የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
رفتن به کانال در Telegram
2 639
مشترکین
-224 ساعت
+87 روز
+5630 روز
آرشیو پست ها
🔴#ስንክሳር የካቲት_14
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
የካቲት ዐሥራ አራት በዚህች ቀን የአንጾኪያ ሀገር ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት #አባ_ሳዊሮስ አረፈ፣ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት #አባ_ቄርሎስ አረፈ፣ የእስክንድርያ አገር ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት #አባ_ያዕቆብ አረፈ፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ሳዊሮስ_ዘአንጾኪያ
በዚህችም ቀን ሃይማኖታቸው ለቀና ምእመናን መምህራቸው የሆነ የአንጾኪያ ሀገር ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት ሳዊሮስ አረፈ። የዚህም ቅዱስ ዘመዶቹ ከሮሜ ሀገር ናቸው አባቱም ስሙ ሳዊሮስ የሚባል ኤጲስቆጶስ ነው እርሱም ስለ ንስጥሮስ በኤፌሶን ከተማ ጉባኤ በሆነ ጊዜ ከሁለት መቶ አባቶች ኤጲስቆጶሳት ጋር መጣ በዚያም እንዲህ የሚለውን ራእይ አየ ከአንተ የሚወለድ ልጅህ ስሙም እንደ ስምህ ሳዊሮስ ተብሎ የሚጠራ እርሱ የቀናች ሃይማኖትን ያጸናታል።
ይህም ኤጲስቆጶስ በአረፈ ጊዜ ልጁን ሳዊሮስ ብለው ጠሩት ከቤተ ክርስቲያን ውጭ የሆነውን ጥበብን ሁሉ ተማረ። ከመምህሩም ወጥቶ ወደ አንድ ቦታ ሲጓዝ በዋሻ ራሱን እሥረኛ አድርጎ የሚኖር ጻድቅ ሰው ተገናኘው በእርሱም ደስ ብሎት የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት ሃይማኖታቸው ለቀና ምእመናን መምህራቸው የሆንክ ሳዊሮስ ሆይ መምጣትህ መልካም ነው አለው ሳዊሮስም ከቶ ሳያውቀው በስሙ በጠራው ጊዜ የሚደረግለትንም ከመሆኑ አስቀድሞ በመናገሩ አደነቀ።
ከዚህም በኋላ ሳዊሮስ ትሩፋት በመሥራት አደገ መልካም ስም አጠራሩና ዜናው ተሰማ በአባ ሮማኖስም ገዳም መንኵሶ ታላቅ ተጋድሎን ተጋደለ ለትሩፋትም ሥራ እጅግ የተጠመደ ሆነ የከበረ ወንጌል በተራራ ላይ የተሠራች መንደር መሠወር አትችልም እንዳለ ዜናው በሁሉ ዘንድ ተሰማ።
የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳትም በአረፈ ጊዜ አዋቂዎች ኤጲስቆጶሳት ይህን የከበረ ሳዊሮስን ይሾሙት ዘንድ ተስማምተው ያለ ውዴታው ወስደው በአንጾኪያ ሀገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት በሹመቱም እስከ ዓለም ዳርቻ ያለች ቤተ ክርስቲያን ብርሃን ሆነላት በሀገሮች ሁሉ ወዳሉ መናፍቃን ከሀድያን ትምህርቱ በሚደርስ ጊዜ ሁለት አፍ እንዳለው ስለታም ሰይፍ ሥራቸውን ይበጥሳልና።
ከጥቂት ቀኖችም በኋላ አማኒው ንጉሥ ሙቶ በርሱ ፈንታ ስሙ ዮስጥያኖስ የሚባል መናፍቅ ነገሠ ንግሥቲቱ ሚስቱ ግን ሃይማኖቷ የቀና ነው ስሟም ቴዎድራ ይባላል። ንጉሡም የኬልቄዶን ወደሆነች ወደረከሰች ሃይማኖቱ ይህን የከበረ አባት ያስገባው ዘንድ ያስፈራራው ነበር እርሱ ግን ፈርቶ አይታዘዝለትም ቁጣውንም የሚፈራ መስሎት በእርሱ ላይ አብዝቶ ተቆጣ ቍጣውንም ባልፈራ ጊዜ በሥውር ሊያስገድለው መከረ ንግሥቲቱም አውቃ ከንጉሡ ፊት ይሸሽ ዘንድ ሊቀ ጳጳሳቱን መከረችው እርሱም በሥውር ወጥቶ ገለል አለ እግዚአብሔር የዚህን አባት ሞት አልፈቀደምና ስለ ምእመናንም ጥቅም ጠበቀው ።
በአንድ ተራ መነኵሴ አምሳል ሁኖ በቦታዎችና በገዳማት የሚዘዋወርና ምእመናንን የሚያጠናክራቸው ሆነ ስካ በሚባል አገርም ስሙ ዶርታኦስ ከሚባል ደግ ምእመን ባለ ጸጋ ሰው ዘንድ ተቀምጦ ሳለ ጌታችን በእጆቹ ብዙ ድንቆች ተአምራቶችን አደረገ ስካ በተባለ ሀገርም እስከ አረፈ ድረስ በቀናች ሃይማኖት ይጸኑ ዘንድ ሁሉንም ያስተምራቸው ነበር ከዚህም በኋላ ወደ ዝጋግ ገዳም አፈለሱት።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አባ_ቄርሎስ
የካቲት ዐሥራ አራት በዚህች ቀን የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት ቄርሎስ አረፈ፡፡ እርሱም ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሰባ አምስተኛ ነው። ይህም አባት ፍዩም ከምትባል ሀገር ነው በእርሷም ቅስና ተሹሞ ኖረ ከዚህም በኋላ ከዚያ ለቆ ከምስር ከተማ ውጭ ወደ ሆነች የኢትዮጵያውያን የጕድጓድ ውኃ ወዳለበት ወደ ቅዱስ ፊቅጦር ገዳም ደረሰ በውስጡም ታላቅ ተጋድሎን እየተጋደለ ብዙ ዘመናት ኖረ።
የዕውቀቱና የቅድስናው ዜና በተሰማ ጊዜ ያለ ውዴታው ይዘው በእስክንድርያ ሀገር ሊቀ ጵጵስና ሾሙት መንጋውንም በበጎ አጠባበቅ ጠበቀ በቊርባንና በጸሎት ጊዜ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሊሠሩት የሚገባቸውን ለካህናት ሥርዓትን ሠራ። በሹመቱም ሰባት ዓመት ከዘጠኝ ወር ከሃያ ሰባት ቀን ኑሮ በሰላም አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አባ_ያዕቆብ
በዚህችም ዕለት የእስክንድርያ አገር ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት አባ ያዕቆብ አረፈ። እርሱም ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ኃምሳኛ ነው።
ይህም አባት እልመቱዝ የተባለ የግብጽ ንጉሥ በነገሠ በዐሥራ ሰባት ዓመት ተሾመ እርሱም ለመኰንኑ ለወልደ ኀሮን ረሽድ ወንድም የሆነ ነው በዚህም አባት ዘመን የአስቄጥስ ገዳማት ታድሰው መነኵሳቱ ወደሳቸው ተመለሱ።
አፎን በሚባል አገር ስሙ መቃርስ የሚባል ሰው ነበረ ወደዚህ አባት ወደ ያዕቆብ መጥቶ ወደቤቱ በመሔድ ቤቱን ይባርክለት ዘንድ ለመነው እርሱም አብሮት ሔደ።
ታሞ የነበረ ልጁም ሞተ ወደ አባ ያዕቆብም አቅርቦ እንዲህ ብሎ ለመነው ከርሱ በቀር ልጅ የለኝምና አባቴ ሆይ ራራልኝ እርሱም እነሆ ሞተ ስለርሱ ወደ እግዚአብሔር ትማልድ ዘንደ እለምንሃለሁ አለው።
አባ ያዕቆብም እንደ እምነትህ ይሁንልህ አትፍራ አለው ሕፃኑንም ከአባቱ ተቀበሎ ታቀፈውና በላዩ ጸለየ በመስቀል ምልክትም አማተበበት ስለርሱም ወደ እግዚአብሔር ለመነ ጌታችንም ልመናውን ተቀበለው የሕፃኑ ነፍስ ተመልሳ ዐይኖቹን ገለጠ ከሞትም ድኖ ተነሣ አባቱንም ልጅህን ውሰድ የሞተ አይደለም ያንቀላፋ ሁኖ ነው እንጂ አለው።
የሕፃኑም አባት ይህን ድንቅ ሥራ በአየ ጊዜ እጅግ ፈራ የገንዘቡንም እኩሌታ ለምጽዋት ብሎ ሰጠው እርሱም ወደ ኢየሩሳሌም ልኮ ሃይማኖታቸው ለቀና ምእመናን ሁሉ ወደርሷ በመጡ ጊዜ መጠጊያ ትሆን ዘንድ ቤተ ክርስቲያንን ሠራበት።
የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት ዲዮናስዮስም ወደ ምስር በመጣ ጊዜ ከአባ ያዕቆብ ጋር ተገናኝቶ ከእርሱ ዘንድ ጥቂት ቀኖች ተቀምጦ ወደ ሀገሩ ተመለሰ። ይህም አባት ያዕቆብ በሹመቱ ዐሥር ዓመት ከስምንት ወር ከሦስት ቀን ኑሮ በሰላም አረፈ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12
ሹመትና ልመና እንዲቀበል ብዙ ሲያግባባው ነበር፤ አባቱም ልጁ በሀሳቡ እንዳልተስማማለት ሲያውቅ ከዲዮቅልጥያኖስ ጋር ተማክሮ ልጁን ቅዱስ ፊቅጦርን ወደ እስክንድርያና ወደ ተለያዩ ሀገሮች በግዞት ተልኮ በዚያም ተሠቃይቶ እንዲሞት ፈደበት፡፡
ወደ ግብፅም ልከው በዚያ እጅግ አሠቃዩት፡፡ መልአክም ነጥቆ ወስዶ በሰማያት የሰማዕታትን ክብር አሳይቶት ወደ ምድር መለሰው፡፡ ክፉዎቹም በብረት አልጋ አስተኝተው ከሥሩ እሳት አነደደዱበት፡፡ በሌላም ልዩ ልዩ በሆኑ ማሠቃያዎች እጅግ አሠቃዩት፡፡ መልአክም ተገልጦ ፈወሰው፡፡ ወደ እንዴናም አጋዙትና በዚያም ብዙ አሠቃዩት፡፡ ምላሱን ቆረጡት፤ በችንካርም ጎኖቹን በሱት፤ ቁልቁል ሰቅለውም ቸነከሩት፤ በእሳትም ውስጥም ጨመሩት፤ ዐይኖቹን አወጡት፤ እሬትና መራራ ሐሞትንም አጠጡት፡፡ ደግመውም ዘቅዝቀው ሰቀሉት፡፡ ጌታችንም ተገልጦ ካጽናናው በኋላ ፈወሰውና ፍጹም ጤነኛ አደረገው፡፡ ፊቅጦር፣ ፋሲለደስ፣ ቴዎድሮስ በናድልዮስ፣ አውሳብዮስና መቃርዮስ እነዚህ ሰማዕታት በአንድነት በአንድ ዘመን አብረው ኖረው ተሰውተው ሰማዕት የሆኑ የሥጋም ዝምድና ያላቸው የነገሥታት ልጆች ናቸው።
ዲዮቅልጥያኖስም የቅዱስ ፊቅጦርን ዐይኑን አስወለቀው፣ ነገር ግን የታዘዘ መልአክ መጥቶ የዓይኑን ብርሃን መልሶለታል፡፡ ሰማዕቱ በመዝለል ባሕር የሚሻገር እንደ አሞራ የሚመስል ፈረስ ነበረው፡፡ ከዚህም በኋላ ማሠቃየቱ ቢሰለቻቸው ሚያዝያ 27 ቀን አንገቱን ሰይፈው በሰማዕትነት እንዲያርፍ አድርገውታል፡፡
ሰማዕቱ ቅዱስ ፊቅጦር አንድ የሚነገር ትልቅ ታሪክ አለው፡፡ እርሱም በሰማዕትነት ካረፈ ከብዙ ዘመን በኋላ በራእይ ተገልጦ በ8ኛው ሺህ ዘመን በሀገራችን በኢትዮጵያና በግብፅ እንዲሁም በቁስጥንጥንያና በሮም ወደፊት የሚሆነውን ነገር ሁሉ በግልጽ የተናገረ መሆኑ ነው፡፡ ‹‹ስለ ሃይማኖት ቅዱስ ፊቅጦር ያየው ራእይ›› የሚል መጠሪያ ያለው ይህ ራእይ በሀገራችን ጎጃም ደብረ ጽሞና ገዳም ውስጥ ይገኛል፡፡
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12
ምሽትም በሆነ ጊዜ ሙሽሪት ወዳለችበት ገብቶ አንገቷን ያዝ አድርጎ ሳማት እኅቴ መልካም ነገርን እነግርሽ ዘንድ እሺ በይኝ አላት በል ተናገር አለችው እርሱም ዕወቂ ይህ ዓለም ፍላጎቱም ሁሉ ኃላፊ እንደሆነ ያንቺም ደም ግባትሽና ላሕይሽ እንደሚጠፋ ከጽድቅ ሥራ ብቻ በቀር የሚጠቅመን የለም አሁንም ሥጋችንን ከምናሳድፍ ድንግልናችንን ጠብቀን መኖር ይሻለናል አላት።
እርሷም ወንድሜ ሆይ እኔም ጋብቻን አልሻም እንዳልክ ይሁን አለችው። በዚህም ምክር ተስማምተው ሁለቱም በአንድነት የጽድቅን ሥራ በመጀመር እየጸለዩ እየጾሙ በየሌሊቱ ከባሕር ውስጥ ቁመው ያድራሉ አትራ ወደምትባልም ቤተ ክርስቲያን እየሔዱ አራት ሺህ ጊዜ ይሰግዳሉ የዳዊትን መዝሙርና የዮሐንስን ወንጌል ያነባሉ ሥጋውንና ደሙን ሳይቀበሉ ሁል ጊዜ እህልን አይቀምሱም።
በአንዲትም ዕለት የሶርያ ንጉሥ ሚስት አውሳብዮስን አይታው እጅግ ወደደችው ከባሮቿም ሁለቱን ልካ ወደርሷ አስወጣችው በዐልጋዋም ላይ ምንጣፎችን አንጥፋ ብጫ ሐር ልብስ አለበሰች በአንገቷም የወርቅ ማርዳ በማድረግ አጌጠች አውሳብዮስንም በልቤ ያለውን እነግርህ ዘንድ ና ከዚህ ተቀመጥ አለችው።
