Rebi Media Network-(RMN)
رفتن به کانال در Telegram
Rebi Channel . . . join join join Create causative Generation
نمایش بیشتر375
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
ማመስገን አታቁም !የጎደለህን አትቁጠር
የተሰጠህን አስብ ፤ ብዙ ያልጠበካቸዉ መልካም ነገሮች በህይወትህ ብዙ ጊዜ ደጋግመዉ
ተከስተዋል ፤የዛሬዉ ቀን አንዱ ስጦታ ነዉ።ትናት ሲስቁ ዉለዉ ዛሬ ጠዋት ግን
ከእንቅልፍቸዉ ያልነቁ ብዙ ሰዎች አሉ፤
ይሄንን ፅሁፍ ለማንበብ ቢያንስ መተንፈስ አለብህ፤በህይወት እስካለህ ደግሞ የማይስተካከል ነገር የለም። ወዳጄ መስጠት በማይሰለቸዉ ፈጣሪህ
ማመስገን አትሰልች !
መልካም የተባረከ ቀን ይሁንላችሁ🙏
ሀሳብህን እወቅ!
መጥፎ ሀሳቦች በአዕምሮ ውስጥ ጎጆ እንድሠሩብህ አትፍቀድ አሉታዊ ሀሳቦች/ስሜቶች መንገድ መንገድ ላይ እንዳሉ ጓድጓድ ናቸው። ጥሩ ችሎታ ካለህ፣ ጓድጓዶችን በዘዬ በማለፍ ጉዞህ የተቃና እንዲሆን ማድረግ ትችላለህ።
መልካም ቀን ይሁንላችሁ🙏
የካንሰር ህመምን አሸነፈ፤ ጎልም አስቆጠረ ..
#Ethiopia | ሰባስቲያን ሃለር (Sebastien Romain Teddy Haller) ይባላል። በፈረንጆቹ አቆጣጠር 1994 ነው በፈረንሳይ የተወለደው። በዜግነት አይቮሪኮስታዊ ሲሆን በአጥቂ ቦታ ላይ ለኮትዲቫር እና ለዶርትሞንድ ይጫወታል።
ይህ የእግር ኳስ ፈርጥ በአንድ ወቅት በካንሰር ምክንያት ከሚወደው እግርኳስ ተለየ። ያ የሚያምር ተክለ ሰውነት እና ችሎታ አልጋ ላይ ዋለ።
ሁሉም አበቃለት በቃ ተሸነፈ አሉት። እሱ ግን ተስፋ ባለመቁረጥ አበቃለት ተስፋ የለውም የተባለበትን የካንሰር ህመም የዛሬ አመት በድል አገግሞ አሸነፈው። ወደ እግርኳሱም ተመለሰ።
በ34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይም ለሀገሩ አይቬሪኮስት እራሷ በደገሰችው ድግስ ላይ ሲጫወት ተመለከትነው። ትላንት ማታም ወደ ደገሰችው የፍፃሜው ጨዋታ ኮትዲቯር ዴሞክራቲክ ኮንጎን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለፍጻሜ ማለፏን ያረጋገጠችበትን ድንቅ እና ብቸኛ ጎል ይህ የካንሰር አርበኛው ሴባስቲያን ሃለር በ65ኛው ደቂቃ በግሩም ሁኔታ አስቆጥሮላት ነው።
ሀገሩ ከምድብ ለማለፍ ተቸግራ እንዴት እንደነበረ ተመልክተን ነበር የእሱም ህይወት እንደዚያው። ታዲያ ይህ ጀግና ትልቅ ትምህርት አልሰጠንም ወድቆ መነሳትን አላስተማረንም! የ
እዚህ ጀግና ልጅ ህይወት ለብዙዎች ምሳሌ በመሆን መነቃቃትን ፈጥሮልናል። ኮትዲቫር እራሷ አዘጋጅታ እራሷ ትበላው ይሆን? ሰባስቲያንም ወድቆ መነሳትን አሳይቶናል በዋንጫም ይደግመው ይሆን? እነዚህን መልሶች የፊታችን እሁድ ዋንጫውን ለማንሳት ኮትዲቯር እና ናይጄሪያ የሚፋለሙበትን የፍፃሜ ጨዋታ ይመልስልናል።
#ራስን_ለመግዛት_የሚረዱ_6_ነጥቦች!
