fa
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

رفتن به کانال در Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

نمایش بیشتر
2 639
مشترکین
+124 ساعت
+167 روز
+5630 روز
آرشیو پست ها
በክፍል አንድ የተነሱ ነጥቦች - የቅዱሳንን ታሪክ ለምን እንማራለን ? - ቅዱስ አትናቴዎስ ማነው ? - የቅዱስ አትናቴዎስ አጠራር - ጉባኤ ኒቂያ እና የቅዱስ አትናቴዎስ ሚና
በክፍል አንድ የተነሱ ነጥቦች - የቅዱሳንን ታሪክ ለምን እንማራለን ? - ቅዱስ አትናቴዎስ ማነው ? - የቅዱስ አትናቴዎስ አጠራር - ጉባኤ ኒቂያ እና የቅዱስ አትናቴዎስ ሚና

የሐዘን መግለጫ የዲ/ን ፍቃዱ ጌታሁን እናት ስላረፉ በመሆኑ ነገ ማክሰኞ መጋቢት 05/2015 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 በደብረ አሚን ተክለሃይማኖት ቤ/ክ ሥርዓተ ቀብራቸው ይፈጸማል መኖሪያ ቤታቸው የቀድሞ 43 ቀበሌ አካባቢ

እርሷም ከሞቱ በኃላ የሰዎች በድኖች አፈርም ከሆኑ ተነስተው ይሰቃያሉን ብላ መለሰችለት። አዎን አላት። ለዚህ ለምትነግረኝ ነገር ምልክቱ ምንድነው እግዚአብሄር ለሙሴ በሰጠው ኦሪት አልተፃፈ አባቶቻችንም ይህን አላመኑም አለችው። እርሱም በፍርድ ቀን ሙታን እንደ ሚነሱ ስለ ኃጥአንም ስቃይ ስለፃድቃንም ተድላ ደስታ በኦሪት መፅሀፍና በሀዲስ ኪዳን መፅሀፍ ተፅፎ እንዳለ ገለጠላት። ትምህርቱና ተግሳፁ በልቧ አደረ በፍርድ ቀንም ሙታን እንደሚነሱ አመነች እንዲህም አለችው ከዚህ ከረከሰ ስራ ብመለስ እግዚአብሔር ይቀበለኛልን። አባ ግርማኖስም ወደ አለም እንደመጣና ተሰቅሎ ደሙን በማፍሰስ ኃጢአታችንን እንዳራቀልን በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ካመንሽ ስለዚህ የነፃችና የፀናች ንስሃ ይሆንልሻል የክርስታና ጥምቀትንም ተጠመቂ እግዚአብሔርም ይቀበልሻል አስቀድመሽ ከሰራሽው ኀጢአት ምንም ምን አያስብብሽም ከእናትሽ ማህፀን እንደተወለደሽበት ቀን ትሆኛለሽ እንጂ። የክብር ባለቤት የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የቀናች ሀይማኖት ደጆችም ይከፈቱልሻል አላት።ያንጊዜም የክርስትና ጥምቀትን ያጠምቃት ዘንድ ለመነችው እርሱም ወደ በአልበክ ከተማ ኤጲስቆጶስ ወስዶ አደረሳት እርሷም በኤጲስቆጶሱ ፊት በልዩ ሶስትነት በመድሃኒታችን ክርስቶስም ሰው በመሆኑና ሞቶ በመነሳቱ አመነች። ኤጲስቆጶሱም ተነስቶ በውኃው ላይ ፀልዮ አጠመቃት እግዚአብሔርም አይነ ልቡናዋን ገልጦላት ብሩህ መልአክ ወደ ውኃው ሲስባት ሌሎች መላእክትም ስለ እርሷ ፈፅሞ ደስ ሲላቸው ተመለከተች። ከዚህም በኃላ ገፃችው የሚያስደነግጥ ጥቋቊሮችን አየች ከእርሳቸውም አንዱ መልኩ የከፋ ሲጎትታት እርሱም በርሷ ላይ ይቆጣ ነበር። ይህንንም ራእይ በአየች ጊዜ የክርስትና ሀይማኖት ፍቅር በልቧ ተጨመረ ኃጢአት በመስራት የሰበሰበችውን ገንዘቧን ሁሉ ለድኆችና ለችግረኞች ሰጠች ከደናግል ገዳማትም ወደ አንዱ ገዳም ገብታ የምንኲስና ልብስ ለብሳ ፍፁም የሆነ ታላቅ ተጋድሎን ተጋደለች። ከአጋንንት ጋር ተዋጋች። ሰይጣንም አስቀድሞ ከእርሷ ጋር ሲያመነዝሩ ከነበሩ በአንዱ ሰው ልብ አደረ ወደ መኰንኑ ሄዶ ነገር ሰራባት መኰንኑም ወደርሱ እንዲያቀርቧት አዘዘ። በደረሰችም ጊዜ ከደጅ ቆመች በሞተው በመኰንኑ ልጅ ለይ ታላቅ ጩኸትና ልቅሶ አየች ገብታም ክብር ይግባውና ወደ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመፀለይ ማለደች የሞተውን የአገር ገዥውንም ልጅ ከሞት አስነሳቸው። መኰንኑም ይህን ድንቅ ተአምር በአየ ጊዜ እጅግ አደነቀ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በእርሷ ምክንያት ፍፁም የፀና እምነት አመነ። ከእርሱ በኃላም ስለ እርሱ ስሙ ዲዮጎኖስ የሚባል ሌላ አገረ ገዢ ተሾመ ።የዚችንም ድንግል ዝናዋን ሰምቶ ወደርሱ አስመጣት ።እርሷም በአደባባይ ውስጥ አይኑ አንድ አይና የሆነ ጎልማሳ አየች ፀለየችና በመስቀል ምልክት በአይኑ ላይ አማተበች ያንጌዜም አይኑ ተገልጦ አየ፡፡ ያደረገችውን ይህን ድንቅ ስራ አይቶ ድንግሊቱን ወደ ቦታዋ መለሳት። ከእርሱም በኃላ ደግሞ ሌላ ስሙ በከኒቶስ የሚባል አገር ገዢ ተሾመ እርሱም ዝናዋን ሰምቶ ይቺን ቅድስት አውዶክስያን ወደርሱ አስመጣት ሊያሰቃያት ፈልጎ። እርሷም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን እድሏን ከሰማእታት ጋራ ይሰጣት ዘንድ ለመነችው እግዚአብሔርም ልመናዋን ተቀበለ። ራሷን በሰይፍ እንዲቆርጡ መኰንኑ አዘዘ በመንግስተ ሰማያትም የሰማእትነት አክሊል ተቀበለች ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን፡፡https://t.me/finotebirhan12

ያን ጊዜ አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስ በመብረቅ ላይ ተጭኖ በረረ እነዚያ አጋንንት ወደአሉበትም ወረደ። ደመናትም ከበቡአቸው መላእክትም በእሳት ሰይፍ መተሩአቸው በመብረቅም አጨዱ አቸው አመድም ሆነው በነፋስ በተኑአቸው። የእነዚያም አጋንንት ቁጥራቸው ሰባት መቶ ሺህ እልፍ ከአንዱ ሺህ ነበር። ከዚህም በኃላ ጌታ ክርስቶስን የካዱ ወዳሉበት ወደ ምእራብ ሀገር ወሰደው። ነገስታቱና መሳፍንቱ መኳንንቱም በሚወጡበትና በሚገቡበት ጉዳና ላይ አቆመው ጌታችንም በዚች ጉዳና ብዙ መከራ ያገኝሀል ግን በርታ ታገስ ብሎት በዚያ ተወው። በዚያን ጊዜም የአርብ ንጉስ ጣዖታቱን አስይዞ መኳንንቱን ሰራዊቱን አስከትሎ በዚያች ጎዳና መጣ አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስን በጎዳና ውስጥ በተገናኙት ጊዜ ጣኦታቱ ወድቀው ተሰባበሩ። ንጉሱም አባታችንን በአየው ጊዜ አንተ ጠጉር ለባሽ ምንድነህ ሰው ነህን አለው።አባታችንም አዎን ክብር ያለው የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያው የሆንኩ ሰው ነኝ ብሎ ለከሀዲው ንጉስ መለሰለት። ንጉሱም ዳግመኛ አባታችንን በዚያ አይሁድ በሰቀሉት ታምናለህን አለው አባታችንም በሰው ፊት አምንበታለሁ።ስለ እኔ በተሰቀለው አላፍርበትም ስለ እኔ ብቻ የተሰቀለ አይደለም ስለ አንተና ከአንተ ጋራ ስለ አሉትም ነው እንጂ ንጉስ ሆይ የዘላለም ህይወትን ታገኛላችሁ እመኑበት አለው። ንጉሱም ይህን ነገር በሰማ ጊዜ ተቆጣ ሰራዊቱንም ጠርቶ በፍጥረት እሳትን አንድዱ ለተሰቀለው ለናዝሬቱ ሰው ባሪያው ነኝ የሚለውን ጠጉር ለባሽ ወስዳችሁ ጨምሩት አላቸው። የእሳቱም ነበልባል በረጅም ዛፍ መጠን ከፍ ከፍ እስከሚል አነደዱ። አባታችን ግን ንጉሱና ሰራዊቱ ሁሉ እያዩት አልፎ በፈቃዱ ወደ እሳቱ ገባ። እሳቱም እንደወንዝ ውኃ ሆነ ሰረዊቱም እጅግ አደነቁ እኩሌቶቹም የክብር ባለቤት በሆነ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ። ንጉሱም ሲያደንቁ በአየ ጊዜ ፈፅሞ ተቆጣ ከሰባ ሰባት አርበኞቹ ጋራ በቁጣ ተነስቶ ያደነቁትንና ያመኑትን አንገታቸውን ቆረጠ ። በዚያችም ቀን የተቆረጡ አርባ መቶ ሺህ ሆነው ተቆጠሩ።ንጉሱም የአባታችንን አንገት ሊቆርጥ ሰይፉን መዞ ተወርውሮ ሄደ። ያን ጊዜም ከመብረቅና ከነጎድጓድ ጋራ ታላቅ ንውፅውፅታ ሆነ ንጉሱንም ከሰራዊቱ ጋራ አጠፋው ከከሀዲው ንጉስ ጋራ የሞቱት ቁጥራቸው አራት ሺህ እልፍ ሆነ። ጌታችንም አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስን ጠላቶችህንና የኔንም ጠላቶች አጠፋሁልህ አለው።አባተችን ግን በመብረቅ የሞቱትን ሬሳቸውን ነፍሳቸውንም መላእክተ ፅልመት ወደ ስቃይ ሲወስዱአቸው በአየ ጊዜ መድኃኒታችንን እሊህን ስሁታን ማርልኝ ሰው ስሁትና ከዳተኛ ነውና አቤቱ አንተ ግን መሀሪ ይቅር ባይ ታጋሽም ነህ አለው።አባታችንም ይህን ሲናገር ጌታችን ተሰወረ። አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስም ከዚያ ሄደ ታላቅ ገደልም አገኘ እግሮቹንም በገመድ አስሮ በገደሉ ውስጥ ተዘቅዝቆ ተሰቀለ።ሰይጣንም መጥቶ ያቺን ገመድ ቆረጣት ወደ ታችም ተወርውሮ ወረደ።ቅዱስ ሚካኤልም ቀድሞ አባታችንን ያዘው በእግርህ ላቁምህ ወይም በራስህ አለው በራሴ እቆም ዘንድ ተወኝ አለው ትቶት ሄደ። በዚያም በራሱ ቁሞ በጥርሶቹም ደንጊያ ነክሶ እስከ ሰላሳ አመት ኖረ አንጀቱና ናላው ሁሉ እየፈሰሰ አልቆ መላ አካሉ እንደእንጨት ቅርፊት ሆነ። ከሰላሳ አመትም በኃላ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አባታችንን ገብረ መንፈስ ቅዱስ እያለ ሶስት ጊዜ ጠራው። እርሱም እነሆኝ ጌታዬ አለ ጌታችንም እነዚያን ከሀዱዎች ምሬልሀለሁ ከዚህ ተነሳ አለው።ያን ጊዜ የነከሰውን ደንጊያ ትቶ ተነሳ።ጥርሱም ተነቅሎ በድንጊያ ተተክሎ ቀረ። ክንፎችም ተሰጥተውት እየበረረ ከእግዚአብሔር ፊት ደረሰ ጌታውንም ከማርክልኝ ከስጋቸው ጋራ ተነስተው በመጠመቅ ክርስቲያኖች ይሁኑ ብሎ ለመነው። መድኃኒታችንም በሽተኞችን ልትፈውስ ሙታንን ልታስነሳ ስልጣን ሰጥቼሀለሁ አሁንም ወደተገደሉት ሄደህ በመስቀል ምልክት በላያቸው አማትብ ህይወት መድኃኒት በሆነ ስሜም አስነሳቸው አለው።ያን ጊዜም በድኖቻቸው ወዳሉበት ሂዶ አስነሳቸው አጥምቆም ክርስቲያኖች አደረጋቸው ከእርሳቸውም ሄደ። ከዚህ ዓለም የሚለይበት በቀረበ ጊዜ እነሆ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እነሆ ተገለጠለት። ስሙን ለሚጠራና መታሰቢያውን ለሚያደርግ እስከ አስራ አምስት ትውልድ የምህረት ቃል ኪዳን ሰጠው።የእድሜውም ዘመናት አምስት መቶ ስልሳ ሁለት ሲሆን በሰላም በፍቅር አረፈ። ጌታችንም ነፍሱን ተቀበለ አቅፎም ሳማት በመላእክትና በቅዱሳን ሁሉ ምስጋና አሳረጋት። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_አባ_ሰርባሞን በዚህች ቀን በአስቄጥስ ገዳም በአባ ዮሀንስ ደብር አበ ምኔት የነበረው ክቡር ቅዱስ መናኝና ገድለኛ አባት አባ ሰረባሞን አረፈ። ይህም ቅዱስ በአስቄጥስ ገዳም በአባ ዮሀንስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከልጅነቱ ጀመሮ መነኰሰ ቅዱሳን አረጋውያንንም እያገለገለና ሰላሳ ሁለት አመት ያህልም ብዙ ተጋድሎን እየተገደለ ኖረ። ከዚህ በኃላም በዚሁ በአባ ዮሀንስ ገዳም አበ ምኔት ሆኖ ተሾመ። የተጋድሎውንም ስራ አበዛ ከመነኰሰበት ጊዜ ጀመሮ እሰከ አረፈበት ጊዜ ድረስ ሁልጊዜ ይፀልይና ይፆም ይተጋም ነበር። በካህናት አለቃ ሹመት ሀያ አመት ከኖረ በኃላ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ራሱን እስረኛ አደረገ። እኒህም አስራ አምስት አመታት እስቲፈፀሙ ከቶ ከሰው ማንንም አላየም በእኒህም በአስራ አምስቱ አመታት ከቅዳሜና ከእሁድ ሰንበት በቀር አይበላም አይጠጣም ነበር። እረፍቱም በቀረበ ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ በህልም ታየው። ይህን መስቀል ያዝ ብሎ የእሳት መስቀል ሰጠው። ቅዱሱም እሳትን መያዝ እንዴት ይቻለኛል ብሎ መለሰለት። መልአኩም አትፍራ ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችን ክርስቶስ በአንተ ላይ ለእሳት ስልጣንን አልሰጣትም ብሎ መለሰለት።የፀናች እጁንም ዘርግቶ ያንን መስቀል ከመልአኩ እጅ ተቀበለ። ሁለተኛም መልአኩ እንዲህ አለው በርታ ስጋውንና ደሙንም ተቀበል። እሰከ አስርም ቀን ድረስ መጥቼ እወስድሀለሁ። ከእንቅልፉም በነቃ ጊዜ ለቅዱሳን አረጋውያን ነግሮ ተሰናበታቸው እነርሱም አለቀሱ በእግዚአብሔርም ፊት እንዲአሳስ ብላቸው ለመኑት እርሱም ደግም በፀሎቶቻቸው ሁል ጊዜ እንዲአስቡት ለመናቸው። ከዚህም በኃላ ስጋውንና ደሙን ተቀበለ። ቅዱሳን አረጋውያንም ከእርሱ ጋራ እያሉ በሰላም አረፈ፡፡ እንደሚገባም በዝማሬና በብዙ ጸሎተ ማኅሌት ገንዘው በጻድቃን መቃብር ቀበሩት፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅድስት_አውዶክሲያ ዳግመኛም በዚህች ቀን የስሟ ትርጓሜ ሰላምና መወደድ የሆነ የከበረች አውዶክሲያ በሰማእትነት አረፈች። ይህቺም የተወደደች ቅድስት በሊባኖስ ተራራዎች አቅራቢያ በበስራ አውራጀ አልበክ በሚባል አገር ከሚኖር ሰዎች ወገን ነበረች። እሷም በሮም ንጉስ በጢባርዮስ ዘመነ መንግስት ነበረች። የአባቷም ስም ዮናስ የእናቷም ጠባቢት ይባላል። የቀደመው ኑሮዋ በዝሙትና በርኲሰት ነበር። ብዙዎችን አሳስታ ከእርሷ ጋራ በኃጢአት ትጥላቸው ዘንድ ፊቷን ታሳምር ነበር። መልኳንም ታስጌጥ ነበር። በዚህ በረከሰ ስራም ብዙ ገንዘብ ሰበሰበች። በኢየሩሳሌምም የሚኖር ስሙ አባ ግርማኖስ የሚባል አንድ ፃድቅ መነኰስ ዝናዋን ሰምቶ ወደ ርሷ መግባት በለመዱ ሰዎች አምሳል ሆኖ ወደርሷ ገባ። ገብቶም ከርሷ ጋራ በቤት ውስጥ ተቀመጠ ፈፅሞ በሚያስፈሩ ቃሎች ሊመክራትና ሊገሰፃት ጀመረ በገሀነምም ትሉ የማያንቀላፋ እሳቱ የማይጠፋ ጨለማው የሚዳሰስ የሚመስል በየአይነቱ የሚአስፈራ ስቃይ መኖሩን አሳሰባት።

