تبلیغاتی
186
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

1} በሱረቱ ሶፍ ምዕራፍ 61 ቁጥር 5 ላይ 2} በሱረቱል አዕራፍ ምዕራፍ 7 ቁጥር 157 ላይ እና 3} ለመርየም (ዐ,ሰ) የተላከው መልዐኩ ጅብሪል (አ,ሰ) እና ወደ ነብዩ ሙሐመድ የመጣው መልዐክ ጅብሪል (አ,ሰ) አንድ ነው ወይ ተብሎ ለተነሳ ጥያቄ የተሰጠ መልስ 👉በኡስታዝ አቡ ሀይደር https://t.me/shemsedinComparativereligion
نمایش همه...
4_6035051056633741377.mp31.88 MB
ይህን ወንድማችንን ተባበሩት‼ ====================== ✍ ዛሬ ከኛ እርዳታ ከመጠየቁ በፊት ባለው አቅም ሌሎችን የሚረዳ ወንድማችን ነበር። በቻላችሁት ሁሉ ተባበሩትና እናሳክመው። «‼️‼️አስቸኳይ የእርዳታ ጥሪ‼️‼️ አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ ወንድም ሙኀመድ አንዋር አያሌው ይባላል ____ ዕድሜዉ አርባ ሶስት (43) ሲሆን የአምስት(5) ልጆች አባት ነዉ ። ወንድም ሙሀመድ ትልቅ ቤተሰብ አስተዳዳሪ ቢሆንም ዛሬ ግን በህመም ምክንያት እንኳን ቤተሰብ ማስተዳደር አይደለም ለራሱም መሆን ቸግሮት እጁን ከአላህ ቀጥሎ ወደ እኛ ዘርግቶ ለአላህ ብላችሁ ሰበቡን አድርሱልኝ፣ የቻለ በገንዘቡ ያልቻለ በዱዓው ከጎኔ ሁኑልኝ ይለናል። ✍ ህመሙን በተመለከተ:- ሙሐመድን እያሰቃየው ያለውና ለአራት አመታት ያክል ሲያሰቃየው የኖረው የኩላሊት ህመም ነው። ይህም ማለት መጨረሻ ደረጃ የደረሰ የኩላሊት በሽታ (Cronic Kideny Disease /CKD)ሲሆን ይህም ማለት ደግሞ ሁለቱም ኩላሊቶቹ ሙሉ በሙሉ የማጣራት ስራቸውን የማቆም /Kideny Failure/ ችግር ነው። ኩላሊት ደግሞ ሙሉ በሙሉ ቀርቶ በጊዜያዊነት እንኳ በኢንፌክሽን ወይም በጠጠር ምክንያት መጠነኛ ችግር ሲገጥመን የሚሰማውን ስሜት የሚያውቅ ያውቀዋል። በሙሐመድ ደረጃ ግን ኩላሊት ምንም መስራት ሲያቆም ምንም አይነት ቆሻሻ ከሰውነት መጣራትና በሽንት በኩል መውጣት አይችልም ማለት ነው። በዚህን ጊዜ ደግሞ ቆሻሻ ሰውነት ውስጥ እየተጠራቀመ በቆየ ቁጥር አሲዱ ሰውነትን እየመረዘ እብጠት ቁስለትና ሌላ ለመቋቋም የሚከብድ ተጨማሪ በሽታ ያስከትላል። ለዚህ ችግር ከዶክተሮች የተሰጠው መፍትሄ ሁለት ነው:- 👉1. ከሱጋ ተመሳሳይ የሆነ ዶነር /ኩላሊት ለጋሽ ከተገኘ ንቅለ ተከላ ወይም የኩላሊት ቅያሬ ህክምና ነው። ይህ ህክምና በውጭ አገር የሚደረግ ሲሆን በትንሹ ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ ይጠይቃል። ነገር ግን በኩላሊት ለጋሽም በብርም የተነሳ እስካሁን መከናወን አልቻለም። 👉2. ሁለተኛው አማራጭ ደግሞ Dialysis /የኩላሊት እጥበት የሚባለው ሲሆን ቢያንስ በሳምንት ሶስት ጊዜ የሚከናወን ደሙን በማሽን እየወጣ ተጣርቶ መልሶ እንድገባ ይደረጋል። አሁንም ህይወቱን ለማቆየት ይህኛውን አማራጭ ሲሆን የሚጠቀመው በሳምንት ለሶስት ቀን በቀን ለአራት ሰዓት የሚሰጥ ህክምና ነው። በቀን ለህክምናው ብቻ (በተጓዳኝ ከሚወስዳቸው መድሃኒቶችና ሰኘሊመንት ውጭ) ከ2,600 ብር በላይ ሲሆን በወር ከ30,000 ብር በላይ ማለት ነው። እንግድህ ይህ ህክምና እንኳን ምንም ገቢ ለሌለው ሙሐመድ ቀርቶ አቅም ያለውን ሰው እንኳ የሚፈታተንና የሚከብድ ነው (ከዚህ አይነት ሙሲባ አላህ በራህመቱ ይጠብቃችሁ) ግን ስቃዩን ማስታገስ ህይወት ማቆየት ደግሞ ለነገ አይባልም። ስለዚህ እህቶች ወንድሞች እናቶች አባቶች ለአላህ እሆናችኋለሁና ለአላህ ብላችሁ በዱዓም በገንዘባችሁም አትጨክኑብኝ ስቃየንም አስታግሱልኝ ልጆቸም አባት አለን እንድሉ /የቲም እንዳይሆኑብኝ እርዱኝ ይላል። መልካም ስራ ለክፉ ቀን ስንቅ ነው። ለአላህ ብላችሁ ሰበቡን አድርሱልኝ። አላህም በቁርአኑ "መልካምንም ሥራ በፈቃደኛነት የሠራ ሰው (አላህ ይመነዳዋል)፤ አላህ አመስጋኝ ዐዋቂ ነውና"፡፡ {ሱረቱ-በቀራህ፡ 158 }_* ለሙሐመድ አንድ ብር ትልቅ ነገር ናት ለአኼራችን ገንዘባችንን እንስራበት። *_مَآ أَغْنَىٰ عَنِّى مَالِيَهْ ۜ_* *_«ገንዘቤ ከእኔ ምንንም አላብቃቃኝ፤ (አልጠቀመኝም)፡፡_* ሱረቱል ሖቃህ 28 በሚያልቀው ገንዘባችን የማያልቀው አኼራችንን እንሸምት ። √ ሰዓዳ ሙሐመድ አያሌው (ልጁ) √ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር፦ 1000344290591 √ የልጁ ስልክ ቁጥር: 0996910472 √ እሱን ለማገኘት: 0912660336 በአላህ ስም እጠይቃችኋላሁ በየ ግሩፑ፣ በየ ቻናሉ፣ በየ ሚዲያው ሁሉ ሼር በማድረግ ሰበቡን አድርሱልኝ "ጋን በጠጠር ይደገፋልና!" የቻላችሁትን...... በዱዓችሁም አደራ። "ሰጭ እጅ ከተቀባይ ትበልጣለች!...." ይህ የድጋፍ መርሃ ግብር የሚካሄድበት የቴሌግራም ግሩፕ: https://t.me/joinchat/AVGeq_Tm0OYyMDY0»
نمایش همه...
