fa
Feedback
📚 የኛ_ግጥም 📚

📚 የኛ_ግጥም 📚

رفتن به کانال در Telegram

نمایش بیشتر
أثيوبيا4 030دسته بندی مشخص نشده است
6 604
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
ጭቃ እሾህ ቢውጥ መዋጋት ቸግሮት አምቆ መያዝን ከ'ግዜሩ ተችሮት ወልከፍ ወልከፍ የሚል ሰበበኛ እግር ዘልቆ ውስጥ ቢገባ ከጭቃ እሾህ ግግር ተወጋሁ እንዳይል ጭቃ ሽፋን ሆኖ እሾህ ተሰውሮ "በጋ ይወጣል" አለ ህመሙን ዋጥ አርጎ። Semir

ለውብ ለይል ቅዳሜ 💛 semir aklu✍ The magic of thinking BIG!!!! ( ሂማ አታሳንሱ!!!!!!!) @ መግቢያ፣ ሂማ በአረብኛ ይሆንልኛል ብለን የምናስበው፣ ራእይ፣ ምኞት፣ ሃሳብ የምንፈጽምበት ትልቅ ወኔ ጭምር ማለት ነው። ሰሞኑን The magic of thinking BIG!!!! በሚል ርእስ የተፃፈ አንድ የፈረንጅ ሃገር መፅሃፍ እጄ ገባና ሳነበው ከረምኩ። አነቃቂና አደፋፋሪ መፅሃፍ ነው። በትልቁ እያሰቡ ፣ በትልቁ እያለሙ ፣በትልቁ እየሰሩ መኖር ለሰው የተሰጠው ፀጋ ነው፣ ለሰማይ ያሰቡት ጣራ ሳይነካ አይመለስም፣ ለተራራ ያለመ ኮረብታውን መነቅነቁ አይቀርም ይለናል። ከሰራነው ታላቅ ታሪክ ይልቅ ገና የምንሰራው ታሪክ ይበልጣልና ዛሬ በዙሪያችን የተሰጠንን ትንሽ እድል በግዙፍ ራእይ አጅበን ትልቅ ታሪክ እንሰራበት ዘንድ አበክሮ ይመክራል። ፈጣሪ በውስጣችን ያስቀመጠው አቅም ተአምር ለመስራት አይገደውምና በምናየው ገደብ ከመታሰር ይልቅ ተግዳሮቱ በውስጣችን ከተሸሸገው ቅምጥ አቅም ( potential) አንፃር ሲታይ ኢምንት ነውና በትልቁ እያለምን፣ በትልቁ እያሰብን ፣ ለትልቅ ታሪክ እንተጋ ዘንድ ወደፊት በሉለት ይለይለት እያለ ወደ ስኬት ዘመቻ ይመራናል። በመፅሃፉ ውስጥ የተቀናበሩትን እሳቤዎች አብዝቼ ባሰብኳቸው ግዜ ከገዛ ዘመዶቼ ጓዳ ከዘመን በፊት ሲነገር የቆየ አንድ ትርክት ወደ ማእደ ትውስታዬ ተዘረጋልኝ። እንዲህ ነው ነገሩ። ባንድ ወቅት አንድ ከራማ ሞልቶ የሚፈስባቸው ትልቅ ሼክ ነበሩ እየተባለ ይነገራል። ዱኣቸው ቅቡል የሆነ፣ ምርቃታቸው ገና ከአፋቸው ሳይወጣ የሚደርስ፣ በቱፍታቸው በሽታ የሚያሽሩ ነበሩ ተብሎ ይተረክላቸዋል። ብዙ ዘመን ሚስት ያገቡ ዘንድ ተለምነው ተለምነው " እምቢኝ ገና ነው የኔ ሰርግ" እያሉ ይመልሱ ነበር። ባንድ ወቅት የቤት ጉዳያቸውን የምታከናውን የቤት ሰራተኛ ( ካዳሚ) ወደ ቤታቸው አመጡላቸው። ጠንካራ፣ስራ ወዳድ፣ ተንከባካቢ ሴት ሆነችላቸው። እነ ሼህ ቅዳሜ ቅዳሜ ዱኣ አያልፋቸውም። ባንድ ቅዳሜ ቀጤማው ተነስንሶ፣ ሳሩ ተጎዝጉዞ፣ እረከቦቱ ተሰይሞ ሳለ የነፍስያቸው መቃኛ የሆነውን የዱኣ ላይ እንጉርጉሮ በሸገነው ድምፃቸው ያወርዱት ጀመር። እንጉርጉሯቸው ለቀዬው ሰው ሁላ ማነቃቂያ፣ ለካዳሚዋ ሴት ደግሞ በየሳምንቱ እየተናፈቀ የሚመጣ በረካ ነው። ካዳሚዋ ሴት የእነ ሸህን እንጉርጉሮ በሰማች ግዜ ነፍሷ ጥፍት ይላል። ድምፃቸውን በሰማች ግዜ ልቧ ይሸፍታል። ስኒው ከእጇ ያመልጣል፣ ጀበናው ገንፍሎ ይኩረፈረፋል፣ ይህ ሁሉ ሲሆን እሷ ግን በአድናቆት ተመስጣ የነሸህን አይን አይናቸውን እያየች አለሙን ሁሉ ትረሳለች። ወደ ዃላ ላይ አድናቆት ወደፍቅር ከፍ ብሎ ተቸገረች። ፍቅር እንደለከፋት አይነውሃዋ ያሳብቅባታል። ይህንን እውነታ ሼሁ በዘወርዋራ መንገድ አወቁት። ""።ይህች አቅሟን የማታውቅ ሴት እኔን መመኘቷ አሳቀኝም፣ አሳቀቀኝም"" እያሉ ከራሳቸው ጋር ሲያወጉ ከረሙ። ታዲያ አንድ ቅዳሜ የዱኣው ሃድራ በሞቀበት፣ ካዳሚዋ ሴት ቡና እያፈላች ሳለ እነ ሸህ ማንጎራጎር ጀመሩ። በቅኔ ተስፋሊያስቆርጧት ፈልገው ኖሮ እንዲህ ሲሉ ተቀኙ። እሳት ነዶ ነዶ፣ ሰማዩን አይፈጅም፣ የማያገኙትን፣ መከጀል አይበጅም። ይህን የሰማችው ካዳሚ እንዲህ መለሰችላቸው። እሳት ምድር ነዶ፣ ሰማይ ላይ ነው ጭሱ፣ አምላክ ለሚያደርገው፣ ሂማ አታሳንሱ። እነ ሸህ ይህንን መብረቅ የሆነ መልስ ሲሰሙ ተብረከረኩ። የልጅቱ ብርታትና የልብአፍቃሪነቷ አሸነፋቸው። ቡናው እየተቀዳ ሳለ እንግዲህ ሚስቴ አንችው ነሽ ብለው በወግ በማረግ ተዳሩ። አያችሁ እነ ሼህ እንዴት የቤት ሰራተኛዬ ጌታዋን ልታገባ ሽቅብ ትመኛለች?? ብለውአሰቡ። ዋናው ምስጢር ያለው ልብ ላይ ነው። ሰው በልቡ እንዳሰበ እንደዚሁ ይሆናል።የቤት ሰራተኛ ተብላ ብትጠራም እሷ ግን ራስዋን እንደ እቴጌ ቆጥራ ነው የኖረችው። ሃገር መንደሩ እንደ ገረድ አድርጎ ቢጥላትም እሷ ግን የእነ ሼህ ማጀት ባለ ሙሉ ሹመኛ እመቤት አድርጋ ነበር ያሰበችው። ለትንሽ ስራ ተጠራች እሷ ግን በትልቁ አሰበች እናም ባለ ትልቅ ህልም ሆና ሃሳቧን አሳካች። ከዚህ ወዲያ The magic of thinking BIG!!!! ይኖራል እንዴ???? የኛ ዘመዶች ከፈረንጆቹ በፊት አቅምና ጉልበት የሚሆን ሃገርኛ ፍልስፍናነበራቸው ማለት ይሆን???? #አንድ ታሪክ ደግሞ ከባህር ማዶ እንጨምር ቦክሰኛው መሀመድ አሊ ቴሬልን ለመግጠም ለጋዜጠኞች መግለጫ ሲሰጡ ቴሬል በድሮ ስሙ ካሲስ ክለይ እያለ ሲጠራው ለምን በባርነት የነጭ ስም ትጠራኛለህ በስሜ "መሀመድ" ለምን አትለኝም? ቢለውም ቴሬል "መሀመድ" ላለማለት "ክለይ" እያለ እምቢ በማለቱ ግብግብ ተፈጠረ። በ ቦክሱ ግጥሚያ ቀን መሀመድ አሊ ከሰባተኛው ዙር በኋላ እየቀጠቀጠው "ስሜ ማን ነው" (What is my name) እያለ ይጮህ ነበር። መሀመድ አሊ በቦክስ አለም እንዲህ ሲናደድ ታይቶ አይታወቅም። መጨረሻ ላይ ምን እንደተፈጠረ HBO በዚህ ጉዳይ documantary ሰርቶበታል በአጭሩ ግን ይህንን ተመልከቱ። ራስህን ሁን ራስህን አስከብር አትሽለጥለጥ። ** ሸንበቆ ቢረዝም ቅል አያንጠለጥልም ሂማ የሌለው ሰው ቢታገል አይጥልም እውነትም ሂማ አታሳንሱ!!!!!!!!!!