🔴#ስንክሳር መጋቢት_5 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መጋቢት አምስት በዚችም ቀን ተአምራቱና ትሩፋቱ የበዛ ቅዱስ አባት #አባ_ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ የእረፍቱ ቀን መታሰቢያ ሆነ፣ ክቡር ቅዱስ መናኝና ገድለኛ አባት #ቅዱስ_አባ_ሰረባሞን አረፈ፣ የከበረች #ቅድስት_አውዶክሲያ በሰማእትነት አረፈች። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #አቡነ_ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ መጋቢት አምስት በዚችም ቀን ተአምራቱና ትሩፋቱ እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ የእግዚአብሔር ማደሪያ የሆነ ቅዱስ አባት ተጋዳይ አባ ገብረ መንፈስ ቅዱስ የእረፍቱ ቀን መታሰቢያ ሆነ፡፡ ይህም ቅዱስ አባት በተወለደባት ቀን ድንቅ የሆነ ስራን ሰራ ተነስቶ ከእናቱ እቅፍ ወርዶ ከጨለማ ወደ ብርሀን ላወጣኸኝ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይሁን እያለ ለስላሴ ሰግዷልና ምስጋናም አቅርቧልና። ህፃኑም ሶስት አመት በሆነው ጊዜ የእግዚአብሔር መልክተኛ ቅዱስ ገብርኤል ወርዶ ህፃኑን ከእናቱ እቅፍ አንስቶ ብዙ ባህታውያን ወዳሉበት ገዳም ወስዶ በደጅ አኖረው ወደ አበምኔቱ ወደ አባ ዘመደ ብርሀንም ገብቶ ስለ ህፃኑ እግዚአብሔር ያዘዘውን ሁሉ ነገረው። በዚያን ጊዜም ነገሩ እውነት እንደሆነ ይረዳ ዘንድ አባ ዘመደ ብርሀን ተነስቶ ወደ ደጅ ወጣ። መልአኩም እንደ ነገረው ህፃኑ ከበር ተቀምጦ ፈገግታን ተሞልቶ አገኘው። እጅግም ደስ ብሎት ለእግዚአብሄር ሰገደ ህፃኑንም አንስቶ ሳመው ታቅፎም ወደ በአቱ አስገባው። በፍቅር በስነስርአት አሳደገው። የዳዊትን መዝሙርና ቤተ ክርስቲያን የምትቀበላቸውን መፃህፍት ሁሉ ብሉይንና ሀዲስን አስተማረው። ከዚያም በኃላም ክህነት ይሰጠው ዘንድ ስሙ አብርሀም ወደሚባል ጳጳስ ወሰደው ጳጳሱም በአየው ጊዜ ደስ አለው። የዲቁና ማእረግንም ሾመው እንደ ቀዳሜ ሰማእት እስጢፋኖስም ፀጋንና ሞገስን የተመላ ሆነ። ከጥቂት ቀኖች በኃላም በጌታችን ትእዛዝ ቅስና ተቀበለ። በፆም በፀሎት በስግደት በብዙ ትጋትም እየተጋደለ በበረሀ ውስጥ ብቻውን ኖረ። በበረሀም ብዙ ዘመናትን ሲኖር ነፍሱን "ነፍሴ ሆይ እወቂ በእግዚአብሔር ፊት ራቁትሽን ትቆሚ ዘንድ እንዳለሽ እንግዲህስ ፅኚ በርቺ ታገሺ!" ይለት ነበር። ቆዳው ከዐጥንቱ እስቲጣበቅ ያለ መብልና ያለ መጠጥ በእንዲህ ያለ ግብር በገድል ተጠምዶ ኖረ።ከእፅዋት ፍሬዎች ወይም ከእንጨት ስሮች አልተመገበምና ለስጋውም የሚጠቅም ምንም ምን ምክንያት አልፈለገም። ለገብረ መንፈስ ቅዱስ እግዚአብሔር እንዲህ አለው ከእንግዲህ በአለም ካሉ ሰዎች ከካህናት ከመነኮሳት ወይም ከምእመናን ህዝባውያን እንዳያውቁህ አደርግልሀለሁ። እንዳንተ ካሉ በቀር አንተ ራስህ ብትፈቅድ እንጂ መላእክትም ይጎበኙሀል። የብርሀን ሰረገላም ይሁንልህ መድረስ ወደምትሻበት ሁሉ ብረር እኔንም ማየትና በፈለግህ ጊዜ ከአባቴና ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ በሶስትነቴ ታየኛለህ። አሁንም ወደ ኢትዮጵያ ምድር ሂድ በዚያም ከደይን የምታወጥቸው ነፍሳት አሉህ አለው። ከዚህም በኃላ ስልሳ አንበሶች ስልሳ ነብሮች በፊት በኃላ አጅበውት ወደ ኢትዮጵያ ምድር ተጓዙ። የእግዚአብሔር መልእክተኛ ቅዱስ ገብርኤልም ከአንበሶችና ከነብሮች ጋር በነፋስ ሰረገላ አሳፍሮ ይመራው ነበር። ወደ ምደረ ከብድም አደረሰው ከዚያም ወደ ልዩ ተራራ ወደ ደብረ ዝቋላ ወሰደው። አባታችንም በባህሩ ቁሞ ምስራቁን ምዕራቡን ሰሜኑን ደቡቡን አራቱን ማእዘን ተመለከተ።የኢትዮጵያ ሰዎች የሚሰሩትን ኃጢአታቸውን በአይኖቹ ፊት የተገለጠ ሆኖ አየ። በራሱም ተዘቅዝቆ ተወርውሮ ወደ ባህሩ ውስጥ ገባ እሊህን የእጅህ ፍጥረቶች የሆኑትን ካልማርካቸው ከእዚህ ባህር እንዳልወጣ በእግሮቼም እንዳልቆም በህያው ስምህ እምላለሁ እያለ ማለ እንዲሁም ሆኖ አርባ ቀን አርባ ሌሊት ኖረ። ስምህን የጠራውን መታሰቢያህን ያደረገውን እምርልሀለሁ የሚል ቃል በመልአክ አማካይነት ወደ አባታችን መጣ። አባታችንም መልአኩን መላውን የኢትዮጵያን ሰው ካልማረልኝ ከዚህ ባህር አልወጣም አለው መልአኩም ከአጠገቡ ሄደ። አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስም በዚያ ባህር ውስጥ መቶ ዓመት ኖረ ስጋው ሁሉ አለቀ ደሙም በባህሩ ውስጥ ፈሰሰ አጥንቶቹም እንደበረዶ ነጭ ሆነው ታዩ። አጋንንትም ከአራቱ ማእዘን በየቀኑ ሰባት መቶ ሽህ ሶስት መቶ ሽህ እየሆኑ በመምጣት በቀስታቸው ይነድፉታል እስከ መቶ አመትም አጥንቶቹን በሻፎ ድንጋይ ይፍቁታል ይህን ሁሉ መከራ በትእግስት ሲቀበል ኖረ። ከዚህም በኃላ ጌታችን ወደርሱ መጥቶ ከባህሩ ዳር ቆመ። አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስንም መላውን የኢትዮጵያ ሰው ምሬልሀለሁና ተነስተህ ውጣ አለው ያንጊዜም ወጣ አጥንቶቹም እንደ ወንፊት ቀዳደሰ የተበሳሱ ሆነው ተገኙ ጌታም ዳሰሰውና ጤነኛ አደረገው ወደ ምድር ከብድም ሰደደው። ከዚያም ወደ ላይ ወጥቶ ከፀሀ ከሰማይ በታች እስከ ሰባት አመት ኖረ። ዳግመኛም ወደ ምድረ ከብድ ተልኮ እንደ አምድም የተተከለ ሆኖ ሰባተረ አመት ቆሞ ኖረ። ወደ ሰማይም ሲመለከት ቅንድቦቹን አልከደነም ራሱንም ወደ መሬት ዝቅ አላደረገም ነበር እጆቹም ወደ ሰማይ ተዘርግተዋል። እነሆ ሰይጣንም በቁራ ተመስሎ መጣ አይኖቹንም ወደ ሰማይ ያንጋጠጡ ሁለቱን አይኖቹን አንቁሮ አሳወረው። እርሱ ግን ምንም ሳያጓድል እስከ ሁለት ሳምንት ድረስ እንደ ቀድሞው በመትጋት ሲፀልይ ኖረ። ከዚህም በኃላ ሚካኤልና ገብርኤል መጥተው በፊቱ ቆሙ በሁለቱ አይኖቹ ላይም እፍ አሉበት ብርሀንም ተሰጥቷቸው እንደ ቀድሞው አዩ። ከሰማይ ታላቅ ኃይል ተሰጥቶሀልና ጠላቶችህን ትበቀላቸው ዘንድ ወደ ዝቋላ ሂድ አሉት ከዚያም መላእክት ከአጠገቡ ሄዱ። እርሱም ተነስቶ ወደ ዝቋላ ተጓዘ በጎዳናም ሲጓዝ ሶስት ሽማግሌዎች ከእንጨት ጥላ በታች ተቀምጠው አየ አባታችንም በአያቸው ጊዜ ልሰውራቸው ብሎ በልቡ አሰበ። እንርሱም ፈጥነው በእግዚአብሔር ዙፋን ተማጥነናልና ሶስታችንንም በጀርባህ እያዘልክ አንዳንድ ምእራፍ ሸኘን እንጂ አትተውን ብለው ተጣሩ። በመጣም ጊዜ ሁለመናቸውን ሽበት የከበባቸው የደከሙ ሽማግሎች ሁነው አገኛቸው አንደኛውንም አንስቶ በጀርባው አዘለው ወደ አንድ ምእራፍም አደረሰው ሽማግሌውም ከዚህ አሳርፈኝ አንተ ደክመሀል የማትበላ የማትጠጣ ስለሆንክ አለው አባታችንም ሽማግሌ ሆይ በምን አወቅከኝ አለ። ሽማግሌውም ሂደህ ባልንጀሮቼን አምጣልኝ አለው ተመልሶ ሁለቱ ወደአሉበትም ደርሶ ሁለተኛውን ሽማግሌ በጀርባው አዝሎ ወደ ቀደመው ሽማግሌ አድርሶ አብሮ አስቀመጠው ሶስተኛም ተመልሶ ሶስተኛውን ሽማግሌ አዝሎ ሁለቱ ወዳሉበት አድርሶ በአንድነት አኖረው፡፡ አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስም እነዚያን አረጋውያን እናነተ ከወዴትናችሁ መአዛችሁ ልብ ይመስጣል እጅግም ደስ ያሰኛል አላቸው።እነርሱ ግን ተነስተው ቆሙ አንድ ሲሆኑ ሶስት ሶስት ሲሆኑ አንድ መሆናቸውን ገለጡለት የአባቶች አለቃ አብርሀም እንደ አየ። ያንጊዜም የእግዚአብሔርን የጌትነቱን ክብር አየ የእሊያ አረጋውያንም ፊታቸው ተንቦገቦገ ከፀሀይና ከመብረቅ ብልጭታም ሰባት እጅ በራ አባታችንም በምስጢራት ጎርፍ የተዋጠ ሆኖ ፈራ ተንቀጠቀጠ በምድር ላይም ወደቀ። ህልምን የሚአልምም መሰለው ከዚያም ጌታችን አባታችንን አነቃውና መቶ አመት ያህል ስጋህን ሲነዱፉህ አጥንቶችህን ሲፍቁህ የኖሩ አጋንንትን ታጠፋቸው ዘንድ ወደ ዝቋላ ተራራ ውጣ አለው። እኔ እንደ ወሰድኩህ ባለማወቃቸው በባህር ውስጥ አለ በማለት በትእቢት ላይ ናቸው ሰባቱ ሊቃነ መላእክትም ይረዱሀል መባርቅትም በፊት በኃላ ሆነው ይከተሉሀል አለው።