ምስኪኗ ኤሊ ራሷን ነፃ እንዳወጣች ታስባለች ፤ ነገር ግን መከላከያ የሆነውን ነገሯን እንዳጣች አታውቅም !! የዚህች ኤሊ ምሳሌ ሙስሊም እህቶች ፦ ግማሽ ፀጉር በግንባር ፣ ጆሮን ከሒጃብ ውጭ አውጥቶ ፤ የተጣበቀ እና ያጠረ ቀሚስም በሉት ጉርድ ብሎም ሱሪ የምትለብሱ ራሳችሁን ነፃ ያወጣን ከመሰላችሁ በጣም ተሳስታችኋል !! የከፈን ቀን ደርሶ ከመጠቅለላችሁ በፊት በህይወት እያላችሁ ተሰተሩ !! የኻቲማን ማማር በህይወት እያለን ያደረግነው ድርጊት ይወስነዋል ። «ነጭ ሽንኩርት ዘርቶ ረይሓን ማጨድ የለምና !!»
نمایش همه...
نمایش همه...
ኑ የሸይክ ዑስማን ቤተሰቦችን እንርዳ-//- በአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

ጥንታዊ ስም አሏህ በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 20፥14 *«እኔ አላህ እኔ ነኝ ያለ እኔ አምላክ የለምና አምልከኝ*፡፡ ሶላትንም በእርሷ እኔን ለማውሳት ስገድ፡፡ إِنَّنِىٓ أَنَا ٱللَّهُ لَآ إِلَٰهَ إِلَّآ أَنَا۠ فَٱعْبُدْنِى وَأَقِمِ ٱلصَّلَوٰةَ لِذِكْرِىٓ “አሏህ” ٱللَّه የሚለው ስም 2699 ጊዜ በቁርአን የመጣ ሲሆን ትርጉሙ “የሚመለክ” ወይም “አምልኮ የሚገባው” ማለት ነው፦ Lane’s Arabic-English Lexicon by Edward William Lane (London: Willams & Norgate 1863) አላህ ኢስሙል ዛት ማለትም የህላዌው ስም ነው፥ አምላካችን አላህ ጥንትም ሙሳን ሲያናግር የነበረው የሙሳ አምላክ አላህ እራሱ ነው፤ አላህ ለሙሳ፦ “እኔ አላህ እኔ ነኝ፥ ያለ እኔ አምላክ የለምና አምልከኝ” ብሎታል፦ 20፥14 *«እኔ አላህ እኔ ነኝ፥ ያለ እኔ አምላክ የለምና አምልከኝ*፡፡ ሶላትንም በእርሷ እኔን ለማውሳት ስገድ፡፡ إِنَّنِىٓ أَنَا ٱللَّهُ لَآ إِلَٰهَ إِلَّآ أَنَا۠ فَٱعْبُدْنِى وَأَقِمِ ٱلصَّلَوٰةَ لِذِكْرِىٓ አላህ ለሙሳ፦ “እኔ አላህ እኔ ነኝ፥ ያለ እኔ አምላክ የለምና አምልከኝ” ብሎ ከማለቱ በፊት «ሙሳ ሆይ» በማለት ጠርቶታል፦ 20፥11 በመጣም ጊዜ «ሙሳ ሆይ» በማለት *”ተጠራ*፡፡ فَلَمَّآ أَتَىٰهَا نُودِىَ يَٰمُوسَىٰٓ ይህንን ጥሪ ጠርቶ ያነጋገረው እራሱ እንደሆነ በመጀመሪያ መደብ ለነቢያችን”ﷺ”፦ “ጠራነው፥ ያነጋገርነውም ሲኾን አቀረብነው” በማለት ሙሴን የጠራው እርሱ እንደሆነ ይናገራል፦ 19፥51 በመጽሐፉ ውስጥ *ሙሳንም አውሳ*፡፡ እርሱ ምርጥ ነበርና፡፡ መልክተኛ ነቢይም ነበር፡፡ وَٱذْكُرْ فِى ٱلْكِتَٰبِ مُوسَىٰٓ ۚ إِنَّهُۥ كَانَ مُخْلَصًۭا وَكَانَ رَسُولًۭا نَّبِيًّۭا 19፥52 ከጡር ቀኝ ጎን በኩልም *ጠራነው፥ ያነጋገርነውም* ሲኾን አቀረብነው፡፡ وَنَٰدَيْنَٰهُ مِن جَانِبِ ٱلطُّورِ ٱلْأَيْمَنِ وَقَرَّبْنَٰهُ نَجِيًّۭا አምላካችን አላህ ለሙሳ "አላህ" ነኝ ብሎ እራሱ ማስተዋወቁ ካየን ዘንድ ለሙሳ እና ከእርሱ በኃላ ላሉት ነቢያት ያወረደው ወሕይ ሥረ-መሠረቱ በዘመናችን ስለሌለ በትክክል አሁን በአህሉል ኪታብ እጅ ያሉት