6 733
مشترکین
+1124 ساعت
+817 روز
+25730 روز
در حال بارگیری داده...
کانالهای مشابه
ابر برچسبها
هیچ دادهای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
دسامبر '24
دسامبر '24
+214
در 0 کانالها
نوامبر '24
+242
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '24
+166
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '24
+171
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '24
+299
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '24
+413
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '24
+297
در 0 کانالها
Get PRO
مه '24
+161
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '24
+313
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '24
+538
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '24
+99
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '24
+167
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '23
+572
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '230
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '230
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '23
+188
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '23
+150
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '23
+3 310
در 0 کانالها
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 21 دسامبر | +6 | |||
| 20 دسامبر | +14 | |||
| 19 دسامبر | +12 | |||
| 18 دسامبر | +3 | |||
| 17 دسامبر | +3 | |||
| 16 دسامبر | +6 | |||
| 15 دسامبر | +58 | |||
| 14 دسامبر | 0 | |||
| 13 دسامبر | 0 | |||
| 12 دسامبر | 0 | |||
| 11 دسامبر | 0 | |||
| 10 دسامبر | 0 | |||
| 09 دسامبر | +5 | |||
| 08 دسامبر | +12 | |||
| 07 دسامبر | +10 | |||
| 06 دسامبر | +11 | |||
| 05 دسامبر | +15 | |||
| 04 دسامبر | +12 | |||
| 03 دسامبر | +12 | |||
| 02 دسامبر | +11 | |||
| 01 دسامبر | +24 |
پستهای کانال
✞ማርያም አርጋለች✞
ማርያም አርጋለች ወደ ገነት(፪)
የሰማይ መላእክት እያረጋጓት
እርሷም እንደ ልጇ ተነስታለች
የአባቷን ዳዊት ትንቢት ልትፈፅም
ወርቁን ተጎናፅፋ በቀኙ ልትቆም
ወደ አምላክ ማደሪያ ወደ ሰማያት
አረገለች በእልልታ ድንግል የእኛ እናት
አርጋለች ማርያም ተነስታለች
አዝ= = = = =
ሰማያት ይከፈት ደመናም ይዘርጋ
ዝምታም አይኖርም እመ አምላክ አርጋ
አንደበት ይከፈት ማርያምን ያመስግን
ከዘላለም ጥፋት በምልጃዋ እንድንድን
አርጋለች ማርያም ተነስታለች
አዝ= = = = =
የአምላክ ማደሪያ ቅዱስ ሥጋሽ
አምላክን ያቀፉት እነዚያ እጆችሽ
ሙስና መቃብር ይዞ አላስቀራቸው
ተነስተዋል በክብር በእምነት አየናቸው
አርጋለች ማርያም ተነስታለች
አዝ= = = = =
ሐዋርያት አበው እንኳን ደስ አላችሁ
በክብር አረገች ማርያም ሞገሳችሁ
ወደ ዓለምም ውጡ ሰበኑዋን ይዛችሁ
የድንግል እርገቷን ንገሩ ተግታችሁ
አርጋለች ማርያም ተነስታለች
ዘማሪ
ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ
"በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና
ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች።"
መዝ ፵፬፥፱
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
| 2 | #ቡሄ_በሉ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 7 104 |
| 3 | እመቤታችን ተወለደች ማለት ጌታ ሊወለድ 15 ዓመት ቀረው ማለት ነው:: እግዚአብሔር ከሴት የተወለደ ልጁን ሊልክ የዘመኑ ፍጻሜ ቀረበ ማለት ነበር። እግዚአብሔር ሃና እና ኢያቄምን ሳይወልዱ ያዘገያቸውም ለዚህ ታላቅ ክብር እንዲበቁ ነበር።
ቀድመው ልጅ ቢወልዱ ኖሮ ይህችን የፍጥረት ደስታ የሆነች ልጅ አይወልዱም ነበር:: የእርስዋ የልደት ቀን የፍጥረት ደስታ ቀን ነው::
ክርስቶስ ፀሐይ ከሆነ የዛሬው ዕለት ሰማይዋ የተዘረጋችበት ዕለት ነው።
ክርስቶስ የሕይወት ውኃ ከሆነ ዛሬ ምንጭዋ የፈለቀችበት ዕለት ነው።
ክርስቶስ መድኃኒት ከሆነ ዛሬ የመድኃኒቱ ሙዳይ የተገኘችበት ዕለት ነው::
ወንጌል በመጥምቁ ዮሐንስ መወለድ ብዙዎች ደስ ይላቸዋል ይላል። በእመቤታችን መወለድ ምን ያህል ሰዎች ደስ ይላቸው ይሆን? የእመቤታችን ልደት በብዙ ሀገራት ብሔራዊ በዓል ሆኖ ይከበራል።
እኛም በሊባኖስ ተራሮች (አድባረ ሊባኖስ) መወለድዋን በማሰብ ከደጅ ወጥተን ቅድም አያቶችዋ በጨረቃ ተመስላ በህልማቸው ያዩአትን የጨረቃችንን (በግሪኩ ሶልያና) ልደት ጨረቃን እያየን እናከብራለን። የልደትዋ ቀን ልደታችን ነው!
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 14 517 |
| 4 | #ዮም_ፍስሐ_ኮነ
