cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

Ethiopian Architecture Construction and Urbanism

It is a platform for information on historical and contemporary architecture, urbanism, landscape, and the construction industry inside Ethiopia. It will also include similar issues from across the world.

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
13 217
مشترکین
+5824 ساعت
+2117 روز
+75230 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

Photo unavailableShow in Telegram
ታሪካዊ ኪነህንጻ። አክሱም ፂዮን ቤተ-ክርስቲያን በግንባታ ላይ። አክሱም። ቤተክርስትያኑን የነደፈው በግዜው በአለም ላይ ስሙ  የታወቀው ከተማ አቃጅ እና ህንጻ ነዳፊ የነበረው ግሪካዊው  ኮንስታንቲኖስ ዶክሲያዲስ ነበር። ዶክሲያዲስ በተጨማሪም ደብረሊባኖስን የሚገኘውን ዘመናዊ ባለጉልላት ቤተክርስትያን ነድፏል። ምስል ምንጭ። ነብዩ ምናሴ ጽሁፍ። ዳዊት በንቲ @ethiopianarchitectireandurbanism
نمایش همه...
👍 14 2
ታሪካዊ ኪነህንጻ። አክሱም ፂዮን ቤተ-ክርስቲያን በግንባታ ላይ። አክሱም። ቤተክርስትያኑን የነደፈው በግዜው በአለም ላይ ስሙ የታወቀው ከተማ አቃጅ እና ህንጻ ነዳፊ የነበረው ግሪካዊው ኮንስታንቲኖስ ዶክሲያዲስ ነበር። ዶክሲያዲስ በተጨማሪም ደብረሊባኖስን የሚገኘውን ዘመናዊ ባለጉልላት ቤተክርስትያን ነድፏል። ምስል ምንጭ። ነብዩ ምናሴ ጽሁፍ። ዳዊት በንቲ @ethiopianarchitectireandurbanism
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
አሁናዊ የከተማ የአየር ምስል። ቸርችል ጎዳና፣ አዲስአበባ ምንጭ። Isaac Abraham @ethiopianarchitectureandurbanism
نمایش همه...
👍 4 4
ሰውሰራሽ አስተውሎት (ሰአ) እና ኪነህንጻ። ሰሞኑን ከቻይና ህንጻ ነዳፊዎች ጋር ስራ እየሰራን ነው። በተቻላቸው መጠን የስራቸውን ብዙውን ክፋይ በ ሰአ መስራት ነው ምርጫቸው። ከ ወለል ቁርጥ ጀምሮ ባለ ሶስት አውታር ንድፍ ( 3D) በጥሩ እይታ ጥራት (resolution) ይሰራሉ በሚሰጠው አስተያየት መሰረት በየደቂቃው ያስተካክሉታል በቃላት ማዘዝ ለማይቻሉ ጥያቄዎች መርጃ የሚሆኑ ገበታዎች (templates) አሏቸው። በሂደት የተገነዘብኩት የእነሱ ሰአ መተግበርያ የሚሰራላቸው ንድፍ ለ ቅድመ ንድፍ አማራጮች (preliminary Design) ሃሳብ ለማቅረብ ጥሩ መሆኑንና ውጤታማ የተሳካ ተተግባሪ ንድፍ ለመስራት ግን የእኛ ነዳፊዎች የሚሰሯቸው ንድፎች የተሻሉ መሆናቸውን አብሬ አሰርቼ አይቼዋለሁ። ሁለቱን አጣምሮ በመስራት ግን የተሳካ ውጤት እያገኘንበት ነው። የእኛዎቹ የሰሩትን ወለል ቁርጥ የቻይኖቹ ሰአ መተግበርያ ላይ በማስገባት ቀሪ ሶስት አውታር ንድፎችን የተለያዩ ገጽታዎችን በማካተት ብዙ አማራጭ በማቅረብ ውጤታማ ስራ እየሰራንበት እንገኛለን ። የእኛ የሰአ አጠቃቀም በብዛት የቋንቋ አበልጻጊ የሆነውን Chat GPT እና በቃላት አዝዘን እራሱ የሚሰጠን የተለያዩ ምስል የምንፈጥርባቸውን DALLE የመሰሉት ላይ የተወሰነ ነው። እኛ የምንፈልገውን ምስል የሚፈጥርልን እና ለሙያዊ እገዛ የሚሆኑ ታዛዥ ( interactive) ሰአ መተግበርያዎች የሉንም ሌሎች የሰሩትንም እየተጠቀምን አይመስለኝም። ከቻይኖቹ እንደተረዳሁት ሰአ መተግበርያ መጪው ትውልድን ከሙዓለ ህጻናት ጀምሮ እንዲጠቀሙበት እያደረጉ ለቀጣዩ ዘመን እያዘጋጇቸው ነው። እኛስ የቱ ጋ ነን? ስንቶቹ የዘንድሮ ተመራቂዎች በሰአ ዙሪያ ሰልጥነው ተዘጋጅተው ይሆን? መጪው ትውልድንስ ለማዘጋጀት ምን ታስቧል? የክረምት ኮርሶችስ አሉን ወይ? በ ደሳለኝ ከበደ (መሀንዲስ፣ ስራተቋራጭ፣ አስተማሪ፣ ጸሀፊ እና አባመላ።) @ethiopianarchitectureandurbanism
نمایش همه...
