1 511
مشترکین
-124 ساعت
-17 روز
-730 روز
آرشیو پست ها
1 511
👉ለአንድሮሜዳ ት/ቤት ቤተሠቦች 🏫📢
ጉዳዩ የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎችን ይመለከታል 📚
✅ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተፈታኞች መፈተኛ ጣቢያ መድረስ ያለባቸው ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት በፊት ሲሆን
✅የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ከሰኞ 8/10/2018 ዓ.ም እስከ 10/10/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 1:30 በፊት ትምህርት ቤት መድረስ ይኖርባቸዋል::
እንዲሁም
✅የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ከቀን 11/10/2018 እስከ 12/10/2018 ዓ ም ከጠዋቱ 1:30 በፊት ትምህርት ቤት መድረስ ይኖርባቸዋል::
✅ተማሪዎች ትምህርት ቤት ከመጡ በሁዋላ በሠርቪስ ወደ መፈተኛ ጣቢያ የሚሔዱ ይሆናል::
✅ወላጆች ተማሪዎቻችን በቀሩት ቀናት በቂ እረፍት እና የስነልቦና ዝግጅት አድርገው ለፈተናው በጊዜ ትምህርት ቤት እንዲገኙልን ድጋፋችሁ አይለየን::
✅ ተፈታኝ ተማሪዎች ወደ ት/ት ቤት ሲመጡ የተሟላ የት/ት ቤት ዩኒፎርም ለብሠው እና ለፈተና አስፈላጊ ቁሳቁሶችን ማለትም 2 እስራስ: መቅረጫና ላጲስ ይዘው መገኘት ይኖርባቸዋል::
✅ተፈታኝ ተማሪዎችን ቀደም ብሎ ትምህርት ቤት አድርሰው ወደ መፈተኛ ጣቢያ ለማድረስ እንዲችሉ ሠሪቪስ ሠጪ መኪኖቻችን ለአንድ ሳምንት ከተለመደው ሰዓት ቀድመው ስለሚመጡ 20 ደቂቃ ቀደም ብላችሁ እንድትጠብቁን በአክብሮት እንጠይቃለን::
ለልጆቻችን መልካም ውጤት እንመኛለን 🙏✨
1 511
ለአንድሮሜዳ ት/ት ቤት ቤተሰቦች
ከወረዳ ትምህርት ፅ/ቤት በደረሰን መረጃ መሠረት ትምህርት ከሠኞ ግንቦት 24 እስከ ረቡዕ ግንቦት 26 የማይኖር መሆኑን እየገለፅን ከሀሙስ ግንቦት 27 ጀምሮ ግን መደበኛው የመማር ማስተማር የሚቀጥል ይሆናል::
ማስታወሻ ለ6ኛና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች የክልላዊ ፈተና የሌሎች ክፍል ደረጃዎችም ማጠቃለያ ፈተና በመቃረቡ በዝጉ ወቅት ተማሪዎች በፕሮግራም እንዲያጠኑ ክትትል እንድታደርጉልን በአክብሮት እንጠይቃለን::
የት/ት ቤቱ አስተዳደር
1 511
ለእስልምና እምነት ተከታይ የአንድሮሜዳ ት/ቤት ቤተሠቦች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛዉ ዓ.ሒ. የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልን በዓሉ የሰላም የደስታ እና የጤና እንዲሆንላችሁ ከልብ እንመኛለን::
1 511
ለአንድሮሜዳ ት/ት ቤት ቤተሠቦች
ጉዳዩ: የሠርቪስ አገልግሎት ክፍያን ይመለከታል::
ወርሀዊ የሠርቪስ ክፍያ የመክፈያ ጊዜ ወር በገባ እስከ 05 መከፈል እንዳለበት ይታወቃል::
በወቅቱ ክፍያውን ከፍላችሁ ደረሰኙን ያወራረዳችሁ ወላጆችን እያመሠገንን ነገር ግን የግንቦት ወር ክፍያና ውስን ውዝፍ ክፍያ ያላጠናቀቃችሁ ወይም ከፍላችሁ ደረሰኝ ያላወራረዳችሁ ወላጆች ግን እስከ አርብ ግንቦት 14 ከፍላችሁ እንድታወራርዱ እናሳስባለን::
ማስታወሻ: ማንኛውም ያልተጠናቀቀ ክፍያ ያለበትን ተማሪ የሰርቪስ አገልግሎት ከሠኞ ግንቦት 17 ጀምሮ የሠርቪስ መኪኖቻችን ስለማይሰጡ ከዛ በፊት ባሉት 3 የስራ ቀናት ያለቦትን ያልተጠናቀቀ ክፍያ ከፍሎ በማጠናቀቅና በማወራረድ ልጆን ካላስፈላጊ መጉላላት እንዲጠብቁ በድጋሚ እናሳስባለን::
የት/ት ቤቱ አስተዳደር
1 511
ሚያዚያ 24,2018 ዓ.ም 06፡00 ጀምሮ ከአንድሮሜዳ ት/ቤት በመቄዶንያ ዩትዩብ ይከታተሉ።
www.youtube.com/@Mekedonia
👆ይህን ቻናል አሁኑኑ Subscribe በማድረግ ሁላችሁም Like👍እያደረጋችሁ ስማችሁንና ክፍላችሁን Comment ላይ እየፃፋችሁ እንዲሁም መቄዶንያን እንደምትደግፉ እየገለፃችሁ እንድትከታተሉ ከወዲሁ እናሳውቃለን።
ከአንድሮሜዳ ት/ቤት ለመቄዶንያ ድጋፍ ለማድረግ የተከፈተ የኢትዮጲያ ንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000747591068
(ከት/ቤቱ እመቤት ረታ እና ከመቄዶንያ ያብስራ ቢሆነኝ)
አዋሽ ባንክ 013470576551902
(ከት/ቤቱ ትምህርተ በሪሁን እና ከመቄዶንያ ሙሉሰዉ ሙንዬ)
፤ አሁኑኑ ይርዱ!
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