🔴#ስንክሳር መጋቢት_4 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መጋቢት አራት በዚች ቀን የአይሁድ ተሳታፊዎች ስለሚባሉ ክፉዎች ሰዎች በአሞር ደሴት #የአንድነት_ስብሰባ ሆነ፣ የከበረና የተመሰገነ #መኰንን_ሐኑልዮስ በሰማዕትነት ሞተ፣ ኢትዮጵያዊቷ ጻድቅ #ቅድስት_ሐይመተ_ሥላሴ ዕረፍቷ ነው፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #የቅዱሳን_ሊቃውንት_ጉባዔ መጋቢት አራት በዚች ቀን የአይሁድ ተሳታፊዎች ስለሚባሉ ክፉዎች ሰዎች በአሞር ደሴት የአንድነት ስብሰባ ሆነ። እነርሱ የከበረ የፋሲካን በዓል በኔሳን ወር ማለት በሚያዝያ አሥራ አራት ቀን ከአይሁድ ጋር ያከብሩ ነበርና። ሰኞ ቢሆን ማክሰኞም ቢሆን ወይም ረብዕ ወይም ሐሙስ ወይም በዓርብ ቀን ወይም በቅዳሜ ሰንበት ከአይሁድ ጋር ያከብሩ ነበርና የደሴታቸውም ኤጲስቆጶስ አወገዛቸው ግን አለተመለሱም። ስለዚህም ወደ ሮሜ ሊቀ ጳጳሳት ወደ ድምትራጥዮስ ወደ አንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት ወደ አባ ሰረባሞን ወደ እስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ወደ አባ ድሜጥሮስ ወደ ኢየሩሳሌሙ ኤጲስቆጶስ ወደ አባ ሲማኮስ መልእክትን ላከ። የእነዚህንም ሰዎች ስሕተታቸውን ነገራቸው። አራቱ ሊቃነ ጳጳሳት ከእነርሱ እየአንዳንዳቸው የከበረ የፋሲካ በዓልን በእሑድ ቀን ካልሆነ በቀር ከአይሁድ በዓልም በኋላ ካልሆነ በቀር አታድርጉ የሚል መልእክትን ላኩ። ይህንም ትእዛዝ የሚተላለፈውን ከምእመናን እንዲለይ አወገዙ። በዚህም ጉባኤ አሥራ ስምንት ኤጲስቆጶሳት ተሰበሰቡ። እነዚያንም ሕግ ለዋጮች አቅርበው የሊቃነ ጳጳሳቱን መልእክቶቻቸውን በፊታቸው አነበቡ ከእነርሱም ከከፋች ምክራቸው የተመለሱ አሉ። በስሕተታቸውም ጸንተው የቀሩ አሉ። ረግመውና አውግዘውም ከምእመናን ለዪአቸው። አባቶቻቸን ቅዱሳን ሐዋርያትም የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተነሣባትን ዕለተ ፋሲካን ያለ እሑድ ቀን የሚያከብር እርሱ በበዓላቸው ከአይሁድ ጋራ ተሳታፊ ነውና ከምእመናን ይለይ ብለው እንዳዘዙ እንዲሁ የፋሲካ በዓል በዕለተ እሑድ እንዲከበርና ሕጉም ጸንቶና ተወስኖ እንዲኖር ተሠራ። እግዚአብሔር ከሰይጣን ስሕተት ይጠብቀን። በተጋድሎአቸውና በትሩፋታቸው ደስ ባሰኙት በቅዱሳን ጸሎትም ከወጥመዶቹና ከሽንገላውም ያድነን ለዘላለሙ አሜን። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ _ሐኑልዮስ_መኰንን በዚህችም ቀን የከበረና የተመሰገነ መኰንን ሐኑልዮስ ከጵንፍልያ አውራጃ ብርግያ በምትባል ከተማ በሰማዕትነት ሞተ።ይህንንም ቅዱስ ምስጋና ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ስለ መውደዱና እርሱንም ስለ ማምለኩ ከዲዮቅልጥያኖስ ተልኮ የመጣ ብርይንኮስ የተባለ መኰንን ያዘው። በመኰንኑም ፊት በቆመ ጊዜ ምስጋና ይግባውና የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ሃይማኖት ከፍ ከፍ ባሉ ቃላት አብራርቶ ገለጠ ።ብዙ ምስጋናዎችንም ለእግዚአብሔር አቀረበ የረከሱ ጣዖታትንም ረገማቸው። መኰንኑም በዕንጨት መስቀል ላይ ይሰቅሉት ዘንድ አዘዘ ስለ ከበረ ስሙም ምስክር ይሆን ዘንድ ስል አደለው ምስጋና ይግባውና ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን አመሰገነው። ከዚያም ምስጋና ይግባውና በእግዚአብሔር እጅ ነፍሱን ሰጠ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅድስት_ሐይመተ_ሥላሴ በዚህች ቀን ኢትዮጵያዊቷ ጻድቅ በዝዋይ ደብረ ጽዮን ሐይቅ ውስጥ ገብታ ለአምስት ዓመት የጸለየች ታላቋ እናት ቅድስት ሐይመተ ሥላሴ ዕረፍቷ ነው፡፡ የትውልድ ሀገሯ ጎጃም ደብረ ጽላሎ ነው፡፡ ብዙ እናቶች በጣና ደሴት ውስጥ እየገቡ እንደጸለዩ ሁሉ እሷም ወደ ዝዋይ ሄዳ በዝዋይ ደብረ ጽዮን ሐይቅ ውስጥ ገብታ አምስት ዓመት ከባሕሩ ላይ የጸለየች ቅድስት እናት ናት፡፡ በታዘዘ መልአክ መሪነት ከሐይቁ ውስጥ ከወጣች በኋላ በገዳሙ ውስጥ ዐሥራ ዘጠኝ ዓመት ቆማ ጸልያለች፡፡ በመልአኩ መሪነት ወደ ቡልጋ ሄዳ በዚያም ዐሥራ አምስት ዓመት በታላቅ ተጋድሎ ኖራለች፡፡ ሰውነቷም እጅግ ከስቶ ሥጋዋ አልቆ ይታይ ነበር፡፡ በመጨረሻም መልአኩ ተገልጦ ጊዜ ዕረፍቷን ከነገራት በኋላ ወዲያው መጋቢት 4 ቀን በሰላም ስታርፍ ሦስት አክሊላት ወርደውላታል፡፡ ቅድስት ሐይመተ ሥላሴን ስንክሳሩም "የጽድቅ ኮከብ" እያለ ይጠቅሳታል፡፡ ቅዱስ ገድሏ በደብረ በግዕ ይገኛል፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን፡፡https://t.me/finotebirhan12

