fa
Feedback
አንድሮሜዳ ት/ቤት ከኬጂ-8ኛ

አንድሮሜዳ ት/ቤት ከኬጂ-8ኛ

رفتن به کانال در Telegram

''ኑ ትውልድ እንፍጠር''

نمایش بیشتر
1 511
مشترکین
-124 ساعت
-17 روز
-730 روز
آرشیو پست ها
👉ለአንድሮሜዳ ት/ቤት ቤተሠቦች 🏫📢 ጉዳዩ የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎችን ይመለከታል 📚 ✅ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል  ተፈታኞች መፈተኛ ጣቢያ መድረስ ያለባቸው ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት በፊት ሲሆን ✅የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ከሰኞ 8/10/2018 ዓ.ም እስከ 10/10/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 1:30 በፊት  ትምህርት ቤት መድረስ ይኖርባቸዋል:: እንዲሁም ✅የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ከቀን 11/10/2018 እስከ 12/10/2018 ዓ ም ከጠዋቱ 1:30 በፊት  ትምህርት ቤት መድረስ ይኖርባቸዋል:: ✅ተማሪዎች ትምህርት ቤት ከመጡ በሁዋላ በሠርቪስ ወደ መፈተኛ ጣቢያ የሚሔዱ ይሆናል:: ✅ወላጆች ተማሪዎቻችን በቀሩት ቀናት በቂ እረፍት እና የስነልቦና ዝግጅት አድርገው ለፈተናው በጊዜ ትምህርት ቤት እንዲገኙልን ድጋፋችሁ አይለየን:: ✅ ተፈታኝ ተማሪዎች ወደ ት/ት ቤት ሲመጡ የተሟላ የት/ት ቤት ዩኒፎርም ለብሠው እና ለፈተና አስፈላጊ ቁሳቁሶችን ማለትም 2 እስራስ: መቅረጫና ላጲስ ይዘው መገኘት ይኖርባቸዋል:: ✅ተፈታኝ ተማሪዎችን ቀደም ብሎ ትምህርት ቤት አድርሰው ወደ መፈተኛ ጣቢያ ለማድረስ እንዲችሉ ሠሪቪስ ሠጪ መኪኖቻችን ለአንድ ሳምንት ከተለመደው ሰዓት ቀድመው ስለሚመጡ 20 ደቂቃ ቀደም ብላችሁ እንድትጠብቁን በአክብሮት እንጠይቃለን:: ለልጆቻችን መልካም ውጤት እንመኛለን 🙏✨

ለአንድሮሜዳ ት/ት ቤት ቤተሰቦች ከወረዳ ትምህርት ፅ/ቤት በደረሰን መረጃ መሠረት ትምህርት ከሠኞ ግንቦት 24 እስከ ረቡዕ ግንቦት 26 የማይኖር መሆኑን እየገለፅን ከሀሙስ ግንቦት 27 ጀምሮ ግን መደበኛው የመማር ማስተማር የሚቀጥል ይሆናል:: ማስታወሻ ለ6ኛና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች የክልላዊ ፈተና  የሌሎች ክፍል ደረጃዎችም ማጠቃለያ ፈተና በመቃረቡ በዝጉ ወቅት ተማሪዎች በፕሮግራም እንዲያጠኑ ክትትል እንድታደርጉልን በአክብሮት እንጠይቃለን::                     የት/ት ቤቱ አስተዳደር

ለእስልምና እምነት ተከታይ የአንድሮሜዳ ት/ቤት ቤተሠቦች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛዉ ዓ.ሒ. የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልን በዓሉ የሰላም የደስታ እና የጤና እንዲሆንላችሁ ከልብ እንመኛለን::

ለአንድሮሜዳ ት/ት ቤት ቤተሠቦች ጉዳዩ: የሠርቪስ አገልግሎት ክፍያን ይመለከታል:: ወርሀዊ የሠርቪስ ክፍያ የመክፈያ ጊዜ ወር በገባ እስከ 05 መከፈል እንዳለበት ይታወቃል:: በወቅቱ ክፍያውን ከፍላችሁ ደረሰኙን ያወራረዳችሁ ወላጆችን እያመሠገንን ነገር ግን የግንቦት ወር ክፍያና ውስን ውዝፍ ክፍያ ያላጠናቀቃችሁ ወይም ከፍላችሁ ደረሰኝ ያላወራረዳችሁ ወላጆች ግን እስከ አርብ ግንቦት 14 ከፍላችሁ እንድታወራርዱ እናሳስባለን:: ማስታወሻ: ማንኛውም ያልተጠናቀቀ ክፍያ ያለበትን ተማሪ የሰርቪስ አገልግሎት ከሠኞ ግንቦት 17 ጀምሮ የሠርቪስ መኪኖቻችን ስለማይሰጡ ከዛ በፊት ባሉት 3 የስራ ቀናት ያለቦትን ያልተጠናቀቀ ክፍያ ከፍሎ በማጠናቀቅና በማወራረድ ልጆን ካላስፈላጊ መጉላላት እንዲጠብቁ በድጋሚ እናሳስባለን:: የት/ት ቤቱ አስተዳደር

ሚያዚያ 24,2018 ዓ.ም 06፡00 ጀምሮ ከአንድሮሜዳ ት/ቤት በመቄዶንያ ዩትዩብ ይከታተሉ። www.youtube.com/@Mekedonia 👆ይህን ቻናል አሁኑኑ Subscribe በማድረግ ሁላችሁም Like👍እያደረጋችሁ ስማችሁንና ክፍላችሁን Comment ላይ እየፃፋችሁ እንዲሁም መቄዶንያን እንደምትደግፉ እየገለፃችሁ እንድትከታተሉ ከወዲሁ እናሳውቃለን። ከአንድሮሜዳ ት/ቤት ለመቄዶንያ ድጋፍ ለማድረግ የተከፈተ የኢትዮጲያ ንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000747591068 (ከት/ቤቱ  እመቤት ረታ እና ከመቄዶንያ ያብስራ ቢሆነኝ) አዋሽ ባንክ 013470576551902 (ከት/ቤቱ ትምህርተ በሪሁን እና ከመቄዶንያ ሙሉሰዉ ሙንዬ) ፤ አሁኑኑ ይርዱ!