#​​እሱን_ተይው ..... 🤦‍♀ ስትወጅው ካልወደደሽ ስትቀርቢው ካልቀረበሽ ስትጠጊው ካልተጠጋ ስለፍቅር ካላወጋ አይሆንሽም እሱን ተይው አትድከሚ ላታገኚው ማፍቀርሽን እያወቀ በፍቅራችሁ ካልፀደቀ በቃልሽ ላይ ካላመነ ጥርጣሬ ከሰፈነ በመውደድሽ እየኮራ የውሸት ፍቅር ከሚሰራ ልብሽ ይቁረጥ እሱን ተይው ላንች ላይሆን አትወትውችው Semir aklu ━━━━━━✦✗✦━━━━━━━ Share & join

ወድቆ በመነሳት ያለፈን በመርሳት ለፍቅር መረታት ሀዘን ብሎ ፌሽታ በናፍቆት ስቅታ ባለፈው ትውስታ  እየተፅናናን በመልካም ልቦና በአምላክ ምስጋና ሂወት ስትቀና ሁሉን አሳልፎ የበላነው ተርፎ የሰራነው ገዝፎ ከፍታን ይዘናል ፍቅር ሰንቀናል ባለፈው አመት ላይ እድገት ጨምረናል፡፡ . Semir ami✍ Artot

💵አንድ ሰውየ ወደ ታላቅ የሱፊ መምህር ይሄድና የገንዘብ ስጦታ ሊያበረክትላቸው እንደፈለገ ይነግራቸዋል። እኚህ የሱፊው መምህርም ጥያቄው ከሰሙ ቡሃሏ"ብርግጥ ሀብታም ከሆንክ ስጦታህን እቀበላለሁ ደሀ ከሆንክ ግን አልቀበልምህም "ይሉታል። 🔆ሰውየውም "በርግጥ ሀብታም መሆኔ አይጠራጠሩ"ይሏቸዋል "ሀብታም ከሆንክ እንግዲያስ ምን ያክል ገንዘብ አለህ?" ይሉታል "ሁለት ሺ ወርቅ አለኝ ብሎ "ብሎ ይመልሳል " መምህሩም "አራት ሺ ቢሆንልህ ትመኛለህ "ይሉታል ሰውየው"በርግጥ እመኛለሁ " ይላል "ስደስት ሺ ወርቅ ቢሆንልህስ ትመኛለህ " ይሉታል ሰውየውም "መመኘቴ እማ አይቀርም" ይላቸዋል እሳቸውም "አስር ሺ ቢሆንልህስ "ይሉታል ሰውየውም "በርግጥም እመኛለሁ " በማለት መለሰ መምህሩም እንዲህ አሉት ተመልከቱ "ስትመጣ ሀብታም ነኝ ብለሀኝ አልነበረምን ነገር ግን አንድ አንዳች የሀብት ምልክት ግን አላየሁብህም። 💎እንዳንተ አይነት ደሀና በዙ የሚመኝ አይቸ ስለማላውቅ ከንተ ገንዘብ መቀበሉ አግባብ መስሎ አልታየኝም ለኔ ልትሰጠኝ የመጣሀውን ገንዘብ በጉደለትህ ጨምርበት እና ደስታ አግኝ ከዛ ሀብታም ስትሆን ያኔ ትሰጠኛለህ "በለው አሰናበቱት። 🔑 ከዚህ ምንረዳው ነገር ቢኖር እውነተኛ ሀብት ገንዘብ ሳይሆን ራስህን በማሸነፍ ስሜቶችን መግድል ሲሆን አንድ ሰው ሀብታም ነው ሚባለው ደሞ ባለው ነገር ሲረካና በቃኝ ሲያውቅ ብቻ ነው። ውብ አሁን❤️ Semir ami✍

