fa
Feedback
EOTC Books ⛪️

EOTC Books ⛪️

رفتن به کانال در Telegram

📚 በዚህ ቻናል/ኦ/ተ/ቤ/ክ የምትቀበላቸውን ቅዱሳት መጻሕፍትን ለምዕመናን ተደራሽ ማድረግ ነው ይኸውም ከሀገራችን እንዲሁም ከውጪ ሀገር (ቤ/ክ የምትቀበለውን) ናቸው ። 💬 contact us @Jared2080 buy Ads? https://telega.io/c/EOTCBooks1 YouTube 👇 https://www.youtube.com/@zeEthiop

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام EOTC Books ⛪️

کانال EOTC Books ⛪️ (@eotcbooks1) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 18 869 مشترک است و جایگاه 4 295 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 1 785 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 18 869 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 09 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 292 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 14 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 10.75% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 5.54% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 2 030 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 046 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 7 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
📚 በዚህ ቻናል/ኦ/ተ/ቤ/ክ የምትቀበላቸውን ቅዱሳት መጻሕፍትን ለምዕመናን ተደራሽ ማድረግ ነው ይኸውም ከሀገራችን እንዲሁም ከውጪ ሀገር (ቤ/ክ የምትቀበለውን) ናቸው ። 💬 contact us @Jared2080 buy Ads? https://telega.io/c/EOTCBooks1 YouTube 👇 https://www.youtube.com/@zeEthiop

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 10 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

18 869
مشترکین
+1424 ساعت
+687 روز
+29230 روز
آرشیو پست ها
ራእየ ኒፎን መናኙ ጳጳስ ቅዱስ ኒፎን፤ የተጋድሎ ሕይወቱ፤ ትምህርቱና ራእዩ ትርጉም፡- በቀሲስ ታምራት ውቤ 2013 ዓ.ም
ራእየ ኒፎን መናኙ ጳጳስ ቅዱስ ኒፎን፤ የተጋድሎ ሕይወቱ፤ ትምህርቱና ራእዩ ትርጉም፡- በቀሲስ ታምራት ውቤ 2013 ዓ.ም

ሥርዓተ_ቤተ_ክርስቲያን_በክንፈ_ገብርኤል_አልታየ_1995_.pdf9.58 MB

ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን አዘጋጅ፦ ሊቀ ካህናት ክንፈ ገብርኤል አልታየ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሊቃውንት ጉባኤ አባል
ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን አዘጋጅሊቀ ካህናት ክንፈ ገብርኤል አልታየ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሊቃውንት ጉባኤ አባል

ቅብአት ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ወይስ ለካቶሊክ ይቅርባል? 🚫«ቅብአት» (የቅብአት እምነት/አስተምህሮ) በዋናነት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ እና የነገረ መለኮት (ክርስቶሎጂ) ክርክሮች ጋር የተያያዘ ነው። ይሁን እንጂ አስተምህሮውን ከሁለቱ አኳያ ስንመዝነው ለካቶሊክ አስተምህሮ ይበልጥ የቀረበ ሆኖ እናገኘዋለን። 🧠ይህንን በግልጽ ለመረዳት የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች እንመልከት፦ 1. የቅብአት አስተምህሮ አመጣጥ በ17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን (በተለይም በአፄ ፋሲለደስ ዘመነ መንግሥት) በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የክርስቶስን ባሕርይ በተመለከተ የተለያዩ የነገረ መለኮት ክርክሮች ተነስተው ነበር። ከእነዚህም አንዱ «ቅብአት» (ቅብዐታውያን) በመባል ይታወቃል። የእነሱ መከራከሪያ፦ «ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው የሆነው በመንፈስ ቅዱስ ቅብአት ነው» የሚል ነበር። ማለትም፣ ሥጋ ከመለኮት ጋር በተዋሐደ ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ መክበርንና መቅባትን አገኘ የሚል አመለካከት ነበራቸው። 2. ለካቶሊክ ወይስ ለኦርቶዶክስ ይቀርባል? ምንም እንኳን የቅብአት ወገኖች ራሳቸውን እንደ ኦርቶዶክስ ቢቆጥሩም፣ በነገረ መለኮት ፍልስፍናቸው ግን ከካቶሊክ (ከሮም/ምዕራባውያን) አስተምህሮ ጋር በእጅጉ ይገናኛሉ። ምክንያቱም፦ የባሕርይ መለየት (Duality) ዝንባሌ፦ የቅብአት ወገኖች «ሥጋ በመንፈስ ቅዱስ ተቀባ» ሲሉ፣ በክርስቶስ መለኮትና ሥጋ መካከል የተወሰነ የደረጃ ወይም የባሕርይ ልዩነት እንዳለ ያሳያሉ። ይህ ደግሞ ክርስቶስ ሁለት የተለያዩ ባሕርያት (መለኮትና ትስብእት) አሉት ከሚለው የካቶሊክ (ኬልቄዶናዊ) አስተምህሮ ጋር ይመሳሰላል። ✔የኦርቶዶክስ (ተዋሕዶ) አስተምህሮ ፦  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ይፋዊ አቋም ግን «ተዋሕዶ» ነው። ትምህርቱም፦ ክርስቶስ በተዋሕዶ ፍጹም አንድ ባሕርይ ሆነ (መለኮትና ሥጋ ያለመቀላቀል፣ ያለመለወጥ፣ ያለመጠፋፋትና ያለመለያየት አንድ ሆኑ)፤ እርሱ ራሱ ቀቢ፣ እርሱ ራሱ ተቀቢ፣ እርሱ ራሱ ቅብዕ ነው የሚል ነው። መንፈስ ቅዱስ ለክርስቶስ ሥጋ የሰጠው የተለየ ክብር የለም፣ በተዋሕዶ የራሱ የመለኮት ክብር የሥጋው ክብር ሆኗል ብላ ታስተምራለች። ☑️ባጭሩ
የቅብአት አስተምህሮ የበቀለውና የተከራከረው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ቢሆንም፣ የሃይማኖት ይዘቱና ፍልስፍናው ግን (የመቀባትና የባሕርይ መከፋፈልን ስለሚያስከትል) ለካቶሊክ አስተምህሮ ይበልጥ የቀረበ ነው። ለዚህም ነው በታሪክ የኦርቶዶክስ ሊቃውንት የቅብአትን ትምህርት ውድቅ አድርገው «ተዋሕዶ»ን ያጸኑት።