ዮም ፍስሐ ኮነ (፪)
በእንተ ልደታ ለማርያም
በባርነት ሳለን
ኃጢአት በአለም ነግሳ
በድንግል መወለድ
ቀረልን አበሳ
እግዚአብሔር መረጠሸ
ልትሆኚው እናቱ
ይኸው ተፈፀመ
የዳዊት ትንቢቱ
#አዝ
የሔዋን ተስፋዋ
የአዳም ዘር ህይወት
የኢያቄም የሐና
ፍሬ በረከት
ምክንያተ ድኂን
ኪዳነምህረት
ድንግል ተወለደች
የጌታዬ እናት
#አዝ
በሔዋን ምክንያት
ያጣነውን ሰላም
ዛሬ አገኘነው
በድንግል ማርያም
የምስራች እንበል
ሀዘናችን ይጥፋ
ተወልዳለችና
የአለም ሁሉ ተስፋ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 12 193 |
| 5 | ☞ግንቦት 1 ቀን የአምላክ እናት የእኛም እናት ለሆነች ለቅድስተ ቅዱሳን
ለንጽህተ ንጹሀን ለወላዲተ አምላክ የዓመታዊ የልደቷ ማታሰቢያ በሰላም
አደረሳችሁ፡፡
☞ በዚች ቀንም የእመቤታችን ወዳጅ ጻድቁ አባታችን አቡነ ቆስጦስ
የተወለዱበትም ቀን ነው፡፡
☞አምላክን የወለደች የእመቤታችን ማርያም እናት ብፅዕት የሆነች የቅድስት
ሐና ተአምር ይህ ነው፡፡ ጸሎቷና በረከቷ ከሁላችንም ጋር ይሁን፡፡
☞ከይሁዳ ወገን የሚሆን አንድ ሰው ነበር፡፡ ስሙም ኢያቄም ይባላል፡፡ ከካህናት
ወገን የምትሆን ሴትም አገባ፡፡ ሰሟም ሐና ይባላል፡፡ ሁለቱም ደጋግና የተወደዱ
ነበሩ፡፡ በእግዚአብሔር ሕግም ይኖሩ ነበር፡፡ ሚስቱም መካን ነበረች፡፡ ዘወትርም
ወደ ቤተ እግዚአብሔር ይሔዱ ነበር፡፡ ልጅ ይሰጣቸው ዘንድም በለቅሶና
በመጨነቅ ለእግዚአብሔር ጸሎት ያቀርቡ ነበር፡፡ ከገንዘባቸው ለድሆች ለጦም
አዳሪዎች ለቤተ ክርስቲያን ይሰጡ ነበር፡፡
☞ከዕለታት በአንዲት ቀንም ኢያቄምና ሚስቱ ሐና መጡ፡፡ ወደ ቤተ መቅደስም
ገቡ፡፡ ለጸሎት ቁመው ሳለም ርግቦች ከልጆቻቸው ጋር ሲደስቱ ተመለከቱ፡፡
ተመልክተውም ልጅ ሰላልነበራቸው ፈጸመው አዘኑ፡፡ ከኃዘናቸው ብዛት የተነሣ
ፈጽመው ተኙ፡፡ ሐናም ተኝታ ሳለች በባሏ በኢያቂሞ እጅ የነበረች በትር አብቤ
አፍርታ ተመለከተች፡፡ ይህቺ ፍሬም በሐና እቅፍ እንዳለች ሆና ነበር፡፡
☞ነቅተውም ተደሰቱ እርስ በርሳቸውም ሰላዩት ነገር ተነጋገሩ፡፡ፈጣሪን
አመሰገኑ፡፡ የፈጣሪ ፈቃድ ይሁን ብለው ወደ ቤታቸው ገቡ፡፡ ከዚህ በኃላ ሐና
ፀነሰች፡፡ ፅንሷም ታወቀ፡፡ ለእግዚአብሔርም ተሳለች ልጅ ከሰጠኝ
ለእግዚአብሔር መሥዋዕት አድርጌ እሰጣለሁም አለች፡፡
☞ጸሎትም ልመናን እያበዛች ኖረች፡፡ ገንዘቧንም ለችግረኞችና ለጦም
አዳሪዎች በፍጹም ደስታ ትሰጥ ነበር፡፡ ከምግብ ሁሉ ተከለከል ነበር፡፡ ልመናንና
ስግደትን ታበዛ ነበር፡፡ የሰጣትን ፈጣሪ ይጠብቅላት ዘንድ ትለምን ነበር፡፡
☞ከስድስት ወር በኃላ የሐና መፅነሷ ታወቀ፡፡ ዘመዶቿ የቧሏ ዘመዶች ሰሙ፡፡
ወደ እርሷም መጡ፡፡
☞ዘመንሽ ካለፈ በኃላ የተደረገው ይህ ነገር ምድንው ነው አሏት፡፡ ፅንሷን
ይመልከቱ ዘንድም ሆዷን ዳሰሱ፡፡ ከሐና እናት ወገን ማየት የተሳናት የአርሳብን
ልጅ የምትሆን አንዲት ሴት ነበረች፡፡ ምንም ሳታውቅ ዐይኗን ዳሰሰች ያን ጊዜ
ዳነች፡፡
☞ሐናንም ሐና ለአንቺ ብፅዓን ይገባሻል፡፡ ከዓለም ፈጥረታት እንደ አንቺ
በማሕፀኑ የዕውራን ዐይን የፈወሰ የለም አለቻት፡፡ ዘመዶቿም ሰገዱላት፡፡፡
☞ሐናም ፀሐይ ከአጥቢያ ኮከብ እንደሚበልጥ በእርሱ ላይ ከፍ ከፍ አለች
ከበረች፡፡ ዜናዋም በዓለም ዳርቻ ሁሉ ተሰማ፡፡ ድውያንን ሕሙማንን ሁሉ
እመጡ፡፡ ማሕፀኗን እየዳሰሱም ይፈወሱ ነበር፡፡
☞ሁሉም በማሕፀኗ ሳለ የፈወሰው ሲወለድማ እንዴት ይሆን አሉ፡፡
☞የእስራኤል ልጆችም ይህ ሰምተው ተሰበሰቡ፡፡ ሰለዚህ ሁኔታ ምን እናድርግ
ኢያቄምና ሐና እንሆ መንግሥት ከፍለዋልና፡፡
☞ሐና ፀነሰች በማሕፀኗም ትፈውሳለች፡፡ በእኛ ላይም ልትነግሥ ነው አሉ፡፡
እንዱ ሰውም ይህ ያስጨንቃችኀል? ኑና እንደ ተጻፈ በድንጋይ ወግረን
እንግደላቸው አለ፡፡ ሁሉም ተገረሙ፡፡
☞በመንፈቀ ሌሊት በሆነ ጊዜም ስሙ ገብርኤል የሚባል መልአክ ከሰማይ
ወረደ፡፡
☞ሐናና ኢያቄምንም በዘመድ የከበራችሁ ሆይ ተነሡ አላቸው፡፡ ወደ ሊባኖስ
ተራራም ወሰዳቸው፡፡ በዚያም ሰወራቸው፡፡
☞የመውለጃዋ ጊዜ በደረሰ ወቅት ግንቦት 1 ቀን ከፀሐይ የምታበራ ልጅን
ወለደች፡፡ የደም ግባቷም ከስኳር ይልቅ ይጣፍጣል፡፡ የመዓዛዋ ሽታም ከሽቱ ሁሉ
ይበልጣል፡፡
☞ብላቴናቱንም ማርያም ብለው ጠሯት፡፡ ሰባቱ ቀን በፈጸሙ ጊዜም በሰላም
ወደ ቤታቸው ገቡ፡፡ ለችግረኞች ለምስኪኖች ምጽዋትን ይሰጡ ነበር፡፡
☞ይቺን የተመረጠች ድንግል ማርያምን ያሰገኘችን ቅድስት ሐና ማርያምን
እናመሰግናት፡፡
☞ቅድስት ሐና ሆይ ካማረ ማኅሌት መጠራት ይልቅ ለሰም አጠራርሽ ሰላምታ
ይገባል፡፡
☞ቅድስት ሐና ሆይ ለአፍሽና በረዶ ለሚመስሉ ጥርችሽ ሰላምታ ይገባል፡፡
☞ቅድስት ሐና ሆይ ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክ ለጠባቸው ለጡቶችሽና
ለእንቺ ጉንጭም ሰላምታ ይገባል፡፡
☞ቅድስት ሐና ሆይ ድንግልን ለተሸከመ ለሆድሽና ንጹሕ ለሆድሽና ንጹሕ
ለሆነው ለልብሽ ሰላምታ ይገባል፡፡
☞ቅድስት ሐና ለሐሳብሽ ምሳሌ የማይገኝለት ቅድስት ሐና ሆይ የምድር
ፍጥረታትና የሰማይ ፍጥረታት ሁሉ ባንቺ ይመካሉ ባንቺ ያርፋሉ፡፡
☞ቅድስት ሐና ሆይ ለኅብርትሽና ለተመረቀው ድንግል ማርያምን ለተሸከመው
ማኅፀንሽ ሰላምታ ይገባል፡፡
☞ቅድስት ሐና ሆይ ለወገብሽና ለጭኖችሽም ከሁለቱ እግሮችሽና ጉልበቶችሽ
ጋር ሰላምታ ይገባል፡፡
☞የማርያም እናት የኢየሱስ ክርስቶስ አያት ቅድስት ሐና ሆን ድንገት እንዳንጠራ
ለንሰሐ ጥቂት ቆይኝ እንጂ ሞትስ በዓለም አይተወኝም፡፡
☞እንደ ዕንቁ የምታበሪ የማርያም እናት ቅድስት ሐና ሆይ የቆሬ ልጆች
አሰቀድመው እንደጠፋ በከንቱ የሚጠሉ የኢትያጵያና የህዝቦቿ ጠላቶች ለፍሬ
ሳይበቁ ይጥፎ፡፡
☞ቅድስት ሐና ሆይ ሰም አጠራርሽ በመለኮት ጨው የጣፈጠ በአርያም
የነገሥሽ የማርያም እናት ቅድሰስት ሐና ሆይ ለአንቺ ሰላምታ ይገባል፡፡
☞እንደ ዕንቁ የምታበሪ ካንቺ የወጣች ነበልባልን የተሸከመችው ድንግል
ማርያም በመሆኗ ቅድስት ሐና ሆይ ለአንቺ ሰላምታ ይገባል፡፡