ጋር አላህ የሚለውን ስም በግልጽ ማግኘት አልተቻለም። ነገር ግን "አላህ" የሚለውን ስም በእነርሱ ቅሪት ውስጥ ስለመኖሩ ፍንጭ የሚሰጡ አናቅጽ በፓሌዎ ዕብራይስጥ አነባነብ አለ። ፓሌዎ ዕብራይስጥ ማለት ከማሶሬት ዕብራይስጥ በፊት የነበረ እና ነቢያቱ ሲጠቀሙበት የነበረ ዕብራይስጥ ነው። ማሶሬት የሚባለው እደ-ክታብ በ 875 ድኅረ-ልደት"AD" ከመዘጋጀቱ በፊት ማሶሬት የሚባሉ የአይሁድ ግሩፕ ዕብራይስጥን ከዐረማይክ ጋር እየደባለቁ የጥንቱን የፓሌዎ ዕብራይስጥ በርዘውታል። "ማሶሬት" מֶסֹרֶת ማለት ቋንቋዊ ፍቺው "እስራት" ማለት ሲሆን ሃይማኖታዊ ፍቺው "ትውፊት" ማለት ነው። በፓሌዎ ዕብራይስጥ "አ-ለ-ሀ" אלוה "አሌፍ-ላሜድ-ሃ" ነው። "አሌፍ" א ሲነበብ "አ" እንጂ "ኤ" አይደለም። "ላ" לו ሲነበብ "ላ" እንጂ "ሎ" አይደለም። "ሀ" ה ሲነበብ "ሀ" ነው ግን የመጨረሻ ፊደል ላይ በሳድስ "ህ" ተብሎ ይሰክናል። በፓሌዎ ዕብራይስጥ ሲነበብ "አ-ላ-ህ" ይሆናል። በፓሌዎ ዕብራይስጥ ውስጥ "ኤ" የምትባል ኃምስ እና "ኦ" የምትባል ሳብዕ አናባቢ የለም። ስለዚህ "ኤ" እና "ሎ" የሚባለውም የማሶሬት ጭማሬ ነው። ግዕዝ ሰባት አናባቢ አሉት፥ እነርሱም፦ ግእዝ "አ" ካዕብ "ኡ" ሣልስ "ኢ" ራብዕ "ኣ" ኃምስ "ኤ" ሳድስ "እ" እና ሳብዕ "ኦ" ናቸው። በፓሌዎ ዕብራይስጥ ግን የዘር መነሻ ግእዝ "አ" ነው። የዘር ግንድ ራብዕ "ኣ" ነው። የዘር መዳረሻ ሳድስ "እ" ነው። ይህንን ከተረዳን "አላህ" אלוה የሚለው ቃል በዕብራይስጡ ባይብል ውስጥ በቅሪት አለ፦ ኢዮብ 3፥4 ያ ቀን ጨለማ ይሁን፤ "አላህ" אֱל֣וֹהַּ ከላይ አይመልከተው፥ ብርሃንም አይብራበት። ኢዮብ 5 ፥17 እነሆ፥ "አላህ" אֱל֣וֹהַּ የሚገሥጸው ሰው ምስጉን ነው፤ ስለዚህ ሁሉን የሚችለውን የአምላክን ተግሣጽ አትናቅ። መዝሙር 139፥19 "አላህ" אֱל֣וֹהַּ ሆይ! አንተ ኃጢአተኞችን የምትገድል ከሆንህስ፥ የደም ሰዎች ሆይ፥ ከእኔ ፈቀቅ በሉ።
نمایش همه...
በአላህ ስም አጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው የወገናችን ጥያቄ መልስ አለህ አምሳያ የለውም። ማስረጃ 1 فَاطِرُ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۚ جَعَلَ لَكُم مِّنْ أَنفُسِكُمْ أَزْوَاجًا وَمِنَ الْأَنْعَامِ أَزْوَاجًا ۖ يَذْرَؤُكُمْ فِيهِ ۚ لَيْسَ كَمِثْلِهِ شَيْءٌ ۖ وَهُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ ሰማያትንና ምድርን ፈጣሪ ነው፡፡ ከነፍሶቻችሁ ሴቶችን ከቤት እንስሳዎችም ዓይነቶችን (ወንዶችና ሴቶችን) ለእናንተ አደረገላችሁ፡፡ በእርሱ ያበዛችኋል፡፡ *የሚመስለው ምንም ነገር የለም፡፡ እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው*፡፡ 42:11 2 وَلَمْ يَكُن لَّهُ كُفُوًا أَحَدٌ *ለእርሱም አንድም ብጤ የለውም*፡፡» 112:4 የወገናችን ጥያቄ አላህ ይነገራል?? 