ከሐሳውያን አጥሚቂ ተብየዎች ተጠንቀቁ! ክርስቲያኖች የማንም መቀለጃ አትሁኑ።

✝እንኳን አደረሳችሁ ! ☞ሠረቀ ወርኀ ሐምሌ ቡሩክ፤ በሰላመ እግዚአብሔር ስቡሕ ወውዱስ፤ አሜን። ወአመ ፩፦ ✝ቅድስት ጾመ ሐዋርያት ንጹሐን (አርድእተ ክርስቶስ አምላክነ) ✝ተዝካረ በዓለ ልደታ ለእግ
✝እንኳን አደረሳችሁ ! ☞ሠረቀ ወርኀ ሐምሌ ቡሩክ፤ በሰላመ እግዚአብሔር ስቡሕ ወውዱስ፤ አሜን። ወአመ ፩፦ ✝ቅድስት ጾመ ሐዋርያት ንጹሐን (አርድእተ ክርስቶስ አምላክነ) ✝ተዝካረ በዓለ ልደታ ለእግዝእትነ ቅድስት ድንግል በ፪ ማርያም፥ ወላዲተ አምላክ፥ ጥዕመተ ስም (እመ ብርሃን፥ እመ ሕይወት ወመድኀኒት) ✝ተዝካረ በዓሉ ለመልአክ ክቡር፥ ራጉኤል ሊቅ፥ ሊቀ መላእክት ✝ወተዝካረ በዓሎሙ ለቅዱሳን፦ ኢያቄም ወሐና፥ ነአኩቶ ለአብ ወሚልኪ ጻድቅ፥ ወበርተሎሜዎስ ሐዋርያ፥ አባ ስልዋኖስ ገዳማዊ ወሊቀ ካህናት አሮን፥ ዮሴፍ ጻድቅ ወልደ ያዕቆብ ፳ኤል ❖ ወበዓለ ቅዱሳን አበው፦ ✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ ጻድቅ ወንጹሕ ወድንግል፥ ሐዋርያሁ ወሰማዕቱ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ፥ ማር ቶማስ ዘሕንደኬ፥ እም፲ወ፪ቱ ሐዋርያት (ዘገብረ መንክረ በላዕለ ብእሲት ዘሐረድዋ) ✝ቅድስት ወቡርክት፥ ስብሕት ወክብርት፥ ድንግል ወብጽዕት፥ መርዓተ ክርስቶስ፥ ቅፍሮንያ ሰማዕት፥ መስተጋድልት ንጽሕት፥ ዘወሀበት ነፍሳ ለእግዚአብሔር ✝ቅድስት ወቡርክት፥ ስብሕት ወክብርት፥ ድንግል ወብጽዕት፥ ኦርያና ኅሪት እመ ምኔት፥ መርዓተ ክርስቶስ፥ ዘሐጸነቶን ለደናግል (እኅታ ለቅፍሮንያ) ✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ ጻድቅ ወንጹሕ ወድንግል፥ ኃያል ወመስተጋድል፥ ሐዋርያሁ ወሰማዕቱ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ፥ ማር አግናጥዮስ ሊቀ ጳጳሳት፥ ምጥው ለአንበሳ ✝ክቡራን ወዐቢያን፥ ጻድቃን ትሩፋን፥ ወካህናት ንጹሐን፥ አባ ብዮክ ወአባ ብንያሚን መስተጋድላን፥ ገባርያነ ኃይል ወመንክር (ዘበልዕዎ ለከይሲ በእንተ ፍቅረ መድኅን) ✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ ጻድቅ ወንጹሕ ወድንግል፥ ጽሙድ ወመስተጋድል፥ ማር አባ ገብረ መድኅን መነኮስ፥ ብእሲ ሔር፥ ወልደ መስፍን ዘወሎ (ኢትዮጵያዊ) ✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ ጻድቅ ወየዋህ፥ ንጹሕ ወድንግል፥ ጽሙድ ወመስተጋድል፥ አባ በርተሎሜዎስ ✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ ጻድቅ ወንጹሕ ወቡሩክ፥ ጽሙድ ወመስተጋድል፥ አባ ክልዮስ መምህር፥ ወሊቀ ጳጳሳት ዘሮሜ ❖ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ። ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡

ልጄ ሆይ"
ዓለም ያለው ሁሉ ያልፋል፤ ነገር ግን የእግዚአብሔር ፍቅር አይያልፍም። ስለዚህ ልብህን በሚያልፍ ነገር አትጣ፤ በሚኖር ነገር ላይ አቆይ ። ”
አባ ጉባ✍️

"መጽሐፈ ወግሪስ" ስለ መነኮሳት አመጋገብ እንዲሁም ስስትንና ሆዳምነትን በማሸነፍ ምግብን ስለመዋጋት የሚያስተምር መጽሐፍ ነው። መጽሐፉ ምግብን ለሥጋ ፍላጎት ማርኪያ ሳይሆን ለነፍስ ዕድገትና ለጸሎት
"መጽሐፈ ወግሪስ" ስለ መነኮሳት አመጋገብ እንዲሁም ስስትንና ሆዳምነትን በማሸነፍ ምግብን ስለመዋጋት የሚያስተምር መጽሐፍ ነው። መጽሐፉ ምግብን ለሥጋ ፍላጎት ማርኪያ ሳይሆን ለነፍስ ዕድገትና ለጸሎት መበርቻ ማድረግ በሚል መርሕ ላይ የተመሠረተ ሐሳብ አለው። በመሆኑም መጽሐፈ ወግሪስ የእውነተኛ መነኮሳት መመርያ ነው። መነኮሳት የምግብ ፍላጎታቸውን ሲገቱ የነፍስ ቁስላቸው እንደሚፈወስ፣ ልቡናቸውም ንጹሕና ንቁ እንደሚሆን መጽሐፉ ያብራራል። በተጨማሪም መነኮሳት ሥጋቸውን ለነፍሳቸው በማስገዛት ከምድራዊ የምግብ ጭንቀትና ምርኮኝነት ወጥተው፣ ነፍሳቸውን "በእውነተኛው የሕይወት እንጀራ" መመገብ እንዳለባቸው ይመክራል። እንደ ታላቁ አባ እንጦንስ ያሉ የጥንት አባቶች አመጋገባቸውን በመወሰን፣ ጥቂትና ቀላል ምግቦችን ለምሳሌ ደረቅ እንጀራ፣ ጨውና ውኃ ብቻ በመጠቀም የብርሃን ልብስን ለመጎናጸፍ እንደበቁ በምሳሌነት ያቀርባል። "መጽሐፈ ወግሪስ" ሆዳምነትን መነኮሳትና መንፈሳውያን ክርስቲያኖች መጀመሪያ ሊዋጉትና ሊያሸንፉት የሚገባ የኃጢአትና የፍትወታት ሁሉ በር አድርጎ ያስረዳል። መጽሐፉ የሰው ልጅ ነፍስን ከሚያረክሱ ስምንት ዋና ዋና አጋንንታዊ ጾሮች መካከል ሆዳምነትን በአንደኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጠዋል። "ጤነኛ ትሆን ዘንድ የመብል ሸክምን አቅልል" በማለትም ያስተምራል። ሆድ በምግብ ሲሞላ ኅሊና እንደሚደነዝዝ፣ ለጸሎትና ለትጋት ስንፍና እንደሚመጣ፣ እንዲሁም ልቡና ሰማያዊ ምሥጢራትን ማየት እንደማይችል ያብራራል። በመሆኑም መነኮሳት ሥጋቸውን በርሃብና በትሕርምት በማስገዛት ነፍሳቸውን ንቁና ዝግጁ ማድረግ እንዳለባቸው ይመክራል። ⏺መምህር ዮሴፍ ፍስሐ

