✍️ጥበብ በእኛ ሰፈር📝🖌
Sil_gitmoch ግጥሞችን፣ ስዕሎችን፣ እና የተለያዩ መሳጭ ታርኮችን የሚታገኙበት channel🙄 👇👇👇👇 🤩🤩 @tibeb_begna_sefer
نمایش بیشترکشور مشخص نشده استزبان مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
190
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
- مشترکین
- پوشش پست
- ER - نسبت تعامل
در حال بارگیری داده...
معدل نمو المشتركين
در حال بارگیری داده...
🍕 በየሆቴሉ አማርጦ እየበላ
tipochin ይሰጣል ይዞ ብዙ መላ
አንድ ዳቦ አቶ ህፃን እየሞተ
ለፋሽን ያስባል ምን ወጣ ወዘተ..
ተዝናንተው መልበሱ ከመርዳት አይቀድምም
እናት ለአንድ ዳቦ መንከራተት ታቁም
የሰጠ ይሰጠዋል እንደሚል መፅሃፉ
ላጣ ሰው አለሁ በል ግባ በበራፉ
✍kina
ከወደዱት share ያድርጉልን😊🙏🙏
@tibeb_begna_sefer
እርሳስ
አንድ ትንሽ ልጅ የሴት አያቱ ሲፅፉ እየተመለከተ ነበር። በመሀሉ አቋርጧቸው ጥያቄ ያቀርብላቸዋል። ‘አያቴ ስለምንድን ነው ፣ የምትጽፊው? ... ስለ ሠራናቸው ነገሮች ነውን? ወይስ የምትጽፊው ሌላ ነገር ነው? ... ፅሁፉ ስለ እኔ ነው የሚያወራው ? '
በማለት ደጋግሞ ይጠይቃቸዋል።
አያቱም መጻፋቸውን ገታ አደረጉና ለልጅ ልጃቸው “ሰማህ” አሉት። ቀጠሉ እና “የምጽፈው በእርግጥም ስለ አንተ ነው። ከቃላቱ በበለጠ ግን ጠቃሚ የሆነው ነገር የምጽፍበት ‘እርሳስ’ ነው። ተስፋ የማደርገውም አንተ ስታድግ እንደዚህ እርሳስ ትሆናለህ ብዬ ነው።” በማለት መለሱለት።
ግራ የተጋባው ልጅም እርሳሱን አተኩሮ ተመለከተው። ምንም የተለየ ገጽታ አላስተዋለበትም ። ሲያድግም እንዴት እንደ እርሳሱ ሊሆን እንደሚችል ለማወቅ እየጓጓ “አያቴ ግን እኮ... ይሄ እርሳስ ልክ እንደማንኛውም ዓይነት እርሳስ ነው።” አለ።
“እርሱ የሚወሰነው አንተ ነገሮችን ለማየት በምትመርጥበት መንገድ ነው። ማንንም ሠው ከዓለሙ ጋር የተስማሙ ሊያደርጉት የሚችሉ አምስት ድንቅ ባህሪያትን ይዟል።” እያሉ አያቱ ያስረዱት ገቡ።
#የመጀመሪያው ባህርይ... በራስህ ብዙ ትልልቅ ነገሮችን የመፈፀም ብቃት አለህ።ቢሆንም ግን ሁል ጊዜ የሚመራህ እጅ እንዳለ አትዘንጋ። ያንን እጅም አምላክ እንለዋለን። ሁል ጊዜም እርሱ በሚመርጥልን መንገድ ይመራናል።
#ሁለተኛው ባህርይ... በምጽፍበት ወቅት አስተውለኸኝ ከሆነ አረፍ አረፍ እያልኩ መቅረጫ እጠቀማለሁ። ያንን ሳደርግ እርሳሱ በመጠኑ መጎዳቱ መሰቃየቱ ባይቀርም ስጨርስ የበለጠ የተሳለ እና ለሥራ ምቹ ይሆናል። አንተም ጥቂት እንግልቶችን እና ሀዘኖችን ማሳለፍ ይኖርብሃል። ያ ግን የተሻልክ ሰው እንድትሆን ያግዝሃል።