🔴#ስንክሳር መጋቢት_3 #አባ_ቆዝሞስ አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መጋቢት ሦስት በዚች ቀን በእስክንድርያ ለተሾሙ ሊቃነ ጳጳሳት ሃምሣ ስምንተኛ የሆነው የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ብፁዕ ወቅዱስ አባ ቆዝሞስ አረፈ። ይህም አባት እውነተኛና ንጹሕ የዋህ ርኅራኄው የበዛ የቤተ ክርስቲያንንም መጻሕፍትና ትርጓሜያቸውን የሚያውቅ ነበር። እግዚአብሔርም በወንጌላዊው ማርቆስ መንበር ላይ ለሊቀ ጵጵስና ሹመት መረጠው የግብጽ ንጉሥ መቅትር በነገሠ በአሥራ ስምንት ዓመት ሊቀጳጳሳት ሆኖ ተሾመ። በተሾመም ጊዜ የክብር ባለቤት የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን መንጋዎች በፈሪሀ እግዚአብሔርና በጥበብ ጠበቃቸው። ለእርሱ ከሚገባው ከግብሩ ገንዘብ የሚተርፈውን ለጦም አዳሪዎች ይሰጣቸው ነበር ደግሞም ቤተክርስቲያን ሕንፃ ማሠሪያ ያወጣ ነበር። መልካም ተጋድሎውንም በአየ ጊዜ ሰይጣን ያለ ኀዘን አልተወውም ነገር ግን የሚያዝንበትን ምክንያት በላዩ አመጣ። ይህም እንዲህ ነው ጴጥሮስ የሚባል ጳጳስ ለኢትዮጵያ አገር ሹሞ ነበር። አባ ጴጥሮስም ወደ ኢትዮጵያ በደረሰ ጊዜ ጥቂት ዘመን በሰላም ኖረ። ከዚህም በኋላ የኢትዮጵያ ንጉሥ ታመመ አባ ጴጥሮስንም ጠርቶ ሁለቱን ልጆቹን አቀረበ ዘውዱንም ከራሱ ላይ አንሥቶ ለአባ ጴጥሮስ ሰጠው እነሆ እኔ ወደ ክብር ባለቤት ወደ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ እሔዳለሁ እነሆም ሁለቱ ልጆቼ በፊትህ ናቸው አንተም ለመንግሥት የሚሻለውን አውቀህ ከሁለቱ አንዱን ከእኔ በኋላ አንግሥ አለው። ንጉሡም ካረፈ በኋላ ጳጳሱ መኳንንቱና የጦር ሠራዊቱ አለቆችና የመንግሥት ሠራዊት አለቆች ተማከሩ እርስ በርሳቸውም ለመንግሥት የሚሻል የሚያንሰው ነው ተባባሉ። ጳጳሱ አባ ጴጥሮስም ታናሹን የንጉሥ ልጅ ቀብቶ አነገሠው በኢትዮጵያ መንግሥት ዙፋን ላይም አስቀመጠው ጥቂት ዘመንም በሰላም ኖረ። በዚያም ወራት ከሶሪያ አገር በሆኑ በሁለት መነኰሳት ልብ ሰይጣን አደረ ከአባ እንጦንስ ገዳም እስከ ሚደርሱ ከቦታ ወደቦታ ይዞሩ ነበር። በዚያም በአባ እንጦንስ ገዳም ጥቂት ቀኖች ተቀመጡ ስለ ሥራቸውም ክፋት አባረሩአቸው። ከዚህም በኋላ አንዱ ጳጳስ ሁለተኛውም ረዳት ሊሆን እርስ በርሳቸው ተስማሙ። ተነሥተውም ወደ ኢትዮጵያ ደረሱ። የሐሰት ጽሑፍንም ጻፉ ያ ጽሑፋቸውም እነርሱ ከእስክንድርያው ሊቀ ጳጳሳት ከአባ ቆዝሞስ ዘንድ ተሹመው እንደ መጡ የሚገልጥ ነበር። በዚያ ጽሑፍም እኛ ያልሾምነውና ወደ እናንተ ያልላክነው ራሱን ጳጳስ ያደረገ ስሙ ጴጥሮስ የተባለ ሰው ወደ እናንተ እንደመጣ ሰምተናል እርሱ ሐሰተኛ ነው እንጂ እውነተኛ አይደለም። ይህን ጽሑፍ ይዞ የሚመጣው ግን ስሙ ሚናስ የሚባል ጳጳስ በእውነት እኛ የሾምነውና ወደ እናንተ የላክነው እውነተኛ ነው አሉ። ሁለተኛም እንዲህ ብለው ጻፉ ጳጳሱ ጴጥርስ ታላቁን ትቶ ታናሹን የንጉሥ ልጅ አነገሠው ይህም የማይገባ ነው ዐመፅ ነውና። እሊህም ክፉዎችና ሐሰተኞች ሁለቱ መነኰሳት ሚናስና ፊቅጦር የሐሰት ጽሑፋቸውን ሳይጽፉ ወደ ጳጳሱ ጴጥሮስ ደርሰው ወርቅ ይስጣቸው ዘንድ ፈለጉ እርሱም ምንም አልሰጣቸውም። ይህንንም የከፋና የረከሰ ሥራ ሰይጣን አስተማራቸው ። የሐሰት ደብዳቤም ጽፈው ወደ ታላቁ የንጉሥ ልጅ ወሰዱ እርሱም ከጥቂት ሰዎች ጋር ለብቻው ይኖር ነበር እነዚያንም የሐሰት ደብዳቤዎች አነበቡለት እጅግም ደስ አለው። ከዚህም በኋላ ብዙ ሠራዊት ሰብስቦ እሊያን የሐሰት ደብዳቤዎች በፊታቸው አነበበላቸው ከንጉሡ ወንድሙ ጋራም ጦርነት ገጥሞ ድል አደረገው ወንድሙንም አሠረው የመንግሥቱንም ሥልጣን ያዘ እንዲሁም ጳጳሱን ጴጥሮስን አሠረው በሩቅ አገርም አጋዘው ያንንም ሐሰተኛ ሚናስን በጳጳሱ በጴጥሮስ ፈንታ አስቀመጠው። ከጥቂት ቀንም በኋላ ሐሰተኞች ፊቅጦርና ሚናስ እርስ በርሳቸው ተጣሉ ፊቅጦርም በመንበረ ጵጵስና ያለውን ገንዘብ ሁሉ ሰርቆ ወደ ግብጽ ሀገር ሸሽቶ ሔደ። ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስንም ካደው። ከመንበረ ጵጵስናው የሰረቀውንም ገንዘብ ሁሉ እግዚአብሔር የማይወደውን ሥራ በመሥራት አጠፋው። ሊቀ ጳጳሳት ቆዝሞስም ሐሰተኛ ሚናስ ያደረገውን በሰማ ጊዜ እጅግ አዘነ ደብዳቤም በመጻፍ አውግዞ ለየው። የኢትዮጵያ ንጉሥም ሰምቶ እጅግ አዘነ ሐሰተኛው ሚናስንም ይዞ ገደለው። ጳጳሱ ጴጥሮስንም ከተሰደደበት ይመልሱት ዘንድ መልእክተኞችን ላከ ግን ሙቶ አገኙት። ይህም ነገር በሊቀ ጳጳሳት በቆዝሞስ ዘንድ ተሰማ ሁለተኛም ጳጳስ አልሾመላቸውም ከእርሱም በኋላ የነበሩ ሊቃነ ጳጳሳት አባ መቃርስ አባ ታውፋንዮስ አባ ሚናስ አባ አብርሃም በእነዚህ ዘመን ከዘጠኝ መቶ አሥራ አንድ ዓመተ ምሕረት እስከ ዘጠኝ መቶ ዘጠና አምስት ዓመተ ምሕረት ድረስ ለሰማንያ አራት ዓመታት ያህል ለኢትዮጵያ ሰዎች ጳጳስ ተሹሞ አልተላከላቸውም። የኢትዮጵያ ንጉሥ ግን የጳጳሱ የጴጥሮስ ረዳት የነበረውን ወስዶ በመምህርህ ፈንታ ጳጳስ ሁነህ ተቀመጥ አለው። እርሱም እኔ ጳጳስ ልሆን አይገባኝም የሐዋርያትንም ሥርዓት ተላልፌ ይህን ልሠራ አይቻለኝም ግን ልቀቀኝና ወደ ግብጽ ልሒድ ጳጳስ እንዲሾምላችሁም ሊቀ ጳጳሱን እለምነዋለሁ ከዚያም በኋላ ወደ እናንተ እመለሳለሁ እያለ ንጉሡን ማለደው። ንጉሡም ወደ ግብጽ እንዲሔድ አላሰናበተውም ያለ ውዴታው ወስዶ የጵጵስናውን ልብስ አለበሰው እንጂ። የጵጵስናውንም ሥራ እንዲሠራ አደረገው። አባ ቆዝሞስም እጅግ ሸመገለ የሹመቱም ዘመን ድኀንነትንና ሰላምን የተመላ ነበር በወንጌላዊ ማርቆስ ወንበርም አሥራ ሁለት ዓመት ኖረ በሰላምም አረፈ፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን፡፡https://t.me/finotebirhan12

"ልጆቼ ሆይ! ከብርሃን ጨለማን ከደግነት ክፋትን ከጽድቅ ይልቅ ኃጢአትን . . . ምነው መምረጣችሁ? እኔ ስለ እናንተ በየቀኑ እየለመንሁ እነሆ አለሁ:: ወደ ጨለማ ገሃነም እንዳትወርዱ እባካችሁ ንስሐ ግቡ!" ቅድስት ድንግል ማርያም ይህንን ለቅዱሱ ሰው ነግራው ቅዱስ ዳዊትን አስከትላ በግሩማን መላእክት ታጅባ ወደ ውሳጤ መንጦላዕት (የእሳት መጋረጃዎች ወደ ተተከሉበት ድንኳን) ገባች:: በዚያም ተመሰገነች:: ለዛም አይደል ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ:- "ይዌድስዋ መላእክት ለማርያም በውስተ ውሳጤ መንጦላዕት : ወይብልዋ : በሐኪ ማርያም ሐዳስዩ ጣዕዋ::" ሲል ያመሰገናት:: ቅዱስ ጐርጐርዮስም ከሰማይ ቆይታ መልስ ያየውን ሁሉ ጽፎ ለአበው ሰጥቷል:: ስለዚህም ረዓዬ ኅቡዓት (ምሥጢራትን ያየ) ይሰኛል:: ቅዱሱ ተረፈ ዘመኑን በተጋድሎ ፈጽሞ በዚህች ቀን አርፏል:: ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን፡፡https://t.me/finotebirhan12