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሰኔ ሠላሳ በዚች ዕለት ነቢይ ሰማዕትና ሐዋርያ የሆነ መጥምቁ ዮሐንስ ተወለደ ።
 ይህም በእናቱ ማኅፀን ውስጥ ሳለ ለእግዚአብሔር ልጅ የሰገደው ነው ። ይህም በመድጎን ክርስቶስ ራስ ላይ እጁን ጭኖ በውኃ ያጠምቀው ዘንድ የተገባው ነው ። በቅዱስ ወንጌል እንደ ተነገረ ወንድ ልጅን ትወልድ ዘንድ የኤልሳቤጥ የፅንሷ ወራት በተፈጸመ ጊዜ ወንድ ልጅን ወለደች ። ዘመዶቿና ጐረቤቶቿ እግዚአብሔር ቸርነቱን እንዳበዛላት በሰሙ ጊዜ ስለርስዋ ደስ አላቸው ። በስምንተኛውም ቀን ሊገዝሩት መጡ በአባቱ ስም ዘካርያስ ብለው ጠሩት ። እናቱ ግን አይሆንም ዮሐንስ ይባል አለች ። ከዘመዶችሽ ስሙ እንዲህ የሚባል የለም አሏት ። አባቱንም ጠቅሰው ማን ሊባል ትወዳለህ አሉት ። እርሱም ብራና ለምኖ ስሙ ዮሐንስ ይባል ብሎ ጻፈ ። ሁሉም አደነቁ ። ያን ጊዜም አንደበቱ ከድዳነት ተፈትቶለት ተናገረ እግዚአብሔርንም ፈጽሞ አመሰገነው ። ስለ ልጁና ስለ መድኃኒታችን መምጣት ልጁ ዮሐንስም የልዑል ነቢይ እንደሚባልና በእግዚአብሔርም ፊት እንደሚሔድ ትንቢት ተናገረ ። ሰብአ ሰገልም መጥተው ከሔዱ በኋላ ሄሮድስ ሕፃናትን በገደላቸው ጊዜ ስለ ሕፃኑ ዮሐንስ ለሄሮድስ ነገሩት እንዲገድሉትም ጭፍሮችን ላከ ጭፍሮችም ወደ አባቱ ዘካርያስ መጡ ሕፃኑንም ከእርሱ ፈለጉት አባቱም አንሥቶ በትከሻዎቹ ተሸክሞ ወደ ቤተ መቅደስ ከእርሱ ጋራ እንዲሔዱና ሕፃኑን ከዚያ እንዲወስዱት ወታደሮችን ለመናቸው ። ከዚህም በኋላ ሕፃኑን በመሠዊያው ጠርዝ ላይ አኖረውና ከዚህ ራሳችሁ ተቀብላችሁ ውሰዱት አላቸው ወዲያውኑ የእግዚአብሔር መልአክ ነጥቆ ወደ በረሀ ወሰደው ። ጭፍሮችም ባላገኙት ጊዜ አባቱ ዘካርያስን ገደሉት ። ሕፃኑ ግን አድጎ ለእስራኤል እስከተገለጠበት ጊዜ ድረስ በበረሀ ውስጥ ኖረ ። የእግዚአብሔርን መንገድ ጥረጉ ጥርጊያውንም አስተካክሉ እያለ በምድረ በዳ የሚጮህ የዐዋጅ ነጋሪ ድምፅ እነሆ ብሎ ኢሳይያስ የተናገረለት ይህ ነው ። ሚልክያስም ስለሱ እንዲህ አለ ። በፊትህ ጐዳናዬን አስተካክሎ የሚጠርግ መልእክተኛዬን እኔ እሰዳለሁ ራሱ መድኃኒታችንም ስለርሱ ሲናገር ሴቶች ከወለዱአቸው መጥምቁ ዮሐንስን የሚበልጠው የለም ብሏል ። ይህ የእግዚአብሔርን ልጅ በአጠመቀውና የማትዳሠሥ ራሱን በዳሠሠው ጊዜ የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት የሚል የአብን ቃል ሰምቷልና ። ዳግመኛም ክብር ይግባውና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ራስ ላይ መንፈስ ቅዱስ ወርዶ ሲቀመጥ አየ ። እኛም መድኃኒታችን እንዲምረንና ይቅር እንዲለን በአማላጅነቱ እያመን መታሰቢያውን እናድርግ በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን።

