cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

ማንበብ ለሕይወት

በዚህ ቻናል የተለያዩ ምርጥ ምርጥ መፅሐፍትን ያገኛሉ። ፡ከማንበብ የምናጣው ድንቁርናን ነውና፡እናንብብ

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استزبان مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
پست‌های تبلیغاتی
201
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

• ሾተላዩ ሰላይ • Eye Of The Needle • • ደራሲ ኬን ፌሎት •ተርጓሚ ፦ ማሞ ውድነህ ★መካከለኛ ጥራት! ሙሉ መጽሐፍ! ቡክዓለም[የመጻሕፍት ዓለም] @BOOKALEM
نمایش همه...
• ሾተላዩ ሰላይ • Eye Of The Needle • • ደራሲ ኬን ፌሎት •ተርጓሚ ፦ ማሞ ውድነህ መካከለኛ ጥራት! ክፍል ፪ ገጽ 204-405(ተፈጸመ) ቡክዓለም[የመጻሕፍት ዓለም] @BOOKALEM
نمایش همه...
• ሾተላዩ ሰላይ • Eye Of The Needle • • ደራሲ ኬን ፌሎት •ተርጓሚ ፦ ማሞ ውድነህ ከፍተኛ ጥራት! ክፍል ፪ ገጽ 204-405(ተፈጸመ) ይህን ምርጥ የስለላ መጽሐፍ እንዲህ ጥራቱን በጠበቀ መልኩ ላዘጋጀው ለወንድሜ Sebah ምስጋናችን ይድረስ. ቡክዓለም[የመጻሕፍት ዓለም] @BOOKALEM
نمایش همه...
• ሾተላዩ ሰላይ • Eye Of The Needle • • ደራሲ ኬን ፌሎት •ተርጓሚ ፦ ማሞ ውድነህ መካከለኛ ጥራት! ገጽ 1-203 ክፍል ፩ ቡክዓለም[የመጻሕፍት ዓለም] @BOOKALEM
نمایش همه...
• ሾተላዩ ሰላይ • Eye Of The Needle • • ደራሲ ኬን ፌሎት •ተርጓሚ ፦ ማሞ ውድነህ ከፍተኛ ጥራት! ገጽ 1-203 ክፍል ፩ ቡክዓለም[የመጻሕፍት ዓለም] @BOOKALEM
نمایش همه...
#ፈጠራና_ለዉጥ_በኢትዮጵያ_ከጥንት_ጀምሮ_እስከ_1930ዎቹ በኢትዮጵያ ከጥንት እስከዛሬ የተለያዩ የፈጠራ ሥራ ሙከራዎችና የሥልጣኔ አሻራዎች ታይተዋል። ታዋቂው ልበ-ኢትዮጵያዊ የታሪክ ተመራማሪ ፕሮፌሰር ሪቻርድ ፓንክረስት እኝህን የለውጥና የሥልጣኔ ጮራዎች፣ በተለይም ከመካከለኛው ዘመን ጀምሮ እስከ 1930ዎቹ የታዩትን በታሪክ መዝገብ ሰንደው አኑረውልናል። እኛም ለናንተ ለተወደዳችሁ አንባቢዎቻችን በሚመች መልኩ እንዲህ ወደ አማርኛ ቋንቋ መልሰን አሰናድተናል። መልካም ንባብ! የኢትዮጵያ ተፈጥሯዊ መልክዓ-ምድር እና በተራሮች የተከበበች አገር መሆኗ አውሮፓዊያን አፍሪካን በተቀራመቱበት ዘመን (scramble for Africa) ነጻነቷን ጠብቃ ለረዥም ዘመናት እንድትኖር ረድቷታል። የዚህች አገር በቅኝ ያለመገዛት ታሪክ እንቆቅልሽ የሆነበት Daniel Thwaite የተባለ ጸሀፊ The Seething African Pot: A Study of Black Nationalism, 1882-1935 በተሰኘ መጽሀፉ ስለኢትዮጵያ ክብር እንዲህ ይላል፤ Ethiopia’s prestige in Africa consequent upon her triumphant success in repelling invasion, and in having remained unconquered throughout the centuries, is practically unfathomable. To the Africans in general, not only to those who invoked her as a liberator, she stands as a granite monument, a living exponent and testimony of the innate puissance of the black race, the shrine enclosing the last sacred spark of African political freedom, the impregnable rock of black resistance against white invasion, a living symbol, an incarnation of African independence.” ይች የአፍሪካ ትንሳኤ ተምሳሌት ፣ የጥቁር ትግል አይበገሬነት ህያው ማሳያ ሲል ይህ ደራሲ የገለጻት አገራችን ኢትዮጵያ በብዙ መልኩ የሄደችበት የታሪክ መንገድ ከሌሎች የአፍሪካ አገራት የተለየ ነው። ይህም መሆኑ አገሪቱ በታሪኳ ያለፈችበት የፈጠራና ለውጥ (innovation and change) ሂደት የራሱ የሆነ አሉታዊም አውንታዊም ገጽታ እንዲኖረው አድርጎታል። #ጥንታዊ_አክሱም ይህ ዘመን በኢትዮጵያ የፈጠራና ለውጥ ታሪክ ውስጥ ወርቃማው ዘመን ነበር ሊባል ይችላል። በስነ-ህንጻው ዘርፍ የአክሱም ሀውልት በዘመኑ ኢትዮጵያዊያን የነበሩበትን የስነ-ህንጻ ደረጃ ሲያመላክት፣ በዘመኑ የነበረው የጽሁፍና የቋንቋ እድገት፣ በገንዘብ የመገበያየት ሥልጣኔ፣ ወዘተ የዘመኑን የእድገት ደረጃ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው። የአክሱም ዘመን ኢትዮጵያ ለውጭው ዓለም እውቀትና ጥበብ በሯን የዘጋች አልነበረችም። ለዚህ እንደማሳያ በክብረ ነገሥት ላይ የሰፈረውን የንግሥት ሳባንና የንጉሥ ሰለሞንን ታሪክ ማንሳት ይቻላል። በዚህ ታሪክ ውስጥ ንግሥተ ሳባ ስለ ሰለሞን ጥበብ ሰምታ ለጥበብ ካላት ታላቅ ፍላጎት የተነሳ እየሩሳሌም ድረስ ተጉዛ ከንጉሥ ሰለሞን መገናኘቷን እናያለን። ከዚህም በተጨማሪ እንደ ዞስካለስ ዓይነቱ የአክሱም ነገሥታት የግሪክን ስነ-ጽሁፍ ጠንቅቀው ያውቁ እንደነበር በታሪክ ድርሳናት ተጽፎ እናገኛለን። ከዚህም በተጨማሪ የግሪክ ፊደላት በአክሱማዊያን ሳንቲሞች ላይ ታትመው ይታዩ ነበር። በአክሱማዊያን ኪነ-ህንጻ ላይም የግሪክ አማልክት የሆኑት ዜዉስ፣አሬስ እና ፖሴይዶን ተቀርጸው ይታያሉ። በሀይማኖቱ ረገድ በአክሱም ዘመነ መንግሥት የታዩትን ለውጦች ስንመለከት፣ የአክሱም ዘመን ኢትዮጵያዊያን በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በንጉሥ ኢዛና ዘመነ መንግሥት ክርስትናን መቀበላቸውን በኋላም ከአረቡ አለም ለተሰደዱ መስሊሞች አምባ መጠጊያ መሆናቸውን ታሪክ ይነግረናል። በዚህ ጊዜ የአክሱም ንጉሥ የነበረው ንጉሥ አርማህ፣ እሱን ተማምነው የመጡትን የነብዪ መሐመድ ተከታዮች ከሳሾቻቸው አሳልፎ እንዲሰጣቸው ሲጠይቁት…..” የወርቅ ተራራ ብትሰጡኝ እንኳን እንኚህን ሰዎች አሳልፌ አልሰጣችሁም”። ነበር ያላቸው። ንጉሥ አርማህ …..”የወርቅ ተራራ ብትሰጡኝ እንኳን እንኚህን ሰዎች አሳልፌ አልሰጣችሁም”። #የአክሱማዊያን_የንግድ_ግንኙነት የአክሱም ዘመን ኢትዮጵያ በመካከለኛው ምስራቅ ተጽዕኖ ፈጣሪ ከነበሩ አገራት መካከል ግንባር ቀደም ነበረች። ለጊዜውም ቢሆን ደቡብ አረቢያን ተቆጣጥረው የነበሩት አክሱማዊያን በታላላቆቹ ኢምፓየሮች ዘንድ ትልቅ ተቀባይነትን እና የዲፕሎማሲ ግንኙነት ጥያቄዎችን ያስተናግዱ ነበር። በዚህም ምክንያት በንግዱ ዘርፍ ከግብጽ፣ኑቢያ፣አረቢያ፣ ፐርሺያና ህንድ ግንኙነት የነበራቸው አክሱማዊያን መርከቦቻቸው ቀይ ባህርን እና የህንድ ውቂያኖስን አቋርጠው ሩቅ ተጓዦች ነበሩ። በቀጣይ ክፍል የመካከለኛውን ዘመን ኢትዮጵያ የፈጠራና የለውጥ ታሪክ እንቃኛለን።
نمایش همه...
በክፍል ሁለት ጽሁፋችን የኢየሱሳዊያንን (jesuits) ወደ ኢትዮጵያ መምጣት ተከትሎ ህዝቡ የቆየ ሃይማኖቱን በሮም ካቶሊክ እምነት ላለመቀየር ያደረገውን ተቃውሞ ተመልክተን ነበር። ኢየሱሳዊያኑም ቢሆኑ የራሳቻውን ሃይማኖት በአገሬው ህዝብ ላይ ለመጫን ያደርጉ የነበረውን ጥረት ያክል የህዝቡን ኑሮ ከመሰረቱ ለመቀየር የሚረዱ የፈጠራና የለውጥ ትምህርቶችን ለማስተማር ያደረጉት ጥረት እዚህ ግባ የሚባል አልነበረም። በፖርቱጋሎች የተጻፉት የታሪክ መዛግብት በግልጽ እንደሚያሳዩት ኢየሱሳዊያኑ ሚሲዮኖች ትልቁ ትኩረታቸው የነበሩት ሃይማኖታዊ ጉዳዮች ነበሩ። ቅዳሜና እሁድን እንደ ሰንበት ተቀብሎ ያከብር የነበረውን የረጅም ዘመን የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታይ እሁድን ብቻ ሰንበት እንዲያከብር፣ ካህናቱ ሳያገቡ በድንግልና እንዲኖሩ ከማስተማር ባሻገር ሰለ ተሻሻለ የግብርና ዘዴ፣ ስለዘመናዊ የከብት እርባታ፣ስለ ደን ጥበቃ ዘዴ እና ስለ ዘመናዊ ገበያና መገበያያ አገሬውን ለማስተማር ፍላጎት አልነበራቸውም። የጣናዋ ጀልባ አንድ ፖርቱጋላዊ ከእንጨት የተጠረበ ጀልባ ሰርቶ በጣና ሀይቅ ላይ ይቀዝፍ ነበር። ይሁንና ኋላቀር በሆነ መንገድ ጀልባዎችን ሰርተው ይጠቀሙ የነበሩ የዘመኑ ሰዎች ይህን ዓይነቱን የቴክኖሎጂ ሽግግር ተከትለው የተሻሻለ ጀልባ ሰርተው ሲጠቀሙ አናስተውልም። በሌላውም ዘርፍ ያየን እንደሆነ ሚሲዮናዊያኑ የራሳቸውን መኖሪያ በዘመናዊ መልክ በግንብ ይገነቡ የነበረ ሲሆን ፣ የአገሬው ህዝብ ግን ኑሮው እዛችው የሳር ጎጆ ውስጥ ነበር። ኢትዮጵያ ውስጥ በዘመኑ የነበሩት ኋላ ቀር የእርሻ መሳሪያ፣ የዲንጋይ ወፍጮ፣ የእንጨት ትራስ ዛሬም ድረስ በአንዳንድ አከባቢ በጥቅም ላይ ሲውሉ ማየት አገሪቱን የኢትኖሎጂካል ሙዚየም ያስመስላታል። ፖርቱጋሎች እና ፖርቱጋሎቹ ከህንድ ያስመጧቸው ባለሞያዎች ጥለው ያለፏቸው ጥቂት የቴክኖሎጂ አሻራዎች ግን አልታጡም። ከነዚህም መካከል በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀሰው ግንባታ ነው። ፖርቱጋሎች የገነቧቸው ቤተ-መንግሥቶች ፣ ድልድዮችና ቤቶች ዛሬም ድረስ በአንዳንድ ቦታ አሻራቸው አልጠፋም። ዘመነ ጎንደር የጎንደር ከተማ በ1636 ዓ.ም. መቆርቆር የፈጠራና ለውጥ እንቅስቃሴን ያነቃቃ ክስተት ነበር። በዘመኑ የተገነቡት የፋሲለደስና የሌሎቹም ነገሥታት ቤተ-መንግሥት የአዲስ ዘመን ጅማሮ ምልክቶች ነበሩ። የታዋቂው ተጓዥ ጀምስ ብሩስ ዘገባ ይህንን ሀሳብ የሚያጠናክር ሆኖ እናገኘዋለን። እንደ ጀምስ ብሩስ ዘገባ አጼ ኢያሱ ዳግማዊ ቤተመንግሥቱን ለማስጌጥና ለማስዋብ የግሪኮቹን እውቀትና ጥበብ በሚገባ ከመጠቀሙም ባሻገር እራሱ አጼ ኢያሱ ዳግማዊ በራሱ እጅ የግሪኮቹን መሳሪያዎች ተጠቅሞ የተለያዩ ሙከራዎችን ያደርግ ነበር። ለዚህም እንደምሳሌ ለመጥቀስ ኮምፓስ በመጠቀም ልክ እንደ ግሪኮቹ ሁሉ የኮከብ ምልክትን መሳል ችሎ ነበር። አጼ ኢያሱ ቀዳማዊም እንዲሁ ለፈጠራና ለውጥ ትልቅ ፍላጎት የነበረው ንጉሥ ነበር። በካይሮ የፈረንሳይ ቆንጽል የነበረው De Maillet እንደጻፈለን ኢያሱ ቀዳማዊ ከካይሮ የተለያዩ ባለሞያዎች (ግንበኞች፣አናጺዎች፣አርክቴክቶች፣ የህክምና ባለሞያዎች፣ወዘተ) እንዲመጡለት ደብዳቤ ይለዋወጥ ነበር። ሌላው ምስክር ፈረንሳዊው ተጓዥ Charles Poncet በጻፈው ማስታወሻ እንደገለጸው አጼ ኢያሱ ወደ ጎንደር የመጡላቸውን መድኃኒቶች ምንነትና አጠቃቀማቸውንም ጭምር እየጠየቁ በጽሁፍ እንዲቀመጥ ያደርጉ ነበር። ከዚህም ባሻገር ንጉሡ የመድኃኒት አዋቂ አውሮፓዊያንን መድኃኒት እንዲቀምሙ በማዘዝ በምስጢር ተሸሽጎ የመድኃኒቶቹን የቅመማ ሂደት ይከታተል ነበር። በቀጣይ የ19ኛውን መቶ ክፍለ ዘመን መባቻ ታሪክ እናነሳለን ። ቸር ቆዩን!
نمایش همه...
​​#ፈጠራና_ለዉጥ_በኢትዮጵያ_ከጥንት_ጀምሮ_እስከ_1930ዎቹ ክፍል 2 በመካከለኛው ዘመን በንጽጽር ኢትዮጵያ ለሌሎች ዓለማት ሥልጣኔ እና እውቀት በሯን መዝጋቷ የአገሪቱን የፈጠራና የለውጥ ጉዞ ተንፏቃቂ አድርጎት ነበር። በዘመኑ ምቹ የነበረው የዓየር ጠባይ የሚሰጠው ምርት ከበቂ በላይ በመሆኑ ጊዜው የደስታና የፈንጠዚያ ነበር ማለት ይቻላል። አንዳንዴ የዓየር ሁኔታው ሲዛባና ህዝቡ ለድርቅ ብሎም ለረሃብ ሲጋለጥ ሁኔታው ከፈጣሪ እንደተላከ ቁጣ ነበር የሚታየው። ይህም ችግሩ የፈጠራና የለውጥ አስተሳሰብ አብዮት እንዳይነሳ እንቅፋት ሆኖ ቆይቷል። ከዚህም በተጨማሪ እንደ ዘርዓያዕቆብ ዓይነት የኦርቶዶክስ ክርስትና ጥብቅ አማኝ ነገሥታት ከፈጠራና ለውጥ እንቅስቃሴ ይልቅ ለሃይማኖታዊ ጉዳዮች ያደሉ ነበሩ። በዘመኑ ከውጭ ዓለማት ጋር ግንኙነት ለማድረግ ከሞከሩት ነገሥታት መካከል አጼ ይስሐቅ ተጠቃሽ ነው። የአጼ ይስሐቅ የውጭ ግንኙነትም ቢሆን በዋነኝነት ትኩረቱን ያደረገው በጦር መሳሪያና በወታደራዊ ጉዳዮች ላይ ነበር። ይህ ንጉሥ የቱርኪሽ ማምሉኮችን በመቅጠር ለወታደሮቹ ሥልጠና እንዲሰጡለት፣የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች እንዲሰሩለትና የግብር ስርዓቱን እንዲያደራጁለት አድርጎ ነበር። ከዚህም በተጨማሪ በ1428 ዓ.ም. በዛሬዋ ስፔን አከባቢ ለምትገኘው የአራጎን ንጉሥ አፎንሶ የእጅ ሥራ ጥበበኞችን(artisan) እንዲልክለት የሚጠይቅ ደብዳቤ ጽፎ ነበር። አጼ ልብነ ድንግል ለፖርቱጋሉ ንጉሥ ማኑኤል ቀዳማዊ በጻፈው ደብዳቤ የወርቅና የብር እንዲሁም የነሃስ ማንጠር ችሎታ ያላቸውን እና በነዚህ ማዕድናት ቤተክርስቲያንን ማስዋብ የሚችሉ ባለሞያዎችን እንዲልክለት ጠይቋል። አክሎም እኝህን ባለሞያዎች ቢልክለት ተንከባክቦ እንደሚይዛቸው እና ወደ አገራቸው መመለስ በፈቀዱ ጊዜም ያለምንም ችግር መመለስ እንደሚችሉ በእግዜብሔር ስም ቃል ገብቶለታል። -Send masters who can make figures of gold and silver, copper, iron, tin, and lead, and send me lead for the churches; and masters of gilding with gold leaf, and of making gold leaf; and this soon, and let them come to remain with me here and in my favor. And when they may wish to return at their desire, I will not detain them and this I swear by Jesus Christ, Son of the Living God.” ከዚህም በተጨማሪ አጼ ልብነ ድንግል ለንጉሥ ማኑኤል ቀዳማዊ ልጅ Joao III ተመሳሳይ ደብዳቤ ጽፎ ነበር። የኋላ ኋላ በአህመድ ግራኝ ወረራ ጊዜ በ1541 ዓ.ም Christovao da Gama የተመራ 400 ወታደሮችንና 130 ባሮችን ያቀፈ ቡድን ከፖርቱጋል መጥቶ በጦርነቱ ላይ ድጋፉን ሰጥቷል። ከጦርነቱም በኋላ አጼ ገላውዲዎስ እነኝህን የውጭ ዜጎች አገር ውስጥ ለማስቀረት ትልቅ ጥረት ማድረጉን ታሪክ ይነግረናል። በዚሁ ጊዜ አጼ ገላውዲዎስ የቀጠራቸው የአርመን፣የግብጽ እና የሶሪያ ዜጎች በቤተመንግሥት ግንባታ ሥራ ላይ ተሳትፈው ነበር። ዘመነ ሰርጸ-ድንግል ሌላው በመካከለኛው ዘመን ከነበሩ የኢትዮጵያ ነገሥታት መካከል የተለያዩ ባለሞያዎችን ከውጭ አገር ለማስመጣት ሙከራ ያደረገው አጼ ሰርጸ-ድንግል ነው። አጼ ሰርጸ-ድንግል በ1589 ዓ.ም. ለፖርቱጋሉ ንጉሥ ፍሊፔ ዳግማዊ በጻፈው ደብዳቤ ፣ የተለያዩ የጦር መሳሪያ ሥራ እውቀት ያላቸውን ባለሞያዎች እንዲልክለት ጠይቆ ነበር። ከዚህም በተጨማሪ ሰርጸ-ድንግል በጉዛራ ቤተመንግሥት እንዲገነቡለት Garneau እና Arnaud የተባሉ ፈረንሳዊያን ባለሞያዎችን ቀጥሮ እንደነበር ይነገራል። የሰርጸ-ድንግል ወንድም ዘ-ድንግልም እንዲሁ ለንጉሥ ፍሊፔ ሶስተኛ የብረት ሥራ ባለሞያዎችን እንዲልክለት በደብዳቤ መጠየቁን ታሪክ ያወሳል። ምጽአተ ኢየሱሳዊያን (jesuits) የ16ኛው እና የ17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያና የአውሮፓዊያን ግንኙነት ወደ አዲስ ምዕራፍ የተሸጋገረው የኢየሱሳዊያንን በ1557ዓ.ም ወደ ኢትዮጵያ መምጣት ተከትሎ ነው። የኢየሱሳዊያንን መምጣት ተከትሎ የአውሮፓን ድጋፍ እጅጉን ይሹ የነበሩት ዘ-ድንግል እና ሱስኒዮስ የሮማን ካቶሊክ እምነት ተቀበሉ። ነገር ግን ኢየሱሳዊያኑ ተስፋ እንዳደረጉት ሰፊው ህዝብ የሮም ካቶሊክ እምነትን ለመቀበል ፍቃደኛ አልነበረም። በዚህም የተነሳ ብዙ ደም አፋሳሽ አመጾች ተከስተው ነበር። ከ1541-1633 ዓ.ም. በነበረው ዘመን ከፖርቱጋሎች ጥቂት እንቅስቃሴዎች በተቀር ኢትዮጵያ ከውጭ አገራት ጋር የነበራት ግንኙነት በአገሪቱ ኢኮኖሚ እንዲሁም በፈጠራና ለውጥ ላይ ያስከተለው ለውጥ እምብዛም ነው። በዘመኑ የነበሩ የአገሪቱ ነገሥታትም ከጦር መሳሪያ በቀር በሌሎች ቴክኖሎጂዎች ላይ ትኩረት ሲያደርጉ አይታይም። በሌላም በኩል ከውጪ የመጡትን ባለሞያዎች እውቀት ወደ አገር ልጅ የሚያሸጋግር ተቋም አልነበረም። የሰውም ሞያውን የመልመድ ፍላጎት ነበር ለማለት የሚያስደፍር አልነበረም። ይቀጥላል
نمایش همه...

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለከተራ እና ለጥምቀት በዓል አደረሳችሁ!! (ማንበብ ለህይወት)
نمایش همه...