🔴#ስንክሳር መጋቢት_2 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መጋቢት ሁለት በዚች ቀን የኒቅዮስ ኤጲስቆጶስ #ቅዱስ_አባ_መከራዊ በሰማዕትነት ሞተ። የሮሀ አገር የሆነ የተሠወረውን የሚያይ #ቅዱስ_ጎርጎርዮስ አረፈ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #አባ_መከራዊ_ዘሃገረ_ኒቅዮስ መጋቢት ሁለት በዚች ቀን የኒቅዮስ ኤጲስቆጶስ አባ መከራዊ በሰማዕትነት ሞተ። ይህም አባት በግብጽ ደቡብ ከምትገኝ ከእስሙናይን ከታላላቆቿ ወገን ነው። ለኒቅዮስ ከተማም ኤጲስቆጶስነት ተሾመ። የስደትና የመከራ ወራት በሆነ ጊዜም ስሙ ዮፋንስ የሚባል መኰንን ወደዚያች አገር ከንጉሥ ተልኮ መጣ። የክርስቲያን ወገኖችንም ያሠቃይ ዘንድ ጀመረ። የዚህንም የቅዱስ ኤጲስቆጶስ አባ መከራዊን ዜና ሰምቶ ወደርሱ ያመጡት ዘንድ ወታደሮቹን ላከ እርሱም ወደ መኰንኑ ከመሔዱ በፊት ወደ ቅዱስ መሠዊያው ገባ እጆቹንም ዘርግቶ ጸለየ። ንዋየ ቅዱሳቱንና የመቀደሻውን ልብሶች በመቅደሱ ውስጥ አኖረ። ከዚያም በኋላ ቤተ ክርስቲያኑን ይጠብቅ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ፈጽሞ ማለደ። በላያችሁ የፀሐይ ብርሃን ይወጣ ዘንድ ያልተዋችሁ የጽዮን ልጅ ደጆች ሆይ ለእግዚአብሔር ቤት ማገልገያ የሆነ ነዋየ ቅዱሳቱን ጠብቁ እያለ ታላቅ ልቅሶ በማልቀስ ጮኸ። ከዚህም በኋላ ከንጉሥ መልክተኞች ጋራ ወጥቶ ሔደ ወደ መኰንኑም ቀረበ። ስለ ስሙና ስለ አገሩ ስም ስለ ሥራውም ጠየቀው። የኒቅዮስ ከተማ ኤጲስቆጶስ እንደሆነም ባወቀ ጊዜ እንዲገርፉትና እንዲያጐሳቁሉት ብርና እርሳስም አቅልጠው በአፉ እንዲጨምሩ አዘዘ። እግዚአብሔርም የሚያጸናውና የሚያስታግሠው ሆነ። ያለ ጉዳትም በጤንነት መልሶ ያነሣው ነበር። ከዚህም በኋላ ወደ እስክንድርያ ገዥ ወደ ኄርሜኔዎስ ሰደደው። እርሱም ቅዱስ አባ መከራዊን እንዲአሥሩት አዘዘ። እግዚአብሔርም በእጆቹ ብዙዎች ድንቆች ተአምራትን አደረገ ከተአምራቱም አንዱ ለአቅፋስ ከተማ ሹም ለሆነ ለዮልዮስ ስሙ አውካሪስጦስ የሚባል እጆቹና እግሮቹ ሽባ የሆነ ልጅ ነበረው አባ መከራዊም በላዩ ጸለየ። ከደዌውም አዳነው። ከዚህ በኋላ በዮልዮስ ቤት ቀድሶ ለአማንያን ሥጋውንና ደሙን አቀበላቸው። ስለ ሥጋውም እንዲአስብና ገድሉንም እንዲጽፍለት ከዮልዮስ ጋራ ስምምነት አደረገ። መኰንኑ ኄርሜኔዎስም አባ መከራዊ ስለ አደረጋቸው አስደናቂ ተአምራት በሰማ ጊዜ በተለያየ ሥቃይ ያሠቃዩት ዘንድ አዘዘ። ሕዋሳቶቹ እስቲቆራረጡ በመንኰራኵሮች ውስጥ አስገብተው አሠቃዩት። ለነጣቂዎች አንበሶችም ጣሉት በባሕርም አሠጠሙት በእሳት ምድጃ ውሰጥም ጨመሩት። ቅዱስ አባ መከራዊ በሥቃዩ ሁሉ በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል የሚታገሥና የሚጸና ሆነ። ጌታም ያለ ጉዳት መልሶ በጤንነት ያስነሣው ነበር። የእመቤታችን የድንግል ማርያምን ቤተ ክርስቲያን የምታገለግል አንዲት ድንግል እኅትም ነበረችው። ሁለት ወንድሞችም ነበሩት የአንደኛው ስም ዮሐንስ የሁለተኛውም ይስሐቅ ይባላል በእሥር ቤትም ሳለ ወደርሱ መጡ አንተ ስለ አባታችን ፈንታ አባት ሆነኽን ነበር እነሆ የሙት ልጆች እንሆን ዘንድ ትተኸን ትሔዳለህ እያሉ በፊቱ አለቀሱ። እርሱም አጽናንቶ ወደ ቤቶቻቸው አሰናበታቸው። ዮልዮስም የዚህን ሽማግሌ ሞት በጽሑፍ እዘዝ ከእርሱም ታርፋለህ ብሎ መኰንኑን መከረው። ቃሉንም ተቀብሎ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ ።በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነትን አክሊል ተቀዳጀ። ዮልዮስም የቅዱስ አባ መከራዊን ሥጋ ወስዶ በከበሩ በወርቅ ልብሶች ገነዘው በደረቱም ላይ የወርቅ መስቀል አደረገ ወደ ሀገሩ ወደ ኒቅዮስም ከአገልጋዮቹ ጋራ ሰደደው። መልካም ነፋስም ሆኖላቸው መርከቢቱ ፈጥና ሔደች በከተማውም በር አንጻር ደርሳ ቆመች። ቀዛፊዎችም ሊያንቀሳቅሱዋት ፈልገው ነበር ግን አልተቻላቸውም አብዝተው በደከሙም ጊዜ ሥጋዬ በውስጡ እንዲኖር እግዚአብሔር የፈቀደው ቦታ ይህ ነው የሚል ቃል ከበድኑ ወጣ። ይህንንም ለሀገር ሰዎች ነገሩአቸው የሰሌን ዝንጣፊም እየያዙ ወደርሱ መጡ በሀገራቸውም ውስጥ እርሱ በመረጣት ቦታ እስከ አኖሩት ድረስ በታላቅ ክብር ተሸክመው ወሰዱት። መላው የሕይወቱ ዘመን አንድ መቶ ሠላሳ አንድ ሆነ። መጻሕፍትን እስከተማረ ድረስ ስምንት ዓመት በዲቁና ሹመት ሃያ አራት ዓመት ከዚያም ቅስና ተሹሞ በቅስና አገልገሎት ሠላሳ ዓመት ኖረ ከዚያም በኋላ ኤጲስቆጶስ ሁኖ ተሾመ። በዚህም ስልሳ ዘጠኝ ዓመት ኑሮ መልካም ተጋድሎውን ፈጸመ። የሕይወት አክሊልንም ከክብር ባለቤት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ተቀበለ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_ጐርጐርዮስ_ረዓዬ_ኅቡዓት ዳግመኛም በዚች ቀን የሮሀ አገር የሆነ የተሠወረውን የሚያይ ቅዱስ ጎርጎርዮስ አረፈ። ይህም ቅዱስ ሰው አስቀድሞ አመፀኛና ኃጥእ ነበረ ከዚህም በኋላ ከዐመፁ ወደ እግዚአብሔር በንስሓ ተመልሶ መነኰሰ። የጻድቃንን ማደሪያና ብዙ ዋጋቸውን የኃጥአንንም ኵነኔና እየራሱ የሆነ ሥቃያቸውን እግዚአብሔር እስከ አሳየው ድረስ ብዙ ተጋደለ። ቅዱስ ጐርጐርዮስ ሃገሩ ሮሃ (ሶርያ አካባቢ) ሲሆን ረዓዬ ኅቡዓት (ምሥጢራትን የተመለከተ) ይባላል:: ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ:- ቅዱሱ ተወልዶ ባደገባት ሃገር ይህ ቀረው የማይባል ኃጢአተኛ ሰው ነበር:: ታዲያ ምንም ኃጢአተኛ ሰው ቢሆን እመቤታችን ድንግል ማርያምን በፍፁም ልቡ ይወዳት ነበርና በመዳን ቀን ጥሪ ለንስሐ አበቃችው:: ከዚያች ዕለት ጀምሮም ቅዱስ የእግዚአብሔር ሰው ንጹሕ የቤተ ክርስቲያን መስዋዕት ጽኑዕ የበርሃ ምሰሶ ሆነ:: ድንግል እመቤታችንም ከነሥጋው ወደ ሰማያት ወስዳ ገነትና ሲዖልን አሳይታ ከአዳም፣ ኖኅ፣ አብርሃም፣ ሙሴ፣ ዳዊትን ከመሰሉ ቅዱሳን ጋር አስተዋውቃ ከዚህም በላይ የሆነና በሰብአዊ አንደበት የማይነገር ብዙ ምሥጢር አሳይታ ወደ ምድር መልሳዋለች:: ቅዱስ ጐርጐርዮስ በሰማይ (በገነት) በነበረው ቆይታ ክብረ ቅዱሳንን ተመልክቶ አድንቋል:: በተለይ በፍጹምነት ድንግልናቸውን የጠበቁ ቅዱሳንና ቅዱሳት ደናግል አኗኗራቸው ከአምላክ እናት ከሰማይ ንግሥት ከእመቤታችን ከድንግል ማርያም ጋር መሆኑን አይቷል:: "የለበሱት ልብስም በፍጡር አንደበት ተከናውኖ ሊነገር የሚቻል አይደለም" ይላል:: የደናግል ፊታቸው ከፀሐይ 7 እጅ ያበራልና ግርማቸው ያስፈራል:: ቅዱሱ ሰው በዚያው በሰማይ ሳለ ደግሞ ይህንን ተመለከተ:: አንድ አረጋዊ ጽሕሙ ተንዠርግጐ የብርሃን ካባ ላንቃ ለብሶ ይመጣል:: ቅዱሳን መላእክት በፊት በኋላ በቀኝ በግራ ከበውት ሳለ እግዚአብሔርን ሊያመሰግን ጀመረ:: "እግዚኦ እግዚእነ ጥቀ ተሰብሐ ስምከ በዲበ ምድር (አቤቱ ጌታችን በምድር ሁሉ ስምህ የተመሰገነ ሆነ)" ሲል . . . መላእክቱ በዝማሬ አጀቡት:: በዚህ ጊዜም ታላቅ መናወጥ ሆነ:: ደናግሉም የቅዱሱን ሽማግሌ በረከቱን ተሳተፉ:: ይህ አመስጋኝ ሽማግሌ ልበ-አምላክ ጻድቅ የዋህና የእሥራኤል ንጉሥ የሆነው ዳዊት ነበር:: በምን ታወቀ ቢሉ:- በበገናው:: አንድም እመቤታችን "አባቴ ዳዊት!" ብላ ስትጠራው ጐርጐርዮስ ሰምቷልና:: በመጨረሻም እመቤታችንን በፍጹም ክብርና ግርማ ተመልክቷት ሐሴትን አድርጓል:: እመብርሃንም "ተወዳጅና ንጹሕ ሰው ነህ" ስትል ቅዱስ ጐርጐርዮስን አመስግናዋለች:: ስለዚህ ዓለምም እንዲህ የሚል መልእክትን ልካለች::

🔴#ስንክሳር መጋቢት_1 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መጋቢት አንድ በዚህች ቀን የኢየሩሳሌም አገር ኤጲስቆጶስ #ቅዱስ_በርኪሶስ አረፈ፣ የሰማዕቱ #የቅዱስ_እለእስክንድሮስ መታሰቢያው ነው፣ የሄኖክ ልጅ #ቅዱስ_ማቱሳላህ የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_በርኪሶስ መጋቢት አንድ በዚህች ቀን የኢየሩሳሌም አገር ኤጲስቆጶስ ቅዱስ በርኪሶስ አረፈ። ይህም አባት ክርስቲያኖችን በሚወዳቸው በቄሣር እለእስክንድሮስ ዘመነ መንግሥት ተሹሞ ሳለ ሐዋርያት ሲጠብቋቸው እንደነበረ በበጎ አጠባበቅ ሕዝቡን ጠበቃቸው። ከጥቂት ጊዜ በኋላ እለእስክንድሮስ ሞተ ከእርሱም በኋላ ቄሣር መክስሚያኖስ ነገሠ፡፡ ክርስቲያኖችንም በጽኑዕ መከራ አሠቃያቸው ከእርሳቸውም ብዙዎችን ገደላቸው። ሀገሮቻቸውን ትተው የተሰደዱም አሉ። ይህም አባት ሽሽቶ ወደ ገዳም ገባ ሕዝቡም ፈልገው አጡት። ከዚህም በኋላ ስሙ ዲዮስ የተባለ ሌላ ኤጲስቆጶስ በላያቸው ሾሙ። እርሱም በጥቂት ቀን አረፈ። ከዚህ በኋላ ስሙ አግርንዲኖስ የሚባል ሌላ ኤጲስቆጶስ ሾሙ። የስደቱም ወራት በአለፈ ጊዜ ይህ አባት በርኪሶስ ወደ ኢየሩሳሌም ከተማ ተመለሰ። አግርንዲኖስ የሚባል ሌላ ኤጲስቆጶስ ሹመው አገኛቸው። ወደርሳቸውም በደረሰ ጊዜ ሕዝቡ በመምጣቱ ደስ አላቸው አግርንዲኖስም ተመልሶ በመንበረ ጵጵስናው ላይ እንዲቀመጥ ለመነው በታላቅ ድካምም በወንበሩ ላይ አስቀመጡት። ከአግርንዲኖስም ጋራ አንዲት ዓመት ኖረ አግርንዲኖስም አረፈ። አባ በርኪሶስም እጅግ እስኪያረጅና እስኪደክም ድረስ ኖረ ወገኖቹንም ሌላ ኤጲስቆጶስ በላያቸው እንዲሾሙ ለመናቸው እነርሱም አይሆንም አሉ። በዚያም ወራት የቀጰዶቅያ ኤጲስቆጶስ ስሙ እለእስክንድሮስ የሚባል አንድ ሰው ነበር። እርሱም በውስጥዋ ሊጸልይና ወዳገሩ ሊመለስ ወደ ኢየሩሳሌም መጣ። ሥራውንም በጨረሰ ጊዜ የበዓሉም ቀኖች በተፈጸሙ ጊዜ ወዳገሩ ሊመለስ ወደደ። በመድኃኒታችን ትንሣኤ በዓል በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ወደ ኢየሩሳሌም ከተማ መግቢያ ወደ ዕገሌ ደጃፍ ውጡ ወደ ደጃፉ መጀመሪያ የሚገባውን ያዙት በጵጵስና ሥራም ይረዳው ዘንድ ከበርኪሶስ ጋራ አድርጉት የሚል ቃል እነሆ ተሰማ። ወጥተውም ወደ ደጃፉ በደረሱ ጊዜ እለእስክንድሮስን አገኙት ይረዳውም ዘንድ ያለ ፈቃዱ ከአባት በርኪሶስ ጋራ አደረጉት። እስከሚአርፍበትም ጊዜ አብሮት ኖረ። መላ የሕይወቱ ዘመን አንድ መቶ አሥራ ሰባት ዓመት ሆነ ኤጲስቆጶስነት ሳይሾም ሰማንያ አንድ ዓመት ኖረ በሹመቱም ላይ ሠላሳ ስድስት ዓመታትን ኖረ። እግዚአብሔርንም አገልግሎ በሰላም አረፈ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_እለእስክንድሮስ በዚህችም ዕለት የሰማዕቱ የቅዱስ እለእስክንድሮስ መታሰቢያው ነው። ይህም ቅዱስ ሰማዕት የሮም ሀገር ሰው ነው ለእርሱ ባለመታዘዙና ለረከሱ ጣዖቶቹ ባለመሠዋቱ ከሀዲው መክስሚያኖስ ጽኑዕ ስቃይን አሠቃየው። እጅግ ከባድና ታላቅ የሆነ ደንጊያ በእጆቹና በእግሮቹ ላይ አሥሮ ሰቀለው። ብዙ ግርፋትንም ገረፈው ጐኖቹንም ቀደደ በፊቱም ላይ የእሳት መብራት ጨመሩ። ሥቃዩንም ባልፈራ ጊዜ ራሱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ። በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕታትን አክሊል ተቀዳጀ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_ማቱሳላ ዳግመኛም በዚህች ዕለት የሄኖክ ልጅ የማቱሳላህ የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው፡፡ እርሱም 969 ዓመት የኖረ ሲሆን የአዳም 7ኛ ትውልድ የሆነው የሄኖክ ልጅ ነው፡፡ አዳም ሴትን ወለደ፣ ሴት ሄኖስን፣ ሄኖስ ቃይናን፣ ቃይናን መላልኤልን፣ መላልኤል ያሬድን፣ ያሬድ ሄኖክንመ ሄኖክ ማቱሳላህን ወለደ፡፡ ማቱሳላህም ላሜሕን ወለደ፣ ላሜህም ኖኅን ወለደ፡፡ ማቱሳላህም 969 ዓመት ከኖረ በኋላ ዐረፈ፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን ልዩ የሆነች በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12