1. ደካማ ጎኖችዎን ይለዩ፦
ደካማ ጎኖቻችሁን ችላ ማለት እንዲጠፉ አያደርጋቸውም። ስለዚህ ጣፋጮችን መብላት የክብደት መጨመሮ ምክንያት ነው? ማህበራዊ ሚዲያ ማዘውተር ምርታማነትዎን ቀንሶታል? ድክመቶችዎን ይወቁ። ድክመቶችዎን ማወቅ አዎንታዊ ለውጥን ለመፍጠር የመጀመሪያው እርምጃ ነው።
2. ግልፅ የሆነ ስልት ይቀምሩ፦
ከፍ ያለ ራስን የመግዛት አቅም በድንገት አይመጣም። ይልቁንም የአእምሮ ጡንቻን ለመገንባት የሚያግዝዎት ስልት ማበጀት ያስፈልግዎታል። ብዙ ጊዜ ወደ ጂም እንደመሄድ ያሉ ጥሩ ልምዶችን መጨመር አልያም ብዙ ሶሻል ሚዲያ መጠቀምን የመሰሉ መጥፎ ልምዶችን ማስወገድ ከፈለጉ እነዚህን ዓላማዎችዎን ወደ ተግባር ለመቀየር ዕቅድ ያስፈልግዎታል። በየቀኑ መውሰድ የሚያስፈልጎትን እርምጃዎችን በግልጽ ይዘርዝሩ።
3. የሚፈታተኖትን ነገሮች ያስወግዱ፦
ቤትዎ ጣፋጮች ምግብ ከተከማቹ ክብደትን ለመቀነስ ራስን የመግዛትን አቅም ያዳክማል። ይልቁን እያንዳንዱን ኩኪስ፣ ቺፕስ እና ሌሎች ጣፋቾችን ላለመብላት በመሞከር ጊዜዎን ያባክናሉ። ድክመትዎ በየሁለት ደቂቃዎች ማህበራዊ ሚዲያዎችን መፈተሽን የሚያካትት ከሆነ ፌስቡክን የሚያግድ መተግበሪያ ይፈልጉ። ፈተናዎችን መገደብ በጊዜ ሂደት የበለጠ ራስን የመግዛትን አቅሞን እንዲገነቡ ይረዳዎታል።
4. ምቾት ማጣትን ይለማመዱ፦
ምቾት ማጣትን ለማስወገድ መሞከር ተፈጥሯዊ ነው። ነገር ግን የአጭር ጊዜ ምቾትን መሻት ብዙውን ጊዜ የረጅም ጊዜ ችግሮችን ያስከትላል። እናም በተሸነፉ ቁጥር ጭንቀትን መቋቋም እንደማይችሉ ለራስዎ ያሳምናሉ። ምቾት ማጣትን ይለማመዱ፤ ያ ማለት እርስዎ ከሚያስቡት በላይ ለተጨማሪ ደቂቃ መሮጥ ወይም ጣፋጭ ምግቦችን የመብላት ፍላጎትን መቃወም ባጠቃላይ ምቾት ማጣት ጠላት አለመሆኑን እንዲያምን አዕምሮዎን ያሰልጥኑ።
5. ግቦቾን ያስታውሱ፦
ፈተናን ሲጋፈጡ ሊያገኟቸው የሚችሏቸውን ነገሮች ለራስዎ ያስታውሱ። ከግቦችዎ ጋር ሲጣበቁ የሚያገኟቸውን ነገሮች ሁሉ ዝርዝር ይፃፉ፤ ተስፋ ለመቁረጥ በሚፈተኑበት ጊዜ ዝርዝሩን ያንብቡ።
6. ለውድቀት ያለዎትን አመለካከት ይቀየሩ፦
መሻሻል ብዙውን ጊዜ በቀጥታ መስመር ላይ አይመጣም። ስህተት ሰርተዋል ማለት ከዚህ በኋላ አይሳካሎትም ማለት አይደለም። ስህተት የመሻሻል ሂደት አካል ነው። ከእነዚህ ስህተቶች የሚመለሱበት መንገድ ነው በጣም አስፈላጊው ነገር፤ ከተሳሳቱት እርምጃዎችዎ በመማር በሚቀጥለው ጊዜ የተሻለ ለማድረግ ቁርጠኛ ይሁኑ።
Learn to #say_NO!!!
ካስቀመጣችሁት የሕይወት መርህ እና እንዲሁም ለትክክለኛና ሚዛናዊ ለሆነው የግል ፍላጎታችሁና ፈጣሪ ከሰጣችሁ ማንነታችሁ አንጻር ግፊት ለሚያደርግባችሁ ሰውም ሆነ ሁኔታ በተረጋጋ መንፈስ “እምቢ” በማለት በራስ እድገት ላይ እስከምታተኩሩ ድረስ ሕይወትን ማጣጣምም ሆነ የወደፊት ራእያችሁን እውን ማድረግ እንደማትችሉ ላስታውሳቸሁ፡፡
✅
ረቢ ሚድያ
#ሳታሸንፍ_እንዳታወራ!
♟ እንዲገምቱህ፣ ዝቅ አድርገው እንዲያዩህ ፍቀድላቸው። በተሳሳተ መንገድ ይረዱህ።
ይህ ላንተ ያላቸው አሉታዊነት ያንተ ችግር አይደለም። ያንተ ችግር እንደገመቱህ፣ ዝቅ አድርገው እንዳዩህ እንደዛው ስትቀር ነው።
♟ ህይወት ስለሌሎች የምትደክማት ለታይታ የምታባክናት ኪሳራህ መሆን የለባትም። ይልቁንስ ስለራስህ -ለራስህ የምትታገልባት ደግመህ የማታገኛት እስትንፋስህን እንደሆነች ተረድተህ ኑር።
ስለዚህ የራስህን እውነት ተከተል። እምነትህን አጽና። ስለሚወራብህ ነገር ሳይሆን ስለምትሰራው ነገር ትኩረት ይኑርህ።
♟ ሰዎች ምን አደረጉ፣ ምን አወሩ ጉዳይህ አይሁን። ይህች አለም የብዙዎች መኖሪያ ብትሆንም ሁሉም የሚኖረው ግን የግሉን ነው። ግላዊነትህ ላይ አተኩር።
ጨዋታህን እያሰብክ ቀጥል ነገሩ ቀድሞ በነገሰ እንዳልሆነ ተረዳ።
ቀድሞ በበላ አሸናፊነት የለም።
ለማሸነፍ መሸነፍህ መቅደም ካለበት ትንሽማ ይሳቅብህ፣ ይቀለድብህ።
እቅድህ እንዳይታይ በልብህ ሰውረው እንጂ እንዲህ ላደርግ ነው አትበል።
♟ ቀድመህ ቦታ ከምታጣ ዝግ ብለህ አፈግፍገህ ሰፊውን ግዛት ያዝ።
☑️ ሳታሸንፍ እንዳታወራ።
#በራስ_መተማመን መጽሐፍ 5ተኛ ዕትም
እንደ ፎርብስ ዘገባ ከ180 ሚሊየን ዶላር በላይ ንብረት ያፈራው ፡ የ25 አመቱ ፈረንሳዊው የእግር ኳስ ኮከብ Kylian Mbappe አሁን የናፈቀው ወጣትነቱን በነጻነት መኖር ነው ።
ፈርምልኝ ፡ አብረን ፎቶ እንነሳ ሳይባል ፡ መጣ ሄደ ፡ በዚህ አለፈ ፡ ሳይባል በነጻነት መንቀሳቀስና ፡ መኖር ናፍቆታል ዝና እና እውቅናው ፡ ከምቾት ይልቅ ሰላሙን ነስቶታል ።
" እንደ ማንም ሰው ዳቦ ቤት ሄጄ መግዛት እፈልጋለሁ ።
በምፈልገው ሬስቶራንት በፀጥታ መመገብ መቻል ናፍቆኛል ። ከጓደኞቼ ጋር ማንም መጥቶ ሳይረብሸኝ ፓርቲ ወጥቶ መዝናናት ፡ ይህንና ይህን መሰል ለሰው ቀላል የሚመስሉ ሰውኛ ነገሮችን ማድረግ ብፈልግም በዚህ ወቅት ይህ ነገር ለኔ ምኞት ብቻ ሆኗል ። በርግጥ ይህ ነገር ለአብዛኛዎቹ ሰወች ቀላል ወይም ተራ ነገሮች ቢሆኑም ለኔ ግን ምኞት ብቻ ሆኖ ቀርቷል ። እናም እንደ ማንም ሰው መንቀሳቀስ የምችልበት ነገር ቢኖር ምንም አይነት ገንዘብ ብከፍል አይቆጨኝም ። ሲል ተናግሯል ።
......