☞አቤቱ የማርያም እናት የእምቤቴ ሐና ፈጣሪ አምላክ ሆይ ኢትያጵያን ህዝቦቿን
ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ አድናቸው፡፡
☞(ድርሳነ ኢያቄብ ወሐና)
☞የእናታችን የድንግል ማርያም አማላጅነት የእናቷ የእናታችን የቅድስ ሀና
ማርያም ጸሎቷ በረከቷ አይለየን፡፡
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@aregawi
@aregawi
@aregawi | 10 811 |
| 6 | ✞ ቸር አገልጋይ ማነው? ✞
ቸር አገልጋይ ማነው ለንጉሥ የታመነ
መክሊቱን ያልቀበረ አትርፎ የከበረ (፪)
ባለ አምስቱ መክሊት መልካም ያደረገው
በመውጣት በመውረድ አትርፎ መጥቶ ነው
በጥቂቱ ታምኖ በብዙ የተሾመው
ባለ አምስቱ መክሊት ሊቀ ጳጳሱ ነው
አዝ
ሳይሰለች የተጋ ባለሁለት መክሊት
የታመነ እረኛ በፍቅርና በእምነት
ግባ የተባለው ወደ ጌታው ደስታ
አጥምቆ ያቆርባል ካህኑ የጌታ
አዝ
ለሚበልጠው ጸጋ ተጠርቶ የነበረ
መክሊቱን ደብቆ ቆፍሮ የቀበረ
ሰነፍ ባርያ ተብሎ ወደ ፍርድ ተጣለ
ማኔ ቴቄል ፋሬስ በአምላክ ፊት ቀለለ
አዝ
ፈቃድህን ማድረግ ነፍሱ ለምትወደው
ወንጌልህን መግለፅ የየዕለት ግብሩ ነው
ህግህ ለዘለላም ተጽፎ ይኖራል
በታላቅ ጉባኤ ጽድቅህ ይነገራል
ዘማሪ ዲያቆን ቀዳሜጸጋ ዮሐንስ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 13 091 |
| 7 | የቀጠለ 👆
በመሆኑም የባለ አምስትና የባለ ሁለት መክሊት ባለቤቶች የሆኑት ወጥተው ወርደው ደክመው፣ መከራ መስቀልን ሳይሳቀቁና ሳይፈሩ፤ ወድደው ፈቅደው የጀመሩትን አገልግሎት በማክበር ሕይወታቸውን ለታመነው አምላክ አደራ በመስጠት የተማሩትን ፍጹም ትምህርት ለሌላው አስተምረው፣ ሠርተው ያገኙትን ለሌላው አካፍለው ወገናቸውን እንደራሳቸው አድርገው ሲመለከቱ
ባለ አንድ መክሊት የተባለው ግን ዓላውያን እሳት ስለት አሳይተው ሃይማኖቴን ሲያስክዱኝ መናፍቃን ተከራክረው ምላሽ ቢያሳጡኝ ብሎ ፈርቶ ሃይማኖቱን በልቡ ከመደበቅና ከመሠወር በቀር የተማረውን ትምህርት ሠርቶ ያገኘውን ሀብት ንብረት ለሌላው ሊያካፍልና የተሰጠውን አደራም ሊወጣ አልወደደም፡፡
ይህ የመክሊቱ ባለቤት የተባለው ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን የተሰጣቸውን ሓላፊነት በአግባቡና በጽንአት ለተወጡት ሁሉ እርሱ ፍጹም ዋጋን የሚሰጣቸው መሆኑን ያመለክታል፡፡
ይህም ሁኔታ “አንተ በጎ ታማኝ ባሪያ በጥቂቱ ታምነሃል በብዙ እሾምሃለሁ። ወደ ጌታህ ደስታ ግባ” በሚል ታላቅ የምስጋና ቃል ተገልጧል፡፡ ይህ ቃል በሃይማኖትና በበጎ ምግባር ለእግዚአብሔር የታመኑ ሁሉ ዘለዓለማዊና ፍጹም ደስታ ወደሚገኝበት መንግሥተ ሰማያት ለመግባት ለሚያደርጉት የእምነት ጉዞ እጅግ ተስፋ የሆነ ቃል ነው፡፡
በዚህ ምንባብ ላይ እንደተገለጸው እግዚአብሔር አምላክ ለሁላችንም እርሱን የምናገለግልበትንና ለእርሱ በመታመን ዘለዓለማዊ ክብርን የምናገኝበትን ዕውቀትን፣ ማስተዋልን፣ እምነትን፣ ተስፋን፣ የሥነ ምግባር ሀብትን፣ ልዩ ልዩ ስጦታዎችን እንጠቀምባቸው ዘንድ ለእኛ ለሰው ልጆች እንደየዓቅማችን መጠን ሰጥቶናል፡፡
እነዚህ ሁሉ ነገሮች የሥጋችንን ምኞት
ለማስፈጸም የተሰጡ ሳይሆኑ ነፍሳችን የምትከብርበትን መልካም ሥራን የምንሠራባቸው መሣሪያዎቻችን ናቸው። በመሆኑም እርሱ በሰጠን የአገልግሎት በር ጸጋ በታማኝነት በማገልገል በሕይወት ዘመናችን ሁሉ መንፈሳዊውን ሀብት የምናተርፍ እንሆን ዘንድ የተላለፈልን አምላካዊ ምክር ነው፡፡
ምክንያቱም እኛ የተጠራነው ፍሬ ልናፈራና ሌላውንም ልናተርፍ መልካም ሥራን ልንሠራ እንጂ የሥጋችንን ፈቃድ በመከተል የኃጢአት ባሮች ልንሆን አይደለም፡፡ መጽሐፍ እንዲህ አለ “ወኲሉ ዘከመ ተጸውአ ከማሁ ለየሀሉ፤ ሁሉ እንደተጠራ እንዲሁ ይኑር” /፩ኛ ቆሮ. ፯፥፳/
ከላይ እንደተመለከትነው በልዑል አምላክ በእግዚአብሔር አንደበት አንተ በጎ ታማኝ አገልጋይ በጥቂቱ ታምነሃልና በብዙ እሾምሃለሁ መባልን የመሰለ አስደሳችና አስደናቂ ነገር የለም፡፡
ይህ ደግሞ የሚገኘው ሃይማኖትን በሥራ በመግለጥ እንጂ ሃይማኖትን በልቡና በመያዝ ብቻ /ሙያ በልብ ነው/ በማለት ብቻ የሚገኝ አይደለም፡፡ ከእነዚህ እንደ አቅማቸው መጠን መክሊት ተሰጥቷቸው በትጋታቸውና በቅንነታቸው ሌላ መክሊት ካተረፉት በጎና ታማኝ አገልጋዮች የምንማረው እውነታም ይህ ነው፡፡
በብዙ ለመሾም ለማደግ ለመጽደቅ በጥቂቱ መታመን መፈተን መጋደል ግድ ነው፡፡ አንድ መክሊት የተሰጠውን ሰው ስንመለከተው ጌታውን ጨካኝና ፈራጅ አድርጎ ከመቁጠር ውጪ በተሰጠው መክሊት ወጥቶ ወርዶ ሊያተርፍ አልወደደም፡፡
መክሊቱንም ባስረከበ ጊዜ በጌታው ላይ የተናገራቸው ቃላት የእርሱን አለመታዘዝና አመጸኝነት ይገልጡ ነበር፡፡ በመሆኑም ይህ ሰው በጥቂቱ መታመን ያቃተውና በአስተሳሰቡ ደካማነት እጅግ የተጎሳቆለ ሰው ነው፡፡
በዚህ ምሳሌ መሠረት ይህ ባለ አንድ መክሊት የተባለው ሰው ዓላውያን ነገሥታት እሳት ስለት አሳይተው ቢያስክዱኝ መናፍቃን ተከራክረው መልስ ቢያሳጡኝ በማለት ሃይማኖቱን በልቡ ሸሽጎና ቀብሮ በተቀደሰ ተግባር ሳይገልጠው ከመያዙ ባሻገር በጌታ ፊት በድፍረት ቆሞ አንተ ሕግ ሳትሠራ በአእምሮ ጠባይዕ አውቃችሁ፤ መምህራንንም ሳትመድብ በሥነ ፍጥረት ተመራምራችሁ በሠራችሁ ብለህ የምትፈርድ ጽኑ ጨካኝ መሆንክን አውቃለሁና ፈርቼ ሃይማኖቴን በልቡናዬ ይዠዋለው በአዕምሮዬ ጠብቄዋለሁ የሚል ሃይማኖቱን ግን በሥራ የማይገልጥ ሰነፍ ሰውን ያመለክታል፡፡
ለዚህ ዓይነት ሰው የጌታ መልስ ደግሞ በምሳሌው መሠረት የሚከተለው ነው። እኔ ሕግ ሳልሠራ በአእምሮ ጠባይዕ አውቃችሁ ፤ መምህር ሳልሰጥ በሥነ ፍጥረት ተመራምራችሁ አውቃችሁ በሠራችሁት ብዬ የምፈርድ ጽኑ ጨካኝ መሆኔን ታውቃለህን? እንዲህስ ካወቅህ ሹመትክን ልትመልስልኝ ይገባኝ ነበር፡፡
ወጥቶ ወርዶ ለሚያስተምር በሰጠሁት ነበር፡፡ አሁንም የእርሱን መምህርነት ሹመት ነሥታችሁ (ወስዳችሁ) ለዚያ ለባለ ዐራቱና ለባለ ዐሥሩ ደርቡለት!
