cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

የፍቅር ቃል ✝️ #የመስቀሉ_ቃል ቻናላችንን ይቀላቀሉ

መንፈሳዊ ቻናል “የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት፥ ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነውና።” — 1ኛ ቆሮንቶስ 1፥18

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
307
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-37 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

نمایش همه...
Miky Mako Vs pastor sofonias ሚኪ ማይኮ ስለ ድምፁ ምላሽ ሰጠ።

በመስቀል ላይ ከኢየሱስ በፊት ወንጀለኛ የተባሉ ተሰቅለዋል ከኢየሱስ ጋርም በግራና በቀኝ ወንበዴዎች በመስቀል ላይ ተሰቅለዋል ። ኢየሱስ ሞትን ድል አድርጎ ተነስቶ ካረገ ቀኋላም ብዙዎች በመስቀል ተሰቅለዋል እኛን ያዳነን መስቀሉ ሳይሆን በኛ ቦታ የተሰቀለው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ያዳነን መስቀሉ ሳይሆን የመስቀሉ ቃል ነው። #አብርሀም_በየነ
نمایش همه...
የኔ እናት አዳር ስንት ነው.....ጠብቂኝማ ልጄ?(ትልቁ ሽማግሌ ከቆምኩበት መሸታ ቤት በር ላይ ፈት ለፊቴ ቆመው አረ እኚ ቅሌታም ሽማግሌ ምን አርጊ ነው ሚሉኝ? (ከቆምኩበት ቦታ ወደኋላ እየሸሸሁ አንድ ጊዜ አድምጪኝ ብር አለኝ እከፍላለሁ.... ቆይ ምን ፈልገው ነው አባባ ለምን አይተውኝም(ቆጣ ብዬ አጭር ቀሚሴን ወደታች እየጎተትኩ የኔ ውብ እንደው ገላሽን አይቼው ስንት እንደሆነ ልጠይቅሽ ነበር? ስንትስ ቢሆን ዋጋው ምን ያደርግሎታል እኔ ከእርሶ ጋ አልተኛም አያርክሱኝ ግድ የለሽም እቺን ብር ያዢያትና ካነሰሽ እጨምራለሁ (በእጃቸው ያንጠለጠሉትን ቦርሳ እየሰጡኝ እንዴ እርሶ ሰውዬ አልፈልግም ገበያ አይዝጉብኝ ይሂዱልኝ በቃ... ግድ የለሽም ያዢው እና ክፍልሽ ገብተሽ ጠብቂኝ ያቺን የተለመደችዋን ገዝቼ መጣለሁ መጣለሁ አደራ ታድያ ሰወር ያለ ቦታ አልጋ ያዢ (ሽማግሌው በልምምጥ እያዩኝ እንደማይሄዱ ስለገባኝ በብር የታጨቀውን ቦርሳ ወስጄ ልጠፋ በውስጤ እያሴርኩ ተቀበልኳቸው ፒያሳ ከጊዮርጊስ ቤ/ክ ትይዩ ካሉ መሸታ ቤቶች ለአመታት ስሰራ በእድሜዬ እንደዚህ ደፋር ሽማግሌ አይቼ አላውቅም ምናልባት ወጣትነቱን ሳይጠቀመው ያለፈበት ነው መሠል ለወሲብ ወጣቱ እንኳ እንደ ሽማግሌው አይንገበገብም።