#ሦስተኛው ባህርይ... እርሳስ ሁልጊዜም የሰራውን ስህተት በላጲስ ለማጥፋት ዝግጁ ነው። ይህም መልሶ ለማስተካከልም መድፈር መጥፎ ነገር እንዳልሆነ ያሳይሃል።
#አራተኛው ባህርይ...የእርሳስ በጣም ተፈላጊው ክፍል ከውጭ የሚታየው እንጨት አይደለም ፤ ከውስጥ ያለው እንጂ። አንተም ትኩረትህን ማሳረፍ ያለብህ የውስጥህ እውነታ ላይ እንጂ የውጭህ ገፅታ ላይ አይደለም።
#አምስተኛው ባህርይ... እርሳስ ሁልጊዜም ምልክት ይተዋል። አሻራውን አኑሮ ያልፋል። በተመሳሳይ መልኩ አንተም የምትሰራው ምንም ነገር ምልክቱን እንደሚተው ልብ በል ! ስለዚህም ድርጊትህን ሁሉ በአስተውሎት ለመከወን ሞክር።” በማለት አያት ምክራቸውን ለልጃቸው ሰጥተው አለፉ።
#እርካብ_እና_መንበር /ገፅ 86-87/
https://t.me/ynshawrat
ማዕተቤን አልበጥስም
አስተያየት ለመስጠት
https://t.me/anduamlak24አዘጋጅ ገብረ ፃዲቅ ድምፀ ተዋህዶ የበጎ አድራጎት ማህበር ቻናላችንን ለመቀላቀል
https://t.me/ynshawratየዚ ዘመን ሰዉ ነኝ የሳያት ዘመን ልጅ
እዉነትን ያገኘዉ በዉሸቶቼ ደጅ🤨
.
የዚ ዘመን ልጅ ነኝ ሊያዩም የአስቱ ትውልድ
አኗኗርን ያየዉ ከሰዎች ስዋደድ በሰዎች ስወደድ☺️
የዚ ዘመን ልጅ ነኝ ያገር ተረካቢ
የዛሬ ገጣሚ የነጌ አንባቢ😌
.
የዚ ዘመን ልጅ ነኝ በራሴ ምኮራ
ስለዉድቀቶቼ ሳላፊር ማወራ😇
.
የዚ ዘመን ልጅ ነኝ ያዉም እትዮጵያዊ
የፈጠረኝ አምላክ አርጎኝ ጥበባዊ🥰
.
ዘመኔን ሰቶኛል አርጎኝ እድለኛ
እንድኖርም ረዳኝ ልክእንደ አርበኛ🤓
.
የዚ ዘመን ልጅ ነኝ
መኖሬን የሚመኝ....!!!🤔
✍kina
ያንቺ ምርቃት ነዉ
ስቴቴን ታግሰሽ ገመናዬን አዝለሽ
ስለኔ እንጨትን ከ ጫካ ቃቅመሸሽ
እኔን ፊት አርገሽኝ ኋላዬ ብትሆኝም
ለ ቀንሽ ደርሰሻል ደክመሽ አልከሰርንም
ለእኔ ኢዚ መቆም ለመንፈሴ ብርታት
እሷ ነች በኔ ዉስጥ የኖረች በብቃት
ለእኔ አይገባኝም ይህ ጋዎን ላንቺ ነዉ
እኔ ብመረቅም ያንቺ ምርቃት ነው!
✍️kina
Photo unavailableShow in Telegram
"ጠልቶኝ ሄደ አትበይ"
ቁንጅናዬን ይንሳኝ ልማልልሽ ውዴ
ይህንን እውነታ ተቀበይ አንዳንዴ
ወዳጄ ያልሺው ሰው ድንገት ካንቺ ሲርቅ
ጠልቶኝ ነው የሄደው ሴትነቴን ቢንቅ
ብለሽ እራስሺን ፈፅሞ አንዳትወቅሺ
ካብሮነት ከፍቅርም ከቶ እንዳትሸሺ
ጠልቶሽ ብቻ አይደለም ሁሉም የሚርቀው
አንዳንድ ሰው እኮ ሲፈጠር ሲኸልቀው
መወደድ መከበር አላርጂክ ሁኖበት
ሲያፈቅሩት ይሸሻል እንዲሁ ጥሎበት 🤷♂
እንደውም
እንደውም
እሰየው ተለየሽ እንኳንም ሄደልሽ
ቁንጅናዬን ይንሳኝ ይሄው ልማልልሽ
ይህ አመል ያለበት ቢኖርም አይበጂሽ 😜
@tibeb_begna_sefer✓
Photo unavailableShow in Telegram
"ከወደድካት ከልብ"
አብራህ ያለችን ሴት ከወደድካት ከልብ
እሷን ለማስደሰት ብዙ ጭንቅ አሰብስብ
እሷኮ ለመሳቅ አትፈጂም ማገዶ
ስለዚህ ወንድሜ
ሞትኩልሽ ማለቱን ተውና በባዶ
ለህትህ ቢገጥማት የምትለው አይነት
የዛ አይነት ወንድ ሁነህ ኑርላት የእውነት
ያ ብቻ በቂ ነው ሙሉ ያደርጋታል
ባንተም የፀና እምነት ሁሌ ይኖራታል
#ሴቶችዬ_እናንተም_ነፍስ_ግዙ 😉
@tibeb_begna_sefer
ተ
ጣ
ል
ተ
ና
ል
/// እ
ን
ዴ 🤔
እንደድሮው ሁኖ አይስቅም ይህ ጥርሴ፣
ቆየሁ ከተጫዎትኩ ሀሴት ሞልታ ነፍሴ
ውሎዬም ጭንቅ ነው ትካዜና ህመም፣
ከቶም ፀድቶ አያቅም ውስጤ ከመቆዘም፣
አይኖቼም እንዲሁ ደርሰው ያነባሉ፣
ሰንብቷል ካስጠላኝ ከሰው ዘንድ መዋሉ፣
ተ
ጣ
ል
ተ
ና
ል
/// እ
ን
ዴ 🤔
በቅጡ አይገባኝም ትርጉም የመኖሬ ፣
ጓጉቼም አልጓዝ ስለ ነገ አስምሬ ፣
ህልምና ምኞቴም ሁነው ወና ባዶ ፣
ከተስፋ መቁረጥ ጫፍ ቁሟል እግሬ ሄዶ ፣
ከሳቅ ተኳርፌ አንገት አቀርቅሬ ፣
ብቼኝነት ሁኗል ውሎዬና አዳሬ ፣
ተ
ጣ
ል
ተ
ና
ል
/// እ
ን
ዴ 🤔
ጎኔም ተደላድሎ እንቅልፍ ለተኛሁ፣
ካሳብ ነፃ ለሊት እንደ ሰው ካነጋሁ ፣
ብዙ ጊዜ ሆነኝ ሳሳዝን ባየኸኝ ፣
አያቅምኮ አኔን እንደዚህ አድርጎኝ ፣
ተ
ጣ
ል
ተ
ና
ል
/// እ
ን
ዴ 🤔
ደህና ነሽ ወይ ሲሉኝ ሰዎች ሲጠይቁኝ
ናፍቆት እንዳዘልኩኝ ትዝታ እንዳቆርኩኝ፣
ዋሽቼ አስመስዬ ደህና ነኝ እያልኩኝ ፣
ብኖርም እንዲሁ ቀን እያሰላሁኝ ፣
ቆየሁ ታምሚያለሁ እርቆኛል ጤና ፣
ተጣልተናል ነው እንዴ ንገረኝ እስኪ "ና"
@tibeb_begna_sefer
ለፍቅሩ ስል ላልቅስ
እኔ እንባዬን ላፍስስ
ላብሮነት ስል ልሞኝ
እኔዋ ልባል ሞኝ
ለመውደዱም ልክሳ
እኔው ልይ አበሳ
.... አንተ ዝም ብለህ ሳቅ ....
መቻሌ ተሟጦ ልቤ ትግስቱ እስኪያልቅ
በል ሲልህ ናቶሎ ሲሻህ ደግሞም እራቅ
@tibeb_begna_sefer
"የኔ ነገር"
የሆነ አንዳንድ ቀን
ሲከበኝ ሰቀቀን
የታከተኝ ጊዜ ሂዎት ሳቅ ተርቦ
እድሜዬ መኖሬ የዃሊት ተስቦ
ወደ ድሮዋ እኔ ተመልሼ ዳግም
እዛውጋ በቆምኩኝ እላለሁኝ ሳልም
በቃ ሁሉም ቀርቶ
በንፁህ ህሊና _ ያላሳብ ተኝቶ
ከልብ እየሳቁ _ ፍንድቅድቅ እያሉ
ብሶት አልባ ቀናት_ በደስታ መዋሉ
....... አብዝቶ ያምረኛል .....
ም ነ ው
ያሁኑ መኖሬ _ ቀርቶብኝ ጨርሶ
የድሮዋን እኔን _ በሆንኩኝ መልሶ
@tibeb_begna_sefer