እርሱን ግን አውጡት የሚል ነው። ምክንያቱም ከበጎ ምግባር የተለየች እምነት የሞተች እንደሆነ ተጽፏልና። ዛሬም እያንዳንዳችን በዓቅማችን መጠን መክሊት ተሰጥቶናል፡፡ ነገር ግን መክሊቱን እንደቀበረው እንደዚያ ሰው የተሰጠንን ቀብረን ለወቀሳና ለፍርድ እንዳንሰጥ በአገልግሎታችን ልንተጋ ይገባናል፡፡
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ይህንኑ ሲገልጥ “ወዘሂ ይትለአክ በመልእክቱ፤ ወዘሂ ይሜህር በትምህርቱ. . .፤ አገልግሎት ቢሆን በአገልግሎታችን እንትጋ የሚያስተምርም በማስተማሩ ይትጋ የሚሰጥም በልግሥና ይስጥ›› (ሮሜ. ፲፪፥፯) በማለት ተናግሯል፡፡
ለመሆኑ አሁን ባለንበት የስግብግብነት ወቅት ዛሬ ‹‹አንተ በጎ ታማኝ አገልጋይ…›› ተብሎ በእግዚአብሔር ሊመሰገን የሚችል ሰው ማን ይሆን? በእውነት እንዲህ ተብሎ የሚመሰገን በጎና ታማኝ ካህን በጎና ታማኝ መምህር በጎና ታማኝ ምእመን ታማኝ ሰባኪና ታማኝ ዘማሪ ማግኘት ይቻል ይሆንን?
ነገር ግን መቼም አምላካችን ቸር ነውና በየዘመናቱ አንዳንድ ታማኝ አባቶችን እንደማያሳጣን ተስፋ አለን። ምክንያቱም ዛሬም ቢሆን እንደአባቶቻችን እንደቅዱሳን ሐዋርያት በእምነት፣ በትዕግሥት በፍቅር በተጋድሎ በየውሐት በትሕርምት በጸሊዓ ንዋይ በትሕትናና በትጋት በማገልገል የተሰጣቸውን መክሊት የሚያበዙ አገልጋዮች አሉ፡፡
የእነዚህ ክብራቸው በምድርም በሰማይም እጅግ የበዛና ራሳቸውን አስመስለው በትምህርት የወለዷቸው ልጆቻቸውም ለቤተ ክርስቲያን የተወደዱ የተከበሩ ልጆች ናቸው፡፡
ለምሳሌ ነቢየ እግዚአብሔር ሙሴ ነቢየ እግዚአብሔር ኢያሱን ፤ ቅዱስ ጴጥሮስ ቀሌምንጦስን፣ ቅዱስ ጳውሎስም ቅዱስ ጢሞቴዎስን ለቤተ ክርስቲያን አበርክተዋል፡፡ ሌሎችም አበው ቅዱሳን በወንጌል ቃል መንፈሳውያንና ትጉሃን የሆኑ ምእመናንን በሚገባ አፍርተዋል፡፡
ያላመኑትንም አሳምነው ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በመመለስ ለዘለዓለማዊ ክብር የበቁ እንዲሆኑ አስችለዋቸዋል። በተሰጣቸው ጸጋም አትርፈው አትረፍርፈው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሀብተ መንፈስ ቅዱስ እንድትጎበኝ አድርገዋል፡፡ የእነርሱም በረከታቸው ረድኤታቸው ቃል ኪዳናቸው ለሌሎች እንዲተርፍ ሆኖላቸዋል፡፡
በመሆኑም ክርስቶስ በደሙ የከፈለውን ወደር የሌለውን ዋጋ ዓለም አምኖና ተቀብሎ በክርስትና ሃይማኖት እንዲድንበትና እንዲጠቀምበት በማድረግ እንዲሁም በታማኝነትና በበጎነት አገልግሎታቸው ጥንትም ዛሬም ላለችዋና ወደፊትም ለምትኖረዋ ቅድስት ቤተክርስቲያን ድምቀትም ውበትም የሆኑት ቅዱሳን አበው ሊገኙ የቻሉት ከእግዚአብሔር ይልቅ ሰውን ደስ ለማሰኘት በመድከማቸው ሳይሆን የተጠሩበትን ዓላማና የጠራቸውን እርሱን በሚገባ አውቀውና ከልብ ተረድተው ለዘለዓለማዊ ሕይወት ተግተው በመሥራታቸው ነው።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 11 448 |
| 8 | የዐብይ ጾም ስድስተኛ ሳምንት ገብርኄር ይባላል፡፡
ገብርኄር ማለት ታማኝ አገልጋይ ማለት ነው፡፡ ስለ ታማኝ አገልጋይ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም ስንኖር ለፈጣሪያችን ያለንን ታማኝነትና የምናገኘውን ዋጋ በመዋዕለ ሥጋዌው
አስተምሯል፡፡
ቅዱስ ያሬድ ለዜማ መክፈያነት የዐብይ ጾምን ሳምንታትን ሲከፍል ገብርኄርን ተጠቅሟልና እኛም ስለ ገብር ሄር ጥቂት እንበል፡፡ ልዑል እግዚአብሔር አምላካችን በነቢዩ አንደበት አድሮ፤ “እከሥት በምሳሌ አፉየ፤ ወእነግር አምሳለ ዘእምትካት፤ አንደበቴን /ነገሬን/ በምሳሌ እገልጣለሁ፤ ከቀድሞ ጀምሮ የነበረ
ታሪክና ምሳሌ እናገራለሁ” አለ፡፡
ይህም ማለት ወንጌልን በምሳሌ አስተምራለሁ፤ በመልከ ጼዴቅ ዘመን አስቀድማ የተሠራችና ታይታ የጠፋችውን ወንጌልን እናገራለሁ፡፡ ይህን ታላቅ ምሥጢር ሐዋርያው ሲያብራራ “ከመ በአሚን ያጸድቆሙ እግዚአብሔር ለአሕዛብ አቅደመ አሰፍዎቶ ለአብርሃም ከመ ቦቱ ይትባረኩ ኲሎሙ አሕዛብ ፤ በአንተ አሕዛብ ሁሉ ይባረካሉ ብሎ ወንጌልን ለአብርሃም አስቀድሞ ሰበከ” ብሏል፡፡ /ገላ. ፫፥፰፣ መዝ. ፸፯፥፪
በዚሁ መሠረት ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌለ መንግሥተ ሰማያትን ለልዩ ልዩ ወገኖች በልዩ ልዩ ምሳሌ አስተምሯል፤ ከላይ በተገለጠው ኃይለ ቃል መነሻነት ሁለት ምሳሌያትና አንድ ቃለ ትንቢት ቀርበዋል፡፡ ከምሳሌያቱ
የመጀመሪያው በዐሥሩ ደናግል አንጻር የቀረበው ምሥጢር ሲሆን፤ ሌላኛው ደግሞ ወጥተው ወርደው ነግደው ያተርፉበት ዘንድ ገንዘቡን ስለሰጠ አንድ ነጋዴ የሚናገረው ነው፡፡
የትንቢቱ ምሥጢራዊ ይዘት የሚያስረዳውም ስለ ኅልቀተ ዓለም አይቀሬነት ነው፡፡ ስለሆነም በዚህ ዕትማችን ወጥተው ወርደው ነግደው እንዲያተርፉበት ከጌታቸው የተሰጣቸውን መክሊት ስለተቀበሉት አገልጋዮች ሕይወት እንመለከታለን፡፡ ፈጣሪያችን አእምሮውን ለብዎውን /ማስተዋሉን/ ያድለን፡፡
ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለደቀ መዛሙርቱ ያስተማራቸው ምሳሌያዊ ትምህርቶች በቅዱስ መጽሐፋችን በሰፊው ተጽፈው እናገኛለን፡፡ የእነዚህ ትምህርታዊ ምሳሌዎች መሠረታዊ ሀሳብና ዓላማም የእግዚአብሔርን መንግሥት የምናገኝበትን የታማኝነትን ሥራ እንዴት መሥራት እንደሚገባንና መሥራትም እንደምንችል ማስተማር ነው፡፡
ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለመንግሥተ ሰማያት ምሥጢር ያስተማራቸው ብዙ ምሳሌዎች ያሉ ሲሆን ከእነዚህ ብዙ ምሳሌያዊ ትምህርቶች መካከልም እንዲያተርፉበት መክሊት ስለተሰጣቸውና ስለተመሰገኑት መልካም አገልጋዮች፣ እንዲሁም መክሊቱን በመቅበሩ ምክንያት በጌታው ስለተወቀሰውና ፍርድን ስለተቀበለው ሰነፍ ሰው ታሪክ፣ የታሪኩም ምሥጢር ምን እንደሚመስል የተጻፈው ትምህርት ነው።
ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህንን ምሳሌ የተናገረው /ያስተማረው/ በሚከተለው መልኩ ነበር፤ ‹‹ወደ ሌላ ሀገር የሚሔድ ሰው ባሮቹን ጠርቶ ያለውን ገንዘብ እንደሰጣቸው እንዲሁ ይሆናልና ለእያንዳንዱ እንደ ዓቅሙ ለአንዱ አምስት መክሊት ለአንዱ ሁለት ለአንዱም አንድ ሰጠና ወደ ሌላ ሀገር ወዲያውኑ ሔደ፡፡
አምስት መክሊትም የተቀበለው ሔዶ ነገደበት ሌላም አምስት አተረፈ፣ እንዲሁም ሁለት የተቀበለው ሌላ ሁለት አተረፈ፣ አንድ የተቀበለው ግን ሔዶ ምድርን ቆፈረና የጌታውን ገንዘብ ቀበረ፡፡
ከብዙ ዘመንም በኋላ የእነዚያ ባሮች ጌታ መጣና ተቆጣጠራቸው፡፡ አምስት መክሊት የተቀበለውም ቀረበና ሌላ አምስት መክሊት አስረክቦ፡- ጌታ ሆይ አምስት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ ሌላ አምስት መክሊት አተረፍሁበት አለ፡፡
ጌታውም፡- መልካም አንተ በጎ ታማኝ ባሪያ በጥቂቱ ታምነሃል በብዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው፡፡
ሁለት መክሊት የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፡- ጌታ ሆይ ሁለት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፡፡ እነሆ ሌላ ሁለት መክሊት አተረፍሁበት አለ፡፡
ጌታውም፡- መልካም አንተ በጎ ታማኝ ባሪያ በጥቂቱ ታምነሃልና በብዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው።
አንድ መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፡- ጌታ ሆይ ካልዘራህበት የምታጭድ ካልበተንህበትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ፤ ፈራሁም ሔጄም መክሊትህን በምድር ቀበርሁት ፤ እነሆ መክሊትህ አለልህ አለው፡፡
ጌታውም መልሶ እንዲህ አለው፡- አንተ ክፉና ሐሰተኛ ባሪያ ካልዘራሁበት እንዳጭድ ካልበተንሁበትም እንድሰበስብ ታውቃለህን? ስለዚህ ገንዘቤን ለለዋጮች አደራ ልትሰጠው በተገባህ ነበር።
እኔም መጥቼ ያለኝን ከትርፉ ጋር እወስደው ነበር፡፡ ስለዚህ መክሊቱን ውሰዱበት ዐሥር መክሊትም ላለው ስጡት። ላለው ሁሉ ይሰጠዋልና ይበዛለትማል። ከሌለው ግን ያው ያለው እንኳ ይወሰድበታል፡፡
የማይጠቅመውንም ባሪያ በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጡት፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል የሚል ነው፡፡
መክሊት ጥንት የክብደት መለኪያ ነበር:: አንድ መክሊት 30 ኪሎ ግራም ያህል ነው፡፡ በዚህ ምሳሌ ላይ እንደተገለጸውም መክሊት የሚለው ቃል ገንዘብን ያመለክታል፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ምሳሌ ውስጥ እርሱን የምናገለግል ሁላችን እንደየዓቅማችን ማድረግ የሚገባንን መንፈሳዊ የአገልግሎት ሥራንና በአገልግሎታችን ውጤታማ በመሆናችንም ከእርሱ የምናገኘውን ዘለዓለማዊ ክብርና ዋጋን እንዲሁም መሥራት የሚገባንን ባለማድረጋችንም ምክንያት የሚገጥመንን መለኮታዊ ቅጣትን አመልክቶናል፡፡
በዚህ ምሳሌ ውስጥ ባለ አምስት የተባለው በቂና ፍጹም ትምህርት ተምሮ ሌላውን መክሮ አስተምሮ ራሱን አስመስሎ የተካ ያወጣ ነው፡፡
በተመሳሳይም ባለ ሁለት የተባለው እንደ መጀመሪያው ሁሉ ተምሮ ሌላውን መክሮ አስተምሮ ራሱን አስመስሎ ያወጣ ሲሆን ባለ አንድ የተባለው ደግሞ ተምሮ ሳያስተምር የቀረ በስንፍና በቸልተኝነት በማን አለብኝነት ሕይወት ተገድቦ የቀረ ሰው ነው፡፡
ይቀጥላል
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 9 744 |
| 9 | #ማረኝ
ማረኝ /3/ መመኪያዬ
አርጅቻለሁ እኔስ በኃጢያት ጎስቁዬ/2/
ከፊቴ ናትና ኃጢያቴ ሁል ጊዜ
ተዉጫለሁ እኔስ በሐዘን በትካዜ
በፊትህ ክፋትን አድርጌያለሁ እኔ
ምንም ጽድቅ አልሰራሁ በሕይወት ዘመኔ
#አዝ
ከፊትህ መቅበዝበዝ መሰደድ ፈለኩኝ
ኃጢያት ከኋላዬ እያሳደደችኝ
ወዴት እሄዳለሁ መሸሸጊያም የለኝ
ምህረትህ መጠጊያ ዋሻ ካልሆነችኝ
#አዝ
የተሰባበረዉ አጥንቴ እንዲጠገን
በምህረት እና በቸርነት ዳሰኝ
የቀና መንፈስን አድስ በልቤ ዉስጥ
ነፍሴ በእልልታ በተስፋ ትለወጥ
#አዝ
ቅዱስ መንፈስህን ከእኔ ላይ አትዉሰድ
በንስሐ ድኜ በተስፋ እንድራመድ
አቤቱ ንፁህ ልብ ፍጠርልኝ እና
በደስታ ልስገድ በፍቅርህ ልፅናና
ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 8 585 |
| 10 | ✞ መልካም ስሞ ይኑረኝ ✞
ጌታ ሆይ በብዙ ስውጠኝ ፪.
ከመልካም ሽቱ መልካም ስሞ ይኑረኝ ፪.
