የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
رفتن به کانال در Telegram
2 616
مشترکین
+724 ساعت
+207 روز
+3530 روز
آرشیو پست ها
በዓለ ጰራቅሊጦስ በደብራችን ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ዋለ።
" ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ ኃይልን ትቀበላላችሁ፥ በኢየሩሳሌምም በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም እስከ ምድር ዳርም ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ" የሐዋ. ሥራ 1፥8
ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተነሳ በሃምሳኛው ባረገ በአስረኛው ቀን ደቀመዛሙርቱ በተዘጋ ቤት ሳሉ መንፈስቅዱስ በተከፋፈሉ የእሳት ላንቃዎች ደቀመዛሙርቱ ላይ የወረደበትና ኅይለ መንፈስቅዱስ የተገለጸበት የቤተክርስቲያን የልደት ቀን በዛሬው እለት ግንቦት 30/2017 ዓ.ም በደብራችን ታቦተ ሕጉ ወጥቶ በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ዋለ።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
+6
''ሥርዓተ ማኅሌት ዘበዓለ ጰራቅሊጦስ''
በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ
ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
+2
''ሥርዓተ ማኅሌት ዘበዓለ ጰራቅሊጦስ''
በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ
ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
የጎፋ መካነ ሕያዋን ሰንበት ት/ቤት ለመቄዶንያ ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ አደረገ !
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል ሰንበት ት/ቤት በርቀት ከሚያስተምራቸው ተማሪዎች ያሰባሰበውን አንድ ሚሊየን አንድ መቶ ሰባ ሺህ ብር በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ቡራኬ ለመቄዶንያ መሥራች ለክቡር ዶክተር ብኒያም አስረክበዋል፡፡
በኢትዮጵያ ከሚገኙ አገር በቀል ተቋማት መካከል በግንባር ቀደምነት የሚጠቀሰው መቄዶኒያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ሕሙማን መርጃ ማዕከል ከተቋቋመ ስምንት ዓመታትን ባስቆጠረው በመቄዶኒያ ከ8,000 በላይ በተለያየ ዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ ተረጂዎች ይገኙበታል፡፡
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ባስተላለፉት አባታዊ መልእክት “መቄዶንያ ለተቸገሩ ሰዎች የሚረዳ ትልቅ ተቋም ነው፡፡ መንግሥትም የማይችለውን ነው መቄዶንያ የያዘው፤ ለዚህ ተቋም ርዳታ የሚያደርጉ ሁሉ በእግዚአብሔር ዘንድ ትልቅ ዋጋ ያገኛሉ፡፡ ሀብታቸውም ይባረክላቸዋል፡፡ እስከ አሁንም ርዳታ ላደረጉት ሁሉ ምስጋና ይገባቸዋል፡፡” ብለዋል፡፡ ቅዱስነታቸው አያይዘውም “በሀገራችን በተለያዩ ምክንያቶች ችግረኞች እየተበራከቱ በመሆኑ፤ የጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል ሰንበት ትምህርት ቤት በኩል ለመቄዶንያ የምትችሉትን ርዳታ በመርዳታችሁ በረከት ታገኛላችሁ፤ብዙ ዋጋ ያስገኝላችኋል፤ይሄ በጎ ሥራችሁ ለሁሉም አርአያ በመሆኑ እግዚአብሔር ይባርካችሁ” በማለት አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