🔴#ስንክሳር የካቲት_30 #ቅዱስ_ዮሐንስ_መጥምቀ_መለኮት አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የካቲት ሠላሳ በዚህች ዕለት የመጥምቁ ዮሐንስ የከበረች ራሱ ተገኘች። ይህም እንዲህ ነው ከሀዲ ኄሮድስ የከበረ ዮሐንስን ራሱን ይቆርጡት ዘንድ በአዘዘ ጊዜ በእሥር ቤት ራሱን ቆርጠው ወደ ኄሮድስ አቀረቧት እርሱም ለወገኖቹ በማሳየት በቅዱስ ዮሐንስ ላይ ስለ አደረገው ሥራ እንደሚያዝን ገለጠላቸው የክቡር ዮሐንስንም ራስ በቤቱ ውስጥ አስቀራት። የፊተኛዪቱ ሚስቱ የንጉሥ አርጣ ልጅ ግን በአበረራት ጊዜ ወደ አባቷ መጥታ በፊቱ አለቀሰች ኄሮድስ በእርሷ ላይ ያደረገውን ሁሉ እርሷን አሳዶ የወንድሙን ሚስት ኄሮድያዳን እንዳገባ ነገረችው። በዚያንም ጊዜ ንጉሥ አርጣ ተቆጥቶ ተነሣ ሠራዊቱንም ሰብስቦ ወደ ገሊላ ዘመተ የገሊላንም ሀገሮች ሁሉ አጠፋ በእሳትም አቃጠለ። ንጉሥ ጢባርዮስ ቄሣር ይህን ነገር በሰማ ጊዜ ኄሮድስ በአባረራት በልጁ ምክንያት ንጉሥ አርጣ ይህን እንዳደረገም በአስረዱት ጊዜ ስለዚህ ንጉሥ ጢባርዮስ ቄሣር ተቆጣ ኄሮድስንም ወደ ሮሜ ከተማ ወደርሱ አስቀረበው በእርሱም ምክንያት የሀገሮች ጥፋት በመደረጉና ታላቁን ነቢይም ስለ መግደሉ ከሹመቱ ሻረውና እንድልኩ ወደሚባል አገር አጋዘው በዚያም በክፉ አሟሟት ሞተ። የቅዱስ ዮሐንስ ራስ ግን በኄሮድስ ቤት ተቀብራ ትኖር ነበር ከዚህም በኋላ ንጉሥ ጢባርዮስ ጭፍሮቹን ልኮ የኄሮድስን ቤት አስፈረሰ ጥሪቱን ሁሉ ወሰደ ለሚያየውም ሁሉ አርአያና ተረት ሆነ ያለ ጣሪያና ያለ ደጃፍ ቀርቷልና ነጋዴዎችም መነሃሪያ አድርገው ያድሩበት ነበር። በዚያንም ወራት በገንዘብ ድኆች በሃይማኖት ባለጸጎች የሆኑ ሁለት ሰዎች ነበሩ እነርሱም ሊሰግዱ የከበረች የአርባ ቀን ጾምንም ሊጾሙ ወደ ኢየሩሳሌም ተጓዙ ይህም ከብዙ ዘመን በኋላ ነው። ምሽትም በሆነ ጊዜ ምድረ በዳ በሆነ በኄሮድስ ቤት ውስጥ አደሩ ቅዱስ ዮሐንስም ከእርሳቸው ለአንዱ በሕልም ተገለጠለትና የከበረች ራሱ ያለችበትን ቦታ አስረዳው ወደቤቱም ተሸክሞ ይወስዳት ዘንድ አዘዘው በነቃም ጊዜ ራእይን እንዳየ ለባልንጀራው ነገረው። ቅዱስ ዮሐንስም ወደአመለከተው ወደዚያ ቦታ ተነሥተው በአንድነት ሔዱ በቆፈሩም ጊዜ የሸክላ ዕቃ አግኝተው ከፈቷት ያን ጊዜ እጅግ የሚመስጥ በጎ መዓዛ ወጣ የቅዱስ ዮሐንስንም ራስ አገኙዋት ከእርሷም ተባረኩ ወደ ሸክላውም ዕቃ መለሱዋትና በፊት እንደ ነበረ አፉን ዘጉ ያም ሰው ከእርሱ ጋር ወደ ቤቱ ወሰዳት ታላቅ ክብርንም አከበራት ሁል ጊዜም የሚያበሩ መብራቶችን በፊቷ አኖረ። የዚያም ሰው ዕረፍቱ በቀረበ ጊዜ ለእኅቱ ነገራት እርሷ ቅድስና ስለአላት እርሱ ሲሠራው እንደነበረ ትሠራ ዘንድ አዘዛት እርሷም የምታከብራትና ሁል ጊዜ መብራትንም የምታበራ ሆነች። የቅዱስ ዮሐንስም ራስ ወደ አርዮሳዊ ሰው እስከ ደረሰች ድረስ ከአንዱ ሰው ወደ አንዱ ሰው የምትፋለስ ሆነች ይህም ሰው በከሀዲው አርዮስ እምነት ውስጥ እያለ የቅዱስ ዮሐንስ ራስ ድንቆች ተአምራቶችን እንደምታደርግ ያስብ ነበር። የከበረ ዮሐንስም ከእርሱ የሚበልጥ ሰው በላዩ አስነሣበትና ከዚያ ቦታ አሳደደው ያም ቦታ አባ ቄርሎስ በኢየሩሳሌም ሀገር አባ አንያኖስ በሀገረ ኀምዳ ኤጲስቆጶስነት እስከ ተሾሙ ድረስ ፈጽሞ ሰው የማይኖርበት ምድረ በዳ ሆነ። ቅዱስ ዮሐንስም ለአባ አንያኖስ በሕልም ተገልጦ የከበረች ራሱ ያለችበትን ቦታ ነግሮ አመለከተው አባ አንያኖስም ሒዶ እንደ ዛሬው ግንቦት ሠላሳ ከዚያ አወጣት ይህም የካቲት ሠላሳ ቀን ከአገኙዋት በኋላ ዳግመኛ ያገኙበት ነው። እንዲህም የሚል አለ የከበረ ዮሐንስ አፈወርቅ ተናገረ ይህም ኄሮድስ በአዘዘ ጊዜ ቅዱስ ዮሐንስ በእሥር ቤት ሳለ ራሱን በሰይፍ ቆርጠው በጻሕል አድርገው ወደ ኄሮድስ አመጡለት እርሱም ለኄሮድያዳ ልጅ ሰጣት እርሷም ለእናቷ ወስዳ ሰጠች። ይቺም የረከሰች አመንዝራ ልትዳስሣት በወደደች ጊዜ በወጭቱ ውስጥ ጠጒሩዋ ተዘርግቶ ወደ አየር በረረች በአየርም ሁና የወንድምህን ሚስት ልታገባ አይገባህም እያለች የምትጮኽ ሆነች እንዲህም እያለች ዐሥራ አምስት ዓመት ኑራ በዓረቢያ ምድር ዐረፉ በዚያ ተቀበረች። ነጋድያንም በዚያ ቦታ የሚያድሩ ሆነ በእግዚአብሔርም ፈቃድ ሁለት አማንያን ነጋዴዎች ወደዚያ ቦታ ደርሰው አደሩ ቅዱስ ዮሐንስም በሕልም ተገለጠላቸውና የከበረች ራሱን ያወጡ ዘንድ አዘዛቸው እነርሱም አወጡዋት ከእርሳቸውም ጋር ወደ ቤታቸው ወስደው ታላቅ ክብርን አከበሩዋት። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም መለኮትን በአጠመቀ በከበረ ዮሐንስ ጸሎት ይማረን፤ ልዩ የሆነች በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12

የፊታችን ቅዳሜ 12:00 ስለ ታላቁ የእስክንድርያ ሊቅ ቅዱስ አትናቴዎስ የከበረች ህይወቱና ኀይል ስለሚሆን ትምህርቱ ለመማማር ቀጥሮ ይዘናል።
የፊታችን ቅዳሜ 12:00 ስለ ታላቁ የእስክንድርያ ሊቅ ቅዱስ አትናቴዎስ የከበረች ህይወቱና ኀይል ስለሚሆን ትምህርቱ ለመማማር ቀጥሮ ይዘናል።

#እናስታውሶ ዛሬ 12:00 ቦታ በደብሩ ልማት ቢሮ ሰዓት ስለምታከብሩ እናመሰግናለን።
#እናስታውሶ ዛሬ 12:00 ቦታ በደብሩ ልማት ቢሮ ሰዓት ስለምታከብሩ እናመሰግናለን።