👍 8 2👌 2
የቆዩ የከተማ ምስሎች። መቀሌ በ1960ዎቹ መጀመርያ ምንጭ። Larry Workman Photographs - Panoramio Archives: http://www.panoramio.com/user/765658?with_photo_id=47445281 በ Historic Ethiopia Through The Camera Lens: 1860s -1990s በኩል። @ethiopianarchitectureandurbanism
نمایش همه...
5
👏 7👍 2 1
የንግድ ቦታ ኪራይ ቅድሚያ ፍላጎትን ለማወቅ የወጣ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፒያሳ ከአድዋ መታሰቢያ ፊት ለፊት የሚገኘውንና የኤሌክትሪክ ህንፃ በመባል የሚታወቀውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና መ/ቤት የነበረውን ህንጻ ከዚህ በፊት ፒያሳ አካባቢ የተለያዩ የንግድ አገልግሎት ሲሰጡ ለነበሩ የወርቅ መሸጫ ሱቆች፣ ባቅላባ ቤት፣ የመዋቢያ እቃ መሸጫ ሱቆች፣ የእጅ ሰዓት መሸጫ፣ አልባሳት መሸጫ ቤቶች፣ ኬክ ቤቶች፣ የቡና ቤቶች (Coffee House) እና ሌሎች በአካባቢው የንግድ አገልግሎት ሲሰጡ ለነበሩ ድርጅቶች ቅድሚያ በመስጠት ማከራየት ይፈልጋል፡፡ በዚሁ መሰረት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉና በዚሁ አካባቢ ከላይ በተገለጹት የንግድ ዘርፍ አገልግሎት ስትሰጡ ስለመሆኑ ከሚመለከተው አካል የተረጋገጠ ማስረጃ በማቅረብ ከሐምሌ 8 እስከ 12 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ፒያሳ በሚገኘው ኤሌክትሪክ ህንጻ ምድር ወለል ቢሮ ቁጥር 001 መከራየት የምትፈልጉትን የቦታ ስፋትና ወለል በመጥቀስ በንግድ ቤቱ ባለቤት/ህጋዊ ወኪል የተፈረመ የኪራይ ፍላጎት ማሳወቂያ ደብዳቤ እንድታስገቡ እያሳወቅን፤ መሟላት የማሚገባቸው መስፈርቶችም፡- 1. ከዚህ ቀደም በአካባቢው የንግድ አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩ ስለመሆኑ ማስረጃ የሚያቀርቡ፣ 2. የታደሰ ንግድ ፍቃድና የዘመኑ ግብር መክፈላቸው ማረጋገጫ የሚያቀርቡ፣ 3. ተቋማችን በሚያስቀምጠው የህንጻ አስተዳደር ህግና አሰራር ለመተዳደር ዝግጁ የሆኑ፣ 4. ምሽትን ጨምሮ የከተማ አስተዳደሩ በሚያስቀምጠው የጊዜ ገደብ አገልግሎት የሚሰጡ፣ 5. ተቋማችን በሚያወጣው የገበያ ኪራይ ዋጋ ተመን ኪራይ የሚከፍሉ፣ ተቋማችንም የሚቀርበውን የተከራዮች ብዛትና የቦታ ኪራይ ፍላጎት መሰረት በማድረግ ከሐምሌ 12 ቀን በኋላ ቀጣይ ሂደቱን የሚያሳውቅ ይሆናል፡፡ በዚህ አጋጣሚ ክቡራን ደንበኞቻችን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋናው መ/ቤት ሜክሲኮ አካባቢ በሚገኘው ንብ ባንክ ህንጻ ላይ የተዛወረ መሆኑን በአክብሮት እናሳውቃለን። ምንጭ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት። @ethiopianarchitectureandurbanism
نمایش همه...