ሞት ሞታለብሰውነ ያቺን ዛፍ ነቅፌ
ያንተን ስሞ ያስጎምዠኝ እርሱ ይሁን ትርፌ
አንተን ብቻ እንዳይ ዓይኔን ኳስው እምነት
አስረህ አስቀምጠኝ በፍቅር ሰንሰለት
አዝ= = = = =
ወንድሙን ሚያታልል ተረከዝ የሚይይዝ
የያዕቆብ ካባው አይታይ በ'ኔ ወዝ
ይኑረኝ መልካም ስሞ ልትታገለኝ ና
እስራኤል ሆይ በለኝ ስሜን ስውጥና
አዝ= = = = =
በደማስቆ መንገድ አይለቅ ዘመኔ
ከሰማይ ብርሃን ያንጸባርቅ ወደ'ኔ
የእውነት ለውጠኝ ትችላለህ አንተ
እንዴት ክፋ ላውጣ አንተ ለ'ኔ ሞተህ
አዝ= = = = =
ስሜን ባገኘውም ሄጄ ጎልጎታ
አሁንም እንዲያው ነኝ ለውጥየለኝም ጌታ
ከሚቃጠለው ስብ ይከፋል ስም ሽታው
አማኝ መባል ብቻ ምንድን ነው የሚጠቅመው/፪/
አዝ= = = = =
በደማስቆ መንገድ አይለቅ ዘመኔ
ከሰማይ ብርሃን ያንጸባርቅ ወደ'ኔ
የእውነት ለውጠኝ ትችላለህ አንተ
እንዴት ክፋ ልሁን አንተ ለ'ኔ ሞተህ
መዝሙር
ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯ | 8 486 |
| 11 | ✞ ኃይልህ ሲገለጥ✞
ኃይልህ ሲገለጥ በሰማይ(፪)
አቤት ማን ይቆም ይሆን ከፊትህ
ማን ይቆም ይሆን(፬)
አቤት ቀንደ መለከት ሲነፋ
አዋጅ ሲታወጅ በይፋ
ጻድቃን ሲጠሩ ለተድላ
ምን ይሆን የእኛ ተስፋ
አዝ= = = = =
አቤት መላእክት ሰማዩን ሲያርሱት
ቀድመው ሲሰሙ መባርቅት
ያልታየና ያልተሰማ
ድምጽ ሲሰማ ከራማ
አዝ= = = = =
አቤት ሰባቱ ነፋስ ተከፍተው
ምድርን ሲያውኩት ቀስፈው
ሲታዘዝ የባህር ሞገድ
ምድሪቱን ሊከድናት ለፍርድ
አዝ= = = = =
አቤት ሲጠሩ ጻድቃን ቅዱሳን
መልካም የሠሩ ቡሩካን
በምድር የሠሩት ትሩፋት
ሲያቀርቡ ለአምላክ ስብሐት
አዝ= = = = =
አቤት ኃጥአን ግን ለፍርድ ሲጠሩ
በጨለማ ዓለም ሊቀሩ
የማይጠቅም ዋይታ ሆኖ
መዋረድ ይሆናል አስሉ
አዝ= = = = =
አቤት ሲጠሩ ጻድቃን ቅዱሳን
መልካም የሠሩ ቡሩካን
በምድር የሠሩት ትሩፋት
ሲያሰሙ ለአምላክ ስብሐት
መዝሙር
ሊቀመዘምራን ይልማ ኃይሉ
"አምላካችን ይመጣል"
መዝ፶፥፫
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯ | 8 482 |
| 12 | ደብረ ዘይት - ምጽዓተ እግዚእነ
🎤 በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ
🙏ለመምህራችን ቃለ ሕይወት ያሰማልን
#ሼር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 10 106 |
| 13 | #በስራዬ
በስራዬ የት ይሆን መግቢያዬ(፬)
ጨነቀኝ ጠበበኝ ኸረ ወዲያልኝ
ጨነቀኝ ጠበበኝ ነፍሴ ወዲያልኝ
ተሽክሜ የኃጢያት ክምር(፪)
ይመሻል ይነጋል በከንቱ ስዞር(፪)
ገሰገሰ ቀኑ ጨለመብኝ(፪)
ዋ ለነብሴ ምንም ስንቅ አልያዝኩኝ(፪)
#አዝ
በድያለሁ ወዳንተ ጮሃለሁ
ይቅር በለኝ እማፀንሃለሁ
ችላ አትበለኝ ከፊትህ ቆሜያለሁ(፪)
#አዝ
አለፈብኝ በከንቱ ጊዜዬ(፪)
እየጓጓሁ ለዚች ለሥጋዬ(፪)
በንስሐ ሳላጥበው እድፌን(፪)
ልትደርስ ነው ያች ፈተና ቀን(፪)
መዝሙር
ኪነጥበብ ወልደቂርቆስ
"በደላችንን ይቅር በለን"
ማቴ፮፥፲፪
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 10 465 |
| 14 | ✞ ወዴት ወድቆ ይሆን ✞
እንክርዳድ ኑፋቄን ገበሬው ለይቶ
መልካም ዘር ሲዘራ ወደ ማሳው ወጥቶ
ለአጨዳው ምጽአት ለበጋው አዝመራ
ወዴት ወድቆ ይሆን ክረምት የተዘራ /2/
ዘወድቀ ውስተ ፍኖት ሲዘራ ያለቀው
አእዋፍ ሰማይ መሳጤ ነጠቀው
ዘወድቀ ዲበ ኮክሕ ጥልቅ አፈር ከሌለው
በደስታ እየሰማ በችግር የካደው
ዘወድቀ ውስተ ሦክ ተጨንቆ እንዳይወጣ
በዓለም ትካዜ በስፍጠተ ብዕል ታንቆ ፍሬ አጣ
አዝ= = = = =
ውስተ ምድር ሠናይ የወደቀም ነበር
ዘወሀበ ፍሬ ሰምቶ ሚተገብር
ጌታዬ ከአራቱ ስፍራዎች በምሳሌ ካልከው
ወዴት ወድቆ ይሆን ከእኔ ልብ የላከው
እባክህ ጎተራ አበጅተህ ለአጨዳ ስትመጣ
ከፍሬያማው ክምር ዕድል እንዳላጣ
አዝ= = = = =
ከእሾህ ከጭንጫ ላይ ከመንገድ እንዳልቀር
ልቤ ልብ አግኝቶ በምግባር እንዲኖር
ራሴን መስማት ትቼ ላንተ ፈቃድ ልደር
መዝሙር
ዲያቆን ቀዳሜጸጋ ዮሐንስ
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯ | 10 114 |
| 15 | ደብረ ዘይት የዐብይ ጾም አምስተኛ ሳምንት
ደብረ ዘይት ማለት ቃሉ “ደብር” ሲል ተራራ ሲሆን “ዘይት” ሲል የወይራ ዛፍን ያመለከታል።
ባጠቃላይ ደብረ ዘይት የወይራ ዛፍ (የዘይት ዛፍ) የበዛበት ተራራ ማለት ነው። ቦታው በቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ከጎለጎታ (ቀራንዮ) ተራራ በስተምስራቅ በግምት ፪ ኪሎሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ ታላቅ ተራራ ነው።
በሁለቱ ተራሮች መካከል ጌቴሴማኒ የሚባለው ለምለም ስፍራ ይኸውም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የመቃብር ስፍራ ይገኛል።
የደብረ ዘይት ተራራ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብዙ ጊዜ የሚያድርበት፣ የሚያስተምርበት፣ ውሎ የሚያርፍበት ሥፍራ ነው። ሉቃ ፳፩፥ ፴፯፣ ሉቃ ፳፪፥ ፴፱፣ ዮሐ ፰፥ ፩
ከዚሁ ተራራ ላይ ነው ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያረገው። ኋላም በዳግም ምጽአት እዚሁ ተራራ ላይ ነው ለፍርድ የሚመጣው። /ሐዋ ፩፥፲፫/። "
" በዚህ ቀን ስለ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ወደ ምድር ስለመምጣቱ (ዳግም ምፅአቱ ) ይሰበካል።