ተግሳጽ ዘቅዱስ ቄርሎስ አንድምታ

Michael_F_Bird_Jesus_among_the_gods_Early_Christology_in_the_Greco.pdf45.22 MB

በውጭው ዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተክርስቲያናት በስፋት እንዲቋቋሙ፣ ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና በጥልቀት እንዲደራጅና በባዕድ ሀገር ጠንካራ መሠረት እንዲይዝ ያደረጉት ታላቅ አባት አባ ላዕከ ማርያም ማንደፍሮ (የኋላው ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ) ናቸው። እኒህ የቀድሞው የካሪቢያንና የሰሜን አሜሪካ ሊቀ ጳጳስ የነበሩ አባት፣ በውጭ ሀገር የሚገኙ መነኮሳት በስደት ምድር ምን ዓይነት መንፈሳዊ ተልዕኮ መፈጸም እንዳለባቸውና ምን ዓይነት መንፈሳዊ ሕይወት መላበስ እንደሚገባቸው በተግባር ያስተማሩ ታላቅ መምህርና በራሳቸው የቆሙ ትልቅ የሕይወት ትምህርት ቤት ናቸው። በአሁኑ ዘመን በውጭ ሀገር የሚኖሩ መነኮሳት ሥጋዊ ምቾትንና ፍቅረ ንዋይን እያሳደዱ ከምንኩስና ክብራቸው በሚንሸራተቱበት በዚህ አስፈሪ ወቅት፣ ዞር ብለው ሊመለከቱትና ሊመስሉት የሚገባው እውነተኛው የመንፈሳዊነት መስተዋት የአቡነ ይስሐቅን ተጋድሎ ነው። ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ በምዕራቡ ዓለም ያከናወኑት ሐዋርያዊ አገልግሎት በቤተክርስቲያን ታሪክ ውስጥ በወርቅ ቀለም የሚጻፍ ነው። እርሳቸው በራሳቸው ከፍተኛ ጥረት ከሦስት መቶ ሺህ በላይ የሚሆኑ የውጭ ሀገር ዜጎችን አስተምረው ወደ ኦርቶዶክሳዊት እምነት በማስገባት ያጠመቁ የ20ኛው ክፍለ ዘመን ሐዋርያ ናቸው። ከዚህም በላይ፣ በስደት ምድር ኦርቶዶክሳዊ እምነት የጸና ማደሪያ እንዲኖረው በራሳቸው መሪነት ከሰባ በላይ የሚሆኑ አብያተክርስቲያናትን ያሳነጹና የመሠረቱ ናቸው። ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ በተግባራዊ ሐዋርያነታቸው ብቻ ሳይሆን፣ በጥናታዊና በምሁራዊ ብቃታቸውም የቤተክርስቲያንን ክብር በዓለም መድረክ ከፍ ያደረጉ ነበሩ። መጻሕፍትን በእንግሊዝኛ ቋንቋ በመጻፍና በተለያዩ የምዕራባውያን መገናኛ ብዙኃን በየጊዜው በመቅረብ ስለ ኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ጥንታዊነት፣ ርቱዕነትና ታሪካዊነት በምክንያትና በእውቀት የመሰከሩ ታላቅ ዲፕሎማት ነበሩ። በዚህም የቤተክርስቲያኗን ገጽታና ዓለም አቀፋዊ ዕውቅና በማይናወጥ መሠረት ላይ ገንብተዋል። ብፁዕነታቸው የኢትዮጵያን ቤተክርስቲያን በከፍተኛ ደረጃ በመወከል አያሌ ዓለም አቀፍ የሃይማኖት ጉባኤዎችን የተሳተፉና በርካታ የምርምር ጥናቶችን በማቅረብ የኦርቶዶክስን ነገረ-መለኮት ያስመሰከሩ እውነተኛ የቤተክርስቲያን ብርሃን ነበሩ። የአቡነ ይስሐቅ ታሪክ የሚያስተምረን፣ የምንኩስና ሕይወት በውጭ ሀገርም ቢሆን ዓለምን አሸንፎ፣ ወንጌልን አስፋፍቶና ክብሩን ጠብቆ መጓዝ እንደሚችል ትልቅ ማሳያ ነው። ምክረ ሐሳብ ለ«ወልታ ጽድቅ ዘተዋሕዶ» ✅ መሠረቱን በሰሜን አሜሪካ ያደረገውና «ወልታ ጽድቅ ዘተዋሕዶ ዓለም አቀፍ የመነኮሳት ጉባኤ» በመባል የሚጠራ ዓለም አቀፍ የመነኮሳት ኅብረት መቋቋሙ ይታወቃል። ይህ ኅብረት ከሌሎች ኦርቶዶክሳዊ ማኅበራት ጋር በመቀናጀት «የጥምረት ለቤተክርስቲያን ዓለም አቀፍ ኦርቶዶክሳዊ ንቅናቄ» አባል በመሆን የራሱን አስተዋጽኦ ለማበርከት የሚጥር ስብስብ ነው። ጉባኤው በተለይ በሀገር ቤት በቤተክርስቲያን ላይ ለሚደርሱ ስልታዊ ጥቃቶች፣ ቀኖናዊ መጣሶች፣ መዋቅራዊ መገለሎች እና አስተዳደራዊ ችግሮች ዙሪያ በተደጋጋሚ ጊዜያት ወቅታዊና ጠንከር ያሉ መግለጫዎችን በማውጣት፣ ለእናቱ ቤተክርስቲያን ድምፅ ለመሆን ሙከራዎችን አድርጓል። ነገር ግን፣ ይህ ኅብረት ከመግለጫዎች በዘለለ፣ የምንኩስና ሕይወት በውጩ ዓለም ክብሩንና የቆመለትን መንፈሳዊ ዓላማ ጠብቆ ይጓዝ ዘንድ ያደረገው አስተዋጽኦና ያሳየው ቁርጠኝነት ገና ብዙ የሚቀረው መሆኑ አይሸሸግም። በውጭ ሀገር የሚኖሩ መነኮሳት ከዓለማዊ ኑሮ ፈተና ወጥተው ወደ ቀደመው ገዳማዊ ሥርዓታቸው እንዲመለሱ በማድረግ ረገድ የኅብረቱ ተቋማዊ ጉዞ ደካማ ነው። ከዚህም በተጨማሪ፣ የመነኮሳት ኅብረቱ በውጭ ሀገር የሚገኙትን መነኮሳት በሙሉ በአባልነት ለማካተት፣ ሰብስቦ ለመምራትና እንቅስቃሴውን በተሟላ መልኩ ዓለም አቀፋዊ ለማድረግ ሰፊ የአቅምና የማስተባበር እጥረቶች ይታዩበታል። ኅብረቱ መነኮሳቱን በጋራ አቅፎ የሚመራበትና ወደ ገዳማዊ ሕይወት የሚመልስበት ተቋማዊ ስልት ይኖረው አይኑረው በግልጽ አይታወቅም። «ወልታ ጽድቅ ዘተዋሕዶ ዓለም አቀፍ የመነኮሳት ጉባኤ» የምንኩስናን ሕይወት በተግባር ለመታደግና ተቋማዊ አሻራውን ለማሳረፍ መተግበር ካለባቸው ቀዳሚ መፍትሔዎች አንዱ ከግብፅና ከሶርያ አብያተ ክርስቲያናት መነኮሳት ስኬታማ ተሞክሮ መማር ነው። የመነኮሳት ኅብረቱ በግብፅ እና በሶርያ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት መነኮሳት ዘንድ እንደሚታየው ሁሉ፣ ገዳማትን በውጭ ሀገር የማደራጀት ሰፊ ሥራ መሥራት ይጠበቅበታል። የእነዚህ አኃት አብያተ ክርስቲያናት መነኮሳት በአውሮፓና በአሜሪካ ያቋቋሟቸው ገዳማት ዛሬ ለምዕመናን የሱባኤ፣ የጸሎት፣ የትምህርት እና በአጠቃላይ የወጣቶችና የቤተሰብ መንፈሳዊ ሕይወት መታደሻ ምሽጎች መሆን ችለዋል። ወልታ ጽድቅም መነኮሳቱ በየከተማው አፓርታማና በአድባራት አስተዳደር ውስጥ ተበታትነው ከሚኖሩ፣ በእንደነዚህ ዓይነት ተቋማዊ ገዳማት ውስጥ ገብተው ጥንታዊውን የመንፈሳዊ ተጋድሎ ሥርዓት እንዲያስጠብቁና የቤተክርስቲያን ሕይወት በውጭ ዓለም በቅድስና ጎዳና እንዲጓዝ የማድረግ ሥራ ቢሠራ የሚበረታታ ነው። ኅብረቱ የአባላቱን መንፈሳዊ ሕይወት የሚገመግም ግብረ ኃይል በማቋቋም፣ ለአባላት ጥብቅ የቀኖናና የሥነ-ምግባር ክትትል ማድረግ ይጠበቅበታል። ከምንኩስና ቀኖና ውጭ የሚንቀሳቀሱትን፣ ሕዝበ ክርስቲያኑን በልዩ ልዩ መንገድ የሚከፋፍሉትን፣ እንዲሁም ከሕገ-ቤተክርስቲያን ውጭ ካሉ አጥማቂያን ጋር በመሻረክ አጥማቂነትን የገንዘብ ማሰባሰቢያ የሚያደርጉትን መነኮሳት በመለየት መገሠጽ፣ ካልተመለሱም ከአባልነት ማገድና ለቅዱስ ሲኖዶስ አሳልፎ መስጠት ይገባል። ይህ መዋቅራዊ እርምጃ ኅብረቱ በውጭ ያሉትን መነኮሳት በሙሉ በአባልነት ለማካተት ለሚያደርገው ዓለም አቀፍ ጉዞ የራሱን ንጽሕናና ታማኝነት ለመጠበቅ በእጅጉ ይረዳዋል። «ወልታ ጽድቅ» በየአድባራቱ ውስጥ በአስተዳደር ጫናና በዓለማዊ ኑሮ ውዝግብ ውስጥ ለሚኖሩ መነኮሳት ራሳቸው ቢያንስ በተወሰነ ጊዜ ልዩ ዕረፍት የሚወስዱበት የመንፈሳዊ ሕይወት መታደሻ ሥርዓት መዘርጋት ላይ መሥራት ይጠበቅበታል። መነኮሳቱ በተወሰኑ ወራት ወይም ሳምንታት ወደ ገዳማቱ እየሄዱ ገዳማዊ የሆነውን የምንኩስና ሕይወታቸውንና መንፈሳዊ ማንነታቸውን የሚያድሱበት የውስጥ መመሪያ ቢኖራቸው መልካም ነው። «ወልታ ጽድቅ» መነኮሳቱ ከዋናው መንፈሳዊ አገልግሎት ወጥተው የምንኩስና ሕይወታቸው በማይፈቅድላቸው ድጋፍ ሰጪ በሆኑ ተግባራት ላይ እንዳይሰማሩ ቁርጠኝነት ያለው ሥራ ቢሠራ ያስመሰግነዋል። ለምሳሌ መነኮሳቱ የገንዘብና ሒሳብ አያያዝን፣ የሕንፃ ግንባታንና አጠቃላይ አስተዳደራዊ የቢሮክራሲ ሥራዎችን ለሕጋውያን ካህናትና ለምዕመናን በመተው፣ በጸሎት፣ በትምሕርት፣ በምክር አገልግሎትና በመሳሰሉት መንፈሳዊ ተግባራት ብቻ ተወስነው እንዲኖሩ ማድረግ የሚቻልበትን ሁኔታ ቢፈጥር ለቤተክርስቲያንም ለራሳቸው ለመነኮሳትም በእጅጉ የሚበጅ ተግባር ነው። በቀሲስ መንግሥቱ ጎበዜ(ዶ/ር)