እርሱም ከንጉሥ ሚስት ጋር አልቀመጥም እንደቆምኩ ንገሪኝ አላት እርሷም አንተን ከመውደዴ ብዛት የተነሣ ሰውነቴ ይናወጣል ሁለመናዬም ይቀልጣልና ና ከእኔ ጋር ተኛ አለችው እርሱም አንተን ከመውደዴ ብዛት የተነሳ ሰውነቴ ይናወጣል ሁለመናዬም ይቀልጣልና ና ከእኔ ጋር ተኛ አለችው እርሱም ከንጉሥ ሚስት ጋር መተኛት የሚገባኝ ሳይሆን የእግዚአብሔርም ትእዛዝ እንዲህ አልሆነምና ለአንቺ ጋር አልተኛም አላት ።
ልትይዘውም በወደደች ጊዜ አመለጣትና ሩጦ ሒዶ ወደ ቤተ ክርስቲያን ገባ እርሷም በታላቅ ድምፅ ጮኸች ባሮቿም ደረሰው እመቤታችን ሆይ ምን ሆንሽ አሏት። እርሷም ይህ ሥራየኛ አውሳብዮስ ወደኔ ገብቶ የማይገባ ነገርን ተናገረኝ አይሆንም ባልሁትም ጊዜ ሥራይን ስላደረገብኝ መንቀጥቀጥና ጻዕር ያዘኝ አለቻቸው።
ከዚህም በኋላ ከቤተ ክርስቲያን አውጥተው ያመጡት ዘንድ ዐሥራ አራት መምህራንን አዘዘች ወደርሷም ባደረሱት ጊዜ በብረት ዘንጎች ይደበድቡት ዘንድ እጆቹንና እግሮቹንም አሥረው ከከተማ ውጭ በአራት ዕንጨቶች ላይ ይሰቅሉት ዘንድ አዘዘች ከባሮቿም አንዲቷን ልካ እርሷም ከተሰቀልክበት እንድታወርድህ ለእመቤቴ ያለችህን እሺ በላት አለችው እርሱም የአመንዝራን ቃል አልሰማም አላት።
በዚያንም ጊዜ መጸለይ ጀመረና እንዲህ አለ አቤቱ የአብርሃም የይስሐቅና የያዕቆብ ፈጣሪ እግዚአብሔር ሆይ አባቶቻችንን ከመከራቸው ሁሉ ያዳንካቸው አንተ ነህና እኔን ባርያህን አውሳብዮስን አድነኝ ዳንኤልንም ከአንበሶች አፍ ሶስናን ከረበናት እጅ ያዳነህ አንተ ነህና ያላንተ ረዳት የለኝምና ከዐመፀኛዪቱና ከግፈኛዪቱ ሴት እጅ አድነኝ።
ከዚህም በኋላ ዳግመኛ አንገቱን በገመድ አንቀው በመቶ ስሳ ፍላፃዎች ይነድፉት ዘንድ አዘዘች ይህንንም በአደረጉበት ጊዜ የመላእክት አለቆች ሚካኤልንና ገብርኤልን ጌታችን አዘዛቸው እነርሱም ከሰውነቱ ውስጥ ፍላፃዎችን አወጡ ያለ ጉዳትም ጤነኛ ሆነ።
ንጉሥም ከሔደበት በገባ ጊዜ ለስቅላትና ለሞት አሳልፈሽ የሰጠሽው የአውስብዮስ በደሉ ምንድን ነው ብሎ ጠየቃት የንጉሡም ሚስት ላንተ መናገርን አፍራለሁ አንተንም እፈራለሁ አለችው አትፍሪኝ በዪ ንገሪኝ አላት እርሷም ብቻዬን ተቀምጬ ሳለሁ ይህ ሥራየኛ ሰው ወደ እኔ ገብቶ ሊናገሩት የማይገባ ሥራ ለመነኝ በከለከልኩትም ጊዜ በሥራዩ አሳመመኝ አለችው።
ንጉሡም አውሳብዮስን ከተሰቀለበት አውርደው ወደርሱ ያቀርቡት ዘንድ አዘዘ ሲቀርብም ንጉሡ አውሳብዮስን በሚስቴ ላይ ክፉ መሥራትን ለምን አሰብክ አለው አውሳብዮስም ይህ ነገር እውነት ይመስልሃልን ብሎ መለሰለት ንጉሥም ይህ የምሰማው ነገር እውነት ነውን በማለት ባሮቹን መረመራቸው ።
እነርሱም ጌታችን ንጉሥ ሆይ እኛ ግን ጩኸት ሰምተን ወደ አደራሹ በደረስን ጊዜ ንግሥት እመቤታችንን እየጮኸች አገኘናት ምን ሆንሽ በአልናትም ጊዜ ይህንኑ ነገረችን አሉት።
ይህንንም በሰማ ጊዜ እንደ አንበሳ ጮኸ ቸብቸቦውንም በሰይፍ እንዲቁርጡ ሥጋውንም እንደ ላም ሥጋ ቁራርጠው ከአደሮ ማር ጋር ከምንቸት ውስጥ ጨምረው አፉን ዘግተው በእሳት ያበስሉት ዘንድ አዘዘ በዚያንም ጊዜ የመላእክት አለቆች ሚካኤልና ገብርኤል መጡ ከምንቸትም ውስጥ አውጥተው ከሞት አድነው አስነሡት።
ከተነሣም በኋላ በሀገር ውስጥ ሲጓዝ ሰዎች አገኙት ሕያው እንደሆነም ለንጉሥ ነገሩት ንጉሥም እንዲአመጡትና አራት ዛንጅሮችን በአካላቶቹ ውስጥ እንዲአስገቡ አንዱን በአንገቱ ውስጥ አንዱን በወገብ አንዱን በጐኑ አንዱን በጉልበቱ ውስጥ አስገብተው እጅና እግሩንም አሥረው ከእሳት ውስጥ ይጨምሩት ዘንድ አዘዘ የከበሩ ሚካኤልና ገብርኤል መጥተው እሳቱን አቀዘቀዙ የመላእክት አለቃ ዑራኤልም ነጥቆ ወደ ሰማይ አሳረገውና በዚያ ዐሥራ አራት ዓመት ኖረ።
ከዚያም በኋላ ወደ ምድር ተመልሶ ወርዶ የወንጌልን ሃይማኖት እያስተማረ አርባ ዓመት ኖረ በእርሱ ትምህርትም ሰማንያ አምስት ሺህ አረማውያን አመኑ ጌታችን ኢየሱስም ስሙን ለሚጠራ መታሰቢያውንም ለሚያደርግ እስከ ሰባት ትውልድ ሊምርለት ቃል ኪዳን ሰጠው።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ሰማዕት_ቅዱስ_ፊቅጦር
በዚህች ቀን ታላቁ ሰማዕት ቅዱስ ፊቅጦር የተወለደበት ነው፡፡ የዚህ ቅዱስ እናቱ ማርታ አባቱ ደግሞ ኅርማኖስ ይባሉ ነበር፡፡ አባቱ የከሃዲው ንጉሥ የዲዮቅልጥያኖስ ባለሟል በነበረ ሲሆን ቅዱስ ፊቅጦርም በገዛ አባቱ እጅግ ተሠቃይቶ ምስክርነቱን የፈጸመው ታላቁ ሰማዕት ነው፡፡
ኅርማኖስ የተባለው ወላጅ አባቱ የክርስቲያኖችን ደም እንደ ውኃ ያፈስ የነበረው የዲዮቅልጥያኖስ ልዩ አማካሪና የሠራዊቱ አለቃ ነበር፡፡ እናቱ ሣራ ግን በክርስቶስ አምና የተጠመቀች ክርስቲያን ነበረች፡፡
እንዲያውም ልጇን ቅዱስ ፊቅጦርን ከመውለዷ በፊት የአምላክ እናት የቅድስት ድንግል ማርያም ሥዕል ወዳለበት ሄዳ "እመቤቴ ማርያም ለኢየሱስ ክርስቶስ ደስ የሚያሰኘውን ልጅ ስጪኝ፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስን ደስ የማያሰኝ ልጅ ከሆነ ግን ማኅፀኔን ዝጊልኝ" ብላ በጸለየችው ጸሎት ነው ቅዱስ ፊቅጦርን ያገኘችው፡፡
ሰማዕቱ ቅዱስ ፊቅጦር በዓለም ላይ ያሉ በክርስቶስ ያመኑ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ክርስቲያኖችን ንጉሡ ዲዮቅልጥያኖስ በግፍ ያስገድል በነበረበት ወቅት የተገኘ ታላቅ ሰማዕት ነው፡፡ ፊቅጦርን ገና 15 ዓመት እንደሆነው ንጉሡ ዲዮቅልጥያኖስ "ከፍ ባለ ስልጣን አስቀምጥሃለሁ፣ እጅግ ብዙ ወርቅና ንብረትም እሰጥሃለሁ፣ በእስክንድርያም ላይ ገዥ አድርጌ እሾምሃለሁ ክርስቶስን ማመንህን ተውና ወደ ቤተ መንግሥቴ ግባ" ቢለውም ቅዱስ ፊቅጦር ግን ብዙ መከራንና ሥቃይን ተቀብሎ ሰማዕት መሆንን መረጠ፡፡ ቅዱስ ፊቅጦርም ዲዮቅልጥያኖስን "ክርስቶስን በምታፈቅረው ጊዜ አፈቀርኩህ ወደ አንተም መጣሁ፤ ክርስቶስን በጠላኸው ጊዜ ግን እኔም ጠላሁህ፣ ቤትህንም ጠላሁ" ብሎታል፡፡
ከብዙ ጊዜም በኋላ ዲዮቅልጥያኖስ ቅዱስ ፊቅጦርን በመንግሥቱ ውስጥ ሦስተኛ ማዕረግ አድርጎ ሾመው፡፡ እርሱ ግን ይጾማል ይጸልያል እንጂ በንጉሡ ቤት አይበላ አይጠጣም ነበር፡፡ ዕድሜውም 27 ነበር፡፡ አባቱንም ከጣዖት አምላኪነቱ እንዲመለስ ቢመክረው ሄዶ ለንጉሡ ከሰሰው፡፡ ፊቅጦርም "ለአንተ ለጣዖት አምላኩ አገልጋይ አልሆንም" በማለት በንጉሡ ፊት ትጥቁን ፈቶ ጣለ፡፡ የቅዱስ ፊቅጦር ወላጅ አባቱ ኅርማኖስ የከሃዲው ንጉሥ የዲዮቅልጥያኖስ የቅርብ እንደራሴና መስፍን ስለነበር ልጁ ፊቅጦርን የንጉሡን
🔴#ስንክሳር የካቲት
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
የካቲት ዐሥራ ሦስት በዚች ቀን የከበረ #ቅዱስ_ሰርግዮስ በሰማዕትነት ሞተ፣ የእስክንድርያ አገር #ሊቀ_ጳጳሳት_ጢሞቴዎስ አረፈ፣ ለሶርያ መስፍን ልጁ የሆነ ለተመሰገነ ለሁለተኛው #ቅዱስ_አውሳብዮስ የምስክርነቱና የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው፣ ታላቁ ሰማዕት #ቅዱስ_ፊቅጦር የተወለደበት ነው፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#የከበረ_ቅዱስ_ሰርግዮስ
የካቲት ዐሥራ ሦስት በዚች ቀን የከበረ ሰርግዮስ በሰማዕትነት ሞተ አባትና እናቱ ወንድሞቹም ከእርሱ ጋር ሌሎችም ብዙ ሰዎች ሞቱ። የዚህም ቅዱስ ሰርግዮስ አባትና እናቱ ደጎች ናቸው ።
የአባቱ ስም ቴዎድሮስ የእናቱ ስም ማርያም ነው ዕድሜውም ሃያ ዓመት ሲሆነው በክብር ባለቤት ክርስቶስ ስም ይሞት ዘንድ በልቡ አሰበ ወደ መኰንኑ ቆጵርያኖስም ቀርቦ በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ታመነ፣
መኰንኑም ጽኑ ሥቃይን ያሠቃዩት ዘንድ ያሥሩትም ዘንድ አዘዘ ጌታችንም ነፍሱን ወደ ሰማይ አምጥቀው የቅዱሳን ሰማዕታትን መኖሪያ ያሳዩዋት ዘንድ አዘዘ አይታም ተጽናናች ከሥቃይ ከሕማሙም ፈወሰው።
ቀሲስ አባ መጹንና ሁለት ዲያቆናትም ተጋድሎውን ሰሙ ያን ጊዜም ተነሥተው ወደ አትሪብ አገር ገዥ ቀርበው በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ታመኑ የጸና ግርፋትንም ይገርፋአቸው ዘንድ አዘዘ እንዲሁም አደረጉባቸው። ሕዝቡም ሁሉ በዙሪቸው ሆነው ይመለከቷቸው ነበር ስለ ቄሱና ከእርሱ ጋር ስላሉትም አዘኑ ቄሱ ግን ፊቱን ወደርሳቸው መልሶ ገሠጻቸው አስተማራቸውም በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በቀናች ሃይማኖት እንዲህ ጽኑ አላቸው።
ከዚህም በኋላ በውኃ ላይ ጸለዮ በላያቸው ረጨ በዚያንም ጊዜ በላያቸው ወርዶአልና የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ ተቀብለው በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ታመኑ ራሶቻቸውንም በሰይፍ ቆረጧቸው የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥት ሰማያት ተቀበሉ።
ከዚህም በኋላ ቄሱን ከውሽባ ቤት ማንደጃ ውስጥ ይጨምሩት ዘንድ መኰንኑ አዘዘ እግዚአብሔርም ከእሳት አዳነው። ከእግዚአብሔርም የታዘዘ መልአክ ተገለጠለትና እርሱ ስለ ክብር ባለቤት ክርስቶስ ስም ሦስት ጊዜ ምስክር እንደሚሆን አስረዳው ከእሳት ማንደጃው ውስጥም አወጣው። መኰንኑም ወደ እስክንድርያ ሀገር ላከው ተጋድሎውንና ምስክርነቱን በዚያ ፈጸመ የምስክርነቱን አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ።
ከዚህ በኋላ መኰንኑ ቆጵርያኖስ የከበረ ስርግዮስን ያቀርቡት ዘንድ አዘዘ ታላቅ ሥቃይንም አሠቃየው የነሐስ መንኰራኩሮችንም አምጥተው ከውስጣቸው አሰገብተው አበራዩት ሕዋሳቱም አራት ክፍል ሁኖ ሥጋው ሁሉ ተቆራረጠ ጌታችንም አድኖ ያለ ጉዳት በጤና አስነሣው።
ዳግመኛም እንዲሰግድለት ጣዖትን አመጡ ቅዱሱ ግን ሲረግጠው ወድቆ ተቀጥቅጦ ደቀቀ መኰንን ቆጵርያኖስም አይቶ በክብር ባለቤት በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ አመነ አምላክ ቢሆን ራሱን ማዳን በቻለ ነበር አለ።
ከዚህም በኋላ የጭፍራ አለቃ ስሙ አውህዮስ የሚባል የከበረ ሰርግዮስን ፈልጎ ያዘው ቆዳውንም ገፈው በተቀላቀለ ኮምጣጤና ጨው ቁስሉን ያሹት ዘንድ አዘዘ ጌታችን ግን በሥቃዮች ላይ ያጸናውና ያበረታው ነበር።
እናቱና እኅቱም ሰምተው ወደርሱ መጡ በአዩትም ጊዜ በላዩ አለቀሱ ከኀዘንም ብዛት እኅቱ ነፍሷን አሳለፈች የከበረ ሰርግዮስም ስለ እኅቱ ወደ ጌታችን ጸለየ ከሞትም ድና በሕይወት ተነሣች።