የአንዱ ትልቅ ምኞት ፡ ለአንዱ ተራ ነገር ነው ።
ከ [ዋሲሁን ተስፋዬ]
በልጅነቴ ቱቦ ውስጥ የጣልሺኝ እናቴ ይቅር ልልሽ እፈልጋለሁና የት ነሽ?
#Ethiopia | በጎንደር ከተማ አዘዞ አካባቢ ተወልዶ ያደገው ወጣት አስና ሞላ በብዙ በደል ያሳደገችውን እናቱን ዛሬም ይቅር ማለት እፈልጋለሁ ይላል፡፡
አስና ሞላ በልጅነቱ ደመናን ቀና ብሎ የማየት ልማድ የነበረው ሲሆን ነገር ግን ይህ ልማዱ በአንድ ክፉ አጋጣሚ የአይን ብርሃኑን አሳጥቶታል፡፡ እንደወትሮው ሁሉ ሰማይና ደመናን ቀና ብሎ በሚያይበት ወቅት ከባድ መብረቅ ጥሎ ኖሮ የአስና የዐይን ብርሃኖች ላይመለሱ ይጨልማሉ፡፡
የልጅነት ጊዜውን በብዙ መከራና ስቃይ እንዳሳለፈ የነገረን አስና ያን ሁላ በደልና መከራ ተቋቁሞ ዛሬ የደረሰበትን ደረጃ ሲያስብ እንደሚገረም ገልጾልናል፡፡
ወላጅ እናቱ ምክንያቱን በማያውቀው ሁኔታ ታንገላተው እንደነበር የሚያስታውሰው ወጣቱ የአይን ብርሃኑን ከማጣቱ ጋር ተዳምሮ ወርቅ የሆነውን የልጅነት ጊዜውን ከባድ አድርጎበታል፡፡ ከዚህም ውስጥ ከሳምንት በላይ ምንም የሚላስ የሚቀመስ ሳትሰጠው ከመቆየቷ በተጨማሪ ቤት መግባት እየከለከለችው ውጪ ታሳድረው እንደነበር ያስታውሳል፡፡ በወቅቱ ጅቦች በአጠገቡ ይዘዋወሩ እንደነበረም ተናግሯል።
አይኑን በመብረቅ ማጣቱን ተከትሎ እናቱ መጥፎ እድል ነው ብላ ታምን የነበረ ሲሆን በዚህም በአንዱ ቀን ለሊት በጀርባዋ አዝላው ወንድሙን አስከትላ ራቅ ወዳለ አካባቢ ታመራለች፡፡ ያቺ ቀን አስና ከእናቱ ጀርባ ጋር የተዋወቀባት የመጀመሪያም የመጨረሻም አጋጣሚ ነበረች፡፡
እናትም አስናን አዝላ ሁለት ዳቦ ገዝታ ወዳገኘችው የውሃ መውረጃ ቱቦ በማምራት አንዱን ዳቦ ሰጥታው እንዲገባ ታስገድደዋለች። በወቅቱ በእንባ የታጀበ ልመና ብለምናትም የምትመለስ አልነበረችም ይላል አስና፡፡
አብሮት የሄደው ወንድሙም ወንድሜን... ወንድሜን..! እያለ የጮኸው ጩኸት ዛሬም እንደ አዲስ እንደሚሰማው ገልፆ እናት ግን በቁጣና ችኮላ ቶሎ ከአካባቢው ተሰወሩብኝ ይላል፡፡
በወቅቱ ህፃን በዛላይ ማየት የተሳነኝ ስለነበርኩ ሁኔታው መቋቋም ከምችለው በላይ ሆኖብኝ ነበር ያለ ሲሆን አምርሬ ሳለቅስ የሰሙ በአቅራቢያው ያሉ ሰዎችም ተሰባስበው ካለሁበት አውጥተውኝ ወደ ቤታቸው ወሰዱኝ ሲል ይገልፃል፡፡
ከዛ የጀመረው የህይወቱ ሌላ ገፅታም በደጋግ ኢትዮጵያዊያንና አሁንም ድረስ በማይረሳት አንዲት አሜሪካዊት መልካምነት ትምህርቱን ተምሮ እንደጨረሰና አሁን ላይ መምህር እና ባለትዳር ብሎም የልጆች አባት እንደሆነ ከአዲስ ዋልታ ዲጂታል ሚዲያ ጋር ባደረገው ቆይታ ገልጿል፡፡
ይህን ሁሉ ፈተና ያለፈው አስና በመጨረሻም ይቅርታ ያለፈውን የምንረሳበት እና ወደፊት የምንሻገርበት ድልድይ እንደሆነ ገልፆ እናቴን አግኝቼ ይቅር ማለት እፈልጋለሁ ብሏል፡፡እናቴ ባታየዉ ይህን መልዕክት ወንድሜ እንዲደርሰዉ ሼር አድርጉልኝ ብሏል።
(Ephrem Yirga Ayu Ethiopia)
ወደ ስራ ስሄድ አንድ የስልክ እንጨት ላይ የተለጠፈ ወረቀት አየሁኝ: ጽሁፉ እንዲህ ይላል
"እዚህ መንገድ ላይ 50 ብር ጠፍቶብኛል: ያገኘ ሰው ካለ እባካችህን አድራሻዬ በሚቀጥለው መንገድ በቀኝ በኩል ስትታጠፉ ያለው አሮጌ ቤት ነው:: አይኔ እንደፈለግኩኝ አያይም: እድሜዬም ገፍቷል: ልጆችም የሉኝም"
ይህንኑ ጽሁፍ ተከትዬ ወደ አሮጌው ቤት ስሄድ አንዲት ሴትዮ ደጃፍ ላይ ተቀምጠዋል: የእግር ኮቴየን ሰምተው "ማነው? ማን ልበል?" አሉኝ
"እዚህ መንገድ ላይ 50 ብር አግኝቼ ነው: እሱን ልሰጥ ነው የመጣሁት" ብዬ መለስኩላቸው
አሮጊቷ እንባ ቀደማቸው - "ልጄ! እስካሁን ድረስ ከ40 በላይ ሰዎች 50 ብር መንገድ ላይ ወድቆ አገኘን ብለውኝ መጥተዋል"