ምንኩስና እና ተግዳሮቱ በውጭው ዓለም ( ቀሲስ መንግሥቱ ጎበዜ ዶ/ር) በውጭው ዓለም በርካታ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መነኮሳት እንደሚገኙ ይታወቃል። እነዚህ አባቶች ከተጋድሎና ከገዳማዊ ሕይወት ወጥተው ወደ ውጭ ሀገር የሚሰደዱባቸው ምክንያቶች መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ገጽታ ያላቸው ውስብስብ ጉዳዮች ናቸው። ይህ በስደት የሚኖሩ መነኮሳት ቁጥር መጨመር በውጭ ለምትገኘው ቤተክርስቲያን የራሱን በጎ አስተዋጽኦ ያበረከተ ቢሆንም፣ ከምንኩስና ቀኖና እና ከተቋማዊ መዋቅር አንጻር ግን ስር የሰደዱ ከባድ ፈተናዎች እንዳሉት አይካድም። በመልካም ተግባራቸው የሚታወቁ መነኮሳት የውጩን ዓለም ዘርፈ-ብዙ ፈተናዎች በጸሎት፣ በመንፈሳዊ ተጋድሎና በትዕግስት በመቋቋም፣ አሰረ ምንኩስናቸውን አስከብረው የሚኖሩ አበው መነኮሳት ይገኛሉ። እነዚህ አባቶች በስደት ለሚገኘው ሕዝበ ክርስቲያን እውነተኛ የነፍስ መጠጊያና የሃይማኖት ጋሻዎች ናቸው። ሳይታክቱ የእግዚአብሔርን ቃል በመስበክ፣ በውጭ ሀገር የሚኖሩ ሕጻናትንና ወጣቶችን በመሰብሰብ የአብነት ትምህርትን ያስተምራሉ፤ የሰንበት ትምህርት ቤቶችንም በማደራጀትና በማጠናከር፣ ታዳጊዎች በትምህርተ ሃይማኖትና በሥነ-ምግባር እንዲጎለምሱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማበርከት ላይ ይገኛሉ። እነዚህ አባቶች በትዳር፣ በልጆች አስተዳደግና በኑሮ ጫና ለሚሰቃዩ ምዕመናን ዘወትር በምክርና በጸሎት በመድረስ፣ ዘርፈ-ብዙ ሥነ-ልቦናዊና መንፈሳዊ ችግሮቻቸውን ለማቃለል ይተጋሉ። እንዲሁም ሕዝበ ክርስቲያኑን በማስተባበር አዳዲስ አብያተ ክርስቲያናት እንዲታነጹ ያደርጋሉ። እነዚህ አባቶች፣ ዓለምን የናቁበትን ጥንታዊ ትውፊት ሳይዘነጉ፣ ባሉበት አጥቢያ ተወስነው በጸሎትና በትሕርምት ይኖራሉ። በአጠቃላይ፣ በቁጥር እምብዛም ያልሆኑት እነዚህ አበው መነኮሳት ሙሉ ጊዜያቸውንና ጉልበታቸውን ያለ ምንም ስስት ለቤተክርስቲያን አገልግሎት የሰጡ፣ ለሕዝበ ክርስቲያኑ መልካም አርአያ በመሆን የእግዚአብሔርን ክብር በውጩ ዓለም የሚገልጡ ናቸው። ዓላማውን የሳተው የምንኩስና ሕይወት✅ ከላይ ከተጠቀሱት ምስጉን አባቶች በተጻራሪ፣ የምንኩስናን መሠረታዊ ዓላማ ወደ ጎን በመተው፣ ስደት ያመጣቸውን ዕድሎች ለግል ጥቅማቸው የሚያውሉ መነኮሳት መኖራቸው ከብዙዎች የተሰወረ አይደለም። ምንኩስና በተፈጥሮው ከዓለም ተለይቶ በጸጥታና በብቻኝነት በገዳም ውስጥ የሚኖርበት ቅዱስ ሕይወት ቢሆንም፣ በውጭ ሀገር ግን አብዛኞቹ መነኮሳት የሚኖሩት ሁከትና ግርግር በበዛባቸው ታላላቅ ከተሞች ውስጥ በመሆኑ ለብቻኝነትና ለጸሎት ምቹ ሁኔታ አያገኙም። ከዚህም በላይ፣ በሀገር ውስጥ እንዳለው ታሪካዊና መንፈሳዊ ድባብ ያላቸው ገዳማትና ቅዱሳን መካናት በስደት ሀገር በበቂ ሁኔታ አለመኖራቸው፣ የአንዳንዶቹን መንፈሳዊ ሕይወት እጅግ ፈታኝ እያደረገው ይገኛል። አንዳንድ መነኮሳት ከበላይ አካል (ከቅዱስ ሲኖዶስ ወይም ከአህጉረ ስብከት) ዕውቅናና ፈቃድ ውጭ በራሳቸው ፍላጎት ወደ ውጭ ሀገር የሚሰደዱ በመሆናቸው፣ በሕገ-ቤተክርስቲያን ለመመራትና ለመታዘዝ ፈቃደኛ ሳይሆኑ የሚቀሩበት ሁኔታ በሰፊው ይንጸባረቃል። ይህ ክትትል አልባ ጉዞ ደግሞ የምንኩስናን ሥነ-ሥርዓትና አስኬማ የሚጥሱ፣ ከቀኖና ጋር የማይጣጣሙ ተግባራት በአንዳንዶች ዘንድ እንዲታዩ በር ከፍቷል። አንዳንዶቹ ከሕገ-ቤተክርስቲያን ውጭ በራሳቸው ፈቃድ ከሚንቀሳቀሱና ከተከለከሉ አጥማቂያን ጋር ስውርና ግልጽ ቁርኝት በመፍጠር ሌላ መዋቅራዊ ቀውስ በመውለድ ይታወቃሉ። እነዚህን ሕገ-ወጥ አጥማቂዎች ወደ ውጭ ሀገር በመጋበዝ፣ በየአድባራቱ እንደልባቸው እንዲሆኑና ምዕመናንን እንዲያደናግሩ ምቹ ሁኔታን ያመቻቹላቸዋል። በሂደቱም ራሳቸው መነኮሳቱ ይህንኑ ሕገ-ወጥ መንገድ በመከተል፣ አጥማቂነትንና ፈዋሽነትን ዋነኛ የገንዘብ ማሰባሰቢያ ዘዴ ሲያደርጉትም ይስተዋላል። ጥቂቶችም በውጭ ሀገር የሚኖረውን የኑሮ ውድነት ሰበብ በማድረግ፣ የዕለት ተዕለት ሕይወታቸውን ለመደገፍ ወይም በሀገር ውስጥ ያሉ ቤተሰቦቻቸውን ለመርዳት በሚል የገንዘብና የኑሮ ዋስትና ፍለጋ ወደ ልዩ ልዩ ዓለማዊ ሥራዎች ውስጥ እንደገቡ ይነገራል። አንዳንዶቹ ፍቅረ ንዋይ ስላሸነፋቸው የምንኩስናን ሥነ-ሥርዓትና አስኬማ ጥለው በግል ስም ንብረት ማፍራት፣ በምዕመናን መዋጮ የተቋቋሙትን አብያተ ክርስቲያናትና ይዞታዎች በግል ስማቸው ወይም በራሳቸው የቦርድ አባላት ስም በማስመዝገብ ለራሳቸው ጥቅም ማዋላቸውም ይነገራል። ይህ ድርጊት ፍርድ ቤት የሚደርሱ ከባድ የሕግ ክርክሮችን በማስከተሉ፣ ለቤተክርስቲያን ትልቅ ማሰናከያና ሕመም ሆኖ ቀጥሏል። አልፎ አልፎም በልማት፣ በረድኤት ወይም በገዳማት እርዳታ ስም ከምዕመናን የሚሰበሰበውን ገንዘብ ያለ ግልጽ የሂሳብ አሠራር ለግል ማበልጸጊያ የሚያውሉ እንዳሉ ይገለጻል። በአንዳንድ የውጭ ሀገር አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ በመነኮሳት፣ በሕጋውያን ካህናትና በሰበካ ጉባኤ አባላት መካከል የአስተዳደር ሥልጣንና የገንዘብ ቁጥጥርን የመሰሉ ጥቅማ ጥቅሞችን ለማግኘት የሚደረጉ ግጭቶች በሰፊው ይነሳሉ። በሕጋውያን ካህናቱና በመነኮሳቱ መካከል የአጥቢያ ቤተክርስቲያንን የበላይነት ለመያዝ በሚደረገው ፍልሚያ ምክንያትም የቤተክርስቲያንና የሕዝበ ክርስቲያኑ ሰላም ይታወካል። መነኮሳቱ «እኛ ዓለምን የናቅን እና የሙሉ ጊዜ የቤተክርስቲያን አገልጋዮች ነን» በሚል ካህናቱን የማናናቅና የመግፋት፣ ካህናቱም በበኩላቸው መነኮሳቱን «ሥርዓት አልባና ዓለማውያን ናቸው» በማለት መተቸት የሚስተዋልባቸው አጥቢያዎች እንዳሉ ይነገራል። በአንዳንድ ቦታዎች መነኮሳቱ የሁሉም አባት መሆን ሲገባቸው፣ ምዕመናንን በጎጥ፣ በክልል፣ በጎሳ ወይም በቋንቋ በመከፋፈል የግል ተከታይና ደጋፊ ለማፍራት ይሞክራሉ፤ ይህ ድርጊት ምዕመናን እርስ በርሳቸው እንዲጠራጠሩና ቤተክርስቲያን የሰላም ማዕከል መሆኗ እንዲቀር ያደርጋል። አልፎ ተርፎም ከሰበካ ጉባኤ ወይም ከአስተዳደሩ ጋር አለመግባባት ሲፈጠር፣ ምዕመናንን በማስተባበር የራሳቸውን የግል አብያተ ክርስቲያናት በመመስረት ቤተክርስቲያንን እስከ መገንጠል የሚደርሱ መነኮሳት መኖራቸውም ይነገራል። በእርግጥ ይህ ችግር በመነኮሳቱ ብቻ ሳይሆን በካህናቱም በኩል በስፋት የሚታይ ተግዳሮት ነው። እነዚህ ሁሉ አስተዳደራዊና ሥነ-ምግባራዊ ጉድለቶች ተደምረው የቤተክርስቲያንን መልካም ስም በእጅጉ ያጠለሻሉ። አባትና መሪ ይሆናሉ ተብለው የሚጠበቁ መነኮሳት በገንዘብ፣ በሥልጣን ወይም በሴሰኝነት በአንዳንድ አጋጣሚዎች ሲታሙና በውጭ ሀገር ፍርድ ቤቶች ፊት ሲቆሙ ማየት የምዕመናንን /በተለይም የኦርቶዶክሳውያን ወጣቶችን/ እምነትና ተስፋ ያጨልማል። በአጠቃላይ፣ እነዚህ መነኮሳት ከመንፈሳዊ አባትነታቸው ይልቅ ወደ ዓለማዊ ጥቅም ሲያደሉ፣ ቤተክርስቲያንን ከመንፈሳዊ ተቋምነቷ አውጥተው ወደ ግል የንግድ ተቋምነት፣ የፖለቲካ መድረክና የክስ ማዕከልነት እንዲቀየር በማድረግ ረገድ የማይናቅ አሉታዊ ድርሻ እያበረከቱ ይገኛሉ። የብፁዕ አቡነ ይስሐቅ ምሳሌያዊ ተግባር