ያን ጊዜ የሰማዕታትን ገድል የሚጽፍ የአቅፋሐስ ሀገር ሰው የከበረ ዮልዮስ መጣ ገድሉንም ሁሉ ከእርሱ ተረዳ ለሥጋውም እንደሚአስብ ቃል ገባለት ።
ከዚህም በኋላ ደግሞ የከበረ ሰርግዮስን በመንኰራኩር ውስጥ ያሠቃዩት ዘንድ በጆሮዎቹ የእሳት መብራቶችን እንዲጨምሩ የእጆቹንና የእግሮቹን ጥፍሮች እንዲነቅሉ በአንገቱም ከባድ ደንጊያ አንጠልጥለው ከብረት ዐልጋ ላይ አስተኝተው ከበታቹ እሳትን እንዲያነዱ አውህዮስ አዘዘ እንዳዘዘውም አደረጉበት ጌታችን ኢየሱስም ያጸናውና ያለ ጥፋት በጤና ያስነሣው ነበር።
የሠራዊት አለቃ አውህዮስም ማሠቃየቱን በደከመ ጊዜ ራሱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ የከበረ ሰርግዮስም ሰምቶ እጅግ ደስ አለው ወደ አባቱና ወደ እናቱ ወደ ወንድሞቹም ላከ ዘመዶቹ ሁሉም የእርሱ የሆኑ ሰዎችም መጡ በአፉም ልጓም ለጉመው ቸብቸቦውን ወደሚቆርጡበት ሲስቡት አገኙትና መኰንኑን የረከሱ ጣዖታቱንም ረገሙ መኰንኑም ከከበረ ሰርግዮስ ጋር ሁሉንም ቸብቸቧቸውን እንዲቆርጡ አዘዘ በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ።
እንዲህም ሆነ ከሕዝቡ ውስጥ አንድ ታናሽ ሕፃን እግዚአብሔር ዐይኖቹን ገልጦለት የቅዱሳን ሰማዕታትን ነፍሶቻቸውን መላእክት ወደ ሰማያት ሲያወጧቸው አይቶ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ይቅር በለኝ እያለ በከፍተኛ ቃል ጮኸ ። እናትና አባቱም መኰንኑ ሰምቶ ስለርሱ እንዳያጠፋቸው አፉን የሚዘጉ ሆኑ እርሱ ግን እንዲህ እያለ መጮኹን አልተወም በላዩ እስከ ተኙበትና ነፍሱን እስከ አሳለፈ ድረስ ከሰማዕታትም ጋር የምስክርነት አክሊልን ተቀበለ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ሊቀ_ጳጳሳት_አባ_ጢሞቴዎስ
በዚህች ዕለት የከበረ አባት የእስክንድርያ አገር ሊቀ ጳጳሳት ጢሞቴዎስ አረፈ። እርሱም ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሠላሳ ሁለተኛ ነው። ይህንንም አባት ስለ ቀናች ሃይማኖት ብዙ መከራና ችግር ደርሶበታል ። እንዲህም ሆነ በዚያ ወራት የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ሳዊሮስ ወደ ግብጽ አገር መጣ እርሱም ከዚህ አባት ጢሞቴዎስ ጋር ምእመናንን እያ
ጽናና ከሀገር ወደ ሀገር ከገዳም ወደ ገዳም ከቦታ ወደ ቦታ የሚዘዋወር ሆነ።
በዚህም አባት ጢሞቴዎስ ዘመን ከቊስጥንጥንያ የመጡ ክፉዎች ሰዎች በግብጽ አገር ተገለጡ እነርሱም የክርስቶስን ተዋሕዶ ምትሐት በሚያደርግ መከራውንና ትንሣኤውንም በሚክድ በረከሰ በአውጣኪ ትምህርት የሚያምኑ ናቸው ይህም አባት አውግዞ ከግብጽ አገር አሳደዳቸው።
ዳግመኛም በዘመኑ ምእመን ንጉሥ አንስጣስዮስ አረፈና በርሱ ፈንታ ኬልቄዶናዊ መናፍቅ ዮስጣትያኖስ ነገሠ እርሱም በአባ ጢሞቴዎስ ፈንታ ሊናርዮስን ሊቀ ጵጵስና ሾመው ሃይማኖታቸው የቀና ምእመናንን ሁሉ በኬልቄዶን ግባኤ ወደተወሰነ ሃይማኖት ሊመልሳቸው ወዶ በቅስጥንጥኒያ ጉባኤ ሰብስቦ የአንጾኪያውን ሊቀ ጳጳሳት አባ ሳዊሮስን ከኤጲስቆጶሳቶቹ ጋር አስመጣው።
በኬልቄዶን ጉባኤ በተወሰነች በተበላሸች ሃይማኖቱ ያምኑ ዘንድ አስገደዳቸው እነርሱ ግን አልተቀበሉትም ትእዛዙንም አልሰሙም ስለዚህም ሃይማኖታቸው በቀና ምእመናን ሁሉ ታላቅ መከራ አደረሰባቸው።
ይህም አባት ጢሞቴዎስ በመንበረ ሢመቱ ዐሥራ ሰባት ዓመት ኑሮ በሰላም አረፈ ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_አውሳብዮስ_ጻድቅ
በዚህችም ዕለት መልካም ስም አጠራርና ጣፋጭ ዜና ያለው ለሶርያ መስፍን ልጁ የሆነ ለተመሰገነ ለሁለተኛው አውሳብዮስ የምስክርነቱና የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው። ለርሱም መንፈስ ቅዱስን የተመላች ስሟ አውሎፊያ የሚባል እኅት አለችው ይህንንም ቅዱስ በተግሣጽና ጥበብን በማስተማር አሳደጉት በአደገም ጊዜ እጅግ ደም ግባት ያላትን የሮሜውን ንጉሥ ልጅ በብዙ ክብር አጋበት።
በዚያችም ዕለት ወደ እኅቱ ገብቶ እስቲ ምከሪኝ ልቤ ይህን ጋብቻ አይሻውም ዓለምን ንቆ መተውን እንጂ አላት እኅቱም የዚህ የኃላፊው ዓለም ጣዕም ምን ይጠቅምሃል እንደ ሊቀ ጳጳሳት ድሜጥሮስ በድንግልና መኖር ይሻልሃል አለችው ።
🔴#ስንክሳር የካቲት_12
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
የካቲት ዐሥራ ሁለት በዚች ቀን የመላእክት አለቃ የከበረ መልአክ #ቅዱስ_ሚካኤል ወደ ረዓይታዊ ወደ ሶምሶን ተልኮ ኃይልን ሰጥቶት ጠላቶቹን ድል እንዲያደርግ የተራዳበት መታሰቢያ ነው፣ ተጋዳይ የሆነ የከበረ አባት #አባ_ገላስዮስ አረፈ፣ ታላቁ አባት #አቡነ_ሠርጸ_ጴጥሮስ አረፉ፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#የመላእክት_አለቃ_ቅዱስ_ሚካኤል
የካቲት ዐሥራ ሁለት በዚች ቀን የመላእክት አለቃ የከበረ መልአክ ሚካኤል ወደ ረዓይታዊ ወደ ሶምሶን ተልኮ ኃይልን ሰጥቶት ጠላቶቹን ድል እንዲያደርግ የተራዳበት መታሰቢያ ነው።
በዚች ዕለት የከበረ ሚካኤልን እግዚአብሔር ወደ ረዓይታዊ ወደ ሶምሶን ላከው የፍልስዔም ሰዎች ሊገድሉት በጠላትነት በተነሡበት ጊዜ ድል እስከ አደረጋቸውና እስከ ገደላቸው ድረስ ረዳው ኃይልንም ሰጥቶ በአህያ መንጋጋ ከእርሳቸው አንድ ሺህ ሰዎችን ገደለ። ተጠምቶም ለሞት በተቃረበ ጊዜ የመላእክት አለቃ ሚካኤል ተገለጠለትና አጸናው እግዚአብሔር ከአህያ መንጋጋ አጥንት ውኃን አፈለቀለትና ጠጥቶ ዳነ።
ዳግመኛም ከሚስቱ ጋር ተስማምተው ዐይኖቹን አሳወሩ የራሱንም ጠጉር ላጩ አሠሩትም ከዚህም በኋላ ለጣዖቶቻቸው በዓልን በአዘጋጁ ጊዜ ሶምሶንን ወደ ጣዖቶቻቸው ቤት ወሰዱት በዚያም ሦስት ሽህ ያህል ሰዎች ተሰብስበው ነበር የከበረ ሚካኤልም ተገለጠለትና ኃይልን መላው የዚያንም ቤት ምሰሶዎች ነቀላቸው ቤቱም በላያቸው ወድቆ ከእርሱ ጋር ሁሉንም ገደላቸው።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_አባ_ገላስዮስ_ገዳማዊ
በዚህችም ቀን ተጋዳይ የሆነ የከበረ አባት አባ ገላስዮስ አረፈ። የዚህ ቅዱስ ወላጆቹ አግዚአብሔርን የሚፈሩ ምእመናን ናቸው ጥበብንና የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት አስተማሩትና ዲቁና ተሾመ።
ከታናሽነቱም ጀምሮ ይህን ዓለም ንቆ ተወ የክብር ባለቤት የሆነ የክርስቶስንም ቀንበር በመሸከም በምንኵስና ሆኖ በትጋት እየጾመ እየጸለየና እየሰገደ ታላቅ ተጋድሎን ተጋደለ እግዚአብሔርም መርጦት በአስቄጥስ ገዳም ባሉ መነኰሳት ላይ ቅስና ተሾመ።
ተጋድሎውንና አገልግሎቱን እየፈጸመ ሳለ ለአባ ጳኵሚስ እንደ ተገለጠ የእግዚአብሔር መልአክ ተገለጠለትና መነኰሳትን ሰብስቦ ፈሪሀ እግዚአብሔርን የምንኵስናንም ሕግ ያስተምራቸው ዘንድ አዘዘው በዚያንም ጊዜ ብዙዎች መነኰሳትን ሰበሰበ መንፈሳዊ የሆነ የአንድነት ማኅበራዊ ኑሮንም ሠራላቸው እርሱ በመካከላቸው እንደ መምህር አልሆነም ከእርሳቸው እንደሚያንስ አገልጋይ እንጂ።
ይህም አባት የዚህን ዓለም ጥሪት ሁሉ ንቆ የተወ ሆነ እጅግም የዋህና ቸር ሆነ ከብሉይና ከሐዲስ መጻሕፍቶችም የተሰበሰበ አንድ ታላቅ መጽሐፍን አጻፈ ለማጻፊያውም ዋጋ ዐሥራ ስምንት የወርቅ ዲናር አወጣ ከርሱ ሊጠቀሙ በሚፈልጉ ጊዜ መነኰሳቱ እንዲያነቡት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በአትሮንስ ላይ አኖረው።
አንድ መጻተኛ ሰውም አረጋዊ አባ ገላስዮስን ሊጎበኝ በገባ ጊዜ ያንን መጽሐፍ አየውና አማረው በጭልታም ከዚያ ሰርቆት ወጣ ወደ ከተማ ውስጥም በገባ ጊዜ ሊሸጠው ወደደ አንድ ሰውም ዋጋው ምን ያህል ነው አለው እርሱም ዐሥራ ሰባት የወርቅ ዲናር ስጠኝ አለው። ያ የሚገዛውም ሰው ያልከውን እሰጥሃለሁ ነገር ግን ለወዳጄ እስካሳየው ታገሠኝ አለው ያሳየውም ዘንድ ሰጠው የሚገዛው ሰው ግን ወደ አባ ገላስዮስ ወሰደውና ተመልከትልኝ መልካም ከሆነ እገዛዋለሁ አለው አባ ገላስዮስም ያመጣውን ሰው ከአንተ ምን ያህል ፈለገ አለው ዐሥራ ሰባት የወርቅ ዲናር አለው ቅዱስ ገላስዮስም መጽሐፉ መልካም ነው ዋጋውም ቀላል ነው ግዛው ብሎ መለሰለት።
ወደ ሌባውም በተመለሰ ጊዜ አባ ገላስዮስ የነገረውን ሠውሮ ለአባ ገላስዮስ አሳየሁት እርሱም ዋጋው በዝቷል አለኝ አለው ሌባውም ያ ሽማግሌ ሌላ የተናገረህ ነገር የለምን አለው አዎን የለም አለው። ሌባውም እንግዲህ እኔ አልሸጠውም ብሎ ወደ አባ ገላስዮስ ሒዶ ከእግሩ በታች ወድቆ ለመነው ሰይጣን አስቶኛልና ይቅር በለኝ መጽሐፍህንም ውሰድ አለው የከበረ ገላስዮስም እኔ መጽሐፉን መውሰድ አልሻም አለው። ሌባውም በፊቱ እያለቀሰና እየሰገደ ብዙ ለመነው በብዙ ድካምም መጽሐፉን ተቀበለው ማንም ያወቀ የለም። እግዚአብሔርም ትንቢት የመናገርን ሀብት ሰጥቶት ድንቆች ተአምራቶችን አደረገ።
በአንዲትም ዕለት ለገዳሙ መነኰሳት ዓሣ አመጡ ባለ ወጡ ዓሣውን አብስሎ በቤት ውስጥ አኑሮ አንዱን ብላቴና ጠባቂ አድርጎ ወደ ሥራው ሔደ ብላቴናውም ከዚያ ዓሣ በላ። ባለ ወጡ በመጣ ጊዜ ተበልቶ አገኘውና በብላቴናው ላይ ተቆጥቶ አረጋውያን አባቶች ሳይባርኩት እንዴት ደፍረህ በላህ አለው የቊጣ መንፈስም በልቡ አደረና ብላቴናውን ረገጠው ወዲያውኑ ሞተ እንደሞተም አይቶ ደነገጠ ታላቅ ፍርሀትንም ፈራ ሒዶ ለአባ ገላስዮስ የሆነውን ሁሉ ነገረው እርሱም ወስደህ ከቤተ መቅደሱ ፊት አስተኛው አለው ሰውየውም እንዳዘዘው አደረገ።
ወደ ማታ ጊዜም አረጋውያን መነኰሳት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተሰብስበው የማታውን ጸሎት አድርሰው ወጡ አረጋዊ አባ ገላስዮስም በወጣ ጊዜ የሞተው ብላቴና ተነሥቶ በኋላው ተከተለው ከመነኰሳትም ማንም አላወቀም እርሱም የገደለውን ባለ ወጥ ለማንም እንዳይናገር አዘዘው።
የተመሰገነ አባ ገላስዮስም ያማረ ትሩፋቱንና ተጋድሎውን ፈጽሞ አድርሶ እግዚአብሔርንም አገልግሎ ይህንንም በጎ መታሰቢያ ትቶ ከዚህ ከኃላፊው ዓለም የሚለይበት ሲደርስ በሰላም አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አቡነ_ሠርጸ_ጴጥሮስ
ዳግመኛም በዚህች እለት ታላቁ አባት አቡነ ሠርጸ ጴጥሮስ አረፉ፡፡ የትውልድ አገራቸው ሸዋ ደብረ ጽላልሽ ሲሆን በሕፃንነታቸው ወደ ወሎ ሄደው ሐይቅ እስጢፋኖስ ገብተው ብዙ ተጋድለዋል፡፡ከተጋድሎአቸውም በኋላ በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ እጅ መነኰሱ፡፡ በገዳሙ ብዙ ካገለገሉ በኋላ በመልአክ ትእዛዝ ወደ ጎጃም ሲሄዱ ዓባይን የተሻገሩት አጽፋቸውን አንጥፈው እርሱን እንደ ጀልባ ተጠቅመው ነው፡፡