👉መልስ አው። ማስረጃ وَلَمَّا جَاءَ مُوسَىٰ لِمِيقَاتِنَا وَكَلَّمَهُ رَبُّهُ قَالَ رَبِّ أَرِنِي أَنظُرْ إِلَيْكَ ۚ قَالَ لَن تَرَانِي وَلَٰكِنِ انظُرْ إِلَى الْجَبَلِ فَإِنِ اسْتَقَرَّ مَكَانَهُ فَسَوْفَ تَرَانِي ۚ فَلَمَّا تَجَلَّىٰ رَبُّهُ لِلْجَبَلِ جَعَلَهُ دَكًّا وَخَرَّ مُوسَىٰ صَعِقًا ۚ فَلَمَّا أَفَاقَ قَالَ سُبْحَانَكَ تُبْتُ إِلَيْكَ وَأَنَا أَوَّلُ الْمُؤْمِنِينَ *ሙሳም ለቀጠሯችን በመጣና ጌታውም ባነጋገረው ጊዜ*፡- «ጌታዬ ሆይ! (ነፍስህን) አሳየኝ ወደ አንተ እመለከታለሁና» አለ፡፡ (አላህም)፡- «በፍጹም አታየኝም ግን ወደ ተራራው ተመልከት፡፡ በስፍራውም ቢረጋ በእርግጥ ታየኛለህ» አለው፡፡ ጌታው ለተራራው በተገለጸ ጊዜ እንኩትኩት አደረገው፡፡ ሙሳም ጮሆ ወደቀ፡፡ በአንሰራራም ጊዜ «ጥራት ይገባህ፡፡ ወዳንተ ተመለስኩ፡፡ እኔም (በወቅቱ) የምእምናን መጀመሪያ ነኝ» አለ፡፡ 7:143 قَالَ يَا مُوسَىٰ إِنِّي اصْطَفَيْتُكَ عَلَى النَّاسِ بِرِسَالَاتِي وَبِكَلَامِي فَخُذْ مَا آتَيْتُكَ وَكُن مِّنَ الشَّاكِرِينَ ( *አላህም) አለው፡- «ሙሳ ሆይ! እኔ በመልክቶቼና በማናገሬ በሰዎች ላይ መረጥኩህ*፡፡ የሰጡህንም ያዝ፡፡ ከአመስጋኞቹም ኹን፡፡» 7:144 وَإِنْ أَحَدٌ مِّنَ الْمُشْرِكِينَ اسْتَجَارَكَ فَأَجِرْهُ حَتَّىٰ يَسْمَعَ كَلَامَ اللَّهِ ثُمَّ أَبْلِغْهُ مَأْمَنَهُ ۚ ذَٰلِكَ بِأَنَّهُمْ قَوْمٌ لَّا يَعْلَمُونَ ከአጋሪዎችም አንዱ ጥገኝነትን ቢጠይቅ *የአላህን ቃል ይሰማ ዘንድ አስጠጋው*፡፡ ከዚያም ወደ መጠበቂያው ስፍራ አድርሰው፡፡ ይህ እነሱ የማያውቁ ሕዝቦች በመኾናቸው ነው፡፡ 9:6 የወገነችን ጥያቄ አላህ ይሰማል ያያል ?? 👉መልስ አው። ማስረጃ *አላህ ሰሚም ተመልካችም ነው* 42:11 *አላህ ሰሚ ዐዋቂው ነው* 2:137 የወገነችን ጥያቄ አላህ አዋቂ ነው?? 👉መልስ አው ማስረጃ وَأَسِرُّوا قَوْلَكُمْ أَوِ اجْهَرُوا بِهِ ۖ إِنَّهُ عَلِيمٌ بِذَاتِ الصُّدُورِ (ሰዎች ሆይ!) ቃላችሁንም መስጥሩ፡፡ ወይም በእርሱ ጩሁ፡፡ *እርሱ በልቦች ውስጥ ያለን ሁሉ ዐዋቂ ነው*፡፡ 67:13 ۞ وَعِندَهُ مَفَاتِحُ الْغَيْبِ لَا يَعْلَمُهَا إِلَّا هُوَ ۚ وَيَعْلَمُ مَا فِي الْبَرِّ وَالْبَحْرِ ۚ وَمَا تَسْقُطُ مِن وَرَقَةٍ إِلَّا يَعْلَمُهَا وَلَا حَبَّةٍ فِي ظُلُمَاتِ الْأَرْضِ وَلَا رَطْبٍ وَلَا يَابِسٍ إِلَّا فِي كِتَابٍ مُّبِينٍ *የሩቅ ነገርም መክፈቻዎች እርሱ ዘንድ ናቸው፡፡ ከእርሱ በቀር ማንም አያውቃቸውም፡፡ በየብስና በባሕር ያለውንም ሁሉ ያውቃል፡፡ ከቅጠልም አንዲትም አትረግፍም የሚያውቃት ቢኾን እንጅ፡፡ ከቅንጣትም በመሬት ጨለማዎች ውስጥ የለም ከእርጥብም ከደረቅም አንድም የለም ግልጽ በኾነው መጽሐፍ ውሰጥ (የተመዘገበ) ቢኾን እንጅ*፡፡ 6:59
نمایش همه...
