fa
Feedback
GLOW KG AND PRIMARY SCHOOL ADDIS ABABA ETHIOPIA.

GLOW KG AND PRIMARY SCHOOL ADDIS ABABA ETHIOPIA.

رفتن به کانال در Telegram

Always strive for Excellence❤!!

نمایش بیشتر
1 423
مشترکین
+124 ساعت
+97 روز
-730 روز
آرشیو پست ها
👫In Glow school with our student's we✨💥 Glow✨💥 together .

ግሎው ት/ቤት  ቀን፡27/09/2017ዓ.ም           ማስታወቂያ ለ8ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ: በነገው እለት ማለትም ሐሙስ ግንቦት 28/2017ዓ.ም በክፍለ ከተማ ባለሙያዎች ስለ ምንስትሪ ፈተና ገለፃ(orientation) ስለሚሰጥ ጠዋት 2:00 ሰዓት ት/ቤት ግቢ ውስጥ እንድትገኙ እናሳስባለን።                          ት/ቤቱ

የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ ለተማሪዎች ➊ የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡ ❷ በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን አራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) ብቻ ማጥቆር አለበት፡፡ ➌ ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው አራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡ ❹ ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን የአራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡ ❺ በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ መልስ (የአራት ማዕዘን ቅንፍ/Square Bracket) ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡ ❻ ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡ ❼ ለመፃፍ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ተፅፎ ወይም ትንሽ ጭረት እና ነጥብ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ  በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ ❽ መልስ በሚጠቆርበት ጊዜ እርሳሱ ከተሰጠው አራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) መውጣት የለበትም። ከወጣም በማጥፊያ ማጥፋት ይጠበቅባችኋል። ❾ መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡ ➓ ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት  እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡ ⓫ በእስክሪብቶ መፃፍ አይፈቀድም። ስለዚህ እርሳስ፣ ላጲስ እና መቅረጫ አይለያችሁ ⓬ ፈተና ጨረስኩ ብሎ አላስፈላጊ የሆነ ነገር፤ ስዕል ወይም ሌላ ከጀርባም ይሁን ከፊት አይፃፍበትም። ⓭ በጣም የተቀረፀ ሹል እርሳስ በምንጠቀም ወቅት ወረቀቱ እንዳይቀደድ መጠንቀቅ አለብን።

ግሎው ት/ቤት  ቀን፡27/09/2017ዓ.ም           ማስታወቂያ ለ8ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ: በነገው እለት ማለትም ሐሙስ ግንቦት 28/2017ዓ.ም በክፍለ ከተማ ባለሙያዎች ስለ ምንስትሪ ፈተና ገለፃ(orientation) ስለሚሰጥ ጠዋት 2:00 ሰዓት ት/ቤት ግቢ ውስጥ እንድትገኙ እናሳስባለን።                          ት/ቤቱ

Wow Nice Dear Director and all teachers. Thank you all.

👫 Story time 📚

የ6ኛና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና መስጫ ጊዜ ሰሌዳ ይፋ ሆናል፡፡ (ግንቦት 4/2017 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2017 የትምህርት ዘመን የ6ኛና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና መስጫ ጊዜ ሰሌዳን ይፋ ያደረገ ሲሆን በዚህ መሰረትም የ6ኛ ክፍል ሰኔ 10 ፣11 እና 12/2017 ዓ.ም ዓ.ም እንዲሁም የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ሰኔ 3 እና 4/2017 ዓ.ም የሚሰጥ ይሆናል፡፡   ከተማ አቀፍ ፈተናዉን ከ739 ትምህርት ቤቶች 80333 የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች በ192 የመፈተኛ ጣቢያዎች እንዲሁም ከ661 ትምህርት ቤቶች 71985 ተማሪዎች በ194 የመፈተኛ ጣቢያዎች የሚወስድ ይሆናል፡፡

ቀን ፡ 26/08/2017 ዓ.ም ውድ ወላጆች ነገ ሰኞ፣ ሚያዝያ 27 ቀን 2017 ዓ.ም የአርበኞች ቀን መታሰቢያ በዓልን በማስመልከት ትምህርት ቤቱ ለተማሪዎች ዝግ መሆኑን እንገልፃለን። ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 28 ቀን 2017 ዓ.ም መደበኛ ትምህርት የሚቀጥል ይሆናል። 🙏🙏ግሎው  ት/ቤት🙏🙏