#እናስታውሶ ዛሬ 12:00 ቦታ በደብሩ ልማት ቢሮ
#እናስታውሶ ዛሬ 12:00 ቦታ በደብሩ ልማት ቢሮ

በአንድም ወቅት በሀገራችን የእህል መታጣት ሆነና ቅድስት እናታችን ዘወትር እንደምታደርገው የኪዳምሕረትን ዝክር ልታደርግ ብላ ዝክሩን የምታደርግበት እህል አጣች፡፡ ደናግል ልጆቿንም ጠርታ ትንሽ ዱቄት እንዲያመጡላት ነግራቸው አመጡላት፡፡ በዚያችም ትንሽ ዱቄት ላይ ጸሎት አድርጋ ከጨረሰች በኋላ ‹ወደ ቦታው መልሱት› አለቻቸው፡፡ በማግስቱም እንስራው ጋኑ ሁሉ በዱቄት ተሞልቶ አግኝተውታል፡፡ ቅድስት እናታችንና ልጆቿም የየካቲት ኪዳነ ምሕረትን በዓል በታላቅ ደስታ አክብረዋል፡፡ መልአኩም እናታችንን ከቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም መልሶ ወደ ኢትዮጵያ ካመጣት በኋላ ዛሬ ገዳሟ ካለበት ቦታ ስትደርስ ከቦታዋ ላይ ዓምደ ብርሃን ተተክሎ በቀስተ ደማና ተከቦ አይታ ‹‹ይህች ቦታ ምንታምር›› ብላ ጠራቻት፡፡ በመድኃኔዓለምም ትእዛዝ የቅድስት ኪዳነ ምሕረትን ቤተ ክርስቲያን በአንዲት ቀን ብቻ ሠርታለች፡፡ ቦታዋ ዛሬም ድረስ ‹ምንታምር› እየተባለች የምትጠራ ሲሆን ቅድስት እናታችን ፍቅርተ ክርስቶስ የሠራቻት በስሚዛ (በሰንሰል) እንጨት፣ በአይጥ ሐረግ፣ በነጠላ ማገር አድርጋ የግድግዳ ቤተ መቅደስ በአንዲት ቀን ብቻ ሠርታ በታኅሣሥ 16 ቀን በዕለተ እሁድ ቅዳሴ ቤቷን አክብራለች፡፡ በዚህም ጊዜ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤልና ቅዱስ መሲፋይል በክንፋቸው አፈር ከኢየሩሳሌም አምጥተው በቦታዋ ላይ ቀላቅለውበታል፡፡ ጌታችንም ከብርሃን እናቱ ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋር ለፍቅርተ ክርስቶስ ተገልጦላት ቦታዋን ባርኮላት እስከዕለተ ምፅዓትም ድረስ እንደማትፈርስ ቃልኪዳን ገብቶላታል፡፡ ለምሳሌ በአንድ ወቅት ከባድ የእሳት ቃጠሎ ተነስቶ ጫካውን ሁሉ ሲያቃጥል ከቤተክርስያኗ ላይ ግን ለምልክት ያህል ጫፏ ላይ ያለችውን የሰጎን እንቁላል ብቻ አቃጥሎ ቤተ መቅደሷን አልፎ ሄዶ ጫካውን ሁሉ አቃጥሏል፡፡ እናታችን ፍቅርተ ክርስቶስ በአንዲት ቀን ብቻ በተአምራት የሠራቻት ቤተ ክርስቲያኗ ተሠርታ ባለቀች ጊዜ ጌታችን ለእናታችን ተገልጦላታል፡፡ ጌታችንም በተገለጠላት ጊዜ ቤተ ክርስቲያኗ በአራቱም አቅጣጫ ለጌታችን ሰግዳለች፡፡ ዛሬም ድረስ ቤተ ክርስቲያኗ በአራቱም አቅጣጫ ሆነው ሲመለከቷት በተቃራኒው አቅጣጫ እየሰገደች ትታያለች፡፡ በምሥራቅ አቅጣጫ ሆነው ቢያዩዋት ወደ ምዕራብ ሰግዳ ትታያለች፤ በምዕራብም ሆነው ቢያዩዋት ወደ ምሥራቅ ሰግዳ ትያለች፡፡ በሰሜን አስራቅ አቅጣጫ ሆነው ቢያዩዋት ወደ ደቡብ ሰግዳ ትታያለች፤ በደቡብም ሆነው ቢያዩዋት ወደ ሰሜን ሰግዳ ትያለች፡፡    እናታችን ፍቅርተ ክርስቶስ በተሰጣት ቃልኪዳን መሠረት በገዳሟም ውስጥ መርዘኛ እባብም ቢሆን ሰውን ወይም እንስሳትን ቢነድፍ መርዙ ምንም አይጎዳም፡፡ እንዲሁም ጌታችን ገዳሟን መናፍቃን ወይም ከሐዲያን እንደማይረግጧት ቃልኪዳን ሰጥቷታል፡፡ ለምሳሌ የጣሊያን ጦር በሀገራችን የተለያዩ ገዳማትን እያጠፋ መነኮሳትን እየገደለ ከፍተኛ ጥፋት ባደረሰበት ወቅት ይህችንም ገዳም ለማጥፋትና መነኮሳቶቹንም ለመግደል መጥቶ ነበር፡፡ መነኮሳቶቹም ይህን ሰምተው ለሰማዕትነት ተዘጋጅተው ጠበቁ ነገር ግን የጦር አዛዡና ሠራዊቱ የገዳሟን ክልል አልፈው መግባት አልቻሉም፣ የገዳሟ ክልል ላይ ሲደርሱ በተአምራት እግራቸው ተሳስሮ መቆም መቀመጥ ሳይችሉ ቀርተዋል፡፡ የጦር አዛዡም ‹‹ክርስቶስ ከዚች ገዳም አለ›› ብሎ ሃምሳ ጠገራ ብር ሰጥቶ ወደመጣበት ተመልሷል፡፡ መድኃኔዓለም ክርስቶስ በዚህች ገዳም ላይ ለቅድስት እናታችን ድንቅ ድንቅ ቃልኪዳን ከሰጣት በኋላ እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ በየካቲት 29 ቀን በታላቅ ክብር ዐርፋለች፡፡ በሥጋዋም ላይ ታላቅ የብርሃን አምድ ተተክሎ የታየ ሲሆን እንደፀሐይም ከጠዋት እስከ ማታ ያበራ ነበር፡፡ በመካነ መቃብሯም ላይ እስከ አርባ ቀን ድረስ ብርሃን ተተክሎ ታይቷል፡፡               ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_ቢላካርዮስ_ዘሃገረ_አርሞኒ  በዚችም ዕለት የአርሞኒ  ሀገር ኤጲስቆጶስ የከበረ ቢላካርዮስ በሰማዕትነት ሞተ። ይህም አባት ፈጽሞ እስከ አረጀ ድረስ በተሾመበት ወንበር ብዙ ዘመናት ኖረ ብዙ ድርሳናትንና ተግሣጻትንም ደረሰ እሊህም ስለከበረች የልደት በዓልና ስለ እምቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስለ ሞትና ስለ መቃብር በኃጥአንም ላይ ስለ ሚደርስባቸው ሥቃይ ስለ መድኃኒታችንም የረቀቀ ጥበብ ስለ ከበሩ በዓላትም ናቸው ሕይወት በሆኑ ትምህርቶቹም ብዙ ነፍሳትን መሥዋዕትን አድርጎ ለእግዚአብሔር አቀረበ። በክርስቲያንም ወገኖች ላይ የስደትና የመከራ ወራት በሆነ ጊዜ በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ደሙን ሊያፈስ ወደደ ሕዝቡንም ሰብስቦ በቀናች ሃይማኖት ይጸኑ ዘንድ አዘዛቸው። ስለ ጌታችን ኢየሱስ ደሙን ሊያፈስ ይሻልና እነርሱ እንግዲህ ፊቱን እንደማያዩት ነገራቸው። ሰምተውም አለቀሱ ስለ መለየታቸውም እጅግ አዘኑ የሙት ልጆች እንሆን ዘንድ ለምን ትተወናለህ አሉት ማስቀረትና ማስተውም ባልተቻላቸው ጊዜ ከእርሳቸው ዘንድ ወጥቶ ወደ መኰንኑ ሔደ በፊቱም ቁሞ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ መኰንኑም ብዙ አሰቃየው። ሕዝቡም ብዙ ልመናን አብዝተው ለመኑት ራስህን አድን ከከተማም ውጣ አሉት እርሱም ልባቸውን ደስ ያሰኝ ዘንድ በሥውር እወጣለሁ አላቸው። በዚያችም ሌሊት ሰማዕትን ትሆን ዘንድ የተመኘኸውን በጎ ምክር ለምን ረሳህ እንደሚለው ሰው ሁኖ ራእይን አየ። ከዚህም በኋላ ተመልሶ ለመኰንኑ ተገለጠለት በዚያንም ጊዜ ራሱን በሰይፍ ይቆርጡት ዘንድ መኰንኑ አዘዘ የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ ሥጋውንም ምእመናን አንሥተው ወሰዱት ለኤጲስቆጶሳትም እንደሚገባ አክብረው ገንዘው በመቃብር አኖሩት። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12

🔴#ስንክሳር የካቲት_29 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የካቲት ሃያ ዘጠኝ በዚች ቀን ታላቋ ሐዋርያዊት እናታችን የእመ ምኡዝ #ቅድስት_ፍቅርተ_ክርስቶስ ዕረፍቷ ነው፣ የአርሞኒ ሀገር ኤጲስቆጶስ የከበረ #ቅዱስ_ቢላካርዮስ በሰማዕትነት ሞተ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅድስት_ፍቅርተ_ክርስቶስ የካቲት ሃያ ዘጠኝ በዚች ቀን ታላቋ ሐዋርያዊት እናታችን የእመ ምኡዝ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ኢትዮዽያዊት ዕረፍቷ ነው፡፡ እናታችን ፍቅርተ ክርስቶስ ወይም እመ-ምዑዝ በጎንደር ክፍለ ሀገር በደራ ፎገራ አንበሳሜ በሚባለው ቦታ የአብርሃምና የሣራ ምግባር ካላቸው ከአባቷ ከላባ ከእናቷ ከወንጌላዊት ጌታችን በተወለደበት ዕለት ታኅሣሥ 29 ቀን በታዘዘ መልአክ አብሳሪነት ተወለደች፡፡ በተወለደችም ጊዜ በእግሯ ቆማ ‹‹በማኅየዊ ቸርነትህ ከጨለማ ወደ ብርሃን ላወጣኸኝ ለአብ ምስጋና ለወልድ ምስጋና ለመንፈስ ቅዱስም ምስጋና ይገባል›› ብላ አምላኳን አመስግናለች፡፡ ቤተሰቦቿ ያገኙዋት በስዕለት ሲሆን ስመ ክርስትናዋም ማርያም ጸዳለ ተባለ፡፡ ፍቅርተ ክርስቶስ የሚለው የቆብ (የምንኩስና) ስሟ ነው፡፡ ዕድሜዋ ለትምህርት እንደደረሰ እግዚአብሔር የላከው አንድ ደገኛ መነኩሴ ወደ እርሷ በመሄድ የዳዊትን መዝሙር፣ የብሉያትና የሐዲሳት መጻሕፍትንና የቤተክርስቲያንን ትምህርት ሁሉ በሚገባ አስተምሯታል፡፡ እናታችን ፍቅርተ ክርስቶስ በነበረችበት ዘመን ዐፄ ሱስንዮስ ‹‹ሁለት ባሕርይ›› የሚለውን የረከሰ የሮማውያንን ሃይማኖት የአገራችን ሕዝዝ ሁሉ እንዲያምን በማወጁ ምክንያት በሀገራችን ከፍተኛ የሆነ የሃይማኖት ግጭት ስለተነሣና ከ8ሺህ በላይ ክርስቲያኖች በግፍ ተጨፍጭፈው ሲያልቁ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ከእነ አቡነ ስምዖንና ከሌሎችም ቅዱሳንና ቅዱሳት ጋር ተሰልፋ ሰማዕትነትን ተቀብላ ለሃይማኖቷ መስክር ሆናለች፡፡ ባለቤቷ ዘርዐ ክርስቶስም በሰማዕትነት ዐርፎ ሰባት አክሊላት ወርደውለታል፡፡ ዐፄ ሱስንዮስ ለፖለቲካዊ ጥቅም ብሎ የረከሰች የሮማውያንን ሃይማኖት በአገራችን ላይ እንዳወጀ ሊቀ ጳጳሱ አቡነ ስምዖን ካህናትንና ክርስቲያን ልጆቻቸውን አነሳስተው እያስተማሩና እያጠነከሩ እያለ በጦር ተወግተው በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡ ሊቀ ጳጳሱ አቡነ ስምዖንም በሰማዕትነት ከማረፋቸው በፊት ግን እነ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስን፣ ቅድስት ወለተ ጴጥሮስን፣ ቅድስት አካለ ክርስቶስን፣ ቅድስት እመ ወተትንና ሌሎቹንም ቅዱሳንና ቅዱሳት አነሳስተው ባራ ሄደው ንጉሡን መክረውታል፣ ገሥጸውታል፡፡ ንጉሡ ግን ከፍተኛ ፖሊቲካዊ ጥቅም እንደሚያገኝ ሮማውያን ቃል ገብተውለት ስለነበር ቅዱሳን አባቶችና ቅዱሳት እናቶ አብዝተው ቢመክሩትም ከክህደቱ ሊመለስ አልቻለም፡፡ ይልቁንም ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስን የሃይማኖቷን ጽናት ስላየ ሥጋዋ እየተቆረሰ መሬት ላይ እስኪወድቅ ድረስ በብረት በትር አጥብቆ ያስገርፋት ጀመር፡፡ በመጨረሻም ምድር እየሰወረቻት ለመግረፍ የማይመቻቸው ቢሆን ከሌሎቹ ሰማዕታት ጋር አንገቷን በሰይፍ አስቆርጦታል፡፡ በዚህም ጊዜ ፍጹም ጨለማ ሆኖ ምድርም ተነዋወጠች፡፡ ስምንት ሺህ አሥር ቅዱሳንም በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስን አንገቷን በሰይፍ ቢቆርጧትና በሞት ብታርፍም ነገር ግን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ገነትንና ሲኦልን አሳይቶ 14 ቀን በሰማያዊት ኢየሩሳሌም ከተቀመጠች በኋላ እንደገና እንደተኛ ወይም ከእንቅልፉ እንደሚነቃ ሰው ከሞት አስነሥቶ ወደ ቦታዋ መለሳት፡፡ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤልም ከሞት ካስነሣት በኋላ እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ መናኒ ሆና በየገዳሙና በየአድባራቱ እየሔደች ዓለምን ስትዞር ያቀናቻቸው ብዙ ገዳማት አሉ፡፡ ለምሳሌ ከተሰዓቱ ቅዱሳን አንዱ በሆኑት በአባ ጉባ ተመሥርታ በግራኝ ወረራ ጠፍታ የነበረችውን ራማ ኪዳነምሕረት አንድነት ገዳምን አቅንታ የወንድና የሴት ገዳም ብላ ሥርዓት ሠርታለች፡፡ ወደ ኢየሩሳሌምም በመሄድ ላይ ሳለች በመንገድ ሰውን የሚበሉ ፍጡሮች ወደሚኖሩበት አካባቢ ስትደርስ 60 የሚሆኑ አገልጋዮቿን ለመብላት ይዘው ሳር ቅጠል እንዲበሉ በማድረግ ዐይናቸውን በጉጠት በማውጣት 4 ወራት በጨለማ ቤት ውስጥ ዘጉባቸው፡፡ ሰይጣንንም ያመልኩ ነበርና ከ4 ወራት በኋላም በዓል አድርገው ለመብላት ከእሳት ውስጥ ጨመሯቸው፣ ነገር ግን ጌታችን በቸርነቱ ጠብቋቸዋልና እነ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስን ምንም አልሆኑም፡፡ ያንጊዜም ሰው በላዎቹ ‹‹እናንተ ሰዎች ምንድን ናችሁ?›› ብለው ጠየቋቸው። ቅድስት እናታችን ፍቅርተ ክርስቶስም ክርስቲያን መሆናቸውንና እነርሱ የሥላሴ ሕንፃ የሆነውን የሰውን ልጅ መብላት እንደሌለባቸው ብታስተምራቸው ‹‹ምን እንበላለን?›› አሏት፡፡ እርሷም ከራማ ኪዳነ ምሕረት ስትነሳ የእህል ዘርን ለአገልጋዮቿ አሰይዛ ስለነበር ከዚያ ስንዴ ወስዳ ዘራችው፡፡ ስንዴውም በአንድ ቀን ብቻ ተዘርቶ በቅሎ፣ ታጭዶ፣ ደርቆ፣ ተፈጭቶ ለምግብነት በቅቷል፡፡ ቅድስት እናታችንም ቀምሳ ስታቀምሳቸው እንደማር እንደወተት የሚጣፍጥ ሆኖላቸው በደስታ ተመግበውታል፡፡ ከዚያም እንደዚህ እያደረጉ እየሠሩ እንዲበሉ አስተምራ አስጠምቃቸው ስድስት አብያተ ክርስቲያናትን አሠርታላቸዋለች፡፡ ወንጌልን፣ ስንክሳርን፣ ሃይማኖተ አበውን፣ ግንዘትን፣ መዝሙረ ዳዊትን፣ አርጋኖንን ሁሉ በእጇ ጽፋ አስቀመጠችላቸው፡፡ እናታችን ፍቅርተ ክርስቶስ ምን ያህል የከበረች ‹‹ሐዋሪያዊት›› እንደሆነች ከዚህ ልብ ይሏል፡፡    የብርሃን እናቱ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ተገልጣላት በልጇ ምክንያት ስለደረሱባት ሀዘኖች አውርታላታለች፡፡ የፈለገችውንም እንድታደርግበት በእጇ ያለውን መስቀል ለፍቅርተ ክርስቶስ ሰጥታታለች፡፡ በዚህም መስቀል እናታችን ፍቅርተ ክርስቶስ ባሕር ከፍላ ደቀ መዛሙርቶቿን አሻግራለች፡፡ የአባታችን የቅዱስ ኤዎስጣቴዎስን ገድል በማንበብና በመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል እርዳታ ባህሩን በአጽፏ ተሻግራ ወደ ሀገረ ናግራን ሄዳለች፡፡ እንዲሁም በበትረ መስቀሏም እንደ ዘርዐ ቡሩክ ከባሕር ውስጥ የሠጠሙ የደቀ መዛሙርቶቿን መጻሕፍት ምንም ሳይሆኑ ማውጣት ችላለች፡፡ እናታችን በሁሉም ሀገር እየዞረች ቅዱሳት መካናትን ትሳለም ነበር፡፡ በደብረ ዳሞም ሄዳ ‹‹ሴቶች መውጣት አይችሉም›› ቢሏት በሀዘን ስታለቅስ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል በሥውር ወስዶ ከዓምባው ላይ አውጥቶ ከቤተ መቅደሱ አድርሷታል፣ አቡነ አረጋዊም ተገልጸውላት ባርከዋታል፡፡ በዚያም ሥጋ ወደሙን በእጃቸው ተቀብላለች፡፡ እናታችን ወደ ኢየሩሳሌምም ሄዳ ቅዱሳት መካናትን እየተሳለመች ለ7 ዓመታት ቆይታለች፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም በዓምደ ብርሃን እየመራት ተመልሳ ወደ ሀገራችን መጥታ በድጋሚ ከሱስንዮስ ጋር ተሟግታለች፡፡ ሙታንንም እያስነሳች እንዲመሰክሩለት ብታደርግም እርሱ ግን ከጥፋቱና ከክህደቱ ሊመለስ አልቻለም፡፡ ነገር ግን እናታችን ፍቅርተ ክርስቶስ የተለያዩ ተአምራትን በማድረግ መልእክቷንም በንስር አሞራ አድርጋ እየላከች ትመክረው ነበር፡፡