ቀጠሉ እማማ - "እኔ ይህንን ጽሁፍ አልጻፍኩኝም: ጽሁፍ ለመጻፍም ሆነ ለማንበብም አይኔ እሺ አይለኝም"
50 ብሩን በእጃቸው አስጨበጥኳቸው
ጽሁፉን ከስልክ እንጨቱ ላይ እንድቀደው ቢነግሩኝም አላደረግኩም: የመጣውን ሰው ሁሉ ይህንኑ ነበር የሚሉት
ይህንን ጽሁፍ የጻፈውን ሰው እንዴት እንዳደነቅኩት : እኚህን ሴትዮ ለመርዳት የሄደበት ርቀት በጣም ነው ያደነቅኩት!
ከሴትዮዋ ቤት ስወጣ አንዲት ወጣት ልጅ አስቆመቺኝ
"ወንድሜ! እዚህ መንገድ ላይ 50 ብር አግኝቼ ነበር: የቤቱ አቅጣጫ በየት በኩል እንደሆነ ታውቃለህ እንዴ?"
በልቤ እየሳቅኩኝ ቤቱን ጠቆምኳት😍
#ሰው_መሆኛ_መንገዱ_ብዙ_ነው ❤️🙌🏼
@T2T4T5
#ጭንቀት
👉 አንዳንድ ሰዎች በየምክንያቱ ይጨናነቃሉ፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ ግን አብዛኛዎቹ የምንጨነቅባቸው ነገሮች ቀድሞውኑ መሰረት የሌላቸው ናቸው፡፡ ለምሳሌነት የሚከተለውን የአንድ ጥናት ውጤት እንመልከት፡፡ የምንጨነቅባቸው ነገሮች . . .
1. 40% በፍጹም ለማይደርስብን ነገር
2. 30% ምንም ልንለውጠው ስለማንችለው ስላለፈው ነገር
3. 12% ሰዎች ስለእኛ ስለሚናገሩብን ፍርድ፣ ወሬና ሃሜት
4. 10% ስለጤንነታችን (ስለተጨነቅን የሚብስ)
5. 8% ስለእውነተኛ ልናስብበት ስለሚገባ ሁኔታ
በፍጹም ለማይደርስብን ነገር ከተጨነቅን . . . ያለን አማራጭ ምክንያታዊነትን ማዳበር ነው፡፡ ሁኔታው ሊደርስብንና ላይደርስብን የሚችልበትን የእድል መጠን አመዛዝነን ያለመድረሱ ሁኔታ ካመዘነ፣ መጨናነቅን የማቆምን ሂደት መጀመርና እየተዉ መሄድ የግድ ነው፡፡ አንዳንድ ሰዎች ግን እንዲሁ ምክንያት ፈልገው የመጨነቅ “ሱስ” አለባቸው፡፡
ይህ ዝንባሌ የሚመጣው ለረጅም ጊዜ በአጣብቂኝ ሁኔታ ከማሳለፍና ስሜታችን የጭንቀት ሰለባ ሆኖ ከመክረሙም የተነሳ ሊሆን ይችላል፡፡ ያም ሆነ ይህ ፍጹም የማይደርስ ነገር ተለይቶ ሊታወቅና ከስሜታችን የደም ዝውውር ውስጥ ሊወገድ ይገባዋል፡፡
ምንም ልንለውጠው ስለማንችለው ስላለፈው ነገር ከተጨነቅን . . . ያለን አማራጭ ፈጽሞ አንዴ የሆነ ነገር መሆኑንና ምንም ብናደርግ ልንለውጠው እንደማንችል በመቀበል አእምሮን በአዳዲ ነገሮች መሙላት ነው፡፡ ይህን ማድረግ ካልፈለግን ግን እስቲ አንዴ የሆነውንና ያለፈውን ነገር ለመለወጥ የአንድ ወር ጊዜ እንስጠውና የምንችለውን ያህል እንሞክርና ካልቻልን ነገሩን ለመተው ለራሳችን እድል እንስጠው፡፡
ሰዎች ስለእኛ ስለሚናገሩብን ፍርድ፣ ወሬና ሃሜት ከተጨነቅን . . . ያለን አማራጭ መቆጣጠር የማንችለውን የሰውን ባህሪይ ለመቆጣጠር ከመጦዝ ይልቅ መቆጣጠር የምንችለውን የራሳችንን በሆነ ባልሆነው የመጨነቅ ዝንባሌ ለመቆጣጠር መስራቱ ይመረጣል፡፡ ሰዎች ስለአንተና በአንተ ላይ የሚሉት ነገር አንተ ካልፈቀድክለት በስተቀር ምንም ሊያደርግህም እንደማይችል አትዘንጋ፡፡ ብትችል ወሬው አንተ ጋር የማይደርስበትን መንገድ ፍጠር፡፡ ካልቻልክ ደግሞ ወሬው ወደ ስሜትህ የማይደርስበትን ጥንካሬ አዳብር፡፡
ስለጤንነታችን (ስለተጨነቅን የሚብስ) ከተጨነቅን . . . ያለን አማራጭ ስለጤነታችን የሚያሳስበን ሁኔታ ካለ ያንን ለማስቀረት ወይም ለመቀልበስ የምንችለውን ያህል መሞከር ነው፡፡ ጭንቀታችን ግን “ምናልባት እታመም ይሆን” የሚል ከሆነ፣ ይህ የራስ በራስ ትንበያ እንደሚፈጸም አትጠራጠር፡፡ ጭንቀት በሽታን የመሳብ ባህሪይ አለውና፡፡
ስለእውነተኛ ልናስብበት ስለሚገባ ሁኔታ ከተጨነቅን . . . ያለን አማራጭ በቅድሚያ፣ ሁኔታው በትክክልም የሚያሳስብና በቅጡ ካልያዝነውም የሚስጨንቅ ጉዳይ ስለሆነ ማሰባችንና በመጠኑም ቢሆን መጨነቃችን ትክክለኛው መሆኑን አምኖ መቀበል አስፈላጊ ነው፡፡ ሲቀጥል ያሳሰበንን ሁኔታ በምን መልኩ ብንጋፈጠው ልናሸንፈው እንደምንችል በሚገባ ማሰብን ይጠይቃል፡፡ አእምሮን በጭንቀት ከመሙላት ይልቅ ትክክለኛውን ምላሽ በማሰብ መሙላት በብዙ እጥፍ ይመረጣል፡፡ በጉዳዩም ላይ ሰውን ማማከሩም አንዱ መንገድ ነው፡፡