#ተነድፈሽ_ክበሪ : : እኔ አልነደፍም የሚለው ፉከራ በገዛ አንደበትሽ በኩራት ሲወራ ካንዴም አስር ጊዜ ደርሶ ሰምቻለው ትክክል ነው ብሎም የሚያጎበጉብ ሰው በቅርብ አይቻለው። : : እውነት ነው ወይ ብዬም በዙሪያሽ ያሉትን ዞሬ ሳጤናቸው መላከፍ ነው እንጂ መንደፍ የማይችሉ ተራ ዝንቦች ናቸው። : : አፍኜው ነው እንጂ ድሮም ያንቺ ነገር ያንገበግበኛል ከንቱ ፉጨት ከቦሽ መኩራትሽ ገርሞኛል። : : ከ ዐጀቦችሽ አንፃር መደምደምሽን ሳይ አናገረኝ እንጂ የሆዴ መከፋት ባንቺ አልተጀመረም አደባባይ ቆሞ በጀሌ ተከቦ አጉል ጉራ መንፋት። : : እውነት እውነት ስልሽ ያለመነደፍሽን ሚስጥሩን ላወቀው ልክ እንደኔ ሁሉ ሆድ ቢብሰው እንጂ ቅንጣትም አይደንቀው። : : ይልቁን አንቺ ሴት አንዣባቢሽ በዝቶ እንዳትዘናጊ የማሩን እንጀራም ያንቺ እንድታደርጊ ተነድፎ ለመክበር በይ ከንብ ተጠጊ። Ami

