Deacon Chernet
رفتن به کانال در Telegram
ነገር ግን በጌታችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና እውቀት እደጉ። ለእርሱ አሁንም እስከ ዘላለምም ቀን ድረስ ክብር ይሁን፤አሜን 2ኛ ጴጥ 3፡18 ጥቆማ ወይም ጥያቄ ካላቹ በዚህ የተለግራም ቦት👉🏽https://t.me/Cher2112bot ይጠቀሙ
نمایش بیشتر1 623
مشترکین
+124 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
-1030 روز
آرشیو پست ها
1 623
#እንኳን_ለገናናው_መልአክ_ለቅዱስ_ሚካኤል_በዓል_በሰላም_በጤና_እና_በፍቅር_አደረሳችሁ።
“ ይትዐየን መልአከ እግዚአብሔር ዐውዶሙ ለእለ ይፈርህዎ ወያድኅኖም ጣዕሙ ወታእምሩ ከመኄር እግዚአብሔር።” መዝ.33 (34)7-8
ቅዱስ ሚካኤል ለፍጥረታት ሁሉ የሚራዳና የሚያዝን የምሕረትና የመዳኛ፤ የሰላም መልአክ ነው፡፡ ‹‹በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል›› /ዳን.12፥1/ በማለት በነቢዩ ዳንኤል የተነገረ ሲሆን በሌላ ቦታ ‹‹ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ›› /ዳን. 10፥13/ በማለት ያስረዳል፡፡ ቅዱስ ሚካኤል በስሙ የተራቡትን ለሚያበሉ የታረዙትን ለሚያለብሱ የተጠሙትን ለሚያጠጡ በዓሉን በክብር በደስታ ለሚያከብሩ ሁሉ ምልጃው ፈጣን የችግረኞች ረዳት ታማኝ ጽኑዕ ኃያል መልአክ ነው።
#ሰኔ_12_ለምን_ይከበራል_ቢሉ_?
1.የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል #ሲመቱ ወይም የ #ተሾመበት ዕለት ነው።
2.በስሙ የታነጸ ቤተ ክርስቲያን የከበረበት #ቅዳሴ_ቤቱ ነው።
3. ቅድስት #አፎምያ ዝክሩን የምትዘክር ወዳጁን ከሳጥናኤል ያዳነበት ዕለት ነው።
4.ምስኪኑ ታዛዡ ልጅ የኃለኛ ስሙ #ባህራን በጎረቤቱ ባለጸጋው ምክንያት የታወጀበት የሞት ደብዳቤ ለውጦ ያዳነው ዕለትም ነው።
ከዚህ በተጨማሪ ይህ ሰኔ 12 ጻድቁ የኢትዮጵያ ንጉስ ላሊበላ ዕረፍቱም ነው።
ካልታሰበ መከራ ይሰውረን አሜን።
1 623
"እውነተኛ ጓደኛህ በፍቅሩ ቅን የሆነ። ግብዝነት የሌለው ፣ መልክም የሆነ አስመሳይነት ወይም ጥርጣሬም የለውም ፣ ስሜቱ ሁሉ ፍጹም ቅን እና እውነተኛ ነው... እውነተኛ ወዳጅ ለልብ ንፅህና፣ ለእግዚአብሔር ፍቅር እና ዘላለማዊ ህይወትህን ለመጠበቅ የሚረዳህ ነው።"
#Pope_Shenouda_III@Deaconchernet
1 623
በነገር ሁሉ በፀሎትና በምልጃ ከምስጋናም ጋር ልመናችሁን በ እግዚአብሔር ፊት አቅርቡ እንጂ ስለ ማነኛዉም ነገር አትጨነቁ።
ወደ ፊሊጵስዩስ ሰዎች ፬÷፮
1 623
ኃጢአትን ብትሠራ እንኳ አትውደቅ፤ ከወደቅህም ተነሥ እንጂ አትደንግጥ። ዕለት ዕለት ብትበድል ዕለት ዕለት ንስሐ ግባ። እንደ ሰውነታችን ዕለት ዕለት እንበድላለን፡፡ በጥምቀት ያገኘነውን ልጅነት እናቆሽሸዋለን፡፡ አዲሱን ሰውነታችን ብሉይ(አሮጌ) እናደርገዋለን፡፡ ነገር ግን ይህን ዕለት ዕለት ማደስ ይቻላል፡፡
አንድ ቤት እያረጀ ቢሄድ እንደ አዲስ እንሠራዋለን፡፡ ክዳኑን፣ ቀለሙን፣ ምንጣፉን እድሳት እናደርግለታለን፡፡ እኛም በኃጢአት ባረጀው ሰውነታችን ላይ እንዲህ ልናደርግ ይገባናል በንስሐ፡፡ ቤት ሲያረጅ ፈርሶ እንደማይጣል ሁሉ፣ ሰውም በኃጢአት ስለወደቀና ስለቆሸሸ ተስፋ ቆርጦ ሊጠፋ አይገባውም። ባለቤቱ መጥቶ እንደሚያድሰው፣ እኛም በንስሐ ወደ እግዚአብሔር ስንቀርብ እርሱ በቸርነቱ ያድሰናል።
#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
1 623
ተስፋችን ሊዘረጋ የሚገባው ሊገራን በሚችለው በእግዚአብሔር ላይ ነው፤ ስለዚህ የእርሱን ምሕረት በመሻት ለእርሱ እንሸነፍ፡፡ ፍጹም እስከምንሆን ድረስም እርሱ ይገራን ዘንድ የሚመጣብንን ሁሉ በጽናት እንቻለው፡፡ አብዛኛውን ጊዜ እኛ በቅጣት መካከል እናልፍ ዘንድ እግዚአብሔር ይፈቅዳል፡፡ የዱር አራዊትን ለመግራት ጅራፍ የምትጠቀሙ ከሆነ እግዚአብሔር እኛን ከአውሬነት የእርሱ ልጆች ለማድረግ ጅራፍ ቢጠቀም ጉዳቱ ምንድር ነው?