🎉🎉🎉🎊🎊የምስራች 🎉🎉🎉🎊 ብዙዎቻችን ለነፍስና ለስጋችን ብዙ ጥቅም ያገኘንበት ሳምንታዊ የረቡዕ ውይይት በአዲስ ርዕስ የፊታችን ረቡዕ 29/06/15 ዓ.ም ይጀምራል። ስለዚህም በውይይቱ
🎉🎉🎉🎊🎊የምስራች 🎉🎉🎉🎊 ብዙዎቻችን ለነፍስና ለስጋችን ብዙ ጥቅም ያገኘንበት ሳምንታዊ የረቡዕ ውይይት በአዲስ ርዕስ የፊታችን ረቡዕ 29/06/15 ዓ.ም ይጀምራል። ስለዚህም በውይይቱ ተገኝተው የነፍስ ስንቅ ይቋጥሩ። ሰዓት ስለምታከብሩ እናመሰግናለን። የወጣት ትምህርት ክፍል

🔴#ስንክሳር የካቲት_28 #ቅዱስ_ቴዎድሮስ_ዘሮም አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የካቲት ሃያ ስምንት በዚች ዕለት በነገሥታት መክሲሞስና መክስምያኖስ ዘመን ሮማዊ ቅዱስ ቴዎድሮስ በሰማዕትነት አረፈ። እርሱም ከእስያ አውራጃ አስጢር ከሚባል አገር ነው። ይህንንም ቅዱስ በነገሥታት ዘንድ አማልክትን በማምለክ እርሱ እንደማይስማማ ወነጀሉት በዚያንም ጊዜ አስጠርተው ለአማልክት ለምን አትሰግድም አሉት እርሱም እኔ ክርስቲያን ነኝ ከሕያው እግዚአብሔር ልጅ ከጌታዬ ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ሌላ አላመልክም ብሎ መለሰላቸው። የበርብዮስጦስ ልጅ ንጉሡም ለአማልክቶቼ ብትገዛ በጭፍራዎቼና በመኳንንቶቼ ሁሉ ላይ አለቃ አድርጌ እሾምሃለሁ ብዙ ወርቅና ብር የከበሩ ልብሶችንም እሰጥሃለሁ አለው ቅዱስ ቴዎድሮስም ወርቅህና ብርህ ለጥፋት ይሁንህ እኔስ በንጉሤ በሕያው እግዚአብሔር ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ ባለጸጋና አለቃ ነኝ አለው። ንጉሡም ለአምላክህ ልጅ አለውን አለው የከበረ ቴዎድሮስም አዎን ከመለኮቱ ባሕርይ የተገኘ ከእርሱ ጋር ዓለምን የፈጠረ በእውነት ልጅ አለው ብሎ መለሰለት ንጉሡም አምላክህን ብናውቀው ልናገኘው እንችላለን አለው ቅዱስ ቴዎድሮስም ወደርሱ ከተመለስክ እንደ እኔ ጭፍራ ትሆናለህ የተወደደ መሥዋዕትም ያደርግሃል አለው። ንጉሡም ነገር አታብዛ ብዙ ገንዘብ እሰጥህ ዘንድ ለአማልክቶቼ መሥዋዕትን አቅርብ እንጂ አለው የከበረ ቴዎድሮስም ንጉሡን ረገመው ጣዖታቱንም ሰደበ በዚያንም ጊዜ ንጉሡ ተቆጣ። ልብሱንም እንዲገፉት በትምህርቱም ከአመኑ አሕዛብ ጋር በጨለማ ቤት ያሥሩት ዘንድ አዘዘ። የከበረ ቴዎድሮስም ጸለየ በሌሊትም ወጣ ዕንጨቶችንም ሰብስቦ ጣዖቶችን ሁሉ አመድ እስኪሆኑ ድረስ አቃጠላቸው እንዳይሰሙ በአገልጋዮቻቸው ላይ እግዚአብሔር ከባድ እንቅልፍ አሳድሮባቸዋልና። ለንጉሡም በነገሩት ጊዜ አጽንቶ አሠረውና ልዩ ልዩ በሆነ በጽኑ ሥቃይ አብዝቶ ያሠቃየው ዘንድ ለመኰንኑ ሰጠው መኰንኑም እንዲህ አለው ለንጉሥ ለምን አትታዘዘም ለአማልክቶችስ ለምን አትሠዋም የከበረ ቴዎድሮስም እኔስ ለረከሱ አማልክት አልሠዋም ለከሀዲ ንጉሥም አልታዘዝም ብሎ መለሰለት። መኰንኑም ይህን በሰማ ጊዜ እጅግ ተቆጣ ከወንበሩም ላይ ተነሥቶ እንደ ነብር ተወርውሮ አንገቱን አነቀውና የከበረ ቴዎድሮስን በምድር ላይ ጥሎ ፊቱን ጸፋው በእግሮቹም ረገጠው እግዚአብሔርም ትዕግስቱን አይቶ የመላእክት አለቃ ገብርኤልን ላከለት መኰንኑንም ገድሎ ከምድር ዐዘቅት አሠጠመው ለከበረ ቴዎድሮስም በእስያ ሀገር ውስጥ እየተዘዋወረ የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስን ሃይማኖት እንዲአስተምር መንፈሳዊ ፀዓዳ ፈረስን ሰጠው። ንጉሡም ይህን በሰማ ጊዜ የከበረ ቴዎድሮስን ከነፈረሱ እንዲይዙት በትምህርቱም የአመኑትን ሁሉ እንዲገድሉ መቶ ፈረሰኞች ወታደሮቹን ላከ። ከሴቶችና ከልጆች በቀር ስድስት ሺህ አርባ ስምንት ሰውን ገደሉ። ሊይዙትም ወደ ቅዱስ ቴዎድሮስ በደረሱ ጊዜ ፈረሱ በላያቸው ተወረወረ ከአፉም እሳትን አውጥቶ አመድ እስኪሆኑ አቃጠላቸው ነገር ግን ሌሎች አግኝተው ያዙትና ወደ ንጉሥ ወሰዱት እርሱም ወደ እሥር ቤት እንዲአስገቡት እንዳይበላና እንዳይጠጣም ደጃፎችን እንዲዘጉበት አዘዘ። ከዚህም በኋላ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጸለትና ቃል ኪዳን ሰጠው በዚያንም ጊዜ ከእሥር ቤት አውጥተው ዘቅዝቀው ሰቀሉት ደሙም እንደ ውኃ እስቲፈስ ከላም ቆዳ በተሠራ ጅራፍ ገረፉት ደሙ የነካቸውም ብዙ በሽተኞች ዳኑ ተአምራቱንም ያዩና የሰሙ በጌታችን አመኑ በዚያችም ቀን መቶ አርባ ስምንት ሰዎች ተገደሉ። እሊህን የተገደሉትንም ሰማዕታት ወደ እሳት ማንደጃ ውስጥ ከእርሱ ጋር ጨመሩአቸው በዚያንም ጊዜ ነፋስ ነፈሰ መብረቅና ነጐድጓድም ሆነ እሳቱንም አቀዝቅዞት የከበረ ቴዎድሮስ ምንም ሳይነካው ከእሳት ውስጥ ወጣ። ከዚህም በኋላ ንጉሡ የሚያደርግበትን በአጣ ጊዜ ኃምሣ አራት ልጥር የሚመዝን ልጓም አምጥተው አፉን እንዲለጒሙት እግሮቹንና እጆቹንም በችንካር ቸንክረው ለአንበሳ እንዲጥሉት አዘዘ። አንበሳውም ዕንባውን እያንጠባጠበ እንደ ሰው አለቀሰለት እንጂ ምንም አልነካውም። ጌታችንም ተገለጠለትና ስሙን ለሚጠራ መታሰቢያውንም ለሚያደርግ ገድሉንም ለሚጽፍ ዕድል ፈንታውን ከርሱ ጋር በመንግሥተ ሰማያት ያደርግ ዘንድ ቃል ኪዳንን ሰጠው። ከዚህም በኋላ የሁለት መቶ ሰው ሸክም ዕንጨት መቶ ልጥር ባሩድ መቶ ልጥር የዶሮማር መቶ ልጥር ነሐስ አመጡ ከማንደጃውም ጨምረው እጅግ እስከሚግል አነደዱት ጸሎቱንም ከፈጸመ በኋላ ቅዱስ ቴዎድሮስን ወደ ነደደው እሳት ወረወሩት ምስክርነቱንም ፈጸመ የመላእክት አለቆች ሚካኤልና ገብርኤል ነፍሱን ተቀበሉ በሦስት አክሊላትም አቀዳጁት ሥጋውንም አውሳብያ የተባለች የመኰንኑ ሚስት ወሰደች ዋጋው ብዙ በሆነ ሽቱም ገነዘችውና ወደ ገላትያ ወሰደችው በዕብነ በረድ ሣጥንም አድርጋ በዚያ ቀበረችው ቤተ ክርስቲያንም ሠራችለት ከሥጋውም ታላላቆች ድንቆች ተአምራቶች ተገለጹ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12

ለሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት በሙሉ የወጣት ትምህርት ክፍል ከፊታችን ቅዳሜ 02/06/2015 ዓ.ም ጀምሮ በቅዳሜ መደበኛ ትምህርት አዲስ ተከታታይ ትምህርት እንጀምራለን። ርዕስ:- ታላቁ ሊቅ ቅ
ለሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት በሙሉ የወጣት ትምህርት ክፍል ከፊታችን ቅዳሜ 02/06/2015 ዓ.ም ጀምሮ በቅዳሜ መደበኛ ትምህርት አዲስ ተከታታይ ትምህርት እንጀምራለን። ርዕስ:- ታላቁ ሊቅ ቅዱስ አትናቴዎስ ህይወቱና ትምህርቱ ሰዓት ስለምታከብሩ እናመሰግናለን።