sticker.webp0.58 KB

☞ ዝክረ ኸሚስ #6 - መሀባ - አንዳንዶቻችን መሀባ ፍቅር የሁሉም ነገር ጅማሮ ፣ የመድረስ ሁሉ መነሻው እንደሆነ ዘንግተነዋል ። እንኳን የሰው ልጅ ቀርቶ የእህል ቡሆ ‘ንኳ ለምጣድ ቢደርስም ሙሀቻው እርሾ አይኖረውም ። " ኺትማ ድረስ ያልዘለቀ እንኳን መሀባ ቡንም ደግ አይደለም ። " ብላናለች ሙሂቧ አቲቃችን ... መሀባ የደግ እድል በር ነው ። የሸጋ እጣ ደጃፍ ነው ፣ የእህል ውሃ መፍለቅለቂያ የዱንያ ሰታቴዋ ነው ። ተውበትን ( ንሰሃን ) ማስታወሻ ነው ። የተጥራራ ኒያ ሸጋ ሀርፍ ፈትሎ " ያረሂም " የሚያስለፈልፍ ያብጀልኝ ደጅህን ማዜሚያ ነው ። የጀነት መሻገሪያው መሰላልም .... መሀባ ፣ ፍቅር ። --- . ወቅቱን ነው አሉ ። . ያ የጎጋ ቅኝት ፣ በቁርበቱ ዜማ ፣ በደግ እድል በሩ ፣ በእጣው ጆሮ ግርጌ ፣ ተንጓጉቶ አንዳልነበር የገረረው ለዝቦ የጠናው ገራለት፣ ዱንያ አውታሩ ብዙ ስልት እየለወጠ ለስልሶ አዜመለት። . ( ማነው ? አይባልም ... ! ) . ካልሆነም ንጋቱ ፣ ካልገጠመም ምሽት ፣ ታጓጉል እሮሮ አፍታ ሳያላዝን ፣ ቀን ሰባራ ፍርዱን በመሀባ ፈጅር ይንጋልኝ እያለው፣ ሰው ብሎ ያለው ነው ... የመቸሩ ጤዛ ደጁን የበቀለው። ---- አንደዎ ሸህ ናቸው ። ደረሳቸውን ለሽንታቸው ማዳረቂያ ( ለኢስቲብራዕ ) የሚሆን ጠጠር ድንጋይ ይዞላቸው እንዲመጣ አዘዙት አሉ ። ደረሳውም በጠጠሩ ፋንታ ትልልቅ ድንጋይ በትክሻው ተሸክሞ መጣና ፊታቸው ላይ አስቀመጠው ። የዛኔ ሸህዮው " ኧረ አኸይ ምነው አንተዬ ይህንን ምን ላደርገው ነው ለመቀመጫ አላልኩህ " ሲሉት « እነሸህ ላንቱ ትንሽ ነገር እንደት ብየ ይዤ ልምጣ ! » ብሎ መለሰላቸው አሉ ። # መሀባ ⇩ አባቴም እንዲህ ሲሉ አዳምጫለሁ ። አንድ ቀን ከቁርአን ቤት ሸሆቹ ገርፈውኝ እያለቀስኩ ቤት ገባሁ ። ምን ሆነህ ነው ? ተባልኩ ። " ሉህህን ከትክሻ ለምን አወረድክ ብለው መቱኝ " አልኩ አቀርቅሬ ። ( ሉህ ) ከእንጨት የተሰራች መድ ቀለም እያጠቀሱ በሽንበቆ ስንጣሪ ገላዋ ላይ ተከትቦባት ተፅፎባት ጀማሪ ልጅ አሊፍ ብሎ የሚቀራባት ማንበቢያ ናት ። ጠፍጠፋ ሆና ከጫፍ እና ከጫፏ ተቦርቡራ ገመድ ገብቶባት ከትክሻ ትንጠለጠላለች ። አባቴም እንዲህ አሉኝ ። « እኔ በደረስነቴ በሸሆቹ ብትር አላለቅስም ። የሸሆቹ ብትር ያሳድጋል ። የትልቅ ሰው ቁጣ በረካ አለው ። » ካሉኝ ቡሀላ አብሯቸውቤት ለተቀመጠው ሰው እንዲህ አሉት ። « ምን የዛሬ ልጅ አዳብ የላቸው ። እኛ ስንቀራ ሸሆቻችን ካላዋጡን ቂረዐቱ አይያዘንም ነበር ። » ሱብሃነሏህ ... # መሀባ ---- መሀባ የሰውነት ግንዱ ዛፉ ነው ፣ ሓድራ ቅርንጫፉ ጥላው ነው ። ሓድራም ገበያ ነው ያደባልቃል ። እንደኒያችን እንደቅዋችን የነፍስ ቀለብ የምንሸምትበት ። ሸሬታው ኸለዋ መጅሊስ ነው ። እገሌ ተገሌ በሚል መኩራራት ሆሳ ጥላ ሓድራ ታዛውን አይዞርበትም ። የእኔ እንዲህ ነኝ የሚል የመኮፈስ አዛ ጠለሽ ሓድራ ቀዬውን አይጥልበትም ። ሰው በመሆን ብቻ በመርሀባ አደጌር የሚታደሙባት የፍቅር ሰርግ ያብሮነት ድግስ ነው ። ተጥራርተው ለአቅል የሶብር ውዱእን ተጅዲድ ( እድሳት ) የሚፈጠምባት የቀልብ ወጌሻነትም ዳኢም አሺት ነው .... መሀባ ። . ዛሬ ዛሬ የሓድራን ልቅና ፣ የመሀባን ደረጃ ፣ የምናይበት መልኩ ያበግናል ። « ታልደረሱ አይደረስም ! » ቢሆንም ነገሩ ፣ ግን ክረምቱን ሳያዩት ስለወንዙ አካሄድ ያለሸርጡ ያለሃቁ በራስ ቢሆን ግልብ የፈትዋ ኩሬ እንቀላቅልበት ማለቱን ስንሰማ ። አንዲት የዘማቾች የሓድራ ስንኝ ድንቅ ትልብናለች በጫሌ ቀበሌ ነው ። አርሂብ ተብሎ ደግ ሳይታደም ፣ ሓድራ አይገባም በመቀዳደም ። - ግደለም ሰው ማለት አያከስርም ጎበዝ ። አተረፈ አሉ ። ማን ? " ሰው ብሎ የገበየ " መገን ። .... ይቅናን ያቀናን ። መሀባም ሓድራ ነውና ቅሉ የገባያም ገድ አለውና .... ተገዱ ሳይታገዱ የወንድም ቁናው ላይንገረበብ ቲም ያለው ሂድያ ይስጠን ። # አሚን . ሀቢቢ ... ረሱል ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል « አንድ ወንድሙ የሚወደውን ነገር በማግኘቱ መደሰቱን የገለፀለት ሰው የትንሣኤ ቀን ልእልናው ከፍ ያለ አላህ ያስደስተዋል » « መልካምን ነገርን ትንሽ ናት ብለህ አትናቅ ። ወንድምህን ፈታ ባለ ፊት ማግኘት ቢሆንም እንኳ » ሙስሊም ሙስሊም ወንድሙን ሲያገኝ እሱን በማግኘቱ ብቻ ከምንም በላይ መደሠትና ደስ መሰኘቱንም በፊቱ ላይ ማስነበብ ይኖርበታል ። የወንድም የወዳጅ ሀቁን ስንቶቻችን እናውቀዋለን ። ----- ያረብ ።።።።።። በአሪፎች ቅልስ ... ከውንህ ይሞጠላል ፣ በተቅዬች ግርዶሽ ... ሀምድ ይንከባለላል ፣ ያመሰጋኝህ ግብር መርሀባን ሲታደል ... ቀኑን ሊደላደል - - ምንዳው ሲሞናደል ... እዝነትህ ሲዘንበው - - በረካህ ሲጎርፈው፣ ሰው ብሎ ይተማል ነፍስያ ሳይጠልፈው። .. ምናለ ጌትዬ ... . ስለሰው ብባባው ፣ ስለሰው ባነባው ፣ ነክሮኝ ብንቧችበት - - ባህሩን ብዋኝበት ... ሰው ብሎ ሰው ሊሆን ሰውነት ካለበት ። ምናለ ... ( እኔም በተመኔ በቀኔ ብቃና ... ! ) በገረረው ንጋት ... ወዙ በተላሰ ድርቅና ሰንጥቆት በተፍረከረከው ፣ የሙሂቡን ኪታብ ገልጦ ካለመቅራት ... አይኔን በገለጥከው - - ልሳኔን ባዳንከው ?! ሓድራ መሀል ውዬ - - ሓድራ መሀል ባድር ፣ በቻልኩት ዘምቼ ፣ ከዘመኔ አልቦ ላይ - - የቀልቤን ብሰድር ?! .. ኸሚስ አባ መደድ ፣ ኸሚስ አባ መውደድ ፣ የሓድራ ወናፉን ባድማሱ ሲያጋግም ፣ ምሽቱን ኮልኩሎ እየገሰገሰ ህዋው ሲያስገመግም፣ እየቀጠቀጠ ፣ ደግ እያቀለጠ ፣ ሆሳን ጊዜ ‘ንዲቆርጥ - - የዛገው ቀን ሊሳል ፣ ሞረድ ያዘለው ለይል ... ሰው በሚል ቡራቁ ከሚኔው ይደርሳል ። . የዛኔ ... ያን የማይሸርፈውን ፣ የመኣና ‘ጀታ አስጨብጠኝ አንተው ፣ ሰው ብዬ ቀን ስዬ ሰው ልሁን እንደሰው ። .. ምናለ ጌትዬ ... አንተ ላይሳንህ - - በትናንት መከለስ ፣ በሙሂቦች ቀለም - - በደግ መሰለስ ፣ ( አኔም በተመኔ በቀኔ ብቃና ... ! ) በገረረው ንጋት ... ወዙ በተላሰ ድርቅና ሰንጥቆት በተፍረከረከው ፣ የሙሂቡን ኪታብ ገልጦ ካለመቅራት ... አይኔን በገለጥከው - - ልሳኔን ባዳንከው !? ሓድራ መሀል ውዬ - - ሀድራ መሀል ባድር ፣ በቻልኩት ዘምቼ ... ከዘመኔ አልቦ ላይ የቀልቤን ብሰድር ?! .. ምናለ ... ?! _ Semir ami✍ @semiraklu