👇
@T2T4T5
ኢትዮጵያችንን በጋራ እንጠብቃት💚
1.በኢትዮጵያ ግብረሰዶማዊነት ህጋዊ ሊሆን ነዉ::
2.በኢትዮጵያ የጾታ መቀየር ህጋዊ ሊሆን ነዉ::
3.በኢትዮጵያ ውርጃ ህጋዊ ሊሆን ነዉ::
4.በኢትዮጵያ የወሲብ ትምህርት ህጋዊ ሊሆን ነዉ::
ባሳለፍነው ህዳር 5 ቀን 2016 ዓም ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአፍሪካ ከካሪቢያንና ከፓሲፊክ የተውጣጡ ሀገራት ለሚቀጥሉት 20 ዓመታት የሚቆይ የንግድና ኢኮኖሚ ትብብር ስምምነትን ከአውሮፓ ህብረት ጋራ ሳሞዋ
በምትባል ሀገር በፈረሙ ወቅት አገራችን ኢትዮጵያም ይህንኑ ስምምነት ተቀማጭነታቸው ብራሰልስ በሆኑ አምባሳደ አማካኝነት በፊርማዋ አጽድቃለች፡፡ ይህ አደገኛ ይዘቶች ያሏቸውን አንቀጾች የያዘው ስምምነት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀድቆ ከሚቀጥለው ጥር ወር ጀምሮ ወደ ትግበራ እንደሚገባ ይጠበቃል፡፡
ይህ የትብብር ስምምነት በውሥጡ የያዛቸውን አስራ ሁለት ዋና ዋና አደገኛ ይዘቶችን ጠቅልለው የሚይዙ የተወሰኑ ሀሳቦች ለመጥቀስ ያህል ፡-
1) የሀገር ሉዓላዊነትን የሚጥሱ አንቀጾች በግልጽ መቀመጣቸው፣
2) ግብረሰዶማዊነት፣ የጾታ መቀየርና፣¸ውርጃና ሁሉን አቀፍ የወሲብ ትምህርትን የመሳሰሉ እኩይ አጀንዳዎች በሰብዓዊ መብት ሽፋንና በሌሎች አሳሳች ሀረጎች ተሰውረው የገቡበት መሆኑ፣
3) ግብረሰዶማዊነት በርካታ ቀውሶች ማለትም በአካል፣ በሥነልቦናና በማህበራዊ ህይወት ላይ የሚያስከትልና ለሀገር ደህንነትም አደጋ መሆኑ፣
4) የወላጆችን መብት የሚጥስና የኢትዮጵያዊ ቤተሰብ እሴቶችን የሚንድ መሆኑ፣
5) የሀገራችንን ሀይማኖት፣ባህልና እሴቶች የሚንዱ ጸያፍ ልምምዶችን እንድንቀበል በሰብዓዊ መብት ሽፋንና በእርዳታ ስም የምንገደድበትና ለዘመናዊ ባርነት ወይንም ቅኝ አገዛዝ ታልፈን የምንሰጥበት መሆኑ፣
በአጠቃላይ ይህ አዲስ የአጋርነት ስምምነት ልዩ ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡና ትውልድንና ብሎም ሀገርን እጅግ የሚጎዱ በርካታ አንቀጾች የተካተቱበት መሆኑ ለሀገራችን ህዝብ ዕድገትን ሳይሆን ውድቀትንና ከፍተኛ የሞራል ዝቅጠትን የሚያስከትል መሆኑን በሚገባ ተረድተናል፡፡
በተጨማሪም ከተጠበቀው ውጭ ሀገራችን ይህንን ስምምነት በመፈረም የተጋረጠብንን እጅግ አሳሳቢ አደጋ ለመቀልበስ አስፈላጊ የሆኑ ሰላማዊና ህጋዊ መንገዶችን ሁሉ በመጠቀም መንግስት ትኩረትን እንዲሰጠው ማድረግ ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ መሆኑን ተገንዝበናል፡፡
በመሆኑም ይህ የመንግስት ውሳኔ እንደገና ተጠንቶ ውሳኔው እንዲቀለበስ ማለትም ስምምነቱ አስፈላጊው ሁሉ ማስተካከያ እስኪደረግበት ድረስ ወይንም እጅግ አደገኛ የሆኑት አንቀጾች ተነቅሰው ወጥተው የማንቀበላቸው መሆናችንን በይፋ ማሳወቅ
(Submission of an Interpretive Declaration) እስከምንችል ድረስ የምንወዳት ሐገራችን ኢትዮጵያ ፊርማዋን በመሰረዝ ከስምምነቱ ራሷን እንድታገልል በሐገራችን ከፍተኛው የሥልጣን አካል ለሆነው ለተከበረው
* የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና
* ለሐገሪቱ መሪ ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ
በታላቅ አክብሮት እጅግ አስቸኳይ ጥሪን እናደርጋለን፡፡
Via CSE
👇
@T2T4T5
መታመን !