❶ عَنْ عَائِشَةَ ـ رضى الله عنها أَنَّ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم تُوُفِّيَ وَهْوَ ابْنُ ثَلاَثٍ وَسِتِّينَ‏ አዒሻ እንደተረከችው የአላህ መልዕክተኛ(ﷺ) ሲሞቱ እድሜያቸው ስልሳ ሦስት (63) ነበር። [ሰሒሕ አል-ቡኻሪ 3536 መፅሐፍ 61 ሐዲስ 45] ❷ حَدَّثَنَا مَطَرُ بْنُ الْفَضْلِ، حَدَّثَنَا رَوْحٌ، حَدَّثَنَا هِشَامٌ، حَدَّثَنَا عِكْرِمَةُ، عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ ـ رضى الله عنهما ـ قَالَ بُعِثَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم لأَرْبَعِينَ سَنَةً، فَمَكُثَ بِمَكَّةَ ثَلاَثَ عَشْرَةَ سَنَةً يُوحَى إِلَيْهِ، ثُمَّ أُمِرَ بِالْهِجْرَةِ فَهَاجَرَ عَشْرَ سِنِينَ، وَمَاتَ وَهُوَ ابْنُ ثَلاَثٍ وَسِتِّينَ‏.‏ የአላህ መልዕክት ወሕይ (ግህደተ-መለኮት) መቀበል የጀመሩት እድሜያቸው አረባ (40) አመት ሳለ ነው። ከዚያ በመካ ውስጥ አስራ ሶስት (13) አመታትን ወሕይ እየተቀበሉ ቆዩ። ለሒጅራ ከታዘዙ ቡኋለ ለአስር (10) አመታት ከኖሩ ቡኋለ በስልሳ ሦስት (63) አመታቸው ሞቱ። [ሰሒሕ አል-ቡኻሪ 3902 መፅሐፍ 63 ሐዲስ 128] ❸ حَدَّثَنِي مَطَرُ بْنُ الْفَضْلِ، حَدَّثَنَا رَوْحُ بْنُ عُبَادَةَ، حَدَّثَنَا زَكَرِيَّاءُ بْنُ إِسْحَاقَ، حَدَّثَنَا عَمْرُو بْنُ دِينَارٍ، عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ، قَالَ مَكَثَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم بِمَكَّةَ ثَلاَثَ عَشْرَةَ، وَتُوُفِّيَ وَهْوَ ابْنُ ثَلاَثٍ وَسِتِّينَ‏.‏ ኢብኑ አባስ እንደተረከው የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) በመካ ለአስራ ሦስት አመታት ከተቀመጡ ቡኋለ በስልሳ ሦስት (63) አመታቸው ሞቱ። [ሰሒሕ አል-ቡኻሪ 3903:- መፅሐፍ 63 ሐዲስ 129] ❹ عَنْ عَائِشَةَ ـ رضى الله عنها ـ أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم تُوُفِّيَ وَهْوَ ابْنُ ثَلاَثٍ وَسِتِّينَ‏.‏ قَالَ ابْنُ شِهَابٍ وَأَخْبَرَنِي سَعِيدُ بْنُ الْمُسَيَّبِ مِثْلَهُ‏.‏ የአላህ መልዕክተኛ ሲሞቱ እድሜያቸው ስልሳ ሦስት (63) ነበር። [ሰሒሕ አል-ቡኻሪ 4466: መፅሐፍ 64, ሐዲስ 481] ❺ حَدَّثَنَا أَحْمَدُ بْنُ أَبِي رَجَاءٍ، حَدَّثَنَا النَّضْرُ، عَنْ هِشَامٍ، عَنْ عِكْرِمَةَ، عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ ـ رضى الله عنهما ـ قَالَ أُنْزِلَ عَلَى رَسُولِ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم وَهْوَ ابْنُ أَرْبَعِينَ، فَمَكَثَ ثَلاَثَ عَشْرَةَ سَنَةً، ثُمَّ أُمِرَ بِالْهِجْرَةِ، فَهَاجَرَ إِلَى الْمَدِينَةِ، فَمَكَثَ بِهَا عَشْرَ سِنِينَ، ثُمَّ تُوُفِّيَ صلى الله عليه وسلم‏.‏ የአላህ መልዕክት (ﷺ) በአርባ (40) አመታቸው ወሕይ ወረደላቸው።ከዚያ በመካ ለአስራ ሦስት (13) አመት ከቆዩ ቡኋለ ወደ መዲና ተሰደዳ። በመዲና ለ አስር (10) አመታት ከቆየ ቡኋለ ሞተ [ሰሒሕ አል-ቡኻሪ 3851 : መፅሐፍ 63, ሐዲስ 77] ➏ وَحَدَّثَنَا ابْنُ أَبِي عُمَرَ، حَدَّثَنَا بِشْرُ بْنُ السَّرِيِّ، حَدَّثَنَا حَمَّادٌ، عَنْ أَبِي جَمْرَةَ الضُّبَعِيِّ، عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ، قَالَ أَقَامَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم بِمَكَّةَ ثَلاَثَ عَشْرَةَ سَنَةً يُوحَى إِلَيْهِ وَبِالْمَدِينَةِ عَشْرًا وَمَاتَ وَهُوَ ابْنُ ثَلاَثٍ وَسِتِّينَ سَنَةً ‏.‏ ኢብኑ አባስ እንደተረከው የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) በመካ ለ አስራ ሦስት (13) አመታት ቆዩ። በመዲና ደግሞ ለ አስር (10) አመታት ከቆዩ ቡኋለ በ ስልሳ ሦስት (63) አመታቸው ሞቱ። [ሲሒሕ ሙስሊም 2351: መፅሐፍ 43, ሐዲስ 155] ❼ حَدَّثَنَا مُحَمَّدُ بْنُ إِسْمَاعِيلَ، حَدَّثَنَا مُحَمَّدُ بْنُ بَشَّارٍ، حَدَّثَنَا ابْنُ أَبِي عَدِيٍّ، عَنْ هِشَامِ بْنِ حَسَّانَ، عَنْ عِكْرِمَةَ، عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ، قَالَ أُنْزِلَ عَلَى رَسُولِ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم وَهُوَ ابْنُ أَرْبَعِينَ فَأَقَامَ بِمَكَّةَ ثَلاَثَ عَشْرَةَ وَبِالْمَدِينَةِ عَشْرًا وَتُوُفِّيَ وَهُوَ ابْنُ ثَلاَثٍ وَسِتِّينَ ‏.