#ቅዱስ_አውግስጢን
1 623
ጥርጣሬን አስወግዱና ምንም ሳትወላውሉ እግዚአብሔርን ለምኑት፡፡
ለራሳችሁ እንዲህ አትበሉ፡- « እርሱን በመቃወም እጅግ በጣም ብዙ ኃጢአቶች መሥራቴ እየታየኝ እንዴት ነው እግዚአብሔርን ለምኜ ከእርሱ የምቀበለው? ልክ እንደዚህ እያላችሁ ለራሳችሁ ምክንያት አትፍጠሩ፡፡ ይልቁንም በሙሉ ልባችሁ ወደ እግዚአብሔር ተመለሱና ምንም ሳትጠራጠሩ ለምኑት፡፡ በዚህ ጊዜ ብዛት ያላቸው ለምለም ምሕረቶቹን ታገኛላቹ፤ ምክንያቱም እርሱ ስለማይተዋችሁ ይልቁንም የነፍሳችሁን ጥያቄ ስለሚመልስላችሁ፡፡
#ቅ_ሔርማስ
1 623
ስራ ማስታወቂያ 📯
የስራ መደቡ መጠሪያ፡ የቪዲዮ አርታኢ/ video editor
የሥራ ዓይነት: የርቀት/Remote - የትርፍ ሰዓት
የስራ ቦታ፡ አዲስ አበባ፡ ኢትዮጵያ
ብዛት : 2
ደሞዝ ፡- 4000 በወር
ማለቂያ ቀን፡ ሰኔ 12፣ 2018
መግለጫ፡-
ለቲኪቶክ፣ ኢንስታግራም ፣ ዩቲዩብ እና ሌሎች የማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች አጓጊ ይዘትን ለመፍጠር ችሎታ ያለው ቪዲዮ አርታዒ/ video editor እየቀጠርን ነው።
ለመመዝገብ :- @kerudesign
መልካም ዕድል !
1 623
ከእግዚአብሔር ርቀህ እየኖርክ ደስታንም አትጠብቅ
" Do not live far from God and expect happiness "
#Pope_Shenouda_III@Deaconchernet
1 623
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚታነባቸው የምዕራፎች ብዛት አስፈላጊ አይደለም, ነገር ግን አስፈላጊው ግንዛቤ እና ማሰላሰል እና አተገባበር ነው።
#Pope_Shenouda_III@Deaconchernet
1 623
ችግሩን ወደሚፈታው እንጂ ወደ ችግሩ አትመልከት በችግርህ ውስጥ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር እንደቆመ የሚሰማህ ስሜት ተስፋና ብርታት ይሰጥሃል
#Pope_Shenouda_III
1 623
“ከሰዎች መካከል አንዱ እንደ ከንቱ እና እንደሌለህ አድርጎ ቢቆጥርህ ከአፈር እንደተፈጠርክና ወደ አፈርም እንደምትመለስ ተናገር፡፡ አንተ
ወራዳ ከንቱ ብሎ ቢሰድብህም አንተ ራስህን አፈርና አመድ ነኝ ብለህ
ጥራ፡፡ ራሱን እንዲህ ብሎ ከጠራውና ከተከበረው አባት ከአብርሃም የበለጥህ አይደለህምና፡፡”
ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ፣ ሃይማኖተ አበው
1 623
የምድር ኃጥአን ሁላችሁ ወደ ቅድስት ድንግል ኑ፡ በእርሷ ስጦታ ጻድቃን ትሆኑ ዘንድ፤ ልብሳችሁም ያደፈ ሁላችሁ ወደዚህች ቅድስት ምንጭ ኑ፡ የይቅርታ ዉሃ ወደ ምታፈስ፤ ልብሳችሁንም በልጇ ደም እጠቡ፡ ለሰማያዊ ሙሽርነት ዝግጁ ትሆኑ ዘንድ፡፡ ድውያነ ሥጋ ሁላችሁ ወደ ድንግል ኑ በጸሎቷ ኃይል እንድትፈወሱ፡፡ የእውቀት ድሆች ሁላችሁ ኑ፡ የእውቀት ምንጭን ከእሷ ትቀዱ ዘንድ፡ ያማረ የተወደደውን የጥበብ ምክር ታገኙ ዘንድ
#አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋስጫ_አርጋኖን
1 623
"ደናግል ሆይ የሰማያዊ ሕይወት አርአያና አምሳል የሆነችው የድንግል ማርያም ሕይወት ይኑራችሁ። እርስዋ ለክርስቶስ እናት ለመሆን በምንም የምታንስ አልነበረችም።
እግዚአብሔር ዳኛዋ እንዲሆንላት ትጸልይ ነበር እንጂ በወንዶች መታየትን አትሻም ነበር። ከቤት ለመውጣት አትቸኩልም ነበር። በሕዝባዊ ሥፍራዎች የሚያውቃት ሰው አልነበረም። ማር እንደምትሠራ ንብ በቤትዋ ውስጥ ብቻ መቆየትን ትመርጥ ነበር። በቤትዋ የቀረውን ሁሉ ለድሆች በቸርነት ትሰጥ ነበር። ቃላትዋ ጥንቃቄን የተመሉ ነበሩ፤ ድምፅዋም የተመጠነ ነበር። ጮኻ አትናገርም ነበር ማንም ላይ ክፉ ነገርን አልተናገረችም። ክፉ ወሬን ለመስማትም አትፈቅድም ነበር።"
ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ
1 623
በሮች ሁሉ ተዘግተው ብታገኛቸው፣ ወደ እግዚአብሔር ተመለስ እሱ የከፈተውን ማንም አይዘጋውምና።
#Pope_Shenouda_III
@Deaconchernet
@Bete_tselot_App
1 623
ቃላቶችህ ያንተን ማንነት ያንፀባርቃሉ ስለዚህ በአንተ ያለውን ማንነትህን በክብር አሳይ
በቃልህ ትጸድቃለህ ከቃልህም የተነሣ ትኰነናለህና።
#Pope_Shenouda_III
@Deaconchernet
@Bete_tselot_App
1 623
ጸሎት በእግዚአብሔር ፊት የመሆን ስሜት ነው።
ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ህብረት ማድረግም ነው።
ወደ እግዚአብሔር ቅርብ። ጸሎት የመላእክት ምግብ ነው
‹እግዚአብሔር ቸር እንደ ሆነ ቅመሱና እዩ› (መዝ. 34፡8)።
#Pope_Shenouda_III
@Deaconchernet
@Bete_tselot_App
1 623
በገነት ውስጥ, እግዚአብሔር ለምን ሐጢያት እንደሰራን ሳይሆን, ለምን ንሰሐ እንዳልገባን ይጠይቀናል.
ስለዚህ ንሰሐ እንግባ!
@Pope_Shenouda_III
አይታችሁ ዝም አትበሉ !
አንድ ጣት ብቻ !
በሉ ለሌሎች ይደርስ ዘንድ Share አድረጉ
1 623
በልብህ ውስጥ ቂም አትያዝ።
ቂም መያዝ በልብህ ውስጥ መርዝ እንደመያዝ ነው።
ያ መርዝ ሌላውን ሳይሆን አንተን ይገድልሃል።
ጠላትህ ቢበድልህ እርሱ ታሟል፤ አንተ ግን ይቅር ባለማለት በሽታው እንዳይጋባብህ ተጠንቀቅ።
የእግዚአብሔር ምሕረት ልክ እንደ ሰፊ ባሕር ነው። ወደዚህ ባሕር ውስጥ ለመግባት የምትችልበት ብቸኛው በር ግን 'ይቅርታ' ነው።
አንተ ለሌሎች ይቅርታን ስትነፍግ፣ ያን በር በራስህ ላይ እየቆለፍክ ነው። እግዚአብሔር ሊምርህ ዝግጁ ነው፤ አንተ ግን ይቅር ለማለት ዝግጁ አይደለህም።
ምክንያቱም ይቅር ማለት የሚችለው ይቅር ማለትን የሚያውቅ ልብ ያለው ብቻ ነውና።
#ቅዱስ_አውግስጢኖስ
@deaconchernet
@Bete_tselot_App