ጻድቁ ታላቋን ተድባበ ማርያምን ለ41ዓመት አጥነዋል፡፡ የንጉሡ ልጅ ሞቶ ሊቀብሩት ሲወስዱት የአቡነ ሠርጸ፡ጴጥሮስ ጥላቸው ቢያርፍበት ከሞት አፈፍ ብሎ ተነሥቶ ድኖ "አምላከ አቡነ ሠርጸ ጴጥሮስ" ብሎ ፈጣሪውን አመስግኗል፡፡ ጻድቁ ሲያርፉም መቋሚያቸው አፍ አውጥታ ተናግራለች፤ ርዕደተ መቃብራቸው ሲፈጸምም እንባ አፍስሳ አልቅሳላቸዋልች፡፡ ይህቺ ተአምረኛ መቋሚያቸው ዛሬም ጎጃም ውስጥ መካነ መቃብራቸው ባለበት በደብረ ወርቅ ገዳም ትገኛለች፡፡ ጻድቁ ደብረ ወርቅ ገዳምን እንደ መሶብ አንሥተው አስባርከዋታል፡፡ አቡነ ሠርፀ ጴጥሮስ የካቲት12 ቀን ያረፉ ሲሆን ዐፅማቸውም በታላቋ ደብረ ወርቅ ይገኛል፡፡ ከሰማይ የወረደላቸው የወርቅ መስቀላቸውም በዚያው ይገኛል፡፡
ጸበላቸው እጅግ ፈዋሽና ኃይለኛ ከመሆኑም በላይ በሰውነት ውስጥ የሚገኝ በሽታንና አጋንንትን የሚያስወጣበት መንገድ ለየት ያለው፡፡
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12
🔴#ስንክሳር የካቲት_11
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
የካቲት ዐሥራ አንድ በዚች ቀን የሮሜ ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት #ቅዱስ_በላትያኖስ በሰማዕትነት ሞተ፣ ተጋዳዩ ባለ አንበሳው #ቅዱስ_አውሎግ አረፈ፣ የአባ ስልዋኖስ ረድእ #ቅዱስ_አባ_በትራ አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#በላትያኖስ_ሰማዕት
የካቲት ዐሥራ አንድ በዚህች ቀን የሮሜ ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት በላትያኖስ በሰማዕትነት ሞተ።
ይህም ቅዱስ ብልህና አዋቂ የሆነ ታላቅ ተጋድሎን የሚጋደል ነው በሮሜ ሀገርም ሊቀ ጵጵስና ተሹሞ በቅዱስ ጴጥሮስ ወንበር ላይ ዐሥራ ሁለት ዓመት በሰላም ኖረ። ሕዝቡን የቀናች ሃይማኖትን እያስተማራቸው ሳለ መኰንኑ ፊሊጶስ በንጉሥ ቀላውዴዎስ ላይ ተነሥቶ በገደለው ጊዜ በርሱ ፈንታ ነገሠ በምእመናንም ላይ ታላቅ መከራን አመጣ በዚህ በንጉሥ ዳኬዎስ እጅ ብዙዎች በሰማዕትነት ሞቱ።
በዘመኑም ሰባት ሰዎች ከእርሱ ሸሹ ሦስት መቶ ሰባ ሁለት ዓመት ተኝተው ነቁ እርሱም በኤፌሶን ከተማ መስጊድ ሠርቶ በውስጡ ጣዖታትን አኖረ ሰዎችን ሁሉ ለጣዖታት እንዲሠዉ አስገደዳቸው ለጣዖታት ያልሠዉትንም ገደላቸው።
ይህ የከበረ በላትያኖስም የጣዖታት አምልኮን እንደሚቃወም ሕዝቡም በክብር ባለቤት በክርስቶስ ሃይማኖት ይጸኑ ዘንድ እንደሚያስተምር ንጉሥ በሰማ ጊዜ ወደ ሮሜ አገር ልኮ ወደ ኤፌሶን ከተማ አስመጣውና ለጣዖታት እንዲሠዋ ለመነው።
እርሱ ግን ቃሉን አልሰማም ተሣለቀበት አማልክቶቹንም ረገመ እንጂ። ንጉሡም ተቆጣ አንዲት ዓመት ያህልም ጽኑዕ ሥቃይን አሠቃየው ማሠቃየቱንም በሰለቸ ጊዜ በሰይፍ ራሱን ቆረጠው የምስክርነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አባ_አውሎግ_አንበሳዊ
በዚህችም ዕለት ተጋዳዩ ባለ አንበሳው አውሎግ አረፈ፡፡ የዚህ ቅዱስ ወላጆች ከሀገረ ንጽቢን የሆኑ በበጎ ሥራ ፍጹማን በወርቅና በብርም የበለጸጉ ናቸው። ለልጃቸውም የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሁሉ አስተማሩት ከጥቂት ቀኖች በኋላ ወላጆቹ ብዙ ገንዘብን ትተውለት ሞቱ።
በአንዲትም ዕለት አውሎግ ያለህን ገንዘብህን ሁሉ ሽጠህ ለድኆች ሰጥተህ መከራ መስቀልህን ተሸክመህ ና ተከተለኝ የሚለውን የከበረ የወንጌልን ቃል አሰበና ወዲያውኑ ገንዘቡን ሁሉ ለድኆችና ለችግረኞች በትኖ ወደ አባ አውሎጊን ሔደ እርሱም በደስታ ተቀበለው።
ስለ ርሱ እንዲህ የሚለውን ራእይ አይቶ ነበር እነሆ ወዳንተ ጐልማሳ ይመጣል ተቀበለውና ከሚያገለግሉ መነኰሳት ጋር ቀላቅለው እየፈተነውም ሦስት ዓመት ያህል ኖረ ፍጹም የሆነ ቅድስናውንም በአየ ጊዜ የምንኵስናን ልብስ የመላእክትንም አስኬማ አለበሰው።
ከሰንበትም እስከ ሰንበት እየጾመ በብዙ ተጋድሎ ኖረ ምግቡም እንጀራና ጨው ነበረ በቀንና በሌሊትም ሰባት መቶ ጊዜ አቡነ ዘበሰማያትን ከስግደት ጋር ይጸልያል በዚህም ተጋድሎ አርባ ዓመት ኖረ።
ከዚህም በኋላ ያሰናብተው ዘንድ መምህሩ አባ አውሎጊንን ማለደውና ወደ በረሀ ሔደ ከአንዲት ታናሽ ዋሻ ውስጥም ገብቶ እየተጋደለ ኃምሳ ዓመት ኖረ። ለፍላጎቱም የሚያገለግሉት ሁለት አንበሶችን እግዚአብሔር ሰጠው በአንዲትም ዕለት ታመመ አንበሶቹንም እጠጣ ዘንድ የሞቀ ውኃ እሻለሁ አላቸው። አንዱ አንበሳም ወደ ተራራ ሒዶ እረኛ አግኝቶ ወደ አባ አውሎግ አመጣው በአየውም ጊዜ ሰገደለትና አባቴ ሆይ ምን ትሻለህ አለው። እርሱም የሞቀ ውኃ ታጠጣኝ ዘንድ እሻለሁ አለው እንዳለውም አደረገለት ከዚህም በኋላ አንበሳው እረኛውን ወደቦታው መለሰው።
ያም እረኛ ለእግሩ ተረከዝ ዓለሙ ሁሉ መጠኑ የማይሆን ጻድቅ ሰውን አገኘሁ ብሎ ለሰው ሁሉ ተናገረ በሰሙ ጊዜም ሰዎች ሁሉ ወደርሱ ተሰበሰቡ በሽተኞችንም ሁሉ አመጡለትና ፈወሳቸው።
በዚያ ወራትም መምህሩ አባ አውሎጊን ጣዖትን የሚያመልኩ የፋርስ ሰዎችን ወደ ቀናች ሃይማኖት ለመመለስ ወደ ፋርስ ሀገር ሊሔድ ፈለገ ዳግመኛም ልጁ አውሎግን ከእርሱ ጋር ሊወስደው ወደርሱ መልእክተኛ ሊልክ ሽቶ ሳለ መንፈስ ቅዱስ አንበሳውን አስገነዘበውና አጽፉንና ወንጌሉን አንሥቶ ተሸከመ። አባ አውሎግንም ጕዞን አመለከተው ተነሥቶም አንበሳውን ተከትሎ ወደ መምህር አውሎጊን ደረሰ እርሱም በደስታ ተቀበለው።
ሲጓዙም ከጤግሮስ ወንዝ ደረሱ ውኃውም ተከፍሎላቸው ተሻገሩ ወደ ሀገሩም ውስጥ በደረሱ ጊዜ አስተማሩአቸው ወደ ቀናች ሃይማኖትም መለሷቸውና በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠመቋቸው።
በአንዲትም ዕለት ደግሞ ቅዱሳን በተራቡ ጊዜ ምግባቸውን ይፈልጉላቸው ዘንድ አባ አውሎግ አንበሶችን አዘዘ ሒደውም እንጀራ በአህያ ላይ ጭኖ የሚጓዝ ሽማግሌ አገኙ ሕፃንም ከእንጀራው ጋር አለ ።
አህያውንም ወደ ቅዱሳን አመጡት ከድንጋጤም የተነሣ ብላቴናው ሞተ ቅዱሳንም ጸልየው ሕፃኑ ድኖ ተነሣ ቅዱሳንም ተመገቡ አንበሶችም አህያውን ከእንጀራውና ከሕፃኑ ጋር ወደ ሽማግሌው መለሱት። ከዚህም በኋላ አባ አውሎግ ወደ በዓቱ ተመለሰና ጥቂት ታሞ አረፈ በታላቅ ክብርም ተቀበረ እነዚያ አንበሶችም መቃብሩን እየጠበቁ ዐሥራ ሁለት ዓመት ኖሩ ከዚያም በኋላ ወደ ዱር ገቡ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አባ_በትራ
በዚህችም ቀን የአባ ስልዋኖስ ረድእ አባ በትራ አረፈ። ይህም ቅዱስ በደብረ ሲና ካለች በዓቱ በነበረ ጊዜ ትርኅምትን ይጠብቅ ነበር በራትም ጊዜ ለሥጋው የሚያሻውን ይመገባል።
ፈርኑ በሚባል አገር ላይ ኤጲስቆጶስ በአደረጉት ጊዜ ትርኅምትን በማብዛት ሰውነቱን እጅግ አደከመ ደቀ መዛሙርቱም አባታችን ሆይ በገዳም በበኣትህ በነበርክ ጊዜ ትርኅምትን እንዲህ አላበዛህም ነበር አሉት ይህም አባት እንዲህ አላቸው "ያን ጊዜ በገዳም በችግር ውስጥ ነበርኩ ዛሬ ግን ከብዙዎች መካከል በአንድነት አለሁ የምሻውም ሁሉ ብዙ አለኝ ነገር ግን ሥጋዬን ቀጥቼ ብገዛው ይሻላል እንዲህም እየተጋደለ ኖረ ከዚህም በኋላ በሰላም አረፈ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12
🔴#ስንክሳር የካቲት_10
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
የካቲት ዐሥር በዚች ቀን ከዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ የእልፍዮስ ልጅ #ሐዋርያው_ቅዱስ_ያዕቆብ በሰማዕትነት ሞተ፣ የንጉሥ ኑማርያኖስ ልጅ #የከበረ_ዮስጦስ በሰማዕትነት ሞተ፣ በገድል የተጠመደ #አባ_ኤስድሮስ አረፈ፣ የፋርስ ሀገር ኤጲስቆጶስ #አባ_ፌሎ በሰማዕትነት ሞተ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ሐዋርያው_ቅዱስ_ያዕቆብ_ወልደ_እልፍዮስ
የካቲት ዐሥር በዚች ቀን ከዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ የእልፍዮስ ልጅ የከበረ ሐዋርያ ያዕቆብ በሰማዕትነት ሞተ። ይህም ሐዋርያ በብዙ ሀገሮች ውስጥ ከሰበከ በኋላ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ ወደ ምኲራብም ገብቶ የክብር ባለቤት የጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን ሃይማኖት በግልጥ አስተማረ። ከእርሱ ለሚሰሙትም ሁሉ ብዙ ተአምራትን አደረገ። ንጹሕ በሆነ ልቡናም በእግዚአብሔር አመኑ። ራሳቸውንም አጸኑ። ሐዋርያው ቅዱስ ያዕቆብም በልቡናው አሰበ፡፡ እንዲህም አለ። ሕዝቡ ከእርሱ ሰምተው እንዴት ያምናሉ አለ። እርሱም ሕዝቡ ወደተሰበሰቡበት ወደ ምኩራብ ገባ። ከአይሁድም የተቀመጡ የተሰበሰቡ ብዙ ሰዎችን አገኘ። በፍጹም ታላቅ ደስታ ያስምራቸው ዘንድም በመካከላቸውም ገባ። ለሁሉም በቃሉ ማስተማሩን አበዛ። ያለመፍራትም ሃይማኖቱን ገለጠ። አንድ ለሆነው ለእግዚአብሔር ልጅ ምስክር ሆነ። "የሕይወት ቃል ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ የዓለም ሁሉ አምላክ ነው። በእውነትም የእግዚአብሔር ልጅ ነው። እርሱ ዓለም ከመፈጠሩ አስቀድሞ ከአብ ጋር ነበርና። እርሱ በአብ አለ፤ አብም በእርሱ አለ። እርሱ የአብ ቃል ነው። እርሱ ሰውን በአርአያችንና በምሳሌያችን እንፍጠር አለ። እርሱ በሰማይ አለ። እርሱ ከአባቱ ጋር አለ። እርሱ በኪሩቤል ሰረገላ ይቀመጣል። ሱራፌልም ያመሰግኑታል። እርሱ በድንግል ማርያም ማሕፀን የተወሰነ በልዕልና በገናንነቱ ሥልጣን ነው። እርሱ ድንግል ማርያም የወለደችው ጌታችን እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ሰው የሆነ አምላክ ነው"። አንድ ሰው ስንኳን ሳይፈራ በተሰበሰቡት መካከል የሐዋርያው ምስክርነት ይህ ነበር። በእውነት አንድ ለሆነው ለእግዚአብሔር ልጅ ልደትም ምስክር ሆነ። እርሱ ነበርና። በሞቱም፣ በትንሣኤውም፣ ወደ አባቱ ወደ ሰማይ ስለማረጉም ምስክ ሆነ። ለተሰበሰቡትም በክርስቶስ ስለማመን አስተማራቸው።