#Ethiopia | Radric Davis ( ጉቺ ሜን ) አሜሪካዊ ራፐር ነው ። ከጎኑ ያለችው ደሞ Keyshia Ka'Oir ትባላለች ፡ ሞዴሊስት ፡ ጎበዝ አክትረስና ፡ ኢንተርፕረነር ነች ።
እና ፡ ከአመታት በፊት ፍቅረኛዋ ጉቺ ሜን ፡ በአንድ ወንጀል ተከሶ ፍርድ ቤት ቀረበና ፡ የሶስት አመት እስር ተፈረደበት ።
.....
ጉቺ ሜን ፡ ይህን የዳኞቹን ውሳኔ እንደሰማም ፡ ፍቅረኛውን ኬይሽያን ፡ ወደ እስር ቤት እንድትመጣ ላከባት ።
....
እየውልሽ ፡ በእስር ቤት ቆይታ ምን እንደሚፈጠር አላውቅም ። ስለዚህ በስሜ ያለውን ሁለት ሚሊየን ዶላር ፡ ወደ አንቺ ባንክ አካውንት እንዲዛወር እፈልጋለሁ አላት ።
...
እና በባንክ ያለውን ብር በሙሉ ፡ አንድም ሳያስቀር ፡ ለፍቅረኛው ኬይሽያ ሰጣት ።
ጓደኞቹ ቀለዱበት ። ታስረህ ስትፈታ ጎዳና ልትወድቅ ነው ? ይህን ሁሉ አመት ትጠብቀኛለች ብለህ አታስብ አሉት ።
.....
Keyshia Ka'Oir ፍቅረኛዋ የሰጣትን ገንዘብ ከባንክ ያወጣችው ብዙም ሳይቆይ ነበር ። እናም በገንዘቡ የራሷን Ka'Oir የሚባል የኮስሞቲክስ ማምረቻ ከፍታ መንቀሳቀስ ጀመረች ።
....
ጊዜው ሳይታወቅ ሄዶ ፡ ፍርደኛው ራፐር ጉቺ ሜን የእስር ጊዜውን ጨርሶ ወጣ ። ጓደኛው ኬይሺያ ፡ በስራ ምክንያት ቢዚ ብትሆንም ፡ አልፎ አልፎ እየመጣች ትጠይቀው ነበር ። እና እንደተፈታ በዘመናዊ መኪና መጥታ ፡ ወደ አዲስ ቤት ይዛው ሄደች ። ከዚህ ሁሉ አመት መለያየት በኋላ ትጠብቀኛለች ብሎ ባያስብም ፡ እሷ ግን ከአመታት በኋላም ሳትቀየር ነበር ያገኛት ።
እና ቤት ደርሰው አረፍ ካሉ በኋላ ፡
" ጉቺ እስር ቤት ስትገባ ፡ በወቅቱ ሚስትህ ሳልሆን ፡ ትክደኛለች ሳትል ፡ ሁለት ሚሊየን ዶላር ሰጠኸኝ ነበር አይደል ? " አለችው ።
አዎ አላት ።
ይኸው ስድስት ሚሊየን ዶላር ሆኖ ጠብቆሀል አለችና ፡ የባንክ ቡኳን እንዲያየው ሰጠችው ።
.....
ዛሬ ላይ ፡ ጉቺ ሜን ፡ ከዛች ፍቅሩን ብቻ ሳይሆን የሰጣትንም ገንዘብ በእጥፍ አሳድጋ ከጠበቀችው Keyshia Ka'Oir ፡ ጋር ተጋብተው ፡ ትዳራቸው በልጅ ደምቆ , አብረው ይኖራሉ ።
Wasihune Tesfaye
#ከስህተታችን_ምን_እንማር?
ቶማስ ኤዲሰን፦ ስለስህተቶቹ ሲያወራ እንዲህ ይላል
. "እኔ ብዙ ስለሞከርኩ ደስተኛ ነኝ ምክንያቱም ሁሌም ስሞክር ወይ ልክ ነኝ ወይ ደግሞ ተምሬበታለው" ይለናል። ያለፉ ስህተቶቻችንን ለከፍታችን መጠቀም አለብን፤ ሰሞኑን ካጋጠመኝ ችግር ምን ተማርኩበት እንበል። ሁለቴ መውደቅ የሚፈልግ የለም መቼም...