ይህን ዓለምንም አሳልፎ ለመረጣቸውና ላከበራቸው ዘላለማዊ መንግሥትን ሊያወርሳቸው እንደሚመጣ ይነገርበታል። ይህ ቀንም እኩለ ፆም በመባል የሚታወቅ ሲሆን በዚህች በተለየች ቀንም ሁሉም እንደ የሥራው ፍርዱን ከአምላክ የሚቀበልበት መሆኑ፤ መልካም ላደረጉ መልካም እንደሚመለስላቸ ክፉም ላደረጉ የክፋታቸውን ዋጋ እንደሚያገኙ ይሰበካል።
ጌታም የአባቴ ቡሩካን የተዘጋጀላችሁን የክብር ቦታ ውረሱ በማለት ወዳጆቹን እንደሚጠራ ይነገራል።
" እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም እሳት በፊቱ ይቃጠላል " ማቴ.፳፬፡፩-፴፮ ኢየሱስም ከመቅደስ ወጥቶ ሄደ፥ ደቀ መዛሙርቱም የመቅደሱን ግንቦች ሊያሳዩት ቀረቡ።
እርሱ ግን መልሶ፦ ይህን ሁሉ ታያላችሁን? እውነት እላችኋለሁ፥ ድንጋይ በድንጋይ ላይ ሳይፈርስ በዚህ አይቀርም አላቸው። እርሱም በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ፥ ደቀ መዛሙርቱ ለብቻቸው ወደ እርሱ ቀርበው ንገረን፥ ይህ መቼ ይሆናል? የመምጣትህና የዓለም መጨረሻ ምልክቱስ ምንድር ነው? አሉት።
ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፦ ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ። ብዙዎች። እኔ ክርስቶስ ነኝ እያሉ በስሜ ይመጣሉና፤ ብዙዎችንም ያስታሉ። ጦርንም የጦርንም ወሬ ትሰሙ ዘንድ አላችሁ፤ ይህ ሊሆን ግድ ነውና ተጠበቁ፥ አትደንግጡ፤ ዳሩ ግን መጨረሻው ገና ነው።
ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣልና፥ ራብም ቸነፈርም የምድርም መናወጥ በልዩ ልዩ ስፍራ ይሆናል፤ እነዚህም ሁሉ የምጥ ጣር መጀመሪያ ናቸው። በዚያን ጊዜ ለመከራ አሳልፈው ይሰጡአችኋል ይገድሉአችሁማል፥ ስለ ስሜም በአሕዛብ ሁሉ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ።
በዚያን ጊዜም ብዙዎች ይሰናከላሉ እርስ በርሳቸውም አሳልፈው ይሰጣጣሉ እርስ በርሳቸውም ይጣላሉ፤ ብዙ ሐሰተኞች ነቢያትም ይነሣሉ ብዙዎችንም ያስታሉ፤ ከዓመፃም ብዛት የተነሣ የብዙ ሰዎች ፍቅር ትቀዘቅዛለች። እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል። "
#ሼር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 8 515 |
| 16 | ✞ለጥያቄዬ መልስ ስላጣሁ✞
ለጥያቄዬ መልስ ስላጣሁ
መጣሁ ከደጅሽ ሱባዔ ገባሁ
ማን አፍሮ ያውቃል ባንቺ ለምኖ
በኪዳንኪ ተማህጽኖ
የነፍሴ እረፍቷ ታዛ መጠጊያ
ካንቺ ተገኝቷል የሞቴ መውጊያ
በሰላምታሽ ድምጽ ተባርኳል ቤቴ
የጌታዬ እናት ለኔም እናቴ
ማርያም ኩኒ ለሕይወትየ ፀወኖ
እስመ ተማኅፀንኩ አንሰ ተማኅፅኖ
ለሥዕልኪ ስዕለ አድኅኖ እሰግድ ለኪ
(ማርያም የሕይወቴ መጠጊያ
ሁኚኝ መማጸንን ተማጽኜሻለሁ
ለሚያድን ስዕልሽ እሰግድልሻለሁ)
አዝ= = = = =
ቀንን ስናፍቅ በለሊት ሆኜ
አላተረፍኩም በሰው ታምኜ
ቁልፉ ልጅሽ ነው ለቋጠሮዬ
አሳስበሽልኝ አልፏል ስቃዬ
ኪዳነ ምሕረት ኩኒ ለልቡናየ ብርሃኖ
እስመ ተማኅፀንኩ አንሰ ተማኅጽኖ
ለስእልኪ ስዕለ አድኅኖ እሰግድ ለኪ
(ኪዳነ ምህረት ሁኚ ለልቤ ብርሃን
መማጸንን ተማጽኜሻለሁ ለሚያድን
ስእልሽ እሰግድልሻለሁ)
አዝ= = = = =
ጉልበቴ ዝሎ ቀልዬ ሳለሁ
በኪዳን ጥላሽ ተስፋ አግኝቻለሁ
ደጅሽ መጥቼ ኃይሌ ታደሰ
ያሳዳጆቼ ምክር ፈረሰ
ወላዲተ አምላክ ኩኒ ለእርቃንየ ክዳኖ
እስመ ተማህጸንኩ አንሰ ተማህጽኖ
ለሥዕልኪ ስዕለ አድህኖ እሰግድ ለኪ
(ወላዲተ አምላክ ለመራቆቴ ልብስ
ሁኚኝ መማጸንን ተማጽኜሻለሁ
ለሚያድን ስዕልሽ እሰግድልሻለሁ)
አዝ= = = = =
የዝናሙ ምንጭ ፈጣን ደመና
ከ ሴቶች ሁሉ ክብርሽ ገናና
አንድያ ልጅሽ ወይን አድርጎኛል
ከትናንት ይልቅ ዛሬ ባርኮኛል
በሊቀ መዘምራን
ዲ/ን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
"የአስጨናቂዎችሽም ልጆች አንገታቸውን
ደፍተው ወደ አንቺ ይመጣሉ፥
የናቁሽም ሁሉ ወደ እግርሽ ጫማ ይሰግዳሉ።"
ኢሳ ፷፥፲፬
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯ | 10 707 |
| 17 | ✞ ባክኛለሁና ✞
ባክኛለሁና በሥጋ ፈተና
የዚህ አለም ሀዘን ጫፍ የለውምና
ፈጥነሽ ወደኔ ነይ ከትንሿ ቤቴ
አጽናኚኝ እመአምላክ ድንግል እመቤቴ
ባህሩ ትልቅ ነው ድንግል እመቤቴ
ትንሽ ናት መርከቤ ድንግል እመቤቴ(፪)
የመንገዴ መሪ ድንግል እመቤቴ
አንቺው ነሽ ወደቤ ድንግል እመቤቴ(፪)
አዝ= = = = =
በመንገዴ ብዝል ድንግል እመቤቴ
ዓለም ትስቃለች ድንግል እመቤቴ(፪)
መመኪያ እናቱ ድንግል እመቤቴ
ወዴት ነች እያለች ድንግል እመቤቴ(፪)
አዝ= = = = =
በቀቢፀ ተስፋ ድንግል እመቤቴ
እንዳልወድቅብሽ ድንግል እመቤቴ(፪)
በቀንም በሌሊት ድንግል እመቤቴ
ተስፋዬ አንቺ ነሽ ድንግል እመቤቴ
ተስፋዬ የሆንሽ ድንግል እመቤቴ
አዝ= = = = =
የለም ያተረፍኩት ድንግል እመቤቴ
ወጥቼ ወርጄ ድንግል እመቤቴ
ትርፌ አንቺ ብቻ ነሽ ድንግል እመቤቴ
የግሸኗ እናቴ ድንግል እመቤቴ
ፅዮን አማላጄ ድንግል እመቤቴ
መዝሙር
ቀሲስ ወንደሰን በቀለ
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯ | 9 664 |
| 18 | join 👇👇👇
https://t.me/ortodoxtewahdomezmur
join👆👆👆 | 3 583 |
| 19 | 👉እንኳን አደረሳችሁ
"ሐና እና ኢያቄም" ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ ድንቅ የልደታ ማርያም መዝሙር
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@aregawi
@aregawi
@aregawi
#ሼር ይደረግ የተዋህዶ ልጆች 🙏 | 3 585 |