https://t.me/semiraklu Share and join Please 🙏

ቢያንስኮ እኔ ከጃይ ነኝ ወሏሂ ወሏሂ . ሊሞላ ሚተጋ ከልቤ አለ አንድ የመንፈስ ቡኃቃ ቢግቱት ዱስቱር ብሎ 'ሚቀበል አንድ የወይን እቃ መቼስ ክብ አርጎ ሰራው ከውኑን ሀኪሙ ቢሻው ሁሉም ባክኖ ባክኖ እንዲመለስ ከመነሻው ቢያበጃጁት እሱንም እንደ መስከረም የሚጠባ አንድ አለ በከውን ውቅይኖስ መሀል የተጣለ መርጋት ሚሻ ጣባ አንድ አለ የልብ ጉድጏድ አንድ አለ የልብ ጉድጏድ ሙሉት እባካችሁ እናንተ - ዱሉበት ባልተኸለቀው ባካኝ ኮነው ውሃ እንዳጣች ዋላ- ሰው እራሱን ቢያውቀው ግድ የለም ወይኑን ተውትና ብርሃን በሉት ብርሃን በሉት ሙሉት ግድ የለም ብርሃን ብርሃን እናንተ እናንተ ሩሃን አዎ ቢያንስ እኔ ከጃይ ነኝ እንደ መከጀል አይደለም - የመንፈስ ራቤ ብታውቁ ብርገፈገፍም መፅናት ብቻ ነው የህይወት ግቤ እሳት እራት ነኝ እሱ ደመራ ለሌት ሃሳቤ መፅናት ከወዴት ግን መሬቱስ ከወደ ምን ? የመኸለቅን አስኳለ ቅኔ አሳዩኝ ሀቄን እንዳምን ማውቅ ብቻ ምን ፈየደ የስንቱ ፅጌ ውበት መሰልህ - ቃል ሳይተነፍስ የተሰደደ ልብ ሳንለው ልብ ሳንለው ጎህ ይስቃል ወይ ምሽት ምን አለው በገና እለው ወይ ይደረድራል የልብ ሙዚቃ ነፍሴን ለሚል ሰው የሚፈስለት የልብ ቋንቋ ሳንመዝነው ሳንፈክረው ስንቱ ድንጋይ ነው እየዘመረ ውሃ ሚፈልቀው እስቲ በጌታ ምስጢር ንገረኝ ባልተኸለቀው ግዑዝ ነኝ ወይ አንተ ቅጠል ነኝ ወይ እሳት ነኝ ወይ አፈር ነኝ ወይ ውሃ ነኝ ወይ ምንድን ነኝ ምንድን ነኝ መልዓክ ነኝ ወይ ክንፍ አለኝ ወይ እስቲ ካሻህም ልቤን ስበረው - ብርሃን ይፍለቀው ባክህ በጌታ ምስጢር ንገረኝ ባልተኸለቀው ለካስ ህመም አለው እንዲጨብጡ ሲጋበዙ አንዱን የነፍስ ሀቅ - መሪር ፅዋዉን ሊጠጡት ስደት ይጀምራሉ በረሃውን ርቀው ከለመዱት ከእናት ጡት አደጉ ተብሎ መራራቅ ከልጅነት ህመም አለው ከድውያን የባሰ ህመም ያባክናል ያጣምናል እንደ ህልም ሩጫ በወዲህ በማይባል በህይወት መም በረቢ ድካ የለውም ስሜቱ ! ከናት እቅፍ መላቀቅ ከዛም ባተት ብለው ሳይዘጋጁ - ከህልውና ጥያቄ ላይ መውደቅ ሰኪና ከወዴት ግን መሬቱስ ከወደ ምን መልህቁስ ወዴት ይረፍ የሩሄ ሀመር ከምኑ ትርጋ መፅናት ከወዴት ይገኛል አጀብ አትልም ወይ የዘነጉት እውነት እንደ ምን ያስመኛል ጌታ ሆይ ነፍሴን ባርካት ነው ያለው እሱም ዋሴን ዋሴን እያለ ነው ልክ እንደ እኔ የባከነው አያ አያ ሙሌ ኦ አያ ሙሌ አባ መሌ እሱስ ጥያቄውን እሱን ትጉርሙን እየናፈቀው የፃፈው እንደ ሿሪ ደርዊሾች እየሾረ - ቅብዓ ሩሁን ነው የተንፈቀፈቀው የተኛው ፀሀይ እንደጠራው ግን እንጃ ብያንስ ገራም አርጎ ምን ሰራው የትኛው የሀቅ ወዳጃ የትኛው የነፍስ መወዳጃ እንጃ የኔስ እንጃ እንጃ ወሏሂ እንጃ ጌታ ሆይ እኔንም እኔን ሶላሁዲንን ልክ እንደዛኛው መልከኛ እንደ ሩሚ ያለ አሳየኛ ቢሻህ ከብረትም አዋደኝ - አርገኝ የቀዬው አንጠራኛ አጋፋሪ አርጌ ሾምኩህ ይበሉኝ ለዛውያዬ "እኔስ ዘምር ዘምር አለኝ መሾር መሾር አለችኝ - ሩሃኒዬ " ብለው የሚሾሙኝ ጠቁመኝ ብቻ ላፍቅርህ እንጂ በብርሃን ፍጥነት ከህዋው ጣለኝ - እንዳንዲት ዝሃ አመንምነኝ ጌታ ሆይ እመነኝ ጌታ ሆይ እመነኝ እናንተም አመላክቱኝ አመላክቱኝ በረቢ (እዩኝ ደግሞ እዩኝ ) ምን ነበረብት የዚች የጉንዳን ንክሻ ቢዘገይ ቀዳዳ ስንጥሬን ባለይ ምርጉዜ መሰበሩን ባላይ ባንዲት ስራይ ምራቅ ባቀፈች ትንኳሽ ማንቃት