👍 2
የአረንጓዴ መተላለፍያዎችን በመጉዳት እና ደንብ በመተላለፍ የተጣለ ቅጣት። በከተማችን መሰረተ ልማቶች ላይ ቆሻሻ የሚጥሉ፣ ከተፈቀደላቸው መንገድ ውጪ የሚሄዱ እንዲሁም በመንገድ አካፋዮች ላይ የተተከሉ ዛፎችን  በተሽከርካሪ በመግጨት ጉዳት ያደረሱ አካላት ተቀጡ:: በዚህም 3 ተቋማት ከተፈቀደ ቦታ ውጪ ቆሻሻ በመጣል እንደየጥፋት ደረጃቸው 100 ሺሕ ፣ 50 ሺ እና 20 ሺሕ ብር የተቀጡ ሲሆን 5 አሽከርካሪዎች በመንገድ አካፋይ ላይ የተተከሉ ዘንባባ ዛፎችን ገጭተው በመጣላቸው እንደየጥፋት ደረጃቸው ከ150 እስከ 300 ሺሕ ብር እንዲሁም 11 ሰዎች ከተፈቀደው የእግረኞች መንገድ ውጪ በመሄዳቸው ከ150 እስከ 1000 ብር ተቀጥተዋል:: ምንጭ። Mayor Office of Addis Ababa @ethiopianarchitectureandurbanism
نمایش همه...
5👍 4😁 1
እየተገነባ ያለ ቤት ፈርሶ ነፍስ አጠፋ። ዛሬ ሀምሌ 3 ቀን 2016 ዓ.ም ከንጋቱ 11:45 ሰዓት ላይ በለሚ ኩራ ክፍለ-ከተማ ወረዳ 14 አርሴማ ቤተክርስቲያን አካባቢ እየተገነባ ያለ መኖሪያ ቤት ከስሩ ባለ መኖሪያ ቤት ላይ ተደርምሶ የአንድ ሰዉ ህይወት አልፏአል። ህይወታቸዉ ያለፈዉ ግለሰብ በቤት ዉስጥ ተኝተዉ የነበሩ በጾታ ወንድ የሆኑ የ50 ዓመት ዕድሜ የተገመቱ ናቸዉ። በስፍራዉ ፈጥነዉ የደረሱት የአደጋ ጊዜ ሰራተኞችና የአካባቢዉ ማህበረሰብ በአደረጉት ርብርብ ሶስት ሰዎችን ከአደጋዉ መታደግ ችለዋል። በአዲስ አበባ የግንባታ ስራ ላይ በተለይም በግለሰቦች የሚገነቡ ግንባታዎች የደህንነት መስፈርቶችን ጠብቆ ባለመስራታቸዉ በሰዉ ህይወትና ንብረት ላይ በተደጋጋሚ አደጋዎች እያጋጠሙ ይገኛል። የግንባታ ስራዎች በሚከናወኑበት ጊዜ የግንባታ ፈቃድ ሰጪዉ አካል ግንባታዎቹ የአደጋ ደህንነት መስፈርት ተጠብቀዉ ስለመሰራታቸዉ የተጠናከረ ቁጥጥር በማድረግ የማስተካከያ እርምጃዎችን መዉሰድና የህግ ተጠያቂነትን ማስፈን እንደሚያስፈልግ ኮሚሽን መ/ቤቱ ያሳስባል። ለእሳትና ለሌሎች ድንገተኛ አደጋዎች እንዲሁም ለአንቡላንስ አገልግሎቶች በ939 ፈጥነዉ ያሳዉቁ! ምንጭ። የ እሳት አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን። @ethiopianarchitectureandurbanism
نمایش همه...
👍 6 3
یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.