ሰቀል ሰቀል አድርግ

ታሪክ ዘንጉሠ ነገሥት አድያም ሰገድ ወንግሥት ብርሃን ሞገሳ
+3
ታሪክ ዘንጉሠ ነገሥት አድያም ሰገድ ወንግሥት ብርሃን ሞገሳ

Repost from EOTC Books ⛪️
🤝 ዐዲስ መጽሐፍ 📢🤝 በዩቱዩብ ሚሊየነር የመሆን ሕልም! ሙሉ የዩቲዩብ ስልጠና መጽሐፍ! ህልምዎን ወደ እውነተኛ ገቢ ይቀይሩት! በዩቲዩብ ስኬታማ ለመሆን ሙሉ መንገዱን ይማሩ! ✍️ ​በአሁኑ ሰዓ
🤝 ዐዲስ መጽሐፍ 📢🤝 በዩቱዩብ  ሚሊየነር የመሆን ሕልም! ሙሉ የዩቲዩብ ስልጠና መጽሐፍ! ህልምዎን ወደ እውነተኛ ገቢ ይቀይሩት! በዩቲዩብ ስኬታማ ለመሆን ሙሉ መንገዱን ይማሩ! ✍️ ​በአሁኑ ሰዓት ዩቲዩብ (YouTube) የትርፍ ጊዜ ማሳለፊያ ብቻ ሳይሆን፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎችን ህይወት የቀየረ ትልቅ የገቢ ምንጭ መሆኑን ያውቃሉ? የእርስዎስ ህልም የት ደረሰ? ​ብዙዎች የዩቲዩብ ቻናል መክፈት ቢፈልጉም፦ ✍️"በምን ርዕስ (Niche) ቪዲዮ ልስራ?" 📱 "ቪዲዮ እንዴት ኤዲት ይደረጋል?" ያውም በእጅ ስልክ ብቻ! ✍️ "ተመልካችና ሰብስክራይበር እንዴት ማግኘት እችላለሁ?" በሚሉ ጥያቄዎች መልስ «በዩቲዩብ ሚሊየነር የመሆን ህልም» ​መጽሐፍ ከምንም ተነስተው ቻናልዎን እስከ ትልቅ ደረጃ ለማድረስ የሚያስችሉዎትን ስልታዊ መመሪያዎች በሙሉ በቀላል አማርኛ እና እንግሊዘኛ ቋንቋ ቀርቦልዎታል። 📚📖 መጽሐፉ ምን ምን ነገሮችን ያካትታል? 💻የእጅ ስልክ በመጠቀም በዩቲዩብ ገቢ መፍጠር መቻል:: 🖥በጠቅላላ የዩቲዩብ ሕግና ደንቦች 💻ዩቲዩብ ገንዘብ ለማን?እንዴት?ለምን ይከፍላል? 👨‍💻በኢትዮጵያ የሚኖሩ ዩቱበሮች ቢፈጥሯቸው አዋጭነታቸው የተጠኑ 8 ዓይነት ይዘቶች 📱ከተለያዩ ሚዲያ የሚገኙ ቪዲዮዎዎችን እንዴት ወደ ዩቲዩብ ወስዶ ገንዘብ መስራት ይቻላል? ✍️ዩቲዩብ ቻናሎች በአጭር ጊዜ የማሳደግ መመሪያዎች በዝርዝር ✍️ ሞኒታይዜሽን ሙሉ ሂደት ✍️ የዩቲዩብ ንግድ( ቻናል ማሳደግ:መሸጥ:መግዛት) ✍️መጠነኛ ስቲዲዮ ማዋቀር ✍️​የቻናል አከፋፈትና አደረጃጀት፦ በአነስተኛ ወጪ በአጭር ጊዜ ተጠቃሚ የሚያደርጉ የቪዲዮ ርዕሶችን እንዴት መምረጥ እንደሚችሉ። ✍️የዩቱዩብየአልጎሪዝም ሚስጥሮች፦ ቪዲዮዎ ለብዙ ተመልካቾች እንዲደርስ (Viral እንዲሆን) የሚያደርጉ ስልቶች። ✍️​የገቢ ማስገኛ መንገዶች፦ የዩቲዩብ መስፈርቶችን አሟልቶ Google AdSenseን በማገናኘት በዶላር ክፍያ ማግኘት የሚቻልበት ሙሉ መመሪያ። 🙏​የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) አጠቃቀም ከዩቱዩብ ጋር እስከ ምን ይገናኛሉ ይለያያሉ የሚሉ ጥልቅ ምስጢራት። 🎁መጽሐፉን አሁኑኑ በማዘዝ "​የስኬት ጉዞዎን ዛሬውኑ ይጀምሩ።" ዋና አከፋፋይ ሀሁ መጻሕፍት መደብር በሁሉም መጽሐፍ መደብሮች ያገኙታል። 📍አድራሻ፦               ቍ1)ዐራት ኪሎ አብርሆት ጎን               ቍ2) ሜክሲኮ ደብረወርቅ ታዎር ግራውንድ ☎️#ስልክ፦ 0911006705 / 0924408461 🖥አስታውሱ! በመደብራችን 10 መጻሕፍት ለሚገዛ 1 መጽሐፍ በነጻ እንሰጣለን!!!        🖥YouTube 📱 Mintesnot media💻 https://youtube.com/channel/UCMjYpNxG6OAUuRy9WgAdulA?si=hemo0b59kVhD-Opt

❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️ ስርዓተ ዋዜማ አመ ሰላሳሁ ለሰኔ በዓለ ልደቱ ለቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ 🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷 ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ ነበባ መልአክ ለኤልሳቤጥ ወይቤላ እዩ ለዮሐንስ ትወልዲ ወልደ ቅዱስ ኢይሰቲ ወይነ ወሜሰ ይመልዕ ላዕሌሁ መንፈስ ቅዱስ ወይሰመይ አርኩ ለመርዓዊ ምልጣን ትወልዲ ወልደ ቅዱስ ኢይሰቲ ወይነ ወሜሰ ይመልዕ ላዕሌሁ መንፈስ ቅዱስ ወይሰመይ አርኩ ለመርዓዊ ፤ ወይሰመይ አርኩ ለመርዓዊ አመላለስ ወይሰመይ አርኩ ለመርዓዊ /2/ ወይሰመይ አርኩ ለመርዓዊ ወይሰመይ አርኩ ለመርዓዊ /2/ ለእግዚአብሔር ምድር በምልዓ ኤልሳቤጥ ወለደቶ ነቢየ ልዑል ሰመየቶ ኤልሳቤጥ ወለደቶ እግዚአብሔር ነግሠ ወሶበ ሰማዕታ ኤልሳቤጥ ቃላ ለማርያም ድንግል እንዘ ትትኃምሐ አንፈራጸ ዕጓል በውስተ ከርሣ በፍስሐ ይትባረክ ተነበየ ዘካርያስ ላዕለ ወልዱ ዮሐንስ ወይቤ ወአንተኒ ሕጻን ነቢየ ልዑል ሰላም ዮሐንስ ክቡር ወንጌላዊ ሰላማዊ ዓርኩ ለመርዓዊ ዘይሰብክ ጥምቀተ ከመ ይመኑ እስራኤል እግዚኡ ዘአጥመቀ በፈለገ ዮርዳኖስ ወገሠፆ እንተ ይትገሠሥ ርዕሶ ኤልሳቤጥ ወለደቶ ነቢየ ልዑል ሰመየቶ አመላለስ ኤልሳቤጥ ወለደቶ /2/ ነቢየ ልዑል ሰመየቶ ነቢየ ልዑል ሰመየቶ /2/ ሼር ✅ 📝📖 Telegram https://t.me/EOTCBooks1 Subscribe    YouTube 📱 https://www.youtube.com/@zeEthiop

ዛሬ ትልቁን ክርስትና ላይ እየሰራሁ ያለሁትን App እየሰራሁ በመሀል ትንሽ free time አግኝቼ ነበር እና ይህችን በእንተ አህዛብ የሚለውን መጽሐፍ ወደ አፕሊኬሽን ቀይሬላችኋለሁ😉 እና ከከተማ ወጣ ያለ ቦታ ያላችሁ ምናምን ያለ ኢንተርኔት በስልክ ለማንበብ እንዲመች አድርጌዋለሁ። እና ብርሃነ ትንሳኤ ብላችሁ አስቡኝ🥰 መልካም ንባብ https://t.me/Palladius21 ✍ ጰላድዮስ

ሰንክሳር ዘወርኃ ሰኔ ፳፰ አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሰኔ ሃያ ስምንት በዚህ ቀን ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሠላሳ ሦስተኛ የሆነው ቅዱስ አባ ቴዎድሮስ የእስክንድርያ ከተማ ሊቀ ጳጳሳት አረፈ። በዚህም ቅዱስ በስሙ በግብጽ ምድር ውስጥ ምእመናን ቴዎድሮሳውያን ተብለው ተጠርተውበታል። ይህም የሆነው እንዲህ ነው ሊቀ ጵጵስና ከተሾመ በኋላ ክፉዎች ሰዎች በእርሱ ላይ ተነሥተው በንጉሥ ምክር ከመንበረ ሢመቱ አሳደዱት በእርሱ ፋንታም አስቀድሞ በእስክንድርያ ከተማ ሊቀ ዲያቆናት የነበረ ስሙ አቃቅያኖስ የሚባለውን አንድ ሰው ሾሙ እርሱም ለአባ ቴዎድሮስ ሊቀ ጵጵስና እንደማይገባው ከፈረሙት ቁጥር ውስጥ ነበረ። ይህም አባት ወደ ግርማዊስ አገር ሒዶ ሦስት ወሮች ኖረ በዚያም ወራት በግብጽ አገር ንቡረ እድ አባ ሳይሮስ ነበረ እርሱም በአባቶቻችን ሐዋርያት እንዲሁም በአትናቴዎስና በዮሐንስ አፈወርቅ የደረሰባቸውን መከራ እያስታወሰ ያጸናናቸው ነበረ። ከዚያም ተነሥቶ መሊባ ወደሚባል አገር ሔዶ በዚያም ሁለት ዓመት ተቀመጠ። የእስክንድርያ ከተማ ሰዎችም የጠበቂያቸው የቴዎድሮስን መመለስ ሽተው በእስክንድርያው መኰንን ላይ ተነሡበት መኰንኑም ወደ መንበረ ሢመቱ መለሰው አቃቅያኖስንም አባረሩት። ይህም ነገር በንጉሥ ዮስጥያኖስና አምላክን በምትወድ በንግሥት ታኦደራ ዘንድ ተሰማ ንግሥቲቱም አስቀድሞ የተሾመው በሹመት ወንበሩ ይቀመጥ ብላ ጻፈች። ሃምሳ ስምንት ካህናትም ጉባኤ አደረጉ አስቀድሞ የተሾመ አባ ቴዎዶስዮስ ነው ሲሉም ጻፉ ። ያን ጊዜም አቃቅያኖስ በሕዝብ ፊት ቁሞ ክፉዎች ሰዎች ስለ አስገደዱኝ ይህን ሥራ ለመሥራት ሕግን ተላልፌአለሁ አለ ። ከዚህም በኋላ አቃቅያኖስ ከውግዘቱ እንዲፈታው ነገር ግን ከህነትም ሆነ ሊቀ ዲቁና ለዘለዓለሙ እንዳይኖረው ሕዝቡ አባ ቴዎዶስዮስን ለመኑት ። አቃቅያኖስም አዎ እንዲሁ ይሁን አለ ይህም አባት ከግዝቱ ፈታው ። ሃይማኖቱን ያጠፋ ንጉሡ ግን በክፉች ሃይማኖቱ ሊቀ ጳጳሳት አባ ቴዎዶስዮስ ከእርሱ ጋራ የሚስማማ መስሎት በእስክንድርያ ወዳሉ መኳንንቶች እንዲህ ብሎ ጻፈ ሊቀ ጳጳሳት አባ ቴዎዶስዮስ በሃይማኖት ከእኛ ጋራ የሚስማማ ከሆነ ሹመት ይጨመርለታል ። ለእስክንድርያ ከተማ ገዥ ይሆናል ። ይህ ካልሆነ ግን ከሹመቱ ይሻር ። ይህም አባት ይህን ነገር በሰማ ጊዜ እንዲህ አለ ሰይጣን በበረሀ ጌታችንን ብትሰግድልኝ የዓለም መንግሥታትንና ክብራቸውን ሁሉ እሰጥሃለሁ አለው ። ያን ጊዜም ይህ አባ ቴዎዶስዮስ ተነሥቶ ከእስክንድርያ ወጣ ወደ ላይኛው ግብጽም ሔደ በዚያም ሕዝቡን እያስተማራቸው በቀናች ሃይማኖትም እያጸናቸው ጥቂት ቀኖች ኖረ ። ንጉሡም አባ ቴዎዶስዮስ ከእስክንድርያ ከተማ እንደ ወጣ በሰማ ጊዜ እየሸነገለው ወደ እርሱ መልእክት ላከ እንዲህም አለው እኔ ከአንተ ጋራ ልነጋገር ከአንተም ልባረክ እንድትመክረኝም እሻለሁ ። ከዚህም በኋላ ወደ ቍስጥንጥንያ ከተማ ሔደ የጳጳሳት አለቆችና ሕዝቡ ሁሉ ሠራዊቱም ተቀበሉት በከፍተኛ ወንበርም ላይ አስቀመጡት ። እርሱ በርሳቸውም ስለ ሃይማኖት ተከራከሩ ንጉሡም አብዝቶ ሲሸነግለው ሊአባብለው ስንት ቅዱስ አባት ቴዎዶስዮስም ከቅዱሳት መጻሕፍት በመጥቀስ ይረታው ነበረ ። ከእርሱም ጋራ ባልተስማማ ጊዜ ከመንበረ ሢመቱ ወደ ላይኛው ግብጽ አሳደደው ። በእርሱም ፈንታ ጳውሎስ የሚባለውን ሰው ሾመው ። ጳውሎስም ወደ እስክንድርያ ከተማ በመጣ ጊዜ ሕዝቡ አልተቀበሉትም ዓመት ሙሉንም ኖረ በእጁም ማንም ቍርባንን አልተቀበለም ። ንጉሡም ይህን በሰማ ጊዜ ለመናፍቁ ጳውሎስ እስኪታዘዙ ድረስ አብያተ ክርስቲያናት እንደዘጉ አዘዘ ። ምእመናንም ከእስክንድርያ በመውጣት ወደ ቅዱስ ወንጌላዊ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ወደ ቆዝሞስና ድምያኖስ ቤተ ክርስቲያን ይሄዱ ነበር ካህናቱም በዚያ እየቀደሱ ያቆርቧቸው ነበር የአገር ልጆችንም የክርስትና ጥምቀትን ያጠምቋቸው ነበር ። ንጉሡም ይህን በሰማ ጊዜ አብያተ ክርስቲያትን እንዲከፈቱላቸው አዘዘ አባ ቴዎድሮስንም ሰምቶ ንጉሡ እንዳያስታቸው ፈራ ማጽናኛ ቃልን የተመላች መልእክትም ጽፎ በቀናች ሃይማኖት እያበረታታቸው ወደ ምእመናን ላካት እንዲህም አላቸው በዚያ ከሀዲ ጳውሎስ እንዳትታዘዙ ተጠበቁ ። ይህም አባት ሃያ ስምንት ዓመት በስደት ኖረ ። መላው የሹመቱ ዘመን ሠላሳ ሁለት ነበር ። ይኸውም በእስክንድርያ አራት ዓመት በስደትም ሃያ ስምንት ዓመት ነው ። ይህም አባት ብዙ ድርሳናትን ደርሷል ምእመናንም በያዕቆብ ዘመን ያዕቆባውያን እንደ ተባሉ በስሙ ቴዎድሮሳውያን እየተባሉ ሲጠሩ ኖሩ ። መልካም ጉዞውንም ፈጽሞ በሰላም አረፈ ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን ። አርኬ ሰላም ለቴዎድስዮስ ዘተወክፈ ክበደ ። ለሕማም ወለተሰዶ ። በቃለ ሃይማኖት እንዘ ይሜህር ውሉደ ። በእንተ ዘገብረ ለክርስቶስ ፈቃደ ። ዐስበ ሐዋርያት ሎቱ ምንተኑ ኢውሕደ ። ዳግመኛም በዚህች ቀን የባስልዮስ የቢፋሞን የባሊዲናስ የኮትሎስ የአርዳሜለም መታሰቢያቸው ነው በረከታቸው ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን ። ሰኔ ፳፰ ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ፩.አባ ቴዎድስዮስ ሊቀ ጳጳሳት ፪.ቅዱስ ያዕቆብ ዘአልበራደይ ፫.ቅዱስ ባስልዮስ ፬.ቅዱስ ባሊዲና ወርኃዊ በዓላት ፩.አማኑኤል ቸር አምላካችን ፪.ቅዱሳን አበው (አብርሃም፡ ይስሐቅና ያዕቆብ) ፫.ቅዱስ አንድራኒቆስና ሚስቱ ቅድስት አትናስያ ፬.ቅድስት ዓመተ ክርስቶስ ፭.ቅዱስ ቴዎድሮስ ሮማዊ (ሰማዕት) ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና። ሲነቅፉአችሁና ሲያሳድዱአችሁ በእኔም ምክንያት ክፉውን ሁሉ በውሸት ሲናገሩባችሁ ብፁዓን ናችሁ። ዋጋችሁ በሰማያት ታላቅ ነውና ደስ ይበላችሁ ሐሴትም አድርጉ፤ ከእናንተ በፊት የነበሩትን ነቢያትን እንዲሁ አሳድደዋቸዋልና። (ማቴ. ፭ ፥ ፲) ※※※※※※※※※※※※※※※※※※※※※※※ ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አአላፈ። እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ። ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ። እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ። እምእለ አብኡ ብዑላን ዘተርፈ። ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን። ሰማዕት ወጻድቃን መላእክት ትጉሃን። ደናግል ዓዲ ወመነኮሳት ኄራን። ባርኩ ባርኩ ጉባኤ ዛቲ መካን። እስከ አረጋዊ ልሒቅ ወቅኑስ ሕፃን። ለዘጸሐፎ በክርታስ ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ። ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ። ወለዘሰምዐ ቃሎ በዕዝነ መንፈስ። በጸሎተ እሙ ማርያም ዐረፍተ ኵሉ እምባእስ። ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ። ※※※※※※※※※※※※※※※※※※※※※※※