አሁን ከነዚህ ሰውዬ ጋ ብተኛ ከፊትለፊቴ ያለው ጊዮርጊስስ ይቅር ይለኛል?ደሞስ እራሱን መሸከም አቅቶት የሚንደፋደፍ ገላው የቀዘቀዘ ሽማግሌ ብሰጠው ምኑን ከምን ሊያደርገው ነው?ብሩን ይዤ ልጥፋ ወይስ ሽማግሌው መጥቶ የሚያደርገውን ጉዱን ልየው?? ውስጤ በሁለት አጓጊ ጥያቄወች ተሞልቶ ውስጥ ያለውን ገንዘብ ብዛት አይቼ ለመወሰን ሽቀላዬን ትቼ ስሮጥ ወደ ክፍሌ ገባሁ... ቦርሳው ከክበብደቱ የተነሳ ውስጡ ያለው ገንዘብ እንኳን ለአንዲት ሴተኛ አዳሪ ይቅርና ለልጃገረድ እንኳ ሲበዛባት ነው ያስብላል። መቼስ ልጥጥ ሽማግሌ ካልሆነ በቀር ለምናምንቴ ይሄንን ረብጣ ገንዘብ እንደቀልድ አቀብሎ ማን ይሄዳል?ልቤ በእጥፍ እየመታ ባለሀብቱ ሽማግሌ የሠጠኝን ቦርሳ እጄ እየተንቀጠቀጠ ከፈትኩት... ድሮ ድሮ ልጅ ሆኜ አንዳች ነገር ሲያስደነግጠኝ የምገባበት ሳጣ የምገልበው የእናቴ ቀሚስ ናፈቀኝ..ቦርሳውን እንዳንጠለጠልኩ በድንጋጤ ከአልጋዬ ስነሳ ሽማግሌው ውስጡ ያስቀመጡት እቃ ጭራሹኑ ከቦርሳው አፈትልኮ መሬቱ ላይ ተገለበጠ....ድንጋጤዬ ገደቡን አልፎ ጉሮሮዬን ሲያንቀኝ ይታወቀኛል ግን ደሞ መጮኽ አልችልም!!እኚ ሽማግሌ በህይወቴ ቀርቤውም ነክቼውም የማላውቀውን ከሩቅ የምሸሸውን መፅሐፍ ቅዱስ ነበር በቦርሳ አድርገው ገንዘብ ብለው የሠጡኝ።እኔ ግን ከድንጋጤ ብዛት ጭራሽ መሬት ላይ ጥዬው ስርበተበት ከመፅሐፉ ገፅ ውስጥ የተሸጎጠች ሌላ ወረቀት አየሁ.. የተዳደፈ ማንነቴን አውቀዋለሁ ስራዬ ዘማዊነቴ ከመፅሐፍ ቅዱስ ሺ እጥፍ እንድርቅ ያስገድደኛል እኔ ግን መተላለፌ ሳያንስ ጭፈራ ቤት ይዤው መግባቴ አንዳች መታወክ ፈጥሮብኝ መፅሐፉን ከመሬት ብርክ ብርክ እያለኝ አነሳሁትና ከገፁ ውስጥ ተወሽቃ የተቀመጠችውን ወረቀት ፈታኋት... ይህንን መልእክት የምታነቢው የመንፈስ ልጄ። አውቃለሁ ገንዘብ ብለሽ ይህንን ቦርሳ ስትከፍቺ ልትናደጂ ልትደነግጪ ትችያለሽ ግን ደሞ ታግሰሽ መልእክቴን ስሚ የገላሽ ዋጋ ስንት ነው??ይህንን ጥያቄ የምጠይቅሽ ገላሽን ሊገዙ እንደሚመጡ ወንዶች ሳይሆን እንደእግዚአብሔር እንደ አባትሽ ነው።አዎ ሰወች ዋጋ ተምነውልሻ፤ እንደሸቀጥም ተደራድረውብሽ ይሆናል ግን ደሞ አንቺ ገላሽ ስንት ያወጣል?? የኔ ልጅ ይህ ሰወችን የሚያማልለው ገላሽ፤ ትኩሱ የወጣትነት ውበትሽ በክርስቶስ ደም ዋጋ እንደተከፈለበት ታቂ ይሆን?? አንቺ ማለት የክርስቶስ አካሉ አምሳያው ነሽ ስለዚህ እዚህ ምድር ላይ ያለ ሀብት እና ገንዘብ ሁሉ ቢሰበሰብ ያንቺን ገላ አይገዛውም!!ታድያ ይህንን ውድ የክርስቶስ የደም ዋጋ መቅደስነትሽን በ700 ብር ሽጠሽ ታረክሺዋለሽ? በዋጋ ተገዝታችኋል፤ የሰው ባሪያዎች አትሁኑ።''