የተሰበሰቡትም የሐዋርያውን ትምህርት በሰሙ ጊዜ ከእርሱ ጋር ካለው ከአባታቸው ከሰይጣን የተነሳ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ ላይ ፈጽመው ተቆጡ። ሁሉም ተሰብስበው ተቀመጡ። የተሰበሰቡት ሁሉ ደሙን ፈለጉ። ነገሩን የሰሙትም የተባረከ ሐዋርያን ያዙት። ከንጉሥ ከቀላውዴዎስም ወሰዱት። የሐሰት ምስክሮችንም በእርሱ ላይ አስነሡ። ለንጉሡም "ይህን ጥፋተኛ ሰው በሀገሩ በአውራጃው ይዘናል" አሉት፤ "እኔ የእግዚአብሔር የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ነኝ ይላቸዋል። ለንጉሡ እንዳይገዙም ይከለክላል" አሉት። ስለተባረከው ሐዋርያ ይህን ነገር በሰማ ጊዜም እስከሚሞት ድረስ በድንጋይ ይወግሩት ዘንድ አዘዘ። አይሁድንም እግዚአብሔር ረገማቸው። ንጉሡ አይሁድን እንዳዘዛቸውም በድንጋይ ወገሩት። ከዚህ በኋላ ቡሩክ የሚሆን የእልፍዮስ ልጅ የሐዋርያው የቅዱስ የያዕቆብ ምስክርነት የካቲት ዐሥር ቀን ሆነ። በኢየሩሳሬም ቤተ መቅደስ ተቀበረ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ዮስጦስ_ሰማዕት
በዚህችም ዕለት የንጉሥ ኑማርያኖስ ልጅ የከበረ ዮስጦስ በሰማዕትነት ሞተ። ይህም ቅዱስ በጦር ሜዳ እያለ እኅቱ ከሀዲ ዲዮቅልጥያኖስን አግብታ ንጉሥም አደረገችው ከጦርነትም በተመለሰ ጊዜ የክብር ባለቤት ክርስቶስን ዲዮቅልጣኖስ ክዶ አገኘውና እጅግ አዘነ።
የሀገሩም ሰዎች በአዩት ጊዜ ወደርሱ ተሰብስበው ዲዮቅልጥያኖስን እኛ እንገድለዋለን አንተም ጌታችን በመንግሥትህ ዙፋን ላይ ትቀመጣለህ አሉት እርሱ ግን ይህን ስለአልፈለገ እንዳይገድሉት ከለከላቸው ከምድራዊት መንግሥት ሰማያዊት መንግሥትን መርጧልና።
ከዚህም በኋላ ወደ ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ቀርቦ በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ ንጉሡም ፈርቶታልና ጌታዬ ዮስጦስ ሆይ ይህን ታደርግ ዘንድ ያስገደደህ ማነው አለው የከበረ ዮስጦስም በምስክርነቴ ደሜን እንዳፈስ ካልጻፍክ ሕዝቡን በአንተ ላይ አስነሥቼ ከመንግሥትህ እንደማስወጣህ የክብር ባለቤት ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሕያው ነው ብሎ ማለ።
በዚያንም ጊዜ ንጉሡ ፈርቶ ከሚስቱ ከታውክልያ ከልጁ ከአቦሊ ጋር ወደ ግብጽ አገር እንዲወስዱአቸው አዘዘ የእስክንድርያንም ገዥ አብዝቶ እንዲሸነግላቸው ምናልባት ልባቸው ቢመለስ እንዳያሳዝናቸውም አለዚያ እያንዳንዱን እንዲለያያቸው አዘዘው።
ወደ ግብጽ አገርም በደረሱ ጊዜ ከእርሳቸው ጋር የንጉሥ ደብዳቤ አገልጋዮችም አሉ የእስክንድርያም ገዥ በአያቸው ጊዜ እጅግ ፈራ ሊሸነግለውም ጀምሮ ቅዱስ ዮስጦስን ጌታዬ እንዲህ አታድርግ ክብርህ ይሻልሃል አለው የከበረ ዮስጦስም ነገር አታብዛ አለው መኰንኑም ፈርቶ ቅዱስ ዮስጦስን ወደ ላይኛው ግብጽ ወደ እንዴናው ከተማ ሰደደው ልጁ አቦሊን ወደ ሀገረ ብስጣ ሚስቱ ታውክልያን ወደ ሀገረ ፃ ላካቸው ከአገልጋዮቹም የሚአገለግሏቸው አንዳንድ ሰጣቸው የከበረ ዮስጦስንም በእንዴናው ከተማ ብዙ ከአሠቃዩት በኋላ ራሱን ቆረጡት የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበለ ከሥጋውም ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ ለበሽተኞችም ታላቅ ፈውስ ሆነ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አባ_ኤስድሮስ_ጻድቅ
በዚህችም ዕለት በገድል የተጠመደ ምሁር የሆነ የአለሙ ሁሉ መምህር አባ ኤስድሮስ ፈርማ ከሚባል አገር አረፈ። የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ በምስር አገር የከበሩ ባለጸጎች ናቸው ለእስክንድርያ ሊቃነ ጳጳሳትም አባ ቴዎድሮስና አባ ቄርሎስ ዘመዶች ናቸው ከእርሱም በቀር ልጅ የላቸውም መንፈሳዊ ትምህርትን ሁሉ የቤተ ክርስቲያንንም መጻሕፍት ሁሉ አስተማሩት ግልጽ አድርጎ አጠናቸው ጠበቃቸውም ዳግመኛም የዮናናውያንን የፍልስፍና ትምህርት የከዋክብትን አካሔድና ዓለምን መዞራቸውን ተማረ በእውቀቱና በጥበቡም ከብዙዎች ከፍ ከፍ አለ በገድልም የተጠመደ ትሑትና የሚተጋ ሆነ።
በሀገሮችም ያሉ ሰዎች ስለርሱ በሰሙ ጊዜ በእስክንድርያ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ይሾሙት ዘንድ ተማክረው ከኤጲስቆጶሳቱ ጋር ተስማሙ። በሌሊትም ወጥቶ ሸሸ ወደ ፈርማ ገዳም ደርሶ በዚያ መነኰሰ ከዚያም ወጥቶ ወደ አንዲት አነስተኛ ዋሻ ገብቶ ብቻውን በውስጧ ብዙ ዘመናት ኖረ ብዙ ድርሳናትንና ተግሣጻትንም ደረሰ ከእርሳቸውም ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንት የደረሳቸው አሉ የቤተ ክርስቲያንን መጻሕፍቶችን ብሉያትና ሐዲሳትን ተረጐመ።
የመጻሕፍቶቹም ቁጥራቸው ዐሥራ ስምንት ሺህ ነው እሊህም ድርሳናት ተግሣጻት ጥያቄዎችና መልሶች ወደ ሊቃነ ጳጳሳትና ኤጲስቆጶሳት የተላኩ መልእክቶች ናቸው ወደ ምእመናንም ወንዞች ውኃዎችን እንደሚያፈልቁ እርሱ በመንፈስ ቅዱስ የሚያፈልቃቸው ሆኗልና።
ይህንንም በጎ ሥራውን ሲፈጽም መልካም ጉዞውንም አከናውኖ ወደ በጎ ሽምግልና ደርሶ እግዚአብሔርንም አገልገሎ በሰላም አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አባ_ፌሎ
በዚህች ቀን የፋርስ ሀገር ኤጲስቆጶስ አባ ፌሎ በሰማዕትነት ሞተ። ይህንንም ቅዱስ ለእሳት እንዲሠዋ ለፀሐይም እንዲሰግድ የፋርስ ንጉሥ አዘዘው እምቢ በአለውም ጊዜ ታላቅ ሥቃይን አሠቃይቶ ራሱን በሰይፍ ቆረጠው በመንግሥተ ሰማያት የሰማዕትነትን አክሊል ተቀበለ።
በሶርያ አገርም አስተማረ በፊታቸው ተአምራትን በአደረገ ጊዜ በትምህርቱ ብዙዎች አመኑ። ዳግመኛም ወደ ታናሹ ቴዎዶስዮስ ንጉሥ ሒዶ በቀናች ሃይማኖት አጸናው ንጉሡም ብዙ ገንዘብን ሰጠው እርሱ ምንም ምን አልወሰደም በአንጾኪያም አገር በኤጲስቆጶሳቱ ሁሉ ላይ ሥልጣን እንዲኖረው ንጉሥ ጻፈለትና ኀቲም ቀለበቱን ሰጠው።
በከሀዲው ንስጥሮስ ምክንያት ሁለት መቶ ኤጲስቆጶሳት በኤፌሶን ከተማ በተሰበሰቡ ጊዜ ከእሳቸው ጋር ይህ ቅዱስ አለ። ከእርሳቸውም ጋር ንስጡርን አወገዘው ዳግመኛም በአንጾኪያ አገር ያሉ መኳንንት መሳፍንት ሹማምንት ሁሉም ይታዘዙለት ዘንድ ንጉሥ ደብዳቤን ጻፈለት እርሱም በጎ ሥራ እንዲሠሩ በሃይማኖት እንዲጸኑ የሚያዝዝ ደብዳቤ በመጻፍ በንጉሥ ኀቲም ቀለበት እያተመ ለሀገሮች ሁሉ የሚልክ ሆነ።
ክፋዎች ሰዎችም ጠሉት በንጉሥም ዘንድ ነገር ሠሩበት እንዲህም አሉት እነሆ አባ በርሱማ እንደ ዓለም ሰው ሁኖ ይበላል ይጠጣል መልካም ልብስንም ይለብሳል ንጉሥም ሰለ አባ በርሱማ የተነገረውን ያረጋግጥ ዘንድ ከባለሟሎቹ አንዱን ላከ።
የንጉሡም ባለሟል ወደ አባ በርሱማ በደረሰ ጊዜ በእርሱ ላይ ከተነገረው ምንም ምን ያገኘው የለም ከዚህም በኋላ ወደ ንጉሥ ወሰደው ንጉሥም ቀድሞ ከሚያውቀው ከመንፈሳዊ ሥራው ልውጥ ሆኖ ያገኘው ነገር የለም ንጉሡም ታላቅ ክብርን አከበረው ወደ ቦታውም መለሰው።
መናፍቁ ንጉሥ መርቅያንም የኬልቄዶንን ጉባኤ በሰበሰበ ጊዜ የንጉሥ አማካሪዎች አባ በርሱማን እንዳያስመጣ ንጉሡን መከሩት እንደማይፈራና እንደማያፍር ለሰው ፊትም እንደማያዳላ ተከራክሮ ረትቶ እንደሚያሳፍራቸውም ስለሚያውቁ ነው።
አንዱን ክርስቶስን ወደ ሁለት የከፋፈሉበት ይህ ጉባኤ በተፈጸመ ጊዜ የከበረ አባ በርሱማ ተጣላቸው ነቀፋቸው ቃላቸውንም በመሻር አወገዛቸው እነርሱም ወደ ንጉሥ ወንጅለው በጽሑፍ ከሰሱት ንጉሡም ልኮ ወደርሱ አስቀረበው ግን በላዩ ስለ አደረ መንፈስ ቅዱስ ጸጋ ሊቃወመው አልቻለም በሊቁ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ላይ ሰለ አደረገችው ክፋት ንግሥቲቱን ረገማት ከጥቂት ቀንም በቀር አልኖረችም በክፉ አሟሟትም ሞተች።
ከዚህም በኋላ መናፍቃን የሚቃወሙት ሆኑ ምእመናን እንዳይታዘዙለት ወደ ሀገሮች ሁሉ ጽፈው የሚልኩ ሆኑ እነርሱ ግን አልተቀበሏቸውም ለእርሱ መታዘዛቸውንም አልተዉም። ዳግመኛም በጐዳና ሸምቀው ይገድሉት ዘንድ ሁለት መቶ መናፍቃን ሰዎች ከመናፍቃን ኤጴስቆጶሳት ጋር ተስማምተው ወደ እርሳቸው እንዲመጣና በአንድነት ወደ ቤተ ክርስቲያን እንደሚሔዱ ሁነው ላኩበት መጥቶም አብሮ በተጓዘ ጊዜ ደንጊያዎችን አንሥተው ጣሉበት ደንጊያዎቻቸውም ወደ ራሳቸው የሚመለሱ ሆኑ በፍርሃትም ከእርሱ ሸሹ።
እግዚአብሔርም ከዚህ ዓለም እሥረኛነት ሊአወጣው በወደደ ጊዜ መልአኩን ወደርሱ ልኮ ከአራት ቀን በኋላ ከዓለም እንደሚፈልስ ነገረው በዚያንም ጊዜ በዙሪያው ወዳሉ አገሮች ምእመናንን ያጽናናቸው ዘንድ ረድኡን ላከው እርሱም ሲዞር የመጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ ራስ ወደምትኖርበት ቦታ ደረሰና የከበረች የቅዱስ ዮሐንስን ራስ እጅ ነሣት ስለ ከሀዲው ስለ ንጉሥ መርቅያን በማልቀስ ለመነ። እንዲህ የሚልም ቃል ከመጥምቁ ዮሐንስ ራስ ወጣ አባ በርሱማ ወደ እግዚአብሔር ስለ ከሰሰው ያ መርቅያን ሙቷልና አትፍራ። የከበረ አባ በርሱማ ረድኡን ባረከውና በሰላም አረፈ።
ከበአቱም ደጃፍ ከምድር እስከ ሰማይ የሚደርስ የብርሃን መሰሶ ተተክሎ ታየ። ምእመናንም ሁሉ ከሩቅ አይተው ወደርሱ መጡ አርፎም አገኙት። ከሥጋውም ተባረኩ በላዩም አለቀሱ ከእርሱም ስለመለየታቸው እጅግ አዘኑ እንደሚገባም አየዘመሩና እያመሰገኑ ገንዘው በመቃብር አኖሩት።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ጳውሎስ_ሶርያዊ
በዚህችም ዕለት የከበረ ሶርያዊ ጳውሎስ በሰማዕትነት ሞተ፡፡ የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ የሶርያ ሰዎችና በእስክንድርያ ከተማ የሚኖሩ ነጋዴዎች ናቸው ከዚህም በኋላ በእስሙናይን ከተማ የሚኖሩ ሆኑ።
ወላጆቹም ሲሞቱ ብዙ ገንዘብ ተዉለት ከዚህም በኋላ ከሀድያን ነገሥታትና መኳንንት በክርስቶስ የሚያምኑ ምእመናንን እንደሚያሠቃዩአቸውና እንደሚገድሏቸው ሰማ በዚያንም ጊዜ ተነሥቶ ገንዘቡን ሁሉ ለድኆችና ለችግረኞች በተነ። ከዚህም በኋላ የወደደውን መንገድ ይመራው ዘንድ ወደ ክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጸለየ ጌታችንም መልአኩን ሱርያልን ላከ እርሱም በክብር ባለቤት ክርስቶስ ስም የሚደርስበትን ሥቃይ ሁሉ ነገረው እነሆ ከአንተ ጋር እንድኖር እንዳጽናናህም እግዚአብሔር አዞኛልና አትፍራ አለው።