አሸናፊ ማለት የማይወድቅ አይደለም፤ ቢወድቅም መልሶ የሚነሳ ነው። የሆነ ነገር አልሳካ ሲለን እስኪ ምንድነው ያጎደልኩት ብለን ጊዜ ወስደን ማሰብ አለብን። ከስህተት በላይ ምን አስተማሪ ነገር አለ? እንዲያውም ምርጥ አድርጌ ደግሜ እንድሰራው እድል ተሰጥቶኛል ማለት አለብን።
✍️Change - የአስተሳሰብ ለውጥ
መታገስ ዋጋ አለው!!!
ህልሞቻችንን እና ግቦቻችንን ለማሳካት ትዕግስት ወሳኝ ነገር ናት።
ትዕግስት ዝም ብሎ የመጠበቅ ችሎታ ሳይሆን ፅናትን፣ አላማን ለማሳካት ተግቶ መስራትና እንቅፋቶችን እና ተግዳሮቶችን ለመቋቋም ፈቃደኛነትን የሚያካትት አስተሳሰብ ነው።
ትዕግስት በጉዟችን ላይ እንቅፋት የሚሆኑ ድንገተኛ ወይም የችኮላ ውሳኔዎችን እንዳንወስን በመከላከል የመረጋጋትና የማስተዋል ስሜት እንድንይዝ ያስችለናል።
ወዳጄ ሆይ ትዕግስትን በማድረግ ሁኔታዎችን በጥንቃቄ መገምገም፣ አማራጭን ማጤን እና በመረጃ ላይ የተመሰረት ምርጫ ማድረግ ትችላለህና ትዕግስትን ተለማመድ።
🙏
አንድ ቅቤ አምራች ገበሬና ዳቦ አምራች ነጋዴ እንደ አጋጣሚ ድግስ ላይ ተገናኝተው ያወራሉ፡፡ በጨዋታቸው በጣም ስለተግባቡ ከዚህ በኋላ አጋጣሚ ፈጥረው ለመገናኘት ይስማማሉ፡፡ ነጋዴው ጠዋት ጠዋት 300 ግራም ዳቦ ሲልክለት ገበሬው ደግሞ ማታ ማታ 300 ግራም ቅቤ ሊልክለት ተስማሙ፡፡
በዚህ መልኩ ብዙ ጊዜ ከቆዩ በኋላ ነጋዴ የቅቤ መጠን እየቀነሰ መሄዱን አየ፡፡ በመጨረሻም ሚዛን ላይ ሲያስቀምጠው 150 ግራም ሆኖ አገኘው፡፡ በዚህም በጣም አዘነ፤ ተበሳጨም፡፡ ገበሬውንም አስጠራው፡፡ ሌሎች ሰዎች እንዲያዳምጡት አድርጎ ‹ከተስማማነው ውጭ የቅቤውን መጠን ለምን ቀነስከው?›ሲል ጠየቀው፡፡ ገበሬውም ‹እኔ ፈጽሞ አልቀነስኩትም› ሲል በአግራሞት መለሰ፡፡ ነጋዴውም ቅቤውን በሚዛን ለክቶ አሳየው፡፡ 150 ግራም ነው፡፡
ገበሬውም አዘነ፡፡ ‹እኔ ቤት ውስጥ የ300 ግራም መለኪያ የለኝም፡፡ አንተ ጠዋት ዳቦውን ስትልክልኝ በእጅ ሚዛኑ አንደኛው ሰሐን ላይ አደርገዋለሁ፤ ከዚያም ቅቤውን በሌላኛው ሚዛን አስቀምጠዋለሁ፡፡ ልክ ከዳቦው ጋር እኩል ሲመዝኑ በዕቃ አዘጋጅቼ እልክልሃለሁ› አለው፡፡ ወዲያውም ጠዋት የላከለትን ዳቦ አውጥቶ ሚዛኑ ላይ አስቀመጠው፡፡ ዳቦው 150 ግራም ነበር የሚመዝነው፡፡ ነጋዴው አፈረ፡፡
‹የምታገኘው ለሌላው ባደረግከው ልክ ነው፡፡ 150 ሰጥተህ 300 ልታገኝ አትችልም፤ እባብ ሰጥተህ ርግብ፣ ድንጋይ ሰጥተህ ዳቦ፣ እሬት ሰጥተህ ማር ልታገኝ አትችልም፤ አንተ ብቻ ብልጥ ልትሆን አትችልም፤ ሻማውን አጥፍተህ ብርሃን ልታገኝ አትችልም፤ ሌላው ገድለህ አንተ በሰላም ልትኖር አትችልም› አለው ገበሬው፡፡
daniel kibret
👇
@T2T4T5
#አዕምሮ ማበልፀግ
የተረጋጋ ህይወት እንዲኖርህ መፅሀፍትን አንብብ። ብዙ አታውራ፤ ማውራት ሲኖርብህ ግን ዝም አትበል። ምክርና አስተያየት ለመቀበል አትፍራ። ለተደረገልህ ጥሩ ነገር አመስግን፤ በቂ እንቅልህ ተኛ፤ የማታውቀውን ጠይቅ፤ በየወሩ ካለህ ገቢ ላይ ትንሽም ቢሆን ቆጥብ፤ ዛሬ መስራት የምትችለውን ነገር ዛሬውኑ ስራ። የሰው ልጅ ሲቸግረው ልብሱን የቤቱን ዕቃ፤ ኩላሊቱንም ሳይቀር ሊሸጥ ይችላል። ህሊናውን ከሸጠ ግን በጠና ቸግሮታል ማለት ነው።
🙏
✨ዶ/ር ምህረት ደበበ
👇
@T2T4T5
እያሳሳቀ ወደ ጨለማ ህይወት የሚወስደው የሱስ ህመም፦ ቁማር-የመጫወት ህመም /pathological Gambling disorder/
ሚስቱን አስይዞ ቁማር ከሚጫወት ሰው በላይ የስብዕና ቀውስ ያጋጠመው፣ የሱስ ሰለባ የሆነ የለም። ህመም መሆኑን ተረድቶ ቀድሞ በመከላከል፤ ከተፈጠረም በኋላ በማሳከም በማከም እገዛ እናድርግ።
ቁማር መጫወት የዚህ ዘመን ወጣቶች ከባድና ሰፊ ችግር እየሆነ መጥቷል። <ቁማርን ነውር >ብሎ በሚያስብ ማህበረሰብ ውስጥ በሱስ ደረጃ ተስፋፍቶ ማየቱ የት ነን እንድንል ያስገድዳል።ችግር አምጪ ልማዶች ቀስ በቀስ ወደ ማህበረሰቡ ውስጥ እንዲዘልቁ የሚደረግበት አግባብ መገታት የሚሻ ጉዳይ ነው።
የቁማር ማጫዎቻዎች በስፋት መሰራጨታቸው ችግሩን እንደ ችግር ማየት ተትቷል፤መኮነን ማውገዝ ቀርቷል። በማወቅም ይሁን ባለማወቅ የሐይማኖት ሰዎችም መዝናኛ እና ግዜ ማሳለፊያ መጫዋቻ መስሏቸው ትውልዱን ማዳን ሲገባቸው ራሳቸውም ወደ መድረኩ ሲመጡ እየታዩ ነው። ከየት ወዴት?