ምን ይባላል በዱኒያ ዛንጅር እንደ ታሰርኩ - ከልብ ሳይሆኑ ማቃቃት ባንዲት ተዓምር መጠራት ባንዲት ጉንዳን ንክሻ ሩሄን በረቢ ተጠርቻላው ማን ሊያመልጥ ካንተ ጥቅሻ ብቻ ብቻውን እንደ ወደደኩት - እንደ ባከንኩት በመውደድ ዋሻ ብቀር የምለው ወሸቴ ውሸቴ የዚች የጉንዳን ንክሻ ባያነቃኝ እንደ ሩሚ ባደባባይ ብንሆልል ምን ነበረበት - የሩሄን ብቻ ብቃኝ ምን ነበረበት ጉዞ አለብህ ባትለኝ ባታባዝተኝ ባታባክነኝ ይሄዋ ቀን ሀዘን በገፍ - ሌት በይባቤ ቀን ዘማሪ ወፍ - በሌት መፃጉእ ቋሚ ዘንግ ያጣ - የወይን ሀረግ ታች ታቹን አፈር ላሽ ባክናፋት ከነፎ ላዩን እንደ ማረግ እንደምን ይቻላል እንደምን በወዲህ ነው ማረፊያው በሉኝ - ሄጄ ልዋደቅ ሄጄ ልለምን ማወቅ ብቻማ መቼ ፈየደ ቋጥርሉኝ ክሩን ልግረፍ ክራሬን - ጅስሜ ነደደ አዎ እኔ ባካኝ አዎ እኔ ባካኝ እንደጣሉት ዋሽንት - የንፋስ አሰር የማይነካካኝ የማይዳብሱኝ የማይዳስሱኝ ይማይደርሱብኝ የሰው ልጅ ጣቶች የተነጠኩኝ በነፍስያ ክንድ መልከኛ ጧቶች እንደ ሙሃመድ የሂራ አባት ሂራ መሸሻ ያፍክሮት ዋሻ - ከፅሞና አግባት አዋዳት አፋቅራት ሩሄን !ጌታሆይ ልክ እንደሳቸው ሊረጉ ቢለው እንደ መሸጉት እንደዚህ ነበር የነፍሴ ጉጉት ያገኘኇቸው ያሃዋዕ ጌቶች - ሳይመሽጉበት በልቤ እልፍኝ እንዳሰኛቸው እንደፈለጉት ይሄዋ እኔው ልብ የማልባል የህይወት መባ በኑሮ መቅደስ መስዋት ቢሆነኝ እምባ የማፈስ መባ መባ በሉት ብርሃን ብርሃን እናንተ እናንተ እናንተ ሩሃን በውዲህ ነው በሉኝ በወዲህ ነው አመላክቱኝ ወደ 'ምስራቅ በር ' ለትንኝ የምንሰፈሰፍ - ግን ልማዕበል የማልበገር እስሊ እንድሆን የማሰላ ከሀቅ ከመክሊቴ ክር ፍንክች የማልል ጉበዝ ለልብ የምመች ዜማ እንድሆን ከንፍስ ደቦት የማልጣላ አመላክቱኝ አመላክቱኝ ይቅር በሉኝ ከቻላችሁ ብናኝ ቅያሜ ከልባችሁ እንዳይቋጠር በኔ ጉዳይ ከዚያ ወዲያ ግድ የለም ዝቅ ልበል እንደ እንጉዳይ ዝቅ ልበል ወደታላላቆቹ እግር ብቻ ቀና አርጉኝ ወደ ጀምበር አመላክቱኝ ወደ ፍኖተ ልቦና አመላክቱኝ ወደ ምስራቅ በር አመላክቱኝ እንደ ሸምሱዲን እንደ ሸምሱ ሸምሱ እንደ ጣዩ ጣዩ አዎ እሱን አመላክቱኝ አዎ ጣዩን ጣዩን ማነህ ሳይሉት ዘልቆ ልብ አቀጣጣዩን አመላክቱኝ ከዚያ ወዲያ አህያ ብቀልብ አላንስም የሰው ደጅ ብጠርግ አላንስም የሰው ቆብ ብሰፋ አላንስም ነብስያ ሚጋልበው ያ አቅል እንደራሴ ገላን ያነገሰ ዘበን ነው - ያራቀኝ ካንድ ራሴ አገልጋይ ብሆን አላንስም - አላንስም አላንስም ባልተቀለኽቀው አላንስም ፈወላሂ አላንስም ድሮም ነገር የጠፋው ገላ ሲነግስ ነው -በልቦናችን ስም ጌታ ሆይ አፍቅረኝ ከጃይ ነኝ ወሏሂ ከጃይ ነኝ ከብርሃንህ ፊት የሚርመሰመስ - ብናኝ አድርገኝ ግን ባከንኩ ደከመኝ አመላክቱኝ ባካችሁ ያንን ብርሃን አዎ ብርሃን ብርሃን እናንተ እናንተ - አዎእናንተ ሩሃን የሩሄ ሀመር ከምኑ ትርጋ መፅናት ከወዴት ይገኛል አጀብ አትልም ወይ የዘነጉት እውነት እንደ ምን ያስመኛል ናፍቆቱኮ ወዲያ ነው እሩቅ ነው ከባሻገር ነው በተዘናጋ የልብ ሀገር የመሸገ ሀቅ - የሩህ ጉጉት ነው መሞት ያስመኛል ናፍቆቱ - አዎ መሄድ መሞት ከዛው ከነፍሲቱ ሀገር - ከጥንቱ ክራሞት ወሶሊላሁማ አላሰይዲና ሙሃመድ (ሰ.ዐ.ወ) ማስታወሻ - ለዖማር #በድምፅ ሞክሬዋለሁኝ....ከዚህ በተሻለ እሰራዋለሁ የሚል ከተገኘም በደስታ ለማስተናገድ ዝግጁ ነኝ!💚 Semir aklu✍ @getamiyan @getamiyan