የሰንበት ትምህርት ቤቱ ሰብሳቢ ቀሲስ ዮናስ ኢሳይያስ እንደገለጹት “የጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል ሰንበት ት/ቤት ከ6‚500 ተማሪዎች ይገኛሉ፡፡ ሰንበት ትምህርት ቤቱ መደበኛ ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች አንዱ በርቀት ትምህርት ማስተማር ነው፡፡ በርቀት ትምህርት የሚማሩት በተሠማሩበት የሥራ ዘርፍ ክርስትናቸውን እንዲገልጹ ማድረግ” መሆኑን አስረድተዋል፡፡ አያይዘውም “በቤተክርስቲያን ተቋማት በርካታ ወጣቶች ይገኛሉ፡፡ ቤተክርስቲያን ከመንፈሳዊ ትምህርቷ በተጓዳኝ በማኅበራዊ ጉዳይ ተሳታፊ እንዲሆኑ መቄዶንያ አረጋውያንን እንዲረዱ እያደረግን ነው፤ በዚህም መሠረት የሰንበት ትቤቱ የርቀት ትምህርት አስተባባሪዎች ተወካዮች ቅዱስነትዎ ጋር መጥተን ለመቄዶንያም የበኩላችንን አስተዋጽኦ እንድናደርግ አባታዊ በረከትዎን ለመቀበል መጥተናል” ሲሉ ገልጸዋል፡፡
“የካቴድራሉ አስተዳዳሪ መልአከ ፀሐይ አባ ኃይለ ኢየሱስ ተመስገን እንዳብራሩት “የሰንበት ትምህርት ቤቱ ወጣቶች በርካታ ሥራዎችን እየሠሩ እንደሚገኙ” ገልጸዋል፡፡ በሰንበት ትምህርት ቤቱ ባዘጋጀው የርቀት ትምህርት በርካታ ተማሪዎች ከተለያዩ ቦታዎች መጥተው ይማራሉ፡፡ ዶክተር ቢኒያም በሀገራችን ላይ በየመንገዱ ወድቀው የሚኖሩ ወገኖቻችንን እያነሡ የጀመሩት ራዕይ ተስፋፍቶ አሁን ፍሬ አፍርቷል፡፡ እኛም በበኩላችን ይህን ለምን አንደግፍም ብለን ካቴድራሉ፣ሰንበት ት/ቤቱ በማስተባበር የገንዘብ ድጋፍ ተደርጓል፤ቅዱስነትዎ ለዶክተር ቢኒያም እንዲሰጡልን” ነው የመጣነው ብለዋል፡፡
አረጋውያንና የአዕምሮ ሕሙማንን ከጎዳና በመሰብሰብ “ሰው ለመርዳት ሰው ብቻ መሆን በቂ ነው” የሚል መርህ አንግቦ ከተነሣ ዓመታት ያስቆጠረው መቄዶንያ፤ በእነዚህ ዓመታትም በርካታ አረጋውያንንና የአዕምሮ ሕሙማንን ከጎዳና ሕይወት መታደግ ችሏል፡፡ የተቋሙ መሥራች ክቡር ዶክተር ቢኒያም እንደገለጹት “መቄዶንያ ምንም ገቢ የለውም፡፡ በቀን ከ 2.5 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የሚያወጣ ማዕከከል ነው፡፡ በአሁኑ ሰዓት በ46 ከተሞች ላይ ከጎዳና ሰዎች ተነሥተው እየተረዱ ይገኛሉ፡፡” ብለዋል፡፡
“ዛሬ የአንድ ቤተክርስቲያን ሰንበት ት/ቤት 1.2 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ያደረገው ሌሎችም አብያተ ክርስቲያናትና ሰንበት ት/ቤቶች ተመሳሳይ ድጋፍ እንዲያደርጉ የሚያነሣሣ ነው፡፡ ሌሎችም ይህን አርአያ አድርገው ተመሳሳይ ድጋፍ እንዲያደርጉ ነው፡፡ አንዳንድ አብያተ ክርስቲያናትም የረዱን አሉ፤ ሌሎችም ድጋፍ በማድረግ እንዲሳተፉ ቢያደርጉ፤ ድጋፍ የሚያደስፈልጋቸውን እነዚህ መርዳት ከእግዚአብሔር ዘንድ ዋጋ ስለሚያሰጥ ሁሉም ኅብረተሰብ እንዲሳተፍ ቅዱስነትዎ መመሪያ ለሁሉም አብያተ ክርስቲያናት ቢያስተልላልፉልን” ብለዋል፡፡
©️ EOTCTV
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
በዓለ ጰራቅሊጦስ
'' የቤተክርስቲያን የልደት ቀን '' በደብራችን ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ በታላቅ ድምቀት ይከበራል።
በዓለ ጰራቅሊጦስ
'' የቤተክርስቲያን የልደት ቀን '' በደብራችን ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ በታላቅ ድምቀት ይከበራል።
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