| 20 | ☞ግንቦት 1 ቀን የአምላክ እናት የእኛም እናት ለሆነች ለቅድስተ ቅዱሳን
ለንጽህተ ንጹሀን ለወላዲተ አምላክ የዓመታዊ የልደቷ ማታሰቢያ በሰላም
አደረሳችሁ፡፡
☞ በዚች ቀንም የእመቤታችን ወዳጅ ጻድቁ አባታችን አቡነ ቆስጦስ
የተወለዱበትም ቀን ነው፡፡
☞አምላክን የወለደች የእመቤታችን ማርያም እናት ብፅዕት የሆነች የቅድስት
ሐና ተአምር ይህ ነው፡፡ ጸሎቷና በረከቷ ከሁላችንም ጋር ይሁን፡፡
☞ከይሁዳ ወገን የሚሆን አንድ ሰው ነበር፡፡ ስሙም ኢያቄም ይባላል፡፡ ከካህናት
ወገን የምትሆን ሴትም አገባ፡፡ ሰሟም ሐና ይባላል፡፡ ሁለቱም ደጋግና የተወደዱ
ነበሩ፡፡ በእግዚአብሔር ሕግም ይኖሩ ነበር፡፡ ሚስቱም መካን ነበረች፡፡ ዘወትርም
ወደ ቤተ እግዚአብሔር ይሔዱ ነበር፡፡ ልጅ ይሰጣቸው ዘንድም በለቅሶና
በመጨነቅ ለእግዚአብሔር ጸሎት ያቀርቡ ነበር፡፡ ከገንዘባቸው ለድሆች ለጦም
አዳሪዎች ለቤተ ክርስቲያን ይሰጡ ነበር፡፡
☞ከዕለታት በአንዲት ቀንም ኢያቄምና ሚስቱ ሐና መጡ፡፡ ወደ ቤተ መቅደስም
ገቡ፡፡ ለጸሎት ቁመው ሳለም ርግቦች ከልጆቻቸው ጋር ሲደስቱ ተመለከቱ፡፡
ተመልክተውም ልጅ ሰላልነበራቸው ፈጸመው አዘኑ፡፡ ከኃዘናቸው ብዛት የተነሣ
ፈጽመው ተኙ፡፡ ሐናም ተኝታ ሳለች በባሏ በኢያቂሞ እጅ የነበረች በትር አብቤ
አፍርታ ተመለከተች፡፡ ይህቺ ፍሬም በሐና እቅፍ እንዳለች ሆና ነበር፡፡
☞ነቅተውም ተደሰቱ እርስ በርሳቸውም ሰላዩት ነገር ተነጋገሩ፡፡ፈጣሪን
አመሰገኑ፡፡ የፈጣሪ ፈቃድ ይሁን ብለው ወደ ቤታቸው ገቡ፡፡ ከዚህ በኃላ ሐና
ፀነሰች፡፡ ፅንሷም ታወቀ፡፡ ለእግዚአብሔርም ተሳለች ልጅ ከሰጠኝ
ለእግዚአብሔር መሥዋዕት አድርጌ እሰጣለሁም አለች፡፡
☞ጸሎትም ልመናን እያበዛች ኖረች፡፡ ገንዘቧንም ለችግረኞችና ለጦም
አዳሪዎች በፍጹም ደስታ ትሰጥ ነበር፡፡ ከምግብ ሁሉ ተከለከል ነበር፡፡ ልመናንና
ስግደትን ታበዛ ነበር፡፡ የሰጣትን ፈጣሪ ይጠብቅላት ዘንድ ትለምን ነበር፡፡
☞ከስድስት ወር በኃላ የሐና መፅነሷ ታወቀ፡፡ ዘመዶቿ የቧሏ ዘመዶች ሰሙ፡፡
ወደ እርሷም መጡ፡፡
☞ዘመንሽ ካለፈ በኃላ የተደረገው ይህ ነገር ምድንው ነው አሏት፡፡ ፅንሷን
ይመልከቱ ዘንድም ሆዷን ዳሰሱ፡፡ ከሐና እናት ወገን ማየት የተሳናት የአርሳብን
ልጅ የምትሆን አንዲት ሴት ነበረች፡፡ ምንም ሳታውቅ ዐይኗን ዳሰሰች ያን ጊዜ
ዳነች፡፡
☞ሐናንም ሐና ለአንቺ ብፅዓን ይገባሻል፡፡ ከዓለም ፈጥረታት እንደ አንቺ
በማሕፀኑ የዕውራን ዐይን የፈወሰ የለም አለቻት፡፡ ዘመዶቿም ሰገዱላት፡፡፡
☞ሐናም ፀሐይ ከአጥቢያ ኮከብ እንደሚበልጥ በእርሱ ላይ ከፍ ከፍ አለች
ከበረች፡፡ ዜናዋም በዓለም ዳርቻ ሁሉ ተሰማ፡፡ ድውያንን ሕሙማንን ሁሉ
እመጡ፡፡ ማሕፀኗን እየዳሰሱም ይፈወሱ ነበር፡፡
☞ሁሉም በማሕፀኗ ሳለ የፈወሰው ሲወለድማ እንዴት ይሆን አሉ፡፡
☞የእስራኤል ልጆችም ይህ ሰምተው ተሰበሰቡ፡፡ ሰለዚህ ሁኔታ ምን እናድርግ
ኢያቄምና ሐና እንሆ መንግሥት ከፍለዋልና፡፡
☞ሐና ፀነሰች በማሕፀኗም ትፈውሳለች፡፡ በእኛ ላይም ልትነግሥ ነው አሉ፡፡
እንዱ ሰውም ይህ ያስጨንቃችኀል? ኑና እንደ ተጻፈ በድንጋይ ወግረን
እንግደላቸው አለ፡፡ ሁሉም ተገረሙ፡፡
☞በመንፈቀ ሌሊት በሆነ ጊዜም ስሙ ገብርኤል የሚባል መልአክ ከሰማይ
ወረደ፡፡
☞ሐናና ኢያቄምንም በዘመድ የከበራችሁ ሆይ ተነሡ አላቸው፡፡ ወደ ሊባኖስ
ተራራም ወሰዳቸው፡፡ በዚያም ሰወራቸው፡፡
☞የመውለጃዋ ጊዜ በደረሰ ወቅት ግንቦት 1 ቀን ከፀሐይ የምታበራ ልጅን
ወለደች፡፡ የደም ግባቷም ከስኳር ይልቅ ይጣፍጣል፡፡ የመዓዛዋ ሽታም ከሽቱ ሁሉ
ይበልጣል፡፡
☞ብላቴናቱንም ማርያም ብለው ጠሯት፡፡ ሰባቱ ቀን በፈጸሙ ጊዜም በሰላም
ወደ ቤታቸው ገቡ፡፡ ለችግረኞች ለምስኪኖች ምጽዋትን ይሰጡ ነበር፡፡
☞ይቺን የተመረጠች ድንግል ማርያምን ያሰገኘችን ቅድስት ሐና ማርያምን
እናመሰግናት፡፡
☞ቅድስት ሐና ሆይ ካማረ ማኅሌት መጠራት ይልቅ ለሰም አጠራርሽ ሰላምታ
ይገባል፡፡
☞ቅድስት ሐና ሆይ ለአፍሽና በረዶ ለሚመስሉ ጥርችሽ ሰላምታ ይገባል፡፡
☞ቅድስት ሐና ሆይ ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክ ለጠባቸው ለጡቶችሽና
ለእንቺ ጉንጭም ሰላምታ ይገባል፡፡
☞ቅድስት ሐና ሆይ ድንግልን ለተሸከመ ለሆድሽና ንጹሕ ለሆድሽና ንጹሕ
ለሆነው ለልብሽ ሰላምታ ይገባል፡፡
☞ቅድስት ሐና ለሐሳብሽ ምሳሌ የማይገኝለት ቅድስት ሐና ሆይ የምድር
ፍጥረታትና የሰማይ ፍጥረታት ሁሉ ባንቺ ይመካሉ ባንቺ ያርፋሉ፡፡
☞ቅድስት ሐና ሆይ ለኅብርትሽና ለተመረቀው ድንግል ማርያምን ለተሸከመው
ማኅፀንሽ ሰላምታ ይገባል፡፡
☞ቅድስት ሐና ሆይ ለወገብሽና ለጭኖችሽም ከሁለቱ እግሮችሽና ጉልበቶችሽ
ጋር ሰላምታ ይገባል፡፡
☞የማርያም እናት የኢየሱስ ክርስቶስ አያት ቅድስት ሐና ሆን ድንገት እንዳንጠራ
ለንሰሐ ጥቂት ቆይኝ እንጂ ሞትስ በዓለም አይተወኝም፡፡
☞እንደ ዕንቁ የምታበሪ የማርያም እናት ቅድስት ሐና ሆይ የቆሬ ልጆች
አሰቀድመው እንደጠፋ በከንቱ የሚጠሉ የኢትያጵያና የህዝቦቿ ጠላቶች ለፍሬ
ሳይበቁ ይጥፎ፡፡
☞ቅድስት ሐና ሆይ ሰም አጠራርሽ በመለኮት ጨው የጣፈጠ በአርያም
የነገሥሽ የማርያም እናት ቅድሰስት ሐና ሆይ ለአንቺ ሰላምታ ይገባል፡፡
☞እንደ ዕንቁ የምታበሪ ካንቺ የወጣች ነበልባልን የተሸከመችው ድንግል
ማርያም በመሆኗ ቅድስት ሐና ሆይ ለአንቺ ሰላምታ ይገባል፡፡
☞አቤቱ የማርያም እናት የእምቤቴ ሐና ፈጣሪ አምላክ ሆይ ኢትያጵያን ህዝቦቿን
ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ አድናቸው፡፡
☞(ድርሳነ ኢያቄብ ወሐና)
☞የእናታችን የድንግል ማርያም አማላጅነት የእናቷ የእናታችን የቅድስ ሀና
ማርያም ጸሎቷ በረከቷ አይለየን፡፡
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@aregawi
@aregawi
@aregawi | 3 405 |