💚ከሆነውም ሆነ እየሆነ ካለው የሚበልጥ ነገር ወደፊትም ይሆናል... ይሄ እውነት ነው... የሁነቱ ሰበብ የመሆንን ያህል እብደት ግን መቼም ሊኖር አይችልም. 💜ሚዛን አልባ በሆነ አነዋወር ተቃኝተን የፈጠርነው ስምምነት እውነትን ደፍጥጦብን እንጂ በዚህ ሰዓት የአማኑኤል ሆስፒታል መሞላት የነበረበት እኮ በፍቅር አውድማችን ላይ ጠላትነትን በሚያበራዩ ሰዎች ነበር... የእውነት ታመናል. ❤️ለአፍታ እንኳ ራሳችንን ለማድመጥ ጊዜ የለንም... የስሜት እጅ የእውር ድንብር ሲመራን እንኳ የማንነቃ ከንቱዎች ሆነናል... 'ምን እያደረግሁ ነው?' ብለን አንጠይቅም... 'የተግባሬ ፍሬ ምን ይሆን?' ብለን አንመረምርም... መሸወዳችንን ላለማመን ታብየን እንጂ እኮ የእውነት ጥልቅ እንቅልፍ ውስጥ ነን... ጥል.....ቅ!!! መጥኔ ለኛስ!! ♥️ ደስተኛ መሆን እንፈልጋለን እንላለን... ታዲያ ደስታ ከሌሎች ደስተኝነት ውስጥ ካልተፈለቀቀ ከየት ይመጣል?... ♥️ ምቾትን እንፈልጋለን እንላለን.. ከቶ ከሌላው የጉስቁልና ማሳ ምቾት እንደምን ሊበቅል ይችላል?... ♥️ ፍቅር ያስፈልገናል እንላለን... ታዲያ እንዴት ነው ከመለያየት መዝሙራችን ውስጥ ሕብር የሚወለደው?... 🔆የእውነት እንቅልፍ ላይ ነን... ጥልቅ እንቅልፍ ላይ... እንዳንነቃ አዚም ያደረጉብንን የነፃነት ጠበቃ ብለን ክበናቸዋል... እሽሩሩ በሚሉን ላይ እንዳንሰለጥን 'ለአንተ ብዬ ነው' ማለታቸውን አምነናል. 🔆ወዳጄ መንቃት ከስጋ እንቅልፍ መላቀቅ አይደለም... እየመራህ ካለው ስውር የስሜት እጅ ነፃ መውጣት እንጂ... አዎን. የራስህ ሃሳብ ጌታ መሆንህን እስካላወጅክ ድረስ የከፋ ባርነት ውስጥ ነህ!! ✍ semir aklu ፍቅርን ከመስጠት በላይ ዕዳ አይኑርባችሁ!!

#አይ_ገጣሚ_ሞኙ : : የገጣሚው ግጥም ሀረጉ ስንኙ ዘንድሮስ ያስብላል አይ ገጣሚ ሞኙ። : : የዋህን እና ሞኝን ባንድ ላይ ሚያዋዛ የዋህ የዋህ ሚሸት ሞኝ ሞኝ የሚሸት ዛሬስ ግጥም በዛ። : : ተቀጥራ ምትቀር ሴት ባትመጪም ቅጠሪኝ ደግሞም የኔ ፍቅር አትመጪም አውቃለው ቢሆንም ሳልታክት እጠብቅሻለው። እያለ ገጠመ እያለ ተቀኘ አይ ገጣሚ ምስኪን እጅጉን ተሞኘ። : : ማይመጣ ሰው መቅጠር የሚቀር ሰው መቅጠር እንደው ምን ይባላል ከሞኝነት በቀር። : : ኮከብ ነው እንትንሽ ፀሀይ ነው እንትንሽ ያ እንትንሽ ደግሞ ጨረቃን ያስንቃል ዘንድሮው ገጣሚው መሬት እየኖረ መሬትን እረስቶ ሰማይን ያደንቃል። : : ለተሸከመችው እትብቱ ላለበት ግጥም ካልነቀሰ ያጠገቡን ትቶ ውበትን ፍለጋ ሰማይ ከጠቀሰ ሰማይ ካንዣበበ ሰማይ ካንጋጠጠ ብልሀት ኮስሶ ሞኝነት በለጠ። : : በየግጥሞቹ ቃል እያረቀቀ በየስንኞቹ ሴት እያደነቀ ውይ እንትኗ ሲያምር ውይ እንትኗ እያለ ባንባቢ ምናብ ውስጥ ቁንጅና እየሳለ ውይ እንትኗስ ይባስ ውይ እንትኗ ደግሞ ሰውነቷን ሙሉ ባድናቆት ቃል ስሞ ወረቀት ብዕሩን ብዙ ጊዜ አናድፏል እራሱን የሚያደንቅ አንድ ግጥም እንኳን ለራሱ ሳይገጥም እየው ዛሬም አልፏል። : : ገጣሚው በሞላ ከራስ በላይ ንፋስ መሆኑን ከረሳ በስንኝ ቋጠሮ በየግጥሞቹ ሌላ ሰው ካወሳ ከሞኝነት ውጪ ምን ይባላል እሳ። : : ያለማንም ግፊያ ያለማንም ሽሚያ ሊያፈቅራት አስቦ ዘንድሮ ገጣሚው ያለ የሌለውን ክፉ ቃል ሰብስቦ የሚያፈቅራትን ልጅ በርግማን አጥቧትል ቁንጅናዋን ነስቶ አስቀያሚ እንድትሆን ስለት አስገብቷል። : : የሚያፈቅሯትን ሴት የሚወዷትን ሴት ክፉዋን መመኘት ከዚህ የተሻለ አይገኝም ሞኝነት። : : ዘንድሮ ... እንዲ ነው ገጣሚው እንዲ ነው ስንኙ አይ ገጣሚ ምስኪን አይ ገጣሚ ሞኙ። #semir aklu