ቆሮ7፥23 እንዳለው የባርነት ቀንበርሽ ተሰብሮልሻል ታድያ የሰው ነው የክርስቶስ የክብር ባርያ መሆንን ትመርጫለሽ?? ምክሬን እንደምትቀበዪ አምናለሁ!!ቦርሳ ውስጥ ባደረግኩልሽ ትንሽ ሳንቲም የዛሬ አዳርሽን ቤትሽ ገብተሽ እራትሽን ብዪና በጠዋት ጊዮርጊስ ቤ/ክ እንድትመጪ አደራ... የማነበውን ወረቀት እንባዬ አርጥቦታል እኚህ ታላቅ አባት የላኩልኝ መልእክት ከልቤ አልፎ በሀጥያት የለፋ አካሌን ሰባብሮት መሬቱ ላይ ተንበርክኬ ትንሿን ቦርሳ ሳብኳት...የተጠቀለሉ ብዙ 200ብሮች አግኝቼ ሳላንገራግር ተነስቼ እንባዬ ያለማቋረጥ በፊቴ ላይ እየተንቆረቆረ ወደቤት ገባሁ። ነግቶልኝ በጠዋቱ ከቡናቤቱ ቅርብ ርቀት አሻግሬ ከማየት በቀር ረግጬ የማላውቀውን የሠማእቱን ደጅ ሰውነቴ እየራደ ተሳልሜው ወደቅፅሩ ያኚን አባት በአይኔ እየፈለኳቸው ገባሁ.. በሰአትሽ ደርሰሻል የኔ ልጅ.(ከኋላዬ ጎርነን ያለ የሽማግሌ ድምፅ ሰምቼ ስዞር ጥቁር ቀሚስና የመለኮሳት ቆብ የደፉ አባት አየሁ ፊታቸው አዲስ አልሆነብኝም ግራ በመጋባት እያየኋቸው... አይዞሽ ነይ የኔ ልጅ እኔው ነኝ ትላንት ያለ ቆብ ስላየሺኝ ነው ድንጋጤ ወሮኝ አስተዋልኳቸው አዎ ትላንት ያመናጨቅኳቸው ያኚ ሽማግሌ ናቸው ጭራሽ መለኩሴ ናቸው??(አጠገባቸው በመሸማቀቅ ቁጭ እያልኩ ይ..ቅርታ አባ እግዜር ይቅር ይበልሽ እንዲ ለብሼ ብመጣ ጭራሹን እንዳትሸሺኝ ብዬ ነው ትላንት ጎረምሳ መስዬ የመጣሁት(ፈገግ ብለው እያዩኝ ምክሬን ሰምተሽ በመመለስሽ ደስ ብሎኛል አይዞሽ እሱ መተላለፍሽን ሳይሆን መመለስሽን ነው ሚያየው አንቺ ብቻ እንደ ጴጥሮስ ሁሉን ትተሽ ተከተዪው።''እኔም ዘማዊ ነበርኩ እናት ቀድሞም ካህን እንድሆንላት ትመኝ ስለነበር ስሜን ካህን ብላ ሰየመቺኝ እኔ ግን ሀሳቧን ትቼ ጭራሽ ዘማዊ ሆኜ አረፍኩት እናም የሠፈሩ ሰው ከግብሬ የተነሣ'ዘማዊው ካህን''እያለ ይጠራኝ ነበር ዘማዊነት ማዕረጌ ሆኖ ሳለ እሱ ግን በንሰሐ በድሌን ረስቶ ይቅር ብሎኝ አሁን አባ ካህን ተብያለሁ። ካወቅሽበት ትላንትና በቦርሳ የሠጠሁሽ ትልቅ ሀብት ገንዘብሽን ነው።ያውም መንዝረሽ የማትጨርሽው የዘላለም ሀብት!! ወንጌሉን ገንዘብ ያደረገ፣ቃሉን የሰማ፣ ክርስቶስን የተከተለ፣በሰማይም በምድርም ባለፀጋ ነው። ያቺ ማርያም እንተ ህፍረትን አታስታውሺም?ዘማዊ ነበረችኮ እሷ ግን ውዱን ሽቱ ወስዳ የክርስቶስን እግር በፀፀት ወድቃ አጠበች እሱም ማራት እንጂ አልፈረደባትም።አንቺም ውድ ማንነትሽን ልብሽን ለሱ ካስገዛሽ አምላክሽ መሀሪ ነው...አሁን ነው የንሰሐ ጊዜ ከዛ የሀጥያት ስፍራ ወጥተሻልና ዳግም አትመለሺ።ገላሽን ሽጠሽ ደልቶሽ ከምትኖሪ እዚህ ቆሎ ቆርጥመሽ ከአምላክሽ ጋ በምድር ለማኝ ሆነሽ በሰማይ የመንግስቱ ወራሽ ብትሆኚ ይሻልሻል።