በዚያንም ጊዜ ተነሥቶ ወደ እንዴናው ከተማ ሔደ በመኰንኑም ፊት ቁሞ በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ መኰንኑም ልብሱን አራቁተው ይገርፉት ዘንድ አዘዘ።
ይህንንም አደረጉበት ከዚህም በኋላ በጐኖቹ ውስጥ መብራቶችን አስገብተው ለበለቡት እሳት ግን አልነካችውም መኰንኑም ለጣዖት እንዲሰግድ ብዙ ገንዘብ አመጣለት የተመሰገነ ጳውሎስም ወላጆቼ ሲሞቱ ዐሥራ ሰባት የወርቅ መክሊት ትተውልኝ ነበር። ስለ ክብር ባለቤት ክርስቶስ ፍቅር ትቼ ለድኆች መጸወትኩት ወደዚህ ወደተናቀ ገንዘብህ እንዴት እመለሳለሁ አለው።
መኰንኑም ሰምቶ ብረቶችን በእሳት አግለው በአፉና በጆሮዎቹ እንዲጨምሩ አዘዘ ይህንንም አደረጉበት ሱርያል መልአክም ወርዶ ዳሠሠውና አዳነው ሁለተኛም እባቦችን በላዩ ሰደዱ አልነኩትም ምላሱንም ቆረጡ ጌታችንም አዳነው።
መኰንኑም ወደ እስክንድርያ ከተማ በሚሔድ ጊዜ ከእርሱ ጋር ወሰደው የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በመርከብ ውስጥ ተገለጠለትና አጽናናው የዚህም ቅዱስ ኤሲ የሚባል ወዳጅ አለው እኅቱ ቴክላም። ጌታችንም ሥጋው ከሥጋቸው ነፍሱ ከነፍሳቸው ጋር እንደሚሆን ነገረው ያን ጊዜ እሊህ ቅዱሳን በእስክንድርያ ከተማ በእሥር ቤት ነበሩ የከበረ ጳውሎስም ወደርሳቸው በደረሰ ጊዜ እርስበርሳቸው ተሳሳሙ በመገናኘታቸውም ነፍሳቸው ደስ ብሏት እግዚአብሔርን አመሰገኑት።
መኰንኑም ወደ እንዴናው ከተማ በሚመለስ ጊዜ የቅዱስ ጳውሎስን ራስ ቆርጠው ሥጋውን ከጥልቅ ባሕር ወረወሩ የሰማዕትነትንም አክሊል በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ ምእመናንም ሥጋውን በሥውር ወስደው በአማሩ ልብሶች ገነዙት በእነርሱም ዘንድ አኖሩት ከእርሱም ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12
🔴#ስንክሳር የካቲት_9
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
የካቲት ዘጠኝ በዚህች ዕለት #የአቡነ_እስትንፋሰ_ክርስቶስ የመነኮሱበት በዓል ነው፣ የከበረ በሶርያ አገር ላሉ መነኰሳት አባት የሆነ ታላቁ #አባ_በርሱማ አረፈ፣ የከበረ #ቅዱስ_ጳውሎስ_ሶርያዊ በሰማዕትነት ሞተ፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አቡነ_እስትፋሰ_ክርስቶስ
የካቲት ዘጠኝ በዚህች ዕለት የአቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ የመነኮሱበት በዓል ነው፡፡ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ አባታቸው መልአከ ምክሩ እናታቸው ወለተ ማርያም ይባላሉ፡፡ የተወለዱበት ልዩ ቦታው ወሎ ክፍለ ሀገር ዳውንት ነው፡፡ በተወለዱ ዕለት ተነሥተው በእግራቸው ቆመው ሦስት ጊዜ ስብሐት ለአብ ስብሐት ለወልድ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ ብለው ፈጣሪያቸውን አመስግነዋል፡፡ የስማቸው ትርጓሜ የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ እስትንፋስ አንድም የክርስቶስ እስትንፋስ ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ሚካኤል እየጠበቃቸውና በመንገዳቸው ሁሉ እየመራቸው ነው ያደጉት፡፡ መንፈስ ቅዱስ ልቡናቸውን ብሩህ አድርጎላቸው በ5 ዓመታቸው የቅዱሳት መጻሕፍት ቃላትን፣ ብሉያትንና ሐዲሳትን፣ ድርሳናትንም ጠንቅቀው ዐውቀዋል፡፡
በተወለዱ በ14 ዓመታቸው ወደ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ደብረ ሐይቅ ገዳም ሄደው ከባሕር ዳር ቆመው የሙሴን ጸሎት ወደ እግዚአብሔር በጸለዩ ጊዜ የታዘዘ መልአክ መጥቶ ባሕሩን አሻግሯቸው ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብተዋል፡፡ ለ3 ዓመታት ያህል በኃይቅ ገዳም ለመነኮሳት እንጨት በመልቀምና ውሃን በመቅዳት ለአባቶች መነኮሳት ምግብ የሚሆናቸው ዓሣ ከባህር ውስጥ በማውጣት አገልግለዋል፡፡ አባታችን እስትንፋሰ ክርስቶስ 40 መዓልትና 40 ሌሊት ከጾሙ በኋላ ምንም እህል ሳይቀምሱ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አስቀድሞ ለሙሴ በደብረ ሲና እንደሰጠው ለአባታችንም ወደ እርሳቸው መጥቶ ዓሥሩን ቃላተ ኦሪትና ስድስቱን ቃላተ ወንጌል በውስጣቸው የተጻፈባቸው ሁለት ጽላቶችን ሰጥቷቸዋል፡፡ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ከሠሩ በኋላ ዕለቱን ስንዴ ዘርተው፣ ወይን ተክለው፣ ጽድን ወይራንና ግራርን ተክለው በአንዲት ቀን ለቤተክርስቲያን አገልግሎት ዕለቱን አድርሰዋል፡፡ ስንዴውን ለመሥዋዕት ወይኑን ለቍርባን በተአምራት አድርሰዋል፡፡
አባታችን በጸሎት ላይ እንዳሉ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ተልኮ መጥቶ አባታችንን በደመና ጭኖ ወስዶ ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ፊት አቆማቸው፡፡ ጌታንም በቅዱሳኑ ሁሉ እንዲባረኩ ካደረጋቸው በኋላ መልአኩን ‹‹ወደ ተወለድኩባትና ወደ ኖርኩባት ቦታ ወደ ኢየሩሳሌም አድርሰው›› ብሎት ኢየሩሳሌምን አሳልሞ ሀገራችን መልሶ አምጥቷቸዋል፡፡ አባታችን ሁሉንም የኢትዮጵያን ቅዱሳት ገዳማትን ተዘዋውሮ ሲጎበኙ በሕይወተ ሥጋ የሌሉት የየገዳማቱ ቅዱሳን ሁሉ በአካል ይገለጡላቸው ነበር፡፡ ጎጃም ውስጥ እያስተማሩ፣ እያጠመቁ፣ የታመሙትን እየፈወሱ፣ የዕውራንን ዐይን እያበሩና ሙታንን እያሥነሱ ብዙ ካገለገሉ በኋላ ለዘጠኝ ዓመታት በባሕር ውስጥ ገብተው ቁልቁል ተዘቅዝቀው ለኢትዮጵያ ጸልየው የምሕረት ቃልኪዳን ተቀብለዋል፡፡ ከዘጠኝ ዓመት በኋላ ጌታችን መጥቶ ‹‹ከመነኮሳት ሁሉ ብልጫ ያለህ ወዳጄ ሆይ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ምሬልሃለሁ ከዚህች ባሕር ውጣ›› በማለት በሞት የሚያርፉበትን ቦታ ነግሯቸዋል፡፡
ጻድቁ ወደ ደብረ አሰጋጅ በሚሄዱበት ጊዜ ጸሐይ ልትገባ ስትል ‹‹በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አውግዤሻለሁ ለመስፍን ኢያሱ በገባኦን እንደቆምሽ አሁንም ቀጥ ብለሽ ቁሚ›› ብለው ገዝተው ፀሐይን አቁመዋል፡፡ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስም ደብረ አሰጋጅ ሲደርሱ ፀሐይ አፍ አውጥታ ‹‹አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ሆይ እገባ ዘንድ ፍታኝ›› ስትላቸው ‹‹እግዚአብሔር ይፍታሽ›› ባሏት ጊዜ ጠልቃለች፡፡
ጻድቁ ሌላው በእጅጉ የሚታወቁበት አንድ ትልቅ ቃል ኪዳን አላቸው፡፡ በአምላክ ልቡና የሚገኝ፣ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ልቡና የሚገኝ፣ በቅዱስ ሚካኤልና በቅዱስ ገብርኤል ልቡና የሚገኝ እንደ መልክአ መድኃኔዓለም ያለች እጅግ አስገራሚ ጸሎት አለቻቸው፤ እርሷን ጸሎት በጸለዩ ጊዜ እልፍ ነፍሳትን ከሲኦል ያወጣሉ፡፡
ጸሎቷም የመድኃኔዓለምን የሰውነት ክፍሎች በሙሉ እየጠቀሰች እያንዳንዱ የሰውነት ክፍሎቹ የተቀበሉትን ጸዋትዎ መከራዎች ሁሉ ታዘክራለች፡፡ በእያንዳንዱ ክፍልም የጸሎት ማሳረጊያ አቡነ ዘበሰማያት ይደግማሉ፡፡ ንስሓ የገባ ኃጢአተኛ ሰው እንኳን ቢሆን ይህችን የአቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስን ጸሎት በጸለየ ጊዜ ሺህ ነፍሳትን ከሲኦል እንደሚያወጣ ጌታችን በማይታበል ቃሉ ለአባታችን ነግሯቸዋል፡፡ እያንዳንዱን የመድኃኔዓለምን የሰውነት ክፍሎች በሙሉ እየጠቀሰች መከራዎቹን የምታዘክረውን ይህቺን በአምላክ ልቡና ያለች ግሩም የሆነች ጸሎት ነፍሳትን ከሲኦል አታወጣም ብሎ የሚጠራጠር ቢኖር መንግስተ ሰማያትን አያያትም፡፡ ጻድቁ ታኅሣሥ 8 ቀን ተወልው ሚያዝያ 9 ቀን በታላቅ ክብር ዐርፈዋል በዚህች ዕለትም የምንኩስናቸው በዓል ይከበራል፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አባ_በርሱማ_ሶርያዊ
በዚህችም ቀን የከበረ በሶርያ አገር ላሉ መነኰሳት አባት የሆነ ታላቁ አባ በርሱማ አረፈ። የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ ሳሚሳጥ ከሚባል አገር ሰዎች ውስጥ ናቸው አንድ በዋሻ ውስጥ የሚኖር ሰው በእርሱ ላይ ትንቢትን ተናገረ ከመወለዱ አስቀድሞ ለአባቱ እንዲህ አለው የትሩፋቱ ዜና በሶርያ ሀገር ሁሉ የሚሰማ ጣዕም ያለው ፍሬ ከአንተ ይወጣል ከእርሱ የሚሆነውንም አስረዳው።
ተወልዶም አድጎ እግዚአብሔርን ወደ ማወቅ በደረሰ ጊዜ ከወላጆቹ ሸሽቶ ወደ ኤፍራጥስ ወንዝ ደርሶ በዚያ ስሙ አብርሃም ከሚባል ሰው ዘንድ ተቀመጠ እርሱም ወላጆቹን ስለፈራ ከዚያ ገዳም ሰደደውና ሒዶ በአለት ውስጥ ኖረ በዚያም ታላቅ ተጋድሎን ተጋደለ ወሬውም በሶርያ አገሮች ሁሉ በተሰማ ጊዜ ብዙዎች ደቀመዛሙርት ወደርሱ ተሰበሰቡ የዚያ ቦታ ውኃ ግን እጅግ መራራ ነበር በላዩ በጸለየ ጊዜ ተለውጦ ጣፋጭ ሆነ።
እግዚአብሔርም በእጆቹ ድንቆች ተአምራቶችን አደረገ ከእርሳቸውም በአንዲት ጊዜ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ከበአቱ ርቆ ሳለ የፀሐይ መግቢያ ሰዓት ተቃረበ የክብር ባለቤት ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን ለመነው ወደ በአቱም እስቲደርስ ያን ጊዜ ፀሐይን አቆመለት።
በሌላ ጊዜም እንዲህ ሆነ ረዓም የምትባል አገር ነበረች ስዎቿም ከሀዲዎች ናቸው። በላያቸውም ዝናብ ተከለከለ በተጨነቁም ጊዜ ወደ ከበረ አባ በርሱማ መጥተው ለመኑት እርሱም ገሠጻቸው እንዲህም አላቸው ከክህደታችሁ ተመልሳችሁ በእግዚአብሔር ብታምኑ እርሱ ብዙ ዝናብን ያዘንብላችኋል እነርሱም እናምንበታለን አሉት። በዚያን ጊዜ ጌታችንን ለመነውና ብዙ ዝናብ ዘነበላቸው የሀገር ሰዎችም ሁሉ በጌታችን አመኑ።
እንዲሁም ሰዎቿ ከሀድያን የሆኑ ሌላ ሀገር ነበረች እነርሱንም ገሥጾ መክሮ አስተምሮ እግዚአብሔርን ወደ ማወቅ መለሳቸው የጣዖቶቻቸውንም ቤቶች አፈረሰ። ይህም ቅዱስ ለራሱ ቦታ አዘጋጅቶ በዚያ ሳይቀመጥ ሃምሣ አራት ዓመት ቁሞ ኖረ ከመትጋት የተነሣ ሲደክመው ከናሱ ግድግዳ ላይ ተደግፎ ያሸልባል በየሰባት ቀንም ይጾማል።
የከበረ አባ ስምዖን ዘዓምድ ሊያየው ወዶ ወደርሱ ላከ የትሩፋቱንና የቅድስናውን ዜና ከብዙዎች ሰዎች ሰምቶ ነበርና እርሱም ወደ አባ ስምዖን መጥቶ እርስበርሳቸው በረከትን ተቀባበሉ ከዚህም በኋላ ወደ ገዳሙ ተመለሰ።
