fa
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

رفتن به کانال در Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

نمایش بیشتر
2 642
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
+5130 روز
آرشیو پست ها
​​ውድ አባሎቻችን የተላለፈው ውሳኔ ይህንን ይመስላል። በጸሎት እንተሳሰብ

​​#መጋቢት 20 የማይቀርበት ጉባኤ በአንዲት ቅድስት ቤተክርስቲያን እናምናለን

​​#ዜና እረፍት የደብራችን አንጋፋና ታላቅ አገልጋይ አባት የነበሩት አባ ገ/ሥላሴ ተገኝ ለረጅም ጊዜ  ባደረባቸው ህመም ምክንያት በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ የካቲት 27 ቀን 2012 ከዚህ ዓለም ያረፉ መሆናቸውን እንገልጻለን ። ሥርዓተ ቀበራቸውም ዛሬ ከቀኑ በ8:00 ሰዓት ከቅዳሴ በኋ!ላ በጽ/ጽ/ሐ/ ጎላ ቅዱስ ሚካኤ ል ቤ/ክ የሚፈጸም በመሆኑ በቀብሩ ላይ መገኘት የምትችሉ አባላት የሰ/ት/ቤቱን የአገልግሎት ልብስ/ዩኒፎርም በመልበስ እንድናገለግል ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። አባታችን በረከታቸው ይደርብን።

#የካቲት 24 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1.ቅዱስ አጋቢጦስ (ጻድቅ ኤዺስቆዾስ) 2.ቅዱስ ጢሞቴዎስ ሰማዕት (ዘጋዛ) 3.ቅዱስ ሚናስ ዘቆዽሮስ #ወርኀዊ በዓላት 1.ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት (መምሕረ ትሩፋት) 2.ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ 3.ቅዱስ ሙሴ ፀሊም 4.ቅዱስ ቶማስ ዘመርዐስ 5.ቅዱስ አብላርዮስ ታላቁ 6."24ቱ" ካኅናተ ሰማይ (ሱራፌል)

​​+++++የካቲት 23 ወረብ+++++ አይ ይእቲ ዛቲ መድኃኒት ኢትዮጵያ እንተ ኃሠሥዋ ወዖድዋ ነቢያት ወይቤሎ ጊዮርጊስ አመ አይኅ ለምኒልክ ግበር ታቦተ በዘትድኅን #ትርጉም፡- ይቺ መድኃኒት ኢትዮጵያ እንዴት ያለች ናት ነቢያት ፈልገው የዞሩባት፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ምኒልክን ከጥፋት ትድን ዘንድ ታቦትን ሥራ አለው

​​አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የካቲት አሥራ ሁለት ቀን በዚህች ዕለት የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤል በዓል መታሰቢያ ነው፡፡ በዚህች ቀን ክብር ምስጋና ይግባውና እግዚአብሔር የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልን የረዓይት ወገን ወደሚሆን ወደ ሶምሶን ልኮታልና፤ ሊገድሉት የፈለጉትን የፍልስጥኤምን ሰዎች ድል እስኪያደርጋቸው ድረስ ረድቶታልና በእነሱ ላይ እግዚአብሔር ኃይል ሰጥቶት አጠፋቸው ከእነሱ በአንዲት ቀን በአህያ መንጋጋ ሺህ ሰው ገደለ፡፡ ውሃ ጠምቶት ሊሞት በደረሰ ጊዜም የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ታይቶ አፀናው ከአህያ መንጋጋ አጥንትም ውሃ አወጣለት ጠጥቶም ከውሃ ጥም ዳነ የፍልስጥኤም ሰዎች ድል በሆኑ ጊዜ ከሚስቱ ጋር ተማክረው ዓይኑን አጥፍተው ወደ ጣዖታቸው ቤት ወሰዱት፡፡ የእግዚአብሔር መልእክተኛ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ታየው ተነጋገረው ኃይልንም ሰጠውና ሁሉንም አጠፋቸው፡፡ ስለዚህ ነገር የቤተክርስቲያን መምህራን በየወሩ በአሥራ ሁለት ቀን የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤልን በዓል መታሰቢያ እናደርግ ዘንድ አዝዘውናል፡፡ ++++++++++++++++++ ሰላም ለዝክረ ስምከ፡፡ ሚካኤል ሆይ የያሬድ ልጅ ሄኖክ እንደጻፈው ከልዑል ስም አጠራር ጋር ለተባበረ ስም አጠራርህ ሰላም እላለሁ፡፡ የእግዚአብሔር የምክሩ አበጋዝ ሆይ የተቸገሩትን የተጨነቁትን ዘወትር እንደምትረዳቸው ሁሉ እኔንም ለመርዳት ክንፍህን ዘርግተህ ፈጥነህ ድረስልኝ፡፡