‏ قَالَ أَبُو عِيسَى هَذَا حَدِيثٌ حَسَنٌ صَحِيحٌ ‏.‏ ኢብኑ አባስ እንደተረከው የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) በአርባ አመታቸው ወሕይን ተቀበሉ። በመካ ለአስራ ሦስት በመዲና ደግሞ ለ አስር አመታት ከቆዩ ቡኋለ በስልሳ ሦስት (63) አመታቸው ሞቱ። [ጃሚዓ-ትርሚዚ መፅሐፍ 49 ሐዲስ 398] ❽ عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ، قَالَ أَقَامَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم بِمَكَّةَ ثَلاَثَ عَشْرَةَ سَنَةً يُوحَى إِلَيْهِ وَبِالْمَدِينَةِ عَشْرًا وَمَاتَ وَهُوَ ابْنُ ثَلاَثٍ وَسِتِّينَ سَنَةً ‏.‏ ኢብኑ አባስ እንደተረከው ወሕይ ወደ አላህ መልዕክት (ﷺ) መምጣት የጀመረው በአርባ (40) አመታቸው ነበር ከዚህ በመካ ለአስራ ሦስት አመታት እንዲሁ በመዲና ለአስርት አመታት ከተቀመጡ ቡኋለ በስልሳ ሦስት አመታቸው ሞቱ። [ሙስነድ አህመድ መፅሐፍ 25, ሐዲስ 2017] ❾ أَنَّ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم تُوُفِّيَ وَهْوَ ابْنُ ثَلاَثٍ وَسِتِّينَ‏ ኢብኑ አባስ እንደተረከው የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) ወሒይ የወረደላቸው በአርባ (40) አመታቸው ሲሆን በመካ ለአስራ ሦስት አመታት ሲቀመጡ በመዲና ደግሞ ለአስር አመታት ከተቀመጡ ቡኋለ በስልሳ ሦስት አመታቸው ሞቱ። [ሙስነድ አህመድ መፅሐፍ 25 ሐዲስ 2110] ❿ أَقَامَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم بِمَكَّةَ ثَلاَثَ عَشْرَةَ سَنَةً يُوحَى إِلَيْهِ وَبِالْمَدِينَةِ عَشْرًا وَمَاتَ وَهُوَ ابْنُ ثَلاَثٍ وَسِتِّينَ سَنَةً ‏.‏ የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) ቁርአን ወደ እርሳቸው መውረድ የጀመረው በአርባ አመታቸው ነበር ከዚያ በመካ ለአስራ ሶስት በመዲና ደግሞ ለአስር አመታት ከተቀመጡ ቡኋለ በስልሳ ሦስት (63) አመታቸው ሞቱ። [ሙስነድ አህመድ መፅሐፍ 25 ሐዲስ 2242]
نمایش همه...
ጥቁር አዝሙድ በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 59፥7 *መልክተኛውም የሰጣችሁን ማንኛውንም ነገር ያዙት! ከእርሱም የከለከላችሁን ነገር ተከልከሉ*፡፡ አላህንም ፍሩ፡፡ አላህ ቅጣተ ብርቱ ነውና። وَمَآ ءَاتَىٰكُمُ ٱلرَّسُولُ فَخُذُوهُ وَمَا نَهَىٰكُمْ عَنْهُ فَٱنتَهُوا۟ ۚ وَٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَ ۖ إِنَّ ٱللَّهَ شَدِيدُ ٱلْعِقَابِ ኢሥላም ዱር ሙሥሊሙ ሐሩር እንዲሆን ቀን ከሌሊት ደፋ ቀና፥ ጠብ እርግፍ የሚሉት አግድም አደግ ዕውቀት ያላቸው ሚሽነሪዎች፦ “ነቢያችሁ"ﷺ"፦ *"በጥቁር አዝሙር ውስጥ ከሞት በስተቀር ከሁሉም በሽታ መድኃኒት ነው” ብለዋል፥ ስለዚህ ጥቁር አዝሙር ለኤች አይቪ ኤድስ፣ ለኮሮና ቫይረስ እና ለመሳሰሉት መድኃኒት እንዴት አልሆነም? እያሉ ይጠይቃሉ። እኛም ደግሞ ጥሬውን ከብስል ምርቱን ከእንክርዳር የሚለዩ ሊሒቃን፦ “ ነገርን ከሥሩ ውኃን ከጡሩ” እንደሚሉት ኢንሻሏህ ከሥሩ ጥናት በማድረግ መልስ እንሰጣለን፦ ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 76, ሐዲስ 11 አቢ ሁራይራህ ሰምቶ እንደተረከው፦ "የአላህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ *"በጥቁር አዝሙር ውስጥ ከሞት በስተቀር ከሁሉም በሽታ መድኃኒት አለው"*። أَنَّ أَبَا هُرَيْرَةَ، أَخْبَرَهُمَا أَنَّهُ، سَمِعَ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم يَقُولُ ‏ "‏ فِي الْحَبَّةِ السَّوْدَاءِ شِفَاءٌ مِنْ كُلِّ دَاءٍ إِلاَّ السَّامَ ‏"‌‏ ፨ አንደኛ እዚህ ሐዲስ ላይ “ኩል” كُلٌّ ማለትም “ሁሉ” የሚለው ቃል ተቀምጧል። “ኩል” كُلٌّ በዐረቢኛ ሰዋስው ውስጥ ፍጹማዊ “Absolute” ሆኖ ሲመጣ “ኩሉል ሙጥለቅ” كُلٌّ ٱلْمُطْلَق ሲባል፥ በአንጻራዊ “Relative” ሆኖ ሲመጣ ደግሞ “ኩሉል ቀሪብ” كُلٌّ ٱلْقَرِيب‎ ይባላል። እዚህ ሐዲስ ላይ "ኩል" የሚለው ቃል ኩሉል ቀሪብ መሆኑን የምናውቀው "ኩል" በሚል ቃል መነሻ ላይ "ሚን" مِنْ ማለትም "ከ"from" የሚል መስተዋድድ መምጣቱ ነው፥ እስቲ ተመሳሳይ ሰዋስው እንመልከት፦ 14፥34 "ከ"ለመናችሁትም ሁሉ የሰጣችሁ ነው፡፡ وَآتَاكُم مِّن كُلِّ مَا سَأَلْتُمُوهُ 13፥3 እርሱም ያ ምድርን የዘረጋ በእሷም ተራራዎችን እና ወንዞችን ያደረገ በውስጧም “ከ”ፍሬዎች ሁሉ ሁለት ሁለት ጥንዶችን ያደረገ ነው*፡፡ وَهُوَ الَّذِي مَدَّ الْأَرْضَ وَجَعَلَ فِيهَا رَوَاسِيَ وَأَنْهَارًا ۖ وَمِن كُلِّ الثَّمَرَاتِ جَعَلَ فِيهَا زَوْجَيْنِ اثْنَيْنِ "የለመናችሁትን ሁሉ የሰጣችሁ ነው" ሳይሆን "ከ"ለመናችሁት ሁሉ" ማለት ከፊልን ያሳያል፥ በተመሳሳይ "ፍሬዎች ሁሉ" ሳይሆን "ከ"ፍሬዎች ሁሉ " ማለት ከፊልን ያሳያል። በተመሳሳይም "ለሁሉም በሽታ መድኃኒት አለው" ሳይሆን "ከ-ሁሉም በሽታ መድኃኒት አለው" ማለት ከፊልን ያሳያል። ፨ ሁለተኛ ሐዲሱ ላይ "ኢላ" إِلَّا ማለትም "በቀር" የሚል ሐርፉል ሐስድ ይጠቀማል። "ሐርፉል ሐስድ" حَرْف الحَصْرْ ማለት "ግድባዊ መስተዋድድ"restriction particle" ማለት ሲሆን ይህም ሐስድ በሁለት ዋና ዋና ዐበይት ክፍሎች ይከፈላል፥ እርሱም አንደኛው “ሐስዱል ሙጥለቅ” حَصْرْ ٱلْمُطْلَق ማለትም “ፍጹማዊ ግድብ“Absolute restriction” ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ “ሐስዱል ቀሪብ” حَصْرْ ٱلْقَرِيب‎ ማለትም “አንጻራዊ ግድብ“Relative restriction” ነው። ይህንን ናሙና እንይ፦ 26፥77 *”«እነርሱም ለእኔ ጠላቶች ናቸው፡፡ ግን የዓለማት ጌታ ሲቀር እርሱ ወዳጄ ነው”*፡፡ فَإِنَّهُمْ عَدُوٌّ لِّي إِلَّا رَبَّ الْعَالَمِينَ 46፥25 *"በጌታዋ ትዕዛዝ አንዳቹን ሁሉ ታጠፋለች፥ ከመኖሪያዎቻቸውም በስተቀር ምንም የማይታዩ ኾኑ፡፡ تُدَمِّرُ كُلَّ شَيْءٍ بِأَمْرِ رَبِّهَا فَأَصْبَحُوا لَا يُرَىٰ إِلَّا مَسَاكِنُهُمْ ኢብራሂም፦ "የዓለማት ጌታ ሲቀር" ሲል ከአሏህ ውጪ ያሉ መላእክት፣ ነቢያት እና ምእመናን ጠላቶቼ ናቸው ማለት እንዳልሆነ ሁሉ፣ እንዲሁ ነፋስ ከመኖሪያዎቻቸው በቀር ሁሉን ታጠፋለች ሲባል መላእክት፣ ነቢያት እና ምእመናን ታጠፋለች ማለት እንዳልሆነ ሁሉ በተመሳሳይ "ከሞት በስተቀር ከሁሉም በሽታ መድኃኒት አለው" ማለት "ሁሉ" የሚለው ቃል አንጻራዊ "በቀር" የሚለው ግድባዊ አነጋገር ነው። ስለዚህ ጥቁር አዝሙድ ለካንሰር እባጭ፣ ለስኳር በሽታ፣ ለተቅማጥ፣ ለደረቅ ሳል፣ ለጆሮ ህመም፣ ለዓይን ህመም፣ ለእይታ ችግር፣ ለፊት ፓራሊሲስ፣ ለጉንፋን፣ ለፍሉ፣ ለሐሞት ጠጠር፣ ለጉበት ጠጠር፣ ለሆድ ትላትል፣ ለሆድ ህመም፣ ለሪህ፣ ለጀርባ ህመም፣ ለአፍ ኢንፌክሽን ቫይረስ፣ ለጡንቻ ህመም፣ ለራስ ህመም፣ ለማይግሬን፣ ለማስታወስ ችሎታ ለፀጉር መሳሳት እረ ስንቱ ተዘርዝሮ ይለቅ? ለዚህ ሁሉ መድኃኒት ነው፥ ቅሉ ግን "ሁሉ" እና "በቀር" የሚለው "ኢሥቲስናእ” اِسْتِثْنَاء‏ ማለትም "ግድባዊ"exceptional" ሆኖ የመጣ ነው። ፨ ሦስተኛ "በጥቁር አዝሙር ውስጥ ከሞት በስተቀር ከሁሉም በሽታ መድኃኒት ነው" ስለተባለ ጥቁር አዝሙድን ዝም ብሎ መውሰድ ያድናል ማለት ሳይሆን እንዴት መቀመም እንዳለበት ጥናት እና ከአሏህ ዘንድ ጥበቡ ያስፈልጋል። ለምሳሌ የፋርማሲይ ምልክቱ የእባብ መርዝ ነው፥ የእባብ መርዝ ፕሮቲን ሲሆን ከእኛ ፕሮቲን ጋር በቀጥታ ስለማይመጣጠን ለእኛ መርዝ ነው። ቅሉ ግን የእባብ ፕሮቱኑ ለምሳሌ ለደም ግፊት አሁን ሥራ ላይ እየዋለ ካሉ መድኃኒቶች ዉስጥ "Angiotensin-converting enzyme (ACE) inhibitors" ከሚባሉት ዉስጥ የዚህ ACE I ግሩፕ አካል የሆነ እና "Prodrug" በመባል የሚታወቀው ''Captopril'' ምንጩ የእባብ መርዝ ነው፥ ታዲያ የእባብ መርዝ "ለደም ግፊት መድኃኒት ነው" ስለተባለ ያለ ጥናት እና ያለ ጥበብ እስቲ ምክረውና ምን እንደሚፈጠር መገመት አያዳግትም። በተመሳሳይም የጥቁር አዝሙር መድኃኒትነትን የሰው ልጅ ሙሉ ለሙሉ አልደረሰበት ማለት ለሁሉ ነገር መድኃኒት አይደለም ማለት አይደለም፥ የእባብ መርዝ አጠቃቀሙ የተነገረበት "ሢያቅ" سِيَاق ማለትም "ዐውድ"context" እንደሚወስነው ሁሉ የጥቁር አዝሙድ አጠቃቀም ዐውዱ ይወስነዋል። ለአንድ በሽታ መድኃኒት ለማግኘት አምላካችን አሏህ ዕውቀቱን እና ጥበቡ እንዲያገኙ ሲፈቅድ ነው፦ ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 39, ሐዲስ 95 ጃቢር እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ *"ለሁሉም በሽታ መድኃኒት አለው፥ መድኃኒቱ በሽታውን ካገኘው በአሏህ አዘ ወጀል ፈቃድ ይፈውሳል"*። عَنْ جَابِرٍ، عَنْ رَسُولِ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم أَنَّهُ قَالَ ‏ "‏ لِكُلِّ دَاءٍ دَوَاءٌ فَإِذَا أُصِيبَ دَوَاءُ الدَّاءِ بَرَأَ بِإِذْنِ اللَّهِ عَزَّ وَجَلَّ የጥቁር አዝሙር መድኃኒትነትን ከላይ በተዘረዘረው የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ ሙግት መረዳት በቀላሉ ይቻላል። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን! አሚን።
نمایش همه...