Watch "EOTC TV | የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ቀጥታ ሥርጭት ከመንበረ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት" on YouTube
https://www.youtube.com/live/wMgJaj5pn4o?feature=share
በዚህች ዕለት በትሩፋቱ ፍጹም የሆነ ታላቅ አረጋዊ የገዳመ ሲሐቱ ኤልያስ አረፈ። የሚያረጋጋው በትሩፋቱ ፍጹም የሆነ አረጋዊ መነኵሴ እንዲልኩለት በመለመን ጻድቁ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ ወደ ገዳመ ሲሐት በላከ ጊዜ ይህን በትሩፋቱ ፍጹም የሆነ ኤልያስን ላኩለት ስለርሱም እንዲህ ብለው ጻፉ "ንጉሥ ሆይ እነሆ በሥራው ኤልያስን የሚመስል ኤልያስ የሚባል ጻድቅ ሰው ልከንልሃል።"
ወደ ንጉሥም በደረሰ ጊዜ ንጉሥ እንዲህ አለው አንተ በገድልህ ነቢይ ኤልያስን እንደምትመስል መነኰሳቱ ስለአንተ ወደእኔ ልከዋል። አረጋዊውም በየውሀትና በትሕትና እንዲህ አለ ፦ "ጻድቅ ንጉሥ ሆይ ይቅርታ አድርግልኝ ሰው ሁሉ በጠባዩና በሥራው ይታወቃል የኤልያስም ገድሉ እንዲህ ነው ስለ ደግነቱ ምግቡን ቊራዎች ያመጡለት ነበር እኔ ግን ምግቤን በፀሐይ ውስጥ ባሰጣው ቊራ ይዞት ይሔዳል" ንጉሡም ሰምቶ ከቃሉ ጣዕም የተነሣ አደነቀ።
ዳግመኛም አባቴ ሆይ ለምን እግዚአብሔር ልጅ አልሰጠኝም አለው አረጋዊውም በምድር ላይ ሃይማኖት የሚከፋፈልበት ዘመን ይመጣል ከመናፍቃን ጋር አንድ እንዳይሆን ስለዚህ እግዚአብሔር ልጅን አልሰጠህም አለው።
ንጉሡም ብዙ ገንዘብን ሊሰጠው ወደደ እርሱ ግን አልተቀበለም። ወደ በአቱም እስከተመለሰ ድረስ እህል እንዳልቀመሰ ስለርሱ ተነገረ በሰላምም አረፈ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12
🔴#ስንክሳር የካቲት_8
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
የካቲት ስምንት በዚህች ዕለት #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ ከከበረ ልደቱ ከአርባ ቀኖች በኋላ ወደቤተ መቅደስ የገባበት ሆነ፣ የከበረች እመቤት #አመተ_ክርስቶስ አረፈች፣ ከአሴር ወገን የሆነች የፋኑኤል ልጅ #ነቢዪት_ሐና አረፈች፣ በትሩፋቱ ፍጹም የሆነ ታላቅ አረጋዊ የገዳመ ሲሐቱ #ቅዱስ_ኤልያስ አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ስምዖን_አረጋዊ
የካቲት ስምንት በዚህች ዕለት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከከበረ ልደቱ ከአርባ ቀኖች በኋላ ወደቤተ መቅደስ የገባበት ሆነ።
ለዚህ ምሥጢር አገልጋይ የሆነ ጻድቁ ዮሴፍና የወለደችው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የክብር ባለቤት እርሱ በእስራኤል ሕዝብ ላይ የሠራውን ሕግ ይፈጽሙ ዘንድ መሥዋዕትም ሊአቀርቡ መጡ። ጻድቅ ሰው ስሞዖን ካህንም ሕፃኑን ተቀብሎ አቀፈው።
እንዲህም ሆነ አባታችን አዳም ከተፈጠረ በአምስት ሽህ ሁለት መቶ ዓመት አሸናፊ የተባለ በጥሊሞስ በነገሠ ጊዜ የአይሁድ ወገኖች ከሥልጣኑ በታች ነበሩ። ወደ ኢየሩሳሌምም ልኮ ከሊቃውንቶቻቸው፡ ከአዋቂዎች መምህራኖቻቸው ሰብዓ ሰዎችን መርጦ ወደርሱ ወሰዳቸው የኦሪትንም መጻሕፍት ከዕብራይስጥ ቋንቋ ወደ ጽርዕ ቋንቋ የተረጕሙ ዘንድ አዘዛቸው። ይህም የሆነ በእግዚአብሔር ፈቃድ ነው ከአይሁድ ሕጉና ሥርዓቱ እንደሚፈልስና በዓለም ሁሉ ላሉ ለክርስቲያን ወገን ይሆን ዘንድ አለውና።
ዳግመኛም ሁለት ሁለት እያደረጉ እንዲለዩአቸው አዘዘ እነርሱ ሰባ ሁለት ስለሆኑ ሠላሳ ስድስት ድንኳን አዘጋጅቶ በዚያ ሁለት ሁለቱን አኖራቸው ተገናኝተው በመስማማት የሚጽፉትን የሕጉን ቃል እንዳይለውጡ በላያቸው ጠባቂዎችን አኖረ። እነርሱ በተንኰል ሥራ የታወቁ ናቸውና።
ለዚህም ለስሞዖን ይተረጒም ዘንድ የነቢዩ ኢሳይያስ መጽሐፍ ደረሰውና እነሆ ድንግል ትፀንሳለች ወንድ ልጅንም ትወልዳለች ስሙንም ዐማኑኤል ትለዋለች ከሚለው ደረሰ። ይህንንም ቃል ይጽፍ ዘንድ ፈራ ይህ እንዴት ይሆናል ብሎ ንጉሥ እንደሚዘብትበት ቃሉንም እንደማይቀበለው አስቧልና እርሱ ራሱም እንዴት ሊሆን ይችላል ብሎ ተጠራጠረ። ይህንንም ሲያስብ እንቅልፍ መጣበትና አንቀላፋ የእግዚአብሔርም መልአክ ተገልጦ የተጠራጠርከውን ከድንግል የሚወለደውን እስከምታየውና እስከምትታቀፈው ሞትን አትቀምስም አለው ከዚህም በኋላ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እስከተወለደና በዚች ዕለት ወደ ቤተ መቅደስ እስከ አስገቡት ድረስ ስምዖን ሦስት መቶ ዓመት ኖረ ሕፃኑን ጌታችንንም በታቀፈው ጊዜ ታውረው የነበሩ ዓይኖቹ ተገለጡ ሁለመናውም ሐዲስ ሆነ መንፈስ ቅዱስም የምትጠብቀው የነበረ ሕፃን ይህ ነው ብሎ ነግሮታልና።
እግዚአብሔርንም አመሰገነው። እንዲህም አለ ባርያህን በሰላም አሰናብተው በአንተ ምክንያት በዚህ በኃላፊው ዓለም ሕይወት ታሥሬ ኑሬአለሁና እነሆ አሁን መጥተህ አየሁህ ወደ ዘላለም ሕይወት እሔድ ዘንድ አሰናብተኝ ዓይኖቼ ትድግናህን አይተዋልና። በወገኖችህ ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸውን ለአሕዛብ ብርሃንን ለወገኖችህ እስራኤልም ክብርን ትገልጥ ዘንድ።
እመቤታችንን እናቱ ድንግል ማርያምንም እንዲህ አላት ይህ ልጅሽ ከእስራኤል ውስጥ ለብዙዎች ለመውደቃቸውና ለመነሣታቸው በሚፈረድባቸውም ገንዘብ ለምልክት የተዘጋጀ ነው።
ዳግመኛም በመከራው ጊዜ በልቧ የሚያድርባትን ኅዘን አስረዳት እንዲህም አላት በአንቺ ግን በልብሽ የሚከፋፍል ፍላፃ ይገባል ከዚህም በኋላ በሰላም አረፈ። በዚያም የከበረ ወንጌል ያወሳት የፋኑኤል ልጅ ነቢዪት ሐና ነበረች እርሷም ስለርሱ ትንቢት ተናገረች እግዚአብሔርን እያመሰገነች እርሱ ከሰይጣን ባርነት የሚያድናቸው መድኃኒት እንደሆነ ነገረቻቸው።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅድስት_ሐና_ነቢዪት
በዚህም ዕለት ከአሴር ወገን የሆነች የፋኑኤል ልጅ ነቢዪት ሐና አረፈች፡፡ የእርሷም ዘመኗ አልፎ ነበር በድንግልና ከኖረች በኋላ ከባሏ ጋር ሰባት ዓመት ኖረች። ሰማንያ አራት ዓመት ፈት ሁና ኖረች በጾምና በጸሎትም እያገለገለች ቀንም ሌትም ከምኲራብ አትወጣም ነበር።
ጌታችን ኢየሱስን ከተወለደ በኋላ በአርባ ቀን ወደ ቤተ መቅደስ በአስገቡት ጊዜ በዚያን ሰዓት ተነሥታ አመነች እግዚአብሔርንም አመሰገነችው። የኢየሩሳሌምን ድኅነት ተስፋ ለሚያደርጉ ሁሉ ስለርሱ ነገረች። ከዚህም በኋላ በሰላም አረፈች።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅድስት_አመተ_ክርስቶስ
በዚህችም ቀን የከበረች እመቤት አመተ ክርስቶስ አረፈች ሁለቱም አገልጋዮቿ። ይችም ቅድስት ከቍስጥንጥንያ አገር ሰዎች ውስጥ ናት ከንጉሥ መሳፍንቶችም ባል ነበራት እርሱም በጐልማሳነቱ ሙቶ ዕድሜዋ ዐሥራ ሁለት ዓመት ሲሆናት ፈት አረጋት።
ከጥቂትም ቀን በኋላ ከመንግሥት ታላላቆች ከሆኑት ውስጥ አንድ ሰው በኃይል ወስዶ ሊአገባት ፈለገ እርሷም ጽኑ ደዌ አለብኝ እስከምድን ጠብቀኝ አለችውና ከዚህ በኋላ ገንዘቧን ሁሉ ለድኆችና ለችግረኞች በተነች ወንዶችና ሴቶች ባሮቿን ነጻ አወጣች ሁለት ሴቶች ባሮቿንም ከእርሷ ጋር ይዛ ማንም ሳያያት በሌሊት ወጣች ከኰረብታ በታች ጥልቅ ከሆነ ቦታ ውስጥ ወዳለ ዋሻ ገብታ በዚያ ዐሥራ አንድ ዓመት ኖረች በየዕለቱም ከዕፀዋት ፍሬ አዕዋፍ እያመጡላት ከአገልጋዮቿ ጋር ትመገባለች።
ከዚህም በኋላ በንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ዘመን ከጸሐፊዎች አንዱ እንዲህ አለ ግብር እሰበስብ ዘንድ ወደ ምሥራቅ አቅጣጫ ሔድኩ ወደ አንድ ገዳምም ደረስኩ መነኰሳቱና አበ ምኔቱም ተቀበሉኝ እርስበርሳችንም እጅ ተነሣሥተን ተቀመጥን ከዚያ በየአይነቱ ፍሬ ያላቸው ዛፎች አሉ አዕዋፍም ቅርንጫፉን ከፍሬው ጋር እየቆረጡ ይበራሉ እነርሱ ራሳቸው አይበሉም።
እኔም አይቼ አደነቅሁ መነኰሳቱንም ይህ ሥራ ምንድን ነው አልኳቸው እነርሱም እንዲህ ሲያደርጉ ዐሥራ አንድ ዓመት ነው የሚሆነውን ግን አናውቅም አሉኝ እኔስ በተራራ ውስጥ ለሚኖር መነኰሳት የሚወስዱ ይመስለኛል አልኳቸው።
ይህንንም ስናገር ቊራ መጥቶ ቅርንጫፍን ቆርጦ ከፍሬው ጋር ይዞ በረረ ሥራውን አውቅ ዘንድ ከአበ ምኔቱ ጋር ተከተልኩት የሚገባበትንም አየን ወደዚያም ቦታ ደርሰን ደንጋይ ጣልን ክርስቲያኖች ከሆናችሁ አትግደሉን የሚል ቃልን ሰማን እናንተ ከወዴት ናችሁ አልናቸው እኛን ለማየት ከፈለጋችሁ ራቁታችንን ስለሆን ሦስት ልብሶችን ጣሉልን አሉን እኛም ልብሶችን ጣልንላቸውና ወደርሳቸው ጭንቅ በሆነች መንገድ ወረድን በደረስንም ጊዜ ተቀበሉን እርስበርሳችንም እጅ ተነሣሥተን አንዲቱ ከእኛ ጋር ተቀመጠች ሁለቱ ግን በፊቷ ቆሙ።
አበ ምኔቱም እናቴና እመቤቴ ሆይ ከወዴት ነሽ ወደዚህስ አወጣጥሽ እንዴት ነው አላት እርሷም ሥራዋን ሁሉ ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው ነገረችው አበ ምኔቱም የምትፈቅጂ ከሆነ ከገዳም ምግብ እናምጣላችሁና ከእናንተ ጋር በአንድነት እንመገብ አላት። እርሷም ወደዚህ ከመጣን ቅዱስ ቁርባንን አልተቀበልንምና የክርስቶስን ሥጋና ደም አምጥቶ እንዲአቀብለን ቄስን እዘዝልን አለችው።
አበ ምኔቱም ቄስን አዘዘላቸውና አቈረባቸው በማግሥቱም አመተ ክርስቶስ ረጅም ጸሎትን ጸለየችና አረፈች አገልጋዮቿም ተከታትለው አረፉ በዝማሬና በማኅሌት ገንዘው በክብር ቀበሩአቸው።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አረጋዊ_ኤልያስ
ይህም አባት ቴዎድሮስ በገድል የተጠመደ ሆነ መልኩም የሚያምር ነው በሰውነቱም ላይ ከውስጥ ማቅ በመልበስ በላዩ የብረት ልብስ መንቈር ይለብስ ነበር በቅንነቱና በትሕትናው ፍጹም ሆነ። በመንፈስ ቅዱስም ፈቃድ ተመርጦ በእስክንድርያ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ተሾመ። የክርስቶስንም መንጋዎች በበጎ አጠባበቅ ጠበቀ ሁልጊዜ መጻሕፍትን በማንበብ ያስተምራቸው ነበር ይልቁንም በሰንበትና በበዓላት ቀን።
የሹመቱም ዘመን ጸጥታና ሰላም ነበረ ቤተ ክርስቲያንም በሰላም ኖረች በወንጌላዊ ማርቆስ ወንበርም ላይ ዐሥራ አንድ ዓመት ተኩል ከኖረ በኋላ በሰላም አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አባ_አብዱልማዎስ_ገዳማዊ