እኔ የሱ ተራ አገልጋይ መለኩሴ ነኝ የኔ ስራ መረብ የተባለውን ወንጌል ወደ ጥልቁ(አለም) ጥሎ አሳዎችን መሠብሰብ፣ቤ/ክ ውስጥ ያለውን ሳይሆን ከውጪ ያለውን መጥራት ሲሆን። የቤ/ክንም ተልእኮዋ "ኑ" ማለት ሳይሆን ሄዳ በጨለማ ውስጥ ያሉትን ወደ ብርሀን ማምጣት ነው።በይ ተነሺ..ንሰሐሽን የሚቀበሉሽ ካህኔ ጋ ወስድሻለሁ .. ማንነቴን ረስቼ የማይታይ አይቼ በአለም ስኳትን ዘማዊ ባልኳቸው አዛውንት ዘማዊነቴ ተሰርዞ የክርስቶስን ልጅነት አገኘሁ።አዎ በዋጋ ተገዝቻለሁ!!! ወደ እቅፉ ይመልሰን!!! 👉 ከfacebook ያገኘሁት ነው #እንደዚህ_የክርስቶስ_ወንጌልን_ወጥተው_የሚሰብኩ ፤ #የጠፉ_በጎችን_ከቤተክርስቲያን_ወጥተው_የሚሰበስቡ_እውነተኛ_የሆኑ_እረኞች_የሆኑ_የኦርቶዶክስ_አባቶችን_ያብዛልን።
نمایش همه...
#የክርስቲያኖች_የመቶ_ብር_ቻሌንጅ_100_ብር “ለፍቅርና ለመልካምም ሥራ እንድንነቃቃ እርስ በርሳችን እንተያይ፤”   — ዕብራውያን 10፥24 በዚህ ግሩፕ ላይ ያለን ክርስቲያን ወንድምና እህቶች በየወሩ 100 ብር በማዋጣት ለተቸገሩ ወገኖች የምንረዳበትን በጎ ስራ ለመስራት አስቤያለሁ። በዚህ ጉዳይ ውስጣችሁ የተነቃቃ ሁሉ በ 0902972418 አብርሀም ብላችሁ በመደወል ወይም በዚህ የቴሌ ግራም ሊንክ @bazaleel1 በመግባት አናግሩኝ። አፍራሽ ሀሳብ አንቀበልም ለፈቃደኞች ብቻ የቀረበ የበጎ ስራ ጥሪ ነው። @bazaleel1  @bazaleel1 “ንጹሕ የሆነ ነውርም የሌለበት አምልኮ በእግዚአብሔር አብ ዘንድ ይህ ነው፤ ወላጆች የሌላቸውን ልጆች ባልቴቶችንም በመከራቸው መጠየቅ፥ በዓለምም ከሚገኝ እድፍ ሰውነቱን መጠበቅ ነው።”   — ያዕቆብ 1፥27 #አብርሀም_በየነ
نمایش همه...
“ለፍቅርና ለመልካምም ሥራ እንድንነቃቃ እርስ በርሳችን እንተያይ፤” — ዕብራውያን 10፥24 በዚህ ግሩፕ ላይ ያለን ክርስቲያን ወንድምና እህቶች በየወሩ 100 ብር በማዋጣት ለተቸገሩ ወገኖች የምንረዳበትን በጎ ስራ ለመስራት አስቤያለሁ። በዚህ ጉዳይ ውስጣችሁ የተነቃቃ ሁሉ በ 0902972418 በመደወል ወይም በዚህ የቴሌ ግራም ሊንክ @bazaleel1 በመግባት አናግሩኝ። አፍራሽ ሀሳብ አንቀበልም ለፈቃደኞች ብቻ የቀረበ የበጎ ስራ ጥሪ ነው። @bazaleel1 @bazaleel1 “ንጹሕ የሆነ ነውርም የሌለበት አምልኮ በእግዚአብሔር አብ ዘንድ ይህ ነው፤ ወላጆች የሌላቸውን ልጆች ባልቴቶችንም በመከራቸው መጠየቅ፥ በዓለምም ከሚገኝ እድፍ ሰውነቱን መጠበቅ ነው።” — ያዕቆብ 1፥27 #አብርሀም_በየነ
نمایش همه...