እየሱስ አምላክ ከሆነ ማንን ነው የሚያመልከው? ሁሉን ከምንም ያስገኘ ሰማይ ምድርን ያፀና የሰውን ልጅ ከእናቱ ማሐፀን የሰራ ከሁሉ የላቀ ጥራት የተገባው የሁሉ ፈጣሪ አምልኮ ለእርሱ ብቻ ሊሆን የተገባ ነው 19|65|(እርሱ) የሰማያትና የምድር በሁለቱም መካከል ላለው ሁሉ ጌታ ነውና ተገዛው፡፡ 20|14|«እኔ አላህ እኔ ነኝ ያለ እኔ አምላክ የለምና ተገዛኝ፡፡ ፈጣሪ ፀሎትን ከባሮች የሚሰማ የሚቀበል ነው 27|62|ወይም ያ ችግረኛን በለመነው ጊዜ የሚቀበል፣ መከራንም የሚያስወግድ፣ በምድርም ላይ ምትኮች የሚያደረጋችሁ፤ (ይበልጣልን ወይስ የሚያጋሩት) ከአላህ ጋር ሌላ አምላክ አለን ጥቂትንም አትገሠጹም፡፡ ፈጣሪ የሁሉ መጠጊያ እንጂ እርሱ ከሌላ የሚሻ ፈላጊ አይደለም ፈጣሪ በራሱ የተብቃቃ ራሱን የቻለ ነው ! እየሱስን በዚህ ሚዛን ስናሰፍረው ብቁ ነው ወይ?! እየሱስ እግሩን ምድር ላይ ከተከለበት ጊዜ ጀምሮ ለፈጠረው ተገዥ ነበር " እርሱም በስጋው ወራት ከሞት ሊያድነው ወደሚችል ከብርቱ ጩኸትና ከእንባ ጋር *ጸሎትን*ና ምልጃን አቀረበ፥ እግዚአብሔርንም ስለ *መፍራቱ* ተሰማለት፤" (ወደ ዕብራውያን 5:7) " ሕዝቡም ሁሉ ከተጠመቁ በኋላ ኢየሱስ ደግሞ ተጠመቀ። *ሲጸልይም* ሰማይ ተከፈተ፥" (የሉቃስ ወንጌል 3:21) " እርሱም በአንድ ስፍራ *ይጸልይ* ነበር፥ በጨረሰም ጊዜ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ። ጌታ ሆይ፥ ዮሐንስ ደቀ መዛሙርቱን እንዳስተማረ እንጸልይ ዘንድ አስተምረን አለው።" (የሉቃስ ወንጌል 11:1) እየሱስ ለማን ነው የሚፀልየው ? ለራሱ ? ከአንድ አምላክ ሌላ የለምና ማንን ነው የሚለምነው ? እርሱ ሊያስተምር ነው የመጣው ስለዛ ፀሎትን እያስተማረን ነው ! ታድያ ማንን ሊያስተምር ነው እየሱስ ምድረ በዳ ጋራ ሸንተረር ተራራ ላይ እየወጣ በመሄድ ከሰው በመነጠል በለሊት አምላኩን የሚማለደው " ሕዝቡንም አሰናብቶ ይጸልይ ዘንድ ብቻውን ወደ ተራራ ወጣ። በመሸም ጊዜ ብቻውን በዚያ ነበረ።" (የማቴዎስ ወንጌል 14:23) " ካሰናበታቸውም በኋላ ሊጸልይ ወደ ተራራ ወጣ።" (የማርቆስ ወንጌል 6:46) " በነዚህም ወራት ይጸልይ ዘንድ ወደ ተራራ ወጣ፥ ሌሊቱንም ሁሉ ወደ እግዚአብሔር ሲጸልይ አደረ።" (የሉቃስ ወንጌል 6:12) " ማለዳም ተነሥቶ ገና ሌሊት ሳለ ወጣ ወደ ምድረ በዳም ሄዶ በዚያ ጸለየ።" (የማርቆስ ወንጌል 1:35) ማንን ነው ሲማፀን ሲለምን ሲጣራ ሲሰግድ ሲማለድ ሲያመልክ... የነበረው እራሱን https://t.me/shemsedinComparativereligion M ነኝ
نمایش همه...
Shemsedin.Jemal ሸምሰዲን ጀማል የንፅፅር መድረክ

በታዳጊው ወጣት ሸምሰዲን በፌስቡክ ያስተማራቸው የኦዲዮ የጹሁፍ እና የቪዲዮ ትምህርቶች ተሰባስበው የሚገኙበት ቻናል ነው።

یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.