ዳግመኛም በዚህች ቀን ገዳማዊው ጻድቁ አብዱልማዎስ አረፉ። ጻድቁ ግብጻዊ ሲሆኑ በበርሃ ሰው ሳያዩ ለ70 ዓመታት በቅድስና ኑረዋል:: በጊዜውም እግዚአብሔር አባ አብዱልማዎስን ወደ አባ ዕብሎይ ልኳቸው ነበር:: ሁለቱ ተገናኝተው አብረው ለ3 ቀናት ሲቆዩ ቅዱስ መልአክ እየተገለጸ አጽናንቷቸዋል:: ከሥውራን ማኅበርም ተቀላቅለው ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀብለዋል::
አባ ዕብሎይ ሲያርፍ አንበሶች እያገዟቸው ቀብረዋቸዋል:: እርሳቸውም "እኔን የሚቀብረኝ ስጠኝ" ብለው ጸልየው ነበርና 3 ገዳማውያን መጥተውላቸዋል:: የካቲት 5 ቀን አባ ዕብሎይን ገንዘው ቀብረው በ3ኛው ቀን አርፈዋል::
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12
🔴#ስንክሳር የካቲት_7
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
የእስክንድርያ ሀገር አርባ ሦስተኛ ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት #ቅዱስ_እለእስክንድሮስ አረፈ፣ የእስክንድርያ አርባ አምስተኛ ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት #ቅዱስ_ቴዎድሮስ አረፈ፣ ገዳማዊው ግብጻዊ ጻድቅ አብዱልማዎስ አረፉ፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አባ_እለ_እስክንድሮስ_ሊቀ_ዻዻሳት
የካቲት ሰባት በዚህች ቀን የእስክንድርያ ሀገር ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት እለእስክንድሮስ አረፈ፡፡ እርሱም ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት አርባ ሦስተኛ ነው። ይህም አባት ታሮን በሚባል ገዳም መነኰሰ ትርጓሜውም የአባቶች ገዳም ማለት ነው በጌታችንም ፈቃድ በእስክንድርያ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ተሾመ እርሱ የተማረ አዋቂ ጻድቅ ሰው ነበረና።
በሹመቱ ወራትም ብዙ መከራ ደረሰበት የግብጽ ንጉሥ ልጁን ሹሞ በመንግሥቱ ላይ አሠለጠነው እርሱም በአስቄጥስ በረሀ ያለውን የመነኰሳቱን ገዳማት አፈረሳቸው። ከክፋቱና ከክህደቱ ብዛት የተነሣ ከምስር በስተሰሜን ወዳለች ገዳም ገብቶ በዚያ አምላክን የወለደች የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን ሥዕሏን አየና ይች ምንድን ናት አለ እርሷም በሽልማት ሁሉ የተሸለመችና ያጌጠች ናት በልብሶቿም ላይ ያማረ የሐር ልብስ ነበረ ስዎችም የክርስቶስ እናት የሆነች የእመቤታችን የድንግል ማርያም ሥዕል ናት አሉት እርሱም ተሳድቦ የረከሰ ምራቁን በፊቷ ላይ ተፍቶ ደኅና ከሆንኩ ክርስቲያኖችን ፈጽሜ አጠፋቸዋለሁ አለ ዳግመኛም በክብር ባለቤት በጌታችን ክርስቶስ ላይ የስድብ ቃልን ተናገረ።
ሌሊትም በሆነ ጊዜ የሚያስፈራና የሚያስደነግጥ ታላቅ ራእይን አየ በነጋም ጊዜ ለአባቱ እንዲህ ብሎ ነገረው ዛሬ በዚች ሌሊት ታላቅ መከራና ብዙ ቅጣት ደረሰብኝ ታላቅ ዙፋንንም አየሁ በላዩ የተቀመጠበት ሰው እጅግ የሚያስፈራ የሚያስደነግጥ ነው ፊቱም ከፀሐይ ይበራል የብዙ ብዙ የሆኑ ሠራዊት የጦር መሣሪያ ይዘው በዙሪያው ቁመው ነበር እኔና አንተም እሥረኞች ሁነን በኋላው ቁመን ነበር እኔም በዙፋን ላይ የተቀመጠው ማነው ብዬ ጠየቅሁ ትላንት አንተ የዘበትክበት የክርስቲያን ንጉሥ ክርስቶስ ይህ ነው አሉኝ ከዚህም በኋላ የጦር መሣሪያ ከተሸከሙት አንዱ ወደ እኔ መጥቶ ጐኔን በጦር ወጋኝ ጦሩንም ከጐኔ ውስጥ አላወጣውም።
አባቱም ሰምቶ ደነገጠ እጅግም አዘነ ያ ልጁም ወዲያውኑ ታመመ አንደበቱም ተዘግቶ በክፉ አሟሟት ሞተ። ዳግመኛም ከአርባ ቀን በኋላ አባቱ ሞተ። በርሱም ፈንታ ሌላ ንጉሥ ተሾመ እርሱም ክርስቲያኖችን እጅግ አሠቃያቸው ይህንንም አባት ሊቀ ጳጳሳት እለእስክንድሮስን አብዝቶ አሠቃየው ከሕዝቡ ሦስት ሺህ የወርቅ ዲናር ለምኖ እስከ ሰጠው ድረስ ጌታችንም ይህን ንጉሥ ፈጥኖ አጠፋው።
ከዚህም በኋላ አሁንም ሌላ ንጉሥ ተሾመ እርሱም ሊቀ ጳጳሳቱን ይዞ እንደ ቀድሞው ሦስት ሺህ የወርቅ ዲናር እንዲሰጠው ፈለገ እርሱም ከወገኖቼ እስከምለምን ታገሠኝ ብሎ ማለደው ንጉሡም ቀጠሮ ሰጠውና ይለምን ዘንድ ወደ ላይኛው ግብጽ ወጣ።
በተራራ ላይ አንድ ገዳማዊ ሰው ነበር ከእርሱም ጋር ሁለት ደቀ መዛሙርት አሉ በተራራውም በአንድ ቦታ እንዲቆፍሩና እንዲጠርጉ አዘዛቸው ወርቅን የተመላ አምስት ማሰሮ አገኙ አንዱን ሸሽገው አራቱን ወደ ገዳማዊ መምህራቸው አመጡ እርሱም ይረዳበት ዘንድ እንዲስጡት ወደ ሊቀ ጳጳሳቱ ላካቸው። እነርሱ ግን እነዚያን የወርቅ ማሰሮዎች ይዘው ተመልሰው ወደ ዓለም ገቡ የምንኵስና ልብሳቸውንም ጥለው ሚስት አገቡ በዚያም ወርቅ ወንዶችና ሴቶች ባሮችን እንስሳትንም ገዙ።
የዚያችም አገር አስተዳዳሪ ያዛቸው ገንዘብንም ከወዴት እንዳገኙ በመግረፍ መረመራቸው እነርሱም አምስት የወርቅ ማሰሮዎችን እንዳገኙ አመኑ መኰንኑም ለንጉሥ የጭፍራ አለቃ አሳልፎ ሰጣቸው እርሱም ወደ ንጉሥ አቀረባቸውና አምስት የወርቅ ማሰሮ እንዳገኙ አስረዳው ንጉሡም ጭፍሮቹን ልኮ የሊቀ ጳጳሳቱን ቤት በረበረ የአብያተ ክርስቲያናት ከሆነ ከንዋየ ቅድሳት ያገኘውን ሁሉ ወሰደ ሊቀ ጳጳሳቱንም አሠረውና ወርቅን የተመሉ አራቱን ማሰሮዎች ደግሞም ሦስቱን ሽህ የወርቅ ዲናር አምጣልኝ አለው እርሱም ከዚህ ከኃላፊው ዓለም ገንዘብ ምንም ምን የለኝም አለው ወደ ሕዝቡ ልኮ ሦስቱን ሽህ የወርቅ ዲናር አምጥተውለት እስከ ሰጠው ድረስ አልተወውም ይህንንም ክፉ ንጉሥ ጌታችን አጠፉው።
ከዚህም በኋላ ከእርሱ የከፋ ሌላ ንጉሥ ተሾመ እርሱም የሐሰተኛውንና የርኵሱን ነቢይ ስም በከበረ መስቀል ፈንታ በእጆቻቸው ውስጥ እንዲአትሙ የክርስቲያንን ወገኖች አስገደዳቸው። ይችም ምልክት የመለኮትን ነገር የሚናገር ወንጌላዊ ዮሐንስ የተናገራት ትንቢት ናት ይህም ክፋ ንጉሥ ወደ ሀገሮች ሁሉ ይህን እንዲአደርጉ አዘዛቸው ሊቀ ጳጳሳቱንም እንዲሁ ያደርግ ዘንድ አዘዘው።
ሊቀ ጳጳሳትም ይተወው ዘንድ ብዙ ለመነው አልተቀበለውም ዳግመኛም እስከ ሦስት ቀን ይታገሠው ዘንድ ለመነው ከዚህም በኋላ ደግሞ እንዳይጥለውና ወደዚህ ወደረከሰ ሥራ እንዳያስገባው ወደ እግዚአብሔር ፈጽሞ ማለደ ጌታችንም ልመናውን ተቀብሎ በጥቂት ደዌ ጐበኘው ወደ ቤቱ እስክንድርያ ይሔድ ዘንድ እንዲአዝዝለት ንጉሡን ለመነው።
ንጉሡም ከለከለው ሰለ እጅ ኀትመት ምክንያት ለመፍጠር ሰለ መሰለው የእግዚአብሔርም መልአክ ተገለጠለትና ነገ ታርፋለህ አለው እርሱም አርድእቱን እግዚአብሔር ነገ ስለሚጐበኘኝ አርፋለሁና መርከብን አዘጋጁ አላቸው። አንዳለውም በማግሥቱ አረፈ ሥጋውንም በመርከብ ተሸክመው ወስደው ከአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሥጋ ጋር ቀበሩት።
በዚህም አባት አለእስክንድሮስ ዘመን በግብጽ አገር ለሚኖሩ መለካውያን ስሙ አንስጣስዮስ የሚባል ሊቀ ጳጳሳት ነበራቸው ያዕቆባውያን ምእመናንን ይወዳቸዋል ስለዚህም ወገኖቹ መለካውያን ተጣሉት። እርሱም ነፍሱን ያድን ዘንድ አስቦ ወደዚህ አባት አለእስክንድሮስ መጥቶ ከሥልጣኑ በታች በመሆን የሚታዘዝ ሆነ እለእስክንድሮስም አንስጣስዮስን በእርሱ ፈንታ የሊቀ ጵጵስናውን ሥልጣን ይዞ መንጋውን ይመራ ዘንድ እርሱ ግን ከመነኰሳት እንዳንዱ ሁኖ በገዳም ይኖር ዘንድ እንዲተወው ለመነው።
አባ አንስጣስዮስም አልወደደም እንዲህም አለ ይህን የምሻ ከሆነ አኔ እስከ ዛሬ ሊቀ ጳጳሳት አልነበርኩምን ላንተ ደቀ መዝሙርህ ሁኜ ላገለግልህ ወደድኩ እንጂ አለ። በመካከላቸው ከተደረገው ከብዙ ልመና ከብዙ ምልልስም በኋላ ኤጲስቆጶስ ይሆን ዘንድ አንስጣስዮስ ፈቀደ በአንዲትም ሀገር ላይ ኤጲስቆጶስነትን ሾመው። መንጋውንም እንደሚገባ በጎ አጠባበቅን ጠበቀ፡፡ አባት እለእስክንድሮስም በወንጌላዊ ማርቆስ ወንበር የኖረው ሃያ አራት ዓመት ከስድስት ወር ነው እግዚአብሔርንም አገለገለው።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ሊቀ_ጳጳሳት_ቴዎድሮስ
በዚህችም ዕለት የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት ቴዎድሮስ አረፈ እርሱም ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት አርባ አምስተኛ ነው። ይህም አባት መርዩጥ በሚባል አገር በአንድ ገዳም ውስጥ መነኰሰ የዚያም ገዳም ስም ጠንቡራ ነው። ለአንድ ፍጹም ጻድቅ የሆነ ሽማግሌ ሰው ደቀ መዝሙሩ ሆነ። እርሱም ልጁ ቴዎድሮስ በእስክንድርያ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና እንደሚሾም በመንፈስ ቅዱስ አይቶ ይህንን ለመነኰሳቱ ነገራቸው።
ይህም አባት ቴዎድሮስ በገድል የተጠመደ ሆነ መልኩም የሚያምር ነው በሰውነቱም ላይ ከውስጥ ማቅ በመልበስ በላዩ የብረት ልብስ መንቈር ይለብስ ነበር በቅንነቱና በትሕትናው ፍጹም ሆነ። በመንፈስ ቅዱስም ፈቃድ ተመርጦ በእስክንድርያ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ተሾመ። የክርስቶስንም መንጋዎች በበጎ አጠባበቅ ጠበቀ ሁልጊዜ መጻሕፍትን በማንበብ ያስተምራቸው ነበር ይልቁንም በሰንበትና በበዓላት ቀን።
የሹመቱም ዘመን ጸጥታና ሰላም ነበረ ቤተ ክርስቲያንም በሰላም ኖረች በወንጌላዊ ማርቆስ ወንበርም ላይ ዐሥራ አንድ ዓመት ተኩል ከኖረ በኋላ በሰላም አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አባ_አብዱልማዎስ_ገዳማዊ
ዳግመኛም በዚህች ቀን ገዳማዊው ጻድቁ አብዱልማዎስ አረፉ። ጻድቁ ግብጻዊ ሲሆኑ በበርሃ ሰው ሳያዩ ለ70 ዓመታት በቅድስና ኑረዋል:: በጊዜውም እግዚአብሔር አባ አብዱልማዎስን ወደ አባ ዕብሎይ ልኳቸው ነበር:: ሁለቱ ተገናኝተው አብረው ለ3 ቀናት ሲቆዩ ቅዱስ መልአክ እየተገለጸ አጽናንቷቸዋል:: ከሥውራን ማኅበርም ተቀላቅለው ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀብለዋል::
አባ ዕብሎይ ሲያርፍ አንበሶች እያገዟቸው ቀብረዋቸዋል:: እርሳቸውም "እኔን የሚቀብረኝ ስጠኝ" ብለው ጸልየው ነበርና 3 ገዳማውያን መጥተውላቸዋል:: የካቲት 5 ቀን አባ ዕብሎይን ገንዘው ቀብረው በ3ኛው ቀን አርፈዋል::
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