ምኞቴን በለገጣ ስገልፀው ይህን ይመስላል። ተስፋ ግን አልቆርጥም #ምህረት : : : ፍቅሬ ... ይህቺን ስሚኝ ዛሬ፣ በገረፍሺኝ ብዛት ላቤንና ደሜን ቀላቅዬ አኑሬ፣ ብሶት ሚባል ቀለም ለራሴው ፈጥሬ፣ እኔ አንቺን ስስልሽ ያሳብ ሸራ ወጥሬ ... «ፍቅርሽ»... ጫካ ኖሮ ኖሮ፣ ፀጉሩን አጎፍሮ፣ ወደ ስልጣን ሰማይ በደም እንዳረገው፣ ህዝብን አመካኝቶ ለራሱ ጥቅም ሲል እንደደነገገው፣ ዘርን መርጦ ብቻ ሚተገበረውን ያን «ህግ» ይመስለኛል፣ «ትዝታሽም» ደግሞ ሀገሬን የሚል ሰው የሚማቅቅበት «ወህኒ ቤት» ሆኖ በቅርብ ይታየኛል። : : ይልቅ የኔ ፍቅር ... ላም ባልዋለበት ኩበትን ለቀማ፣ የሚል ቃል ሳልሰማ፣ ፍቅርና ያን ህግ ትዝታና ወህኒን ምን ያገናኘዋል በሚል ሳልታማ፣ እንዴት አዋህጄ እንዴት አሳክሬ፣ ቀለምን ቀምሬ ሸራዬን ወጥሬ፣ ፍቅርሽን ከዚያ ህግ ወህኒን ከትዝታሽ፣ እንዳመሳሰልኩት ስሚኝ ቆይ ላስረዳሽ። : : ያኔ ባማን ደና፣ ፍቅራችን ሳይታመም እያለ በጤና፣ ባንድ ላይ ተሳስረን፣ ስንት ሽንቁር ደፍነን ስንት ካብ ሰርስረን፣ ኖረን ኖረን ኖረን፣ ሁሌ አንቺን አንቺን ስል ድንገት በቀን መጥፎ ባልሰራውት ጉድፍ፣ ሚዛነ ቢስ «ፍቅርሽ» እጅግ ጨክኖብኝ ህሊናዬ እስኪያድፍ፣ «በትዝታሽ» ጎጆ በናፍቆት ሰንሰለት እጅ እግሬን አስሮ፣ ፍርድሽ በኔ ፀንቶ እንደ ዕድሜ ይፍታ ያለ አመክሮ፣ ካንዴም ሁለት ሶስቴ ይግባኝ ጠይቄያለሁ፣ «ሰማይ አይታረስም ንጉስ አይከሰስም» የምትለው አንቀፅ አንቺም ቤት እንዳለች በርግጥ አውቄአለሁ። : : እርግጥ አውቅሻለሁ... ፍርድን አገምድሎ በመዶሻ ማለም፣ ሲያደርጉ አይተሽ እንጂ ያንቺ አሳብ አይደለም። : : ቢሆንም ቢሆንም ባገራችን ሰማይ አሁን ፀሀይ ወጥቷል፣🤣 ነገን የሚያበራ አዲስ ተስፋም ታይቷል፣🤣 ማሰር ሚለው ቀርቶ መማር ሚለው ፀንቷል፣🤣 ይህንም ታውቂያለሽ ጠማማውም ቀንቷል። : : እንዳምና ታችአምና እውነት ከቶ አይቀልም፣😂🤣 ዛሬ ባገራችን እንኳን ፍቅር ቀርቶ በርባን አይሰቀልም። ሀገሩን ሚያፈቅር ንፁ አፍቃሪ እንጂ አሸባሪ አይባልም። 🤣🤣🤣🤣🤣 : : እናልሽ የኔ እናት ያኔ አተሺው ቅጡን፣ እውነቱ ሳይጠፋሽ እያወቅሽ እርግጡን፣ የናፍቆትን ሾተል የትዝታ ማጡን፣ አንቺን በማለቴ ምንም ሳላጠፋ በኔ እንደበየንሺው፣ አሁን ነግቷል እና ካገርሽ ተምረሽ በይ በምህረት አንሺው። #semir aklu

ኗሪ እንጂ ሐጅ ቤት አይሰራም (ታደሰ ደምሴ) እየተቃቀፍን አንራራቅ እየተካበርን አንናናቅ ስንቀራረብ አንቃቃር እየተሳሳምን ፊት አንዟር በልሳን ውበት መካን ይብቃን ከወረት ጸድተን ፍቅር ይግባን ባንድ ተኝተን አይብረደን የበረዶ ማት አያስምጠን የቃል ሽንገላ ግብር አይሆንም ኗሪ እንጂ ሐጅ ቤት አይሰራም የናፍቆት ጅራፍ ካልገረፈን የትዝታ ወጀብ ካላማታን የዕምባ ማዕበል ካላጠበን መለየት ከሆነ ተገናኝተን የመውደድ ጥጉ መቸ ገባን! ይልቅ... ነፍስሽ ከነፍሴ ይወዳጁ ልብሽ ከልቤ ቀን ይዋጁ ከየራስ አለም ተሰብስበን አብረን እንክነፍ ሁሉን ትተን ያኔ ... አብረን ስንከንፍ... የጸሀይ ግለት አያጠቁረን~የብርድ በትር አያጠቃን በኛ ውስጥ ንግስናን ሽቶ ~ሀገረ ገዢ ንቆ አይደፍረን "ንጉስሽና ንግስቴ"~ መሆናችንን ችሎ አይነጥቀን! አዋን...! አብረን ስንከንፍ... የሲኦል ነፍሳት ግድ አይሰጠን የኩነኔ እዳው አያስፈራን አዎን... አብረን ስንከንፍ...! ፈጣሪ ከጽድቅ አይነጥለን ከፍቅር በላይ ምግባር ሽቶ~ትዛዛቶቹን አይጠይቀን እኔ ባንቺ አንቺ በኔ ~የገነትን በር እንሾልካለን! : : : ሹልክ...! semir aklu @getamiyan