በአለም ላይ ብዙ ጨዋታዎች ሰዎችን ወደ ሱስ መጋዘን ሲያጓጉዙ እናያለን። በተለያየ ዘመን ከዘመን ጋር አብረው የሚወለዱ የሱስ አምጪ የጨዋታ አይነቶች አሉ። ካርታ ጨዋታ ብዙዎችን ከባለሐብት ማማ ከስክሶ ፣ቤተሰብ አፈራርሶ መጨረሻ ተጨዋቾቹ በራሳቸው ላይ የማይቀለበስ ውሳኔ ሲፈፅሙ አይተናል። ዛሬ ከካርታ ዘመን ወደ ተለያዩ የቁማር ማጫወቻ ዘዴዎች ተሸጋግረናል።
ብዙ የቁማር ማጫወቻዎችን መጥቀስ ይቻላል። በተለይ ከኳስ ጋር ተያይዞ ያለው በሰደድ እሳት ፍጥነት ሀገሪቷን አዳርሷታል። ሁሉም ሐላፊነቱን ይወጣ። በሌላ የስራ ዘርፍ በመሳተፍ ገቢ ማግኘት እንደሚቻል ማሳወቅ ያሻል። ትውልድ ከገንዘብ በላይ ነው። ትውልድን አጥፍቶ የሚከማች ሐብት ተመልሶ በጠፉት ሊጠፋ እንደሚችል አውቀው ሐላፊነታቸውን ይወጡ።
ሱስ በቀልድ መልክ ይጀምራል። ቀጠል አድርጎ ጉርሻ ጀባ በማለት ወደ ራሱ የጡዘት ዛቢያ ይከታል። ሱሱ ሰዎችን ማዘዝ እስከሚጀምር እያዋዛ እያሳሳቀ ብር እየሸለመ ቀስ በቀስ የራሱ ተገዢ የሚያደርግ የአእምሮ ጤና እክል ነው። የቁማር ጨዋታዎች ስራ ተብለው መታየት መጀመራቸው ችግሩን እያቀጣጠሉት ነው።
ቁማር ፈቃድ ያለው እና ህገ ወጥ ተብሎ ይከፋፈላል። ቁማርን ጤናማና ጤናማ ያልሆነ ብለው ለመክፈል ይሞከራል። ጤናማ የተባለው በሒደት ወደ ህመም የመቀየር ቁልፍ አቀባይ ነው። ፈቃድም ኖረው አልኖረው ፤ቁማር ወደ ሱስ የሚቀየር መጥፎ ልማድ ነው እንላለን።
ቁማር የመጫወት ልምድ የአእምሮ ህመም ደረጃ ደርሷል ለማለት የሚያስፈልጉ መልክቶች የሚከተሉት ናቸው።
1) የመወራረጃ ብር መጠኑን በመጨመር ከችግሩ/ሱስ የሚገኝ ደስታን ለማግኘት የመፈለግ ልማድ፣
2) መቅበዝበዝ እና እረፍት አልባ ሙከራዎችን በማድረግ መወራረጃ መጠኑን ለመቀነስ መፍጨርጨር /ለመታቀብ መሞከር ግን አለመቻል፣
3)ተደጋጋሚ ውጤታማ ያልሆኑ ቁማር የማቆም ፣የመቀነስ አለያም የመቆጣጠር እርምጃ ማድረግ፣
4) ወደ ቁማር ለመመለስ መሞከር፣
5)የቁማር ጨዋታቸውን ለሌሎች ለመደበቅ ሲሉ መዋሸት፤
6)ቁማር በመጫወት ምክንያት ቤተሰብ መበተን፣ማህበራዊ መስተጋብሮች ማጣት፣ስራን ማጣት፤
7)የቁማር እዳን ለመክፈል የብር ማምጫ መንገዶችን ፍለጋ ፍላጎት መጨመር፣
..
..
...
እነዚህና ሌሎች ምልክቶች ለተከታታይ አንድ አመት ከታዩ ያ ግለሰብ pathological gambling disorder አእምሮ ህመም ተጠቂ መሆኑን ማረጋገጥ ይቻላል።
ልብ ይበሉ ስለ ችግሩ በጥልቅ ለማወቅ ሐኪም ማማከርዎን አይርሱ።
ዶ.ር መስፍን በኃይሉ
Via Hakim
👇
@T2T4T5
