fa
Feedback
Addis Ababa City Manager Office

Addis Ababa City Manager Office

رفتن به کانال در Telegram
1 474
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-37 روز
-2130 روز
آرشیو پست ها
እይታችን እሩቅ ፣ እሳቤዎቻችን አሻጋሪ ፣ ቃላችን የሚተገበር ፣ ልማታችን ፍትሀዊ ነው። በመደመር መንግስት ዕይታ የዘርፎች እመርታ ! የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ጉብኝት

ውድ የአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት የማህበራዊ ገጽ ተከታዮቻችን;- የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ተልእኳችንን ለማሳካትና የነዋሪዎቻችን ተሳትፎና እርካታ ለማረጋገጥ የምናደረገው ዋነኛ ጥረት አካል የሆነው የተግባቦት ስራችንን በማጠናከር ሂደት መረጃዎችን ስናጋራ ላይክና ሼር በማድረግና አስተያዬት በመስጠት እያደረጋችሁ ላላችሁት ተሳትፎ ከፍ ያለ ምስጋናችንና አክብሮታችን እናቀርባለን!🙏🙏 ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

በመዲናዋ ህዝብን በማሳተፍ የተከናወኑ የልማት ተግባራት ውጤታማ ሆነዋል-ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአዲስ አበባ ህዝብን በማሳተፍ የተከናወኑ የልማት ተግባራት ውጤት ማስገኘታቸውን የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡ የብልፅግና ፓርቲ የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የከፍተኛ አመራሮች ስልጠና የአባላቱን አቅም የሚገነቡ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሰሞኑን ስልጠና እየተሰጠ መሆኑ ይታወቃል። የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት ስልጠና በሀገሪቷ መሰረታዊ የኢኮኖሚ ዘርፎች በግብርና፣ ቱሪዝም፣ ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ዘርፎች ላይ ያተኮረ እንደነበር ተገልጿል፡፡ የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት በአዲስ አበባ የኮሪደር እና የወንዝ ዳር ልማት፣ የቤት ልማት እና አቅርቦት ስራዎችን በመጎብኘት ላይ ናቸው፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ በመዲናዋ ህዝብን በማሳተፍ የተከናወኑ የልማት ተግባራት ውጤት አምጥተዋል፡፡ በዚህም አዲስ አበባን በአፍሪካ ተጠቃሽ ያደረገ ውጤቶች የተገኘበት ነው ብለዋል። በቤት ልማትና አቅርቦት ላይ የግሉን ዘርፍ በማሳተፍ የተከናወኑ ስራዎች አቅርቦቱን ለማሳደግ ማስቻላቸውን ገልጸዋል፡፡ በተሰሩ ስራዎች በርካታ አቅመ ደካሞች ቤት ማግኘታቸውን የገለጹት ከንቲባዋ፤ በትምህርት ቤት ምገባ መርሃ ግብር ውጤት መገኘቱን ጠቅሰዋል፡፡ በመዲናዋ ህጻናትንና ወጣቶችን ታሳቢ ያደረጉ የስፖርት ማዘውተሪያ ቦታዎች ተገንብተው ለአገልግሎት ክፍት ተደርገዋል ያሉት ከንቲባ አዳነች ፥ መፍጠርና መፍጠን መርህን በመከተል ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡

በመደመር መንግስት ዕይታ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሀሳብ የተሰጠውን ሀገር አቀፍ ስልጠና ሲከታተሉ የሰነበቱት የፓርቲያችን እና የመንግስታችን ከፍተኛ አመራሮች በተምሳሌታዊቷ አዲስ አበባ የተገነቡ የልማት ፕሮጀክቶችን እየጎበኙ ነው ! Addis Ababa Prosperity Party - ብልፅግና ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በአዲስ አበባ ከተማ የተከናወኑ የተለያዩ የልማት ስራዎች ላይ ያደረጉት ጉብኝት (በፎቶ)፦

የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በአዲስ አበባ ከተማ የተከናወኑ የተለያዩ የልማት ስራዎች ላይ ያደረጉት ጉብኝት (በፎቶ)፦ #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

የብልጽግና ፓርቲ አመራሮች በአዲስ አበባ ከተማ የመስክ ጉብኝት እያካሄዱ ይገኛሉ የብልጽግና ፓርቲ የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የከፍተኛ አመራር ስልጠና የአባላቱን አቅም የሚገነቡ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሰሞኑን በአዳማ ከተማ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑ ይታወቃል። የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት ስልጠና በኢትዮጵያ የግብርና፣ ቱሪዝም፣ ኢንዱስትሪ እና ከተማ ልማት መሰረታዊ የኢኮኖሚ ዘርፎች ላይ ያተኮረ እንደነበር ተገልጿል፡ የፓርቲዉ አመራሮች ከስልጠናዉ በተጓዳኝ በአዲስ አበባ ከተማ የመስክ ጉብኝት እያካሄዱ ይገኛሉ፡፡ አመራሮቹ መነሻቸዉን ከአራዳ ፓርክ እና ከሳይንስ ሙዚየም በማድረግ በአራት ቡድን በተለያዩ አቅጣጫዎች በመዲናዋ የተከናወኑ የተለያዩ የልማት ስራዎችን መጎብኘት ጀምረዋል፡፡ በስልጠናዉ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት አመራሮቹ በአዲስ አበባ ከተማ የተገነቡ የተለያዩ የልማት ስራዎችን የኮሪደርና ወንዝ ዳርቻ ልማት ስራዎችን፤ ፓርኮችን፤ የገበያ ማዕከላትን፤ ሙዚየሞችንና ሌሎች የልማት ስራዎችን መጎብኘት ጀምረዋል፡፡ AMN-Addis Media Network ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

በባህር ዳር ከተማ በነበረን ጉብኝት የባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየምን እንዲሁም ከተማዋን ለቱሪዝም ዘርፍ ምቹ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን ተመልክተና… See more

የወንዝ ዳርቻ ልማት ሥራዎች እና ሰው ተኮር ፕሮጀክቶች በአዲስ አበባ የወንዝ ዳርቻ ልማት ሥራዎች እና የሥራ ጥራቱ፤ ከተማና ከተሜነትን ለማሳደግ የሚኖራቸውን አስተዋፅኦ ላይ ትኩረት ያደረገ ጉብኝት እየተካሄደ ነው። ጉብኝቱ ላለፉት ተከታታይ 10 ቀናት ሲካሄድ የነበረውና "በመደመር መንግሥት እይታ፣ የዘርፎች እምርታ" በሚል መሪ ቃል የተካሄደውን የብልፅግና ፓርቲ የ2018 ዓመታዊ የከፍተኛ አመራሮች ስልጠና አንዱ አካል ነው። በጉብኝቱም የወንዝ ዳርቻ ልማት ሥራዎች እንዲሁም ሰው ተኮር ፕሮጀክቶች ትኩረት ይደረግባቸዋል ተብሏል። ለ10 ቀናት በነበረው ስልጠና ከ2 ሺህ በላይ ከፌዴራልና ከክልል የተወጣጡ ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል። #ebcdotstream #addisababa #